Mereja.net -መረጃ.net

Mereja.net -መረጃ.net ታማኝ መረጃዎችን ወደናንተ እናቀርባለን እንዲሁም የስራ ቅጥ?

ልብ ይነካል 👉🏾እናቱ የተገደለበት ልጅ የገዳዩን እንባ አበሰው ❤️....*****.....👉🏾በዕለተ ቅዳሜ ጥቅምት20 የሰፈሩ አድባር በሁሉ የሚወደዱ እናታችን የሺ ውድነህ ኮልፌ07 ከሚገኘው ...
30/01/2022

ልብ ይነካል 👉🏾እናቱ የተገደለበት ልጅ የገዳዩን እንባ አበሰው ❤️....*****.....
👉🏾በዕለተ ቅዳሜ ጥቅምት20 የሰፈሩ አድባር በሁሉ የሚወደዱ እናታችን የሺ ውድነህ ኮልፌ07 ከሚገኘው ቤታቸው ሁሌም እንደሚያደርጉት አማኑኤል ቤተክርስቲያን ለመሳለምና ለቅሶ ቀብር ለመሄድ በጠዋት ይወጣሉ!
👉🏾እማማ ኖክ ኮልፌ18 ጋር ደርሰው የእግረኛ መንገዱን እየተሻገሩ አንድ ከባድ መኪና ድንገት ይገጫቸዋል😭
👉🏾ያለአባት 8 ልጆቻቸወን ታግለው ያሳደጉት እናት የሺ ወንዱ ልጃቸው ቴዲ ሆስፒታል እየሮጠ ቢደርስም ህይወታቸው አልተረፈላቸውም😭 ሞቱባቸው😭
👉🏾ለቅሶ ደርሼ በዛው ፀሎት አድርሼ እመለሳለው ያሉት ደጓ እናት እግዚአብሔር ቀናቸው ነው ብሎ ጠርቶ ወሰዳቸው!እሁድ ጥቅምት 21 ልጆቻቸው አምርረው እያለቀሱ ከወዳጅ ዘመድ ጋር ቀበሯቸው😭
👉🏾ይህ ደግ ቤተሰብ የሚወዷት እናታቸው ሀዘን ገና ከልባቸው ሳይወጣ ገጭቶ ከገደላቸው ሹፌር ጋር ለእርቅ ተቀምጠው ይቅር ተባብለው ሁሉም ነገር በሽምግልና አልቋል🙏 ቤታቸው የነበረው ድባብ ሁሉንም አስለቅሷል😭::
👉🏾ምንም ወገንና ዘመድ የሌለው የገጫቸው ሹፌር ሽማግሌ አጥቶ ሲንከራተት እናት የሞተባቸው ልበወርቆች አይዞህ ብለው ደግፈውት በጎደለው ሽማግሌእንዲሆኑ አባት አመቻችተውለት በእርቁ ሰዓት እንባውን መቆጣጠር አቅቶት ሙሉ ሰአቱን ስቅስቅ ብሎ ሲያለቅስ ውሏል😭::
👉🏾ካሳ ተብሎ የተሰጠውንም ሙሉ 80, 000ብር ላዘኑት እንባ ማበሻ ይሁንልን ለአረጋውያኑ አስቤዛ ተገዝቶ ይሰጥልንብለው ልጆቻቸው ለባይሽኮልፌ በጎአድራጎት አስረክበዋል🙏💖 እንዲህ አይነት ደግነት እንዴትስ
ይገኛል???
👉🏾ከሁሉ የሚገርመው መጨረሻ ላይ ሊለያዩ ሲሉ ገጭቶ የገደላቸው ሹፌር ራሱን መቋቋም አልቻለም! ይቅር ያሉት የእናት የሺ ልጆች ደግነት የበለጠ እንድፀፀት አደረገኝ ብሎ ስቅስቅ ብሎ እንደገና አለቀሰ😭 "በቃ እግዚአብሔር የጠራት በዚህ ነው አታልቅስ" እያሉ አባባዮቹ ደግሞ ከ3ወራት በፊት እናታቸውን ያጡት ልጆቿ እነቴዲ ነበሩ🙏::
…..*****…..
እናታችን ፅጌማርያም ነፍስ ይማር
ልበወርቆች ቀሪ ዘመናቹ በደስታ ይለቅ🙏
"ለመልካም ስራ ረፍዶ አያውቅም::"
…..*****…..
መረጃ ምንጭ:
…..*****…..

በአንድ ቃል ግለፁት?     እኔ👉👉👉       👍👍👍👍👍👍💪💪💪💪💪💪
22/09/2021

በአንድ ቃል ግለፁት? እኔ
👉👉👉 👍👍👍👍👍👍💪💪💪💪💪💪

የትኟው አለባበስ ተመቻችሁ?
31/08/2021

የትኟው አለባበስ ተመቻችሁ?

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያሌሎች የሥራ ማስታወቂያዎች እንዲደርስዎ ፔጁን ይቀላቀሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
11/08/2021

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ
ሌሎች የሥራ ማስታወቂያዎች እንዲደርስዎ ፔጁን ይቀላቀሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

08/08/2021
08/08/2021

ፈታ በሉ ሽሮ😂
የእውነት ትችላለህ ያሬዶ ጉድህ ፈላ👇👇👇👇👇👇👇👇👇


አታልቅሺ! ~ [ 🇪🇹 ኢትዮጵያ አሸንፋለች ]  | በቶኪዮ ኦሎምፒክ በተደረገው የ 10,000 ሜትር ውድድር ከአንድ እስከ ሦስቱ የወጡት ትውልድ ኢትዮጵያውን ናቸዉ።ሲፋን አንደኛ በመውጣት ወር...
07/08/2021

አታልቅሺ! ~ [ 🇪🇹 ኢትዮጵያ አሸንፋለች ]
| በቶኪዮ ኦሎምፒክ በተደረገው የ 10,000 ሜትር ውድድር ከአንድ እስከ ሦስቱ የወጡት ትውልድ ኢትዮጵያውን ናቸዉ።
ሲፋን አንደኛ በመውጣት ወርቅ - ለባህሬን የምትሮጠው የሀገራችን ልጅ ቃልኪዳን ገዛኸኝ ሁለተኛ በመውጣት የብር ሜዳልያ - ለኢትዮጵያ የምትሮጠው ለተሰንበት ግደይ ሦስተኛ በመውጣት ለሀገሯ ኢትዮጵያ ነሐስ አሸንፋለች።
👌እናመሠግናለን ለቱ 🇪🇹
ባልተባበሩ በሚጠላለፉ በሚወቃቀሱ ደጋግመው ሃላፊነታቸውን ዘንግተው በወደቁ [ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ እና አትሌቲክስ አመራሮች ] መሃል የተገኘ የጀግኖቹ አትሌቶች ውጤት ነው ።
- ኢትዮጵያ የዛሬውን ነሀስ ጨምሮ በቶኪዮ ኦሎምፒክ አንድ ወርቅ፣ አንድ ብር እና ሁለት ነሀስ አሸንፋለች።
***
ሲፋን ሀሰን የ10ሺ ሜትር ወድድር ማሸነፋን ተከትሎ ብቻዋን 2 ወርቅና 1ነሐስ በማግኘት በሜዳልያ ሰንጠረዥ ከኢትዮጵያ በላይ ሆና መቀመጥ ችላለች።
Via Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

07/08/2021

Rare Image of Forgotten Ethiopian Woman who fought in Italo-Ethiopian War. The role of Women in the Battle of Adwa🇪🇹 Victory cannot be underestimated,the truth must be told.

🌍

06/08/2021

The ongoing conflict in Ethiopia indicates that, they wanna destroy what is left of African heritage

የተባረከ ውበት
04/08/2021

የተባረከ ውበት

ሳማንታ ፓወር ከ ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል እና ከ ዶ/ር ሊያ ጋር ተወያዩሳማንታ ፖወር ማምሻውን የሰጡት መግለጫ፡የአሜሪካው ዓለም አቀፍ ልማት ኤጀንሲ (ዩ ኤስ ኤድ) ኃላፊ ሳማንታ ፓወር አሸባሪ...
04/08/2021

ሳማንታ ፓወር ከ ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል እና ከ ዶ/ር ሊያ ጋር ተወያዩ
ሳማንታ ፖወር ማምሻውን የሰጡት መግለጫ፡
የአሜሪካው ዓለም አቀፍ ልማት ኤጀንሲ (ዩ ኤስ ኤድ) ኃላፊ ሳማንታ ፓወር አሸባሪው ሕወሃት እያደረገ ያለው ወታደራዊ እንቅስቃሴ አሳስቦአቸዋል።
*******************
በኢትዮጵያ ጉብኝት እያደረጉ ያሉት የአሜሪካው ዓለም አቀፍ ልማት ኤጀንሲ (ዩ ኤስ ኤድ) ኃላፊ ሳማንታ ፓወር በኢትዮጵያ ዛሬ ምሽት ላይ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም፤ ቀደም ብለው በትግራይ ክልል ስላለው የሰብዓዊ ድጋፍ በተመለከተ ከሠላም ሚኒስትርና ከሌሎች የሥራ ሃላፊዎች ጋር ገንቢ ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸዋል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ በክልሉ የሚቀርበው የሰብዓዊ ድጋፍ አሁንም መፋጠን እንዳለበት ጠቁመው በዚህም ከመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች ጋር መግባበት ላይ መድረሳቸውን ጠቁመዋል።
ይሁንና በዚህ የሰብዓዊ ቀውስ ወቅት አሸባሪው ሕወሃት ወደ አጎራባች ክልሎች የሚያካሂደው ወታደራዊ እንቅስቃሴ አንዳሳሰባቸው ነው ሃላፊዋ ሳማንታ ፓውር የተናገሩት።
በዚህ ሕወሃት በሚያደርገው ወታደራዊ እንቅስቃሴ በአማራ ክልል 150 ሺህ ሰዎች በአፋር ደግሞ 76 ሺህ ሰዎች ከቀያቸው መፈናቀላቸውን ነው ያረጋገጡት።
በኢትዮጵያ ጉብኝት እያደረጉ ያሉት የአሜሪካው ዓለም አቀፍ ልማት ኤጀንሲ (ዩ ኤስ ኤድ) ኃላፊ ሳማንታ ፓወር ላለፉት አራት ቀናት በሱዳን ጉብኝት አድርገዋል።
አሸባሪው የህወሃት ቡድን ኢትዮጵያን ለማፍረስ በተግባር በመንቀሳቀስ በአገር መከላከከያ ሰራዊት ላይ ጥቃት መፈፀሙን ጨምሮ በዜጎች ላይ ከፍተኛ ሰብአዊ ጉዳት እያደረሰ መሆኑ ይታወቃል።
ኢ ፕ ድ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ፦ እንደ ቱርኩ መሪ ኤርዶጋን፣ እንደ ቬንዙዌላው መሪ ኒኮላስ ማድሮ፣ እንደ ኩባው ፕሬዚዳንት ፊደል ካስትሮ የአሜሪካንን ጫና ተቋቁመው አገረዎን ይታደጋሉ.! ወይስ እንደ የመኑ...
04/08/2021

ጠቅላይ ሚኒስትሩ፦ እንደ ቱርኩ መሪ ኤርዶጋን፣ እንደ ቬንዙዌላው መሪ ኒኮላስ ማድሮ፣ እንደ ኩባው ፕሬዚዳንት ፊደል ካስትሮ የአሜሪካንን ጫና ተቋቁመው አገረዎን ይታደጋሉ.! ወይስ እንደ የመኑ መሪ አብዱሮቦ መንሱር፣ እንደ ሶሪያው መሪ በሽረል አሳድ፤ እንደ አፍጋኒስታኑ መሪ ካህናን'' የአሜሪካን ማዕቀብ ፈርተው ህዝባቸውንና አገራቸውን የመከራ ዝናብ ማወራረጃ ያደርጋሉ .? መልሱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያውቁታል። በርግጥም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ ጉዳይ ከሆነ አንገቴን እሰጣለሁ እንጅ አንድም ነገር አልደራደርም ብለው አቋማቸውን አበክረው ነግረውናል።
የኢትዮጵያ ህዝብስ፣ በመሪህ የመጣን ልክ እንደቱርክ ህዝብ ከብረት ለበስ ታንክ ፊት ተኝተህ መሪህን ከምዕራባውያን ሴራ ትታደጋለህ፣ ልክ እንደ ቬንዙዌላ ህዝብ ድንጋይ ፈልጠህ ግጠህ የሀገርህን ኢኮኖሚ ትታደጋለህ፤ ልክ እንደ ኩባ ህዝብ እጅ ለጅ ታያይዘህ ችግርንም ረሀብንም ችለህ ሀገርን ከመፈራረስ ትጠብቃለህ ወይስ፣ እንደ ሶሪያና የመን ኢራቅና ሊቢያ፣ በ21ኛው ክፍለ ዘመን የመንደር ሸማቂዎችን አምነህ አገርህን ታፈረሳለህ ? መልሱ ያለው ከኛ ጋር ነው። ሀገራችንን
ከነ ሙሉ ክብሯ ጠብቀን የጥላቶቻንን ህልም አቀጭጨን ኢትዮጵያን ማስቀጠል ከኛ ከልጆቿ የሚጠበቅ ግዴታና አደራ ነው !
Via ሱሌማን አብደላ

03/08/2021

# #ትክክል ብለሀል ማሜ 👍👍👍👍👍

01/08/2021

👑👑👑
# 💚💛❤💪💪💪

አልተረዳናትም እንጂ እንደ አዲስ አለም ጌታነህ ኢትዮጵያዊነትን ለማሳየት የሞከረ የለም    💚💛❤ 🇪🇹🇪🇹🇪🇹
26/12/2020

አልተረዳናትም እንጂ እንደ አዲስ አለም ጌታነህ ኢትዮጵያዊነትን ለማሳየት የሞከረ የለም 💚💛❤ 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

25/12/2020

"አርቀን እናስባለን" የሚሉ አንዳንድ ደደብ ካድሬዎች "በእናንተ ጽሑፍ ነው ሕዝቡ የሚጨፈጨፍ" ሲሉ ይሰማሉ።
ቆይ እኔ እምለው...
በጸጋየ አራርሳና በብርሐነ መስቀል ንግግር የተቆጡ አመራሮች ኦሮሞዎች ላይ ጥቃት ማድረስ አለባቸው ማለት ነው?
በዳንኤል ብርሐነ ቃላት የተበሳጩ ፖለቲከኞች የትግራይ ሕዝብ ላይ ጥቃት ያደርሳሉ ማለት ነው?
ምን አይነት መንግሥታዊ ድድብና ነው?

የፖል ካጋሜ ምክር - ለኢትዮጵያ!የሩዋንዳው ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ጠቃሚ ምክር አስተላልፈዋል ፡"በአመራር ላይ ያሉ በጎሳ ፣ በሃይማኖት ፣ በብሄር ወይም...
25/12/2020

የፖል ካጋሜ ምክር - ለኢትዮጵያ!
የሩዋንዳው ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ጠቃሚ ምክር አስተላልፈዋል ፡
"በአመራር ላይ ያሉ በጎሳ ፣ በሃይማኖት ፣ በብሄር ወይም መሰል ልዩነትን እና መከፋፈልን [ መሰረት ያደረገ ፖለቲካ ] በምንም መልኩ ተቀባይነት እንደሌለው አስረግጠው ሊናገሩ ይገባል። የእልቂት መነሻው ይኸው ነው!"]
ከኛ አስከፊ ተሞክሮ ተማሩ ይሉናል - ፖል ካጋሜ!

ኢትዮጵያዊነት የሚል ነገር ጭራሽ የሌለውን፣ በዘር ከፋፍሎ የሚያባላ ህገመንግስት ታቅፈህ በብሔር ተከፋፈልን ይባላል እንዴ?አስቂኝ 😀
24/12/2020

ኢትዮጵያዊነት የሚል ነገር ጭራሽ የሌለውን፣ በዘር ከፋፍሎ የሚያባላ ህገመንግስት ታቅፈህ በብሔር ተከፋፈልን ይባላል እንዴ?
አስቂኝ 😀

የብሄር ብሄረሰቦች መብት አማራን እስከመጨፍጨፍ?የአማራ እንዲህ መጨፍጨፍና መዋረድ ለፌድራሉም ለክልልም ባለስልጣናት የስልጣን ስጋት ባለመሆኑ ነው አይደል እንዲህ ደሙ ከውሻ በታች ሆኖ መጨፍጨ...
23/12/2020

የብሄር ብሄረሰቦች መብት አማራን እስከመጨፍጨፍ?

የአማራ እንዲህ መጨፍጨፍና መዋረድ ለፌድራሉም ለክልልም ባለስልጣናት የስልጣን ስጋት ባለመሆኑ ነው አይደል እንዲህ ደሙ ከውሻ በታች ሆኖ መጨፍጨፉ በቁጥርነት ብቻ እየተዘገበ የሚያልፈው? ሌላ የትኛውም ብሄር ኦሮሞ፣ ሶማሌ፣ አፋር፣ ሲዳማ፣ ወላይታ….ሌሎችም.. እንዲህ ቢጨፈጨፉ የፌደራልም የክልል ባለስልጣናትም ጉዳቸው ፈልቶ ለእርምጃ ይራወጡ ነበር! የቤንሻንጉል ክልል ስንት አማራ ካላቀ በኋላ ነው የዚህ ክልልን አስተዳደር፣ በተለይም የመተከል ዞንን አስተዳደር እና የጸጥታ ሰዎችን በሀላፊነት መጠየቅ የሚቻለው?
ሀገር ጭንቅ ውስጥ ስትገባ ደምና አጥንቱን እየከሰከሰ ለሀገር ዘብ የቆመ ህዝብ እንዴት አባቶቹ ሞተው በጠበቁት ሀገር ላይ እንዲህ ይዋረዳል? እስከመቼ የአማራ ሞት ቁጥር ብቻ ይሆናል? የአማራ ሞት በተለይ በቤንሻንጉልና በወለጋ እንዴት የአዘቦት ሁነት ሆኖ ይቀጥላል? የዚህ ተከታታይ ግድያና ጭፍጨፋ መንስዔና ውጤት፣ ከዚህ ግድያ በስተጀርባ ያሉ፣ ሀላፊነታቸውን በአግባቡ ያልተወጡ አመራሮችን ጉዳይ በይፋ እና ለዚህ የዘር ማጥፋት ተግባር ተጠያቂ የሚሆንን አካል መንግስት እንዴት ለኢትዮጵያውያን አያሳውቀንም? ይህች ሀገር እንዳትፈርስ አማራ ምን ያህል መታገስ ነው ያለበት? ስንት እድል ይስጥ? አማራን እያስጨፈጨፉ ያለተጠያቂነት እስከመቼ መቀጠል ይቻላል? አንድን ትልቅ ህዝብ እያዋረዱ፣ እየጨፈጨፉ እና እያሳደዱ እንኳን ስርዓት የጋራ ሀገርስ እንዴት ይኖረናል? የብሄር ብሄረሰቦች መብት እስከ አማራን መጨፍጨፍ እስከመቼ ይቀጥላል! በጥብቅ፣ አፍርጠነው መነጋገር ያለብን ጊዜ አሁን ነው!

23/12/2020

የኢትዮጵያ የጎሳ ፌደራሊዝም የፈጠራቸው ክልሎች በሙሉ ለኢትዮጵያ የየራሳቸው የሆነ የሕልውና አደጋ ጋርጠዋል። የኦሮሚያ ክልል ግን ለኢትዮጵያ የተለየ አደጋ እንዳዘለና በአስቸኳይ ወደ ብዙ ክልሎች መበተን እንዳለበት #ታምራትነገራ በተራራው አጀንዳ ፕሮግራም ላይ ያብራራል።




https://www.youtube.com/watch?v=O3jZfLwW4p4

18/12/2020
ከአማርኛ ቋንቋ አተረፍን እንጂ አልጎደለብንም....!የOMN ጋዜጠኞች እዚህ ጅጅጋ ዩኒቨርስቲ መጥተዋልና በትምህርት ፍኖተ ካርታው ላይ ሀሳብህን ይፈልጋሉ አሉኝ። ግዴለም ይቅርብኝ፣ አቋሜ ለአ...
18/12/2020

ከአማርኛ ቋንቋ አተረፍን እንጂ አልጎደለብንም....!
የOMN ጋዜጠኞች እዚህ ጅጅጋ ዩኒቨርስቲ መጥተዋልና በትምህርት ፍኖተ ካርታው ላይ ሀሳብህን ይፈልጋሉ አሉኝ። ግዴለም ይቅርብኝ፣ አቋሜ ለአቋማቸው ስለማይጥም አያስተላልፉትም አልኳቸው። እውነቴን ነው።
ለምሳሌ በቋንቋ ጉዳይ የሶማሌ ልጆች አማርኛን በደንብ መማር አለባቸው። እኛ አማርኛን የቻልን እና በአማርኛ የተለያዩ እውቀትን የገበየን፣ ቅኔን፣ ተረትና ምሳሌውን፣ ቀልድና ተረቡን፣ አሽሙርና የቃላት ስንጠቃውን አሳምረን ያወቅን የሶማሌ ተወላጆች ከዚህ ቋንቋ አተረፍን እንጂ አልጎደለብንም። የሶማሌ ልጅ በኢትዮጵያ ሀገሩ ጉዳይ በደንብ ከዳር ወደ መሀል መጥቶ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር ጥቅሙን ለማስከበር፣ መብቱን ለመጠየቅ፣ የራሱን የሚገባውን ከሀገር ሀብት ድርሻውን በአፅዕኖት አስረግጦ ለመከራከር የአማርኛ ቋንቋ ያስፈልገዋል ።
የሚያስፈልገው ለእራሱ ጥቅም ሲል እንጂ ለማንም አይደለም። አማርኛን ስላወቀ ሶማሌነቱ አይጠፋበትም፣ እንዲህ የሚያስቡ ሰዎች ለፖለቲካ ትርፍ ትውልድ የነሱን ሀቲት ብቻ እንዲሰማ ፣ ዞርዞር ብሎ ታሪክ እንዳያይ የሚፈልጉ ናቸው።
ቋንቋ መግባቢያ ነው። ብንችል ሰማንያ ቋንቋን ብናውቅ ጥሩ ነበር። ሰው ቋንቋን ካወቀ ስራን፣ ቢዝነስን እና እድሉን ከማስፋት አልፎ ጠላት እንኳ ቢኖረው ቋንቋን በማወቁ ከሞት ይተርፋል። ታሪክ ማወቅ ጥሩ ነው። አብርሆት ይሰጣል። በኢማም አህመድ (አህመድ ግራኝ) ጊዜ ሰራዊቱ የንጉሱን ካንፕ ሾልኮ ለመሰለል ስለፈለገ አህመድ ሶማሌ ወታደሮችን አማርኛ እንዲማሩ አድርጎ ነበር። በጥቂት ወራት ለምደው የንጉሱን የካምፕ ጠባቂዎች "እየህ ቤቶች፣ እንደምን ዋላችሁ" እያሉ አልፈው ሰልለው ይወጡ ነበር።
ይህ ታሪክ ነው። ከዚህ ኢማም በታች የሚያስቡ ሰዎች አሁን መኖራቸው በጣም ይገርማል። በ1535 አካባቢ ሰው የቋንቋን ጥቅም አውቆ ሀገር ሲመራ፣ አሁን ሀገርን የመምራት እድሉን ያገኘ አካል እንዴት ስለቋንቋ እንዲህ
የተዛባ አመለካከት ይኖረዋል ። በጣም ነው የሚገርመኝ።
ሙስጠፋ ዑመር፣ የሶማሊ ም/ርዕሰ መስተዳድር

"ድንበር አካባቢ የተከሰተው ግጭት የሱዳን መንግስት የታችኛው እርከን ችግር ነው።"አምባሳደር ዲና ሙፍቲበሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ሱዳንና ኢትዮጵያ በሚዋሰኑበት የድንበር አካባቢ የተከሰተው ግጭ...
17/12/2020

"ድንበር አካባቢ የተከሰተው ግጭት የሱዳን መንግስት የታችኛው እርከን ችግር ነው።"
አምባሳደር ዲና ሙፍቲ
በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ሱዳንና ኢትዮጵያ በሚዋሰኑበት የድንበር አካባቢ የተከሰተው ግጭት በስፍራው ባለ የሱዳን መንግሥት መዋቅር ውስጥ በተከሰተ ችግር ምክንያት መሆኑን የኢትዮጵያ መንግሥት ገለጸ።
በድንበር አካባቢ ስለተከሰተው ጉዳይ በቢቢሲ የተጠየቁት የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፤ "የተወሰኑ የሱዳን ታጣቂዎች ድንበር ተሻግረው የአርሶ አደሩን ንብረት ለመውሰድ ሙከራ በሚያደርጉበት ወቅት ለመከላከል የተደረገ ክስተት ነው" ሲሉ ግጭቱን ገልፀውታል።
አምባሳደር ዲና ስለክስተቱ ጨምረው እንደተናገሩት ታጣቂዎቹ "የአርሶ አደር ማሳ ውስጥ ገብተው አንዳንድ ነገሮችን የመውሰድ፣ ወደዚያ የማስፋፋትና ከሕግ አግባብ ውጪ የመሄድ ሁኔታ ስለታየ ይህንን ነገር መመለስ ስለሚያስፈልግ እርምጃ ተወስዷል" ብለዋል።
BBC News Amharic

ጠ/ሚ አብይ በቅርቡ በመቀሌ ከከፍተኛ የመከላከያ መኮንኖች ጋር ስብሰባ አድርገው ነበር። በዚህ ስብሰባ ያስተላለፉት መልዕክት ለአገር ውስጥም ሆነ ለአፍሪካ ቀንድ አገራት ምን አይነት አንደምታ...
17/12/2020

ጠ/ሚ አብይ በቅርቡ በመቀሌ ከከፍተኛ የመከላከያ መኮንኖች ጋር ስብሰባ አድርገው ነበር። በዚህ ስብሰባ ያስተላለፉት መልዕክት ለአገር ውስጥም ሆነ ለአፍሪካ ቀንድ አገራት ምን አይነት አንደምታ ይኖረዋል? ጌታሁን ንጋቱና ታምራት ነገራ በዛሬው የዜና ትንታኔ ፕሮግራማችን ላይ ይወያዩበታል።



https://www.youtube.com/watch?v=5BgJULiN6Xw

ጠ/ሚ አብይ በቅርቡ በመቀሌ ከከፍተኛ የመከላከያ መኮንኖች ጋር ስብሰባ አድርገው ነበር። በዚህ ስብሰባ ያስተላለፉት መልዕክት ለአገር ውስጥም ሆነ ለአፍሪካ ቀንድ አገራት ምን አይነት አ...

17/12/2020

Sheger Times Media has been in the media business for the last four years with its most acclaimed magazine "Sheger Times" which could achieve a wide public a...

Address

Addis Ababa

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00
Sunday 09:00 - 17:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mereja.net -መረጃ.net posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share


Other Media/News Companies in Addis Ababa

Show All

You may also like