AFTA MEDIA አፍታ ሚዲያ

AFTA MEDIA አፍታ ሚዲያ Afta Media ‘Voice of Reason’ is your Ethiopian idea platform. We provide you with the la

ነጋዴውን ከገበያተኛው የሚያገናኝ ኢትዮጋይድ የተሰኘ የሞባይል መተግበርያ  ይፋ ተደረገ።በፍለጋ አይድከሙ በማለት የተለያዩ ድርጅቶችን(መደብሮችን)፤ ሆቴሎችን  እና የተለያየ የሙያ ዘርፍ ነጋዴ...
19/10/2023

ነጋዴውን ከገበያተኛው የሚያገናኝ ኢትዮጋይድ የተሰኘ የሞባይል መተግበርያ ይፋ ተደረገ።

በፍለጋ አይድከሙ በማለት የተለያዩ ድርጅቶችን(መደብሮችን)፤ ሆቴሎችን እና የተለያየ የሙያ ዘርፍ ነጋዴዎችን በቀላሉ ለማግኘት የሚችል መተግበሪያ ይፋ ተደረገ።

የተለያዩ የንግድ ድርጅት ባለቤቶች ኢትዮጋይድ የተሰኘ መተግበርያውን በመጠቀም (Yellow Page) እንዲመዘገብ በማድረግ ለተጠቃሚዎች አድራሻቸውን ፣ የስልክ ቁጥራቸውን፣ የቅርንጫፋቸውን ብዛት እና መሰል መረጃዎችን በቀላሉ እንዲገኙ የሚያደርግ አፕሊኬሽን መሆኑ ተገልጿል ።

ኢትዮጋይድ(Ethioguide) የተሰኘው መተግበሪያ በቴክኖሎጂ በመታገዝ እጅግ ዘመናዊ እና ጊዜውን የዋጀ አገልግሎት እንዲሆን ከፍ ተደርጎ የተሠራ የሞባይል መተግበሪያ መሆኑ የአይቲ ባለሙያ የሆኑት አቶ ኃይለየሱስ ዘሪሁን ገልጸዋል መተግበርያው በአሜሪካን ኮሎራዶ ከተማ እየሰራ ያለ መሆኑን ጠቅሰው ወደ ኢትዮጵያም በማምጣት የንግድ ድርጅቶች ከደንበኞቻቸው ጋር በቀላሉ እንዲተዋወቁ ብሎም ተጠቃሚዎች በአቅራቢያቸው ያሉትን ጠቃሚ መደብሮች በስልካቸው ላይ በማሳየት እና ከመደብሮቹ ጋር እንዲገናኙ የሚያደርግ ቴክኖሎጂ ነው ሲሉ አስረድተዋል።

መተግበርያውንም በመጠቀም የትኛውም ግለሰብ በቀላሉ የሚፈልገውን የንግድ ድርጅት ስም ወይንም ስልክ በማስገባት መረጃ ማግኘት እንዲችል የሚያደርግ መድረክ(Platform) መሆኑን የገለጹት የድርጅቱ የሚፈለገው የንግድ ድርጅት(መደብር) የት እንደሚገኝ ፤ ምን አገልግሎት እንደሚሰጥ ፣ ደብሩን ማነጋገር ቢፈለግ በቀላሉ መደወል፤ ቦታውን በመጠቆም ወይም መልዕክት መላክ እንዲቻል ተደርጎ የተሠራ መተግበሪያ ነው።

መተግበሪያው ለተጠቃሚዎች ቀላል ፣ ግልጽ እና ተደርጎ የተሠራ ስለሆነ ተጠቃሚዎች ብዙ ሳይደክሙ በቀላሉ የሚፈልጉትን የንግድ መደብሮችን ፣አሁነኛ እና የተጣሩ መረጃዎች ለተጠቃሚዎች ቀላል በሆነ መልኩ ይዞ መቅረቡንም መስራቾቹ አስታውቀዋል።

ታዳጊ ሴቶች የነገ ሳይንቲስቶች፣ መሪዎች እና የሀገር ተረካቢዎች ስለሆናችሁ ጠንክራችሁ ተማሩ፣ ብቁ ዜጋ ለመሆን ትጉ"የዘንድሮው የታዳጊ ሴቶች ቀን በአለም ለ11ኛ ጊዜ "Invest in gir...
19/10/2023

ታዳጊ ሴቶች የነገ ሳይንቲስቶች፣ መሪዎች እና የሀገር ተረካቢዎች ስለሆናችሁ ጠንክራችሁ ተማሩ፣ ብቁ ዜጋ ለመሆን ትጉ"

የዘንድሮው የታዳጊ ሴቶች ቀን በአለም ለ11ኛ ጊዜ "Invest in girls right: our leadership our well-being!" በሀገራችን ለ10ኛ ጊዜ "ታዳጊ ሴቶችን እናብቃ፣ መብትና ደህንነታውንም እናስጠብቅ!" በሚል መሪ-ቃል በፓናል ውይይት ባሳለፍነው አርብ ተከበረ፡፡
የፓናል ውይይቱ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከፕላን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ሲሆን የፕላን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ምክትል ካንትሪ ዳይሬክተር ወ/ሮ መቅድም ጉልላት፣ የወጣቶች መማክርት ቦርድ ምክትል ሰብሰቢ ወ/ሪት ሐናዲ የሱፍ እንዲሁም የካናዳ አምባሳደር በኢትዮጵያ የተከበሩ ጆሽዋ ታባህ በመድረኩ ላይ በመገኘት መልዕክቶቻቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ከተከበረው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሴቶች ኮከ ሰብሳቢን ወክለው የተገኙት የተከበሩ ወ/ሮ ታፈሰች ሙላት ደግሞ ዕለቱን በማስመልከት ለታዳጊ ሴቶች አነቃቂ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
በንግግራቸውም "ይህች ቀን የተለየች ናት ለብዙዎቻችን የበፊት የወጣትነት ጊዜያችንን የሚያስታውስ ነው ያሉ ሲሆን፣ የአሁን ታዳጊ ሴቶች የነገ ሳይንቲስቶች፣ መሪዎች እና የሀገር ተረካቢዎች ስለሆናችሁ ጠንክራችሁ ተማሩ፣ ብቁ ዜጋ ለመሆን ትጉ" ሲሉ መክረዋል፡፡
የእለቱን መድረክ በይፋ የከፈቱት የሴቶች ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አማካሪ ወ/ሮ ዘቢደር ቦጋለ በንግግራቸውም ላይ በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ ግጭቶች ምክንያት ታዳጊ ሴቶች ለከፋ ችግር እንዳይጋለጡ ልንጠብቃቸው ይገባል ያሉ ሲሆን ሚኒስቴር መ/ቤቱ በዚህ ረገድ እየሰራ ያለውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አጽንኦት ሰጥተው ገልፀዋል፡፡
በበአሉ ላይ ጽሁፍ እና የፎቶ ኤግዚቢሽን የቀረበ ሲሆን በዓሉን አስመልክቶ በተዘጋጀው የፓናል ውይይትም ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከትምህርት ሚኒስቴር፣ ከኢትዮጵያ ወጣቶች ካውንስል፣ ከትምራን ኢትዮጵያ እንዲሁም ከዩኤን ውሜን የሴት አምባሳደርና ከወጣቶች ፓናል አድቫይዘሪ የተውጣጡ አካላት ተሳትፈዋል፡፡

ከአብርሆት ቤተ መጽሐፍት ወደ 24 ሚሊዮን የሚጠጋ መጽሐፍ መዘረፉ ተነገረ😳😳ከአብርሆት ቤተ መጽሐፍት ወደ 24 ሚሊዮን የሚጠጋ መጽሐፍ መዘረፉ ተነገረ። የቤተ መጽሐፍቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ው...
09/10/2023

ከአብርሆት ቤተ መጽሐፍት ወደ 24 ሚሊዮን የሚጠጋ መጽሐፍ መዘረፉ ተነገረ😳😳

ከአብርሆት ቤተ መጽሐፍት ወደ 24 ሚሊዮን የሚጠጋ መጽሐፍ መዘረፉ ተነገረ። የቤተ መጽሐፍቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ውብአየሁ ማሞ እንደተናገሩት በጣም ከፍተኛ ዋጋ የሚያወጡ መጽሐፍት መወሰዳቸውን ተናግረዋል።

በዚህ የመጽሐፍ ዘረፋ የአብርሆት ስታፍ ሰራተኞች መሳተፋቸውን የተናገሩ ሲሆን፣ አስራት አራት የሚሆኑት መያዛቸውን ተናግረዋል። በአብርሆት ማንኛውንም እንቅስቃሴ የሚቆጣጠሩ ስድስት ካሜራዎች ባሉበት ሁኔታ መጽሐፍቶች መሠረቃቸው ተነጎሯል።

ከዚህ ሌላ መጽሐፍቶች ከላይብረሪ ያለፈቃድ ሲወጡ አላርም የሚያሰሙ ሲስተሞችም አሉት። ከእነዚህ ሌላ ፖሊሶች በህንጻው ላይ ቁጥጥር ያደርጋሉ። በአጠቃላይ የቴክኖሎጂና የፖሊስ ሀይል ቢኖርም የመጽሐፍ ስርቆቱን ሙሉ ለሙሉ መቆጣጠር አልተቻለም።

በአብርሆት መጽሐፍት ቤት ከ10ሺህ ብር በላይ የሚያወጡ በጣም ብዙ መጽሐፍት ይገኛሉ። በምስራቅ አፍሪካ አንደኛ ደረጃ እንዲሁም በአፍሪካሪ ከአስር ምርጥ ላይብረሪዎች አንዱ ነው።

ለቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት  የድጋፍና የልማት ማህበር  አባላቱና ቤተሰቦቻቸው ድጋፍ አደረገ  የኢትዮጵያ ሰራዊት የድጋፍና የልማት ማህበር በህግ አግባብ የተቋቋመ እና በመላው ሀገራችን 295 ...
03/10/2023

ለቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት የድጋፍና የልማት ማህበር አባላቱና ቤተሰቦቻቸው ድጋፍ አደረገ

የኢትዮጵያ ሰራዊት የድጋፍና የልማት ማህበር በህግ አግባብ የተቋቋመ እና በመላው ሀገራችን 295 ቅርንጫፍ ቢሮዎችን በመክፈት ሜዳ ላይ ተበትነው የሚገኘውን የቀድሞ ሠፊዊትና ቤተሰቦቹን በማደራጀት ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸውን ሥራዎች በመስራት ላይ ይገኛል።

ይሁን እንጂ ማህበራችን ሰራዊቱ ካለው ብዛት አንፃር የማህበሩ አባላትን ለመደገፍ አቅም
ካለመኖሩ የተነሳ በዓላት በመጣ ቁጥር በጎ ህሊና ያላቸው ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ለሰራዊቱ አባላትና በህልውና የማስከበር ዘመቻ ወቅት ወደ ግዳጅ የገቡ የሰራዊት አባላት ቤተሰብን ጨምሮ ለበዓል የሚሆን አቅም የፈቀደን የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ የመጀመሪያ ባይሆንም

በዛሬው ቀን የመስቀል በዓልና የመውሊድ በዓልን ምክንያት በማድረግ አዳማ፣ሰበታ፣ወሊሶ ላሉት አባሎች ጨምሮ ለበዓል የገንዘብ ድጋፍ ተደረገላቸው

የኢትዮጵያ የቀድሞ ሰራዊት ድጋፍ እና ልማት ማህበር በስሩ ላሉት ለቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት አባላት የመውሊድ እና የመስቀል በአልን ምክንያት በማድረግ (የማዕድ ማጋራት)ገንዘብ ድጋፍ አድርጓል።

የገንዘብ ድጋፉ የተደረገው በአሜሪካ ከምትኖረው ቤቲ ግርማ(Tik tok family)ሲሆን ድጋፉም አንድ መቶ(100) ለሚሆኑ በኢኮኖሚ አንስተኛ ለሆኑ አባላቱ ነው።

ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።የመንበረ መንግስት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል እና የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የነበሩት ብ...
29/09/2023

ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።

የመንበረ መንግስት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል እና የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የነበሩት ብፁዕ አቡነ ሰላማ ዛሬ መስከረም 18 ቀን 2016 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።

ብፁዕ አቡነ ሰላማ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በአዲስ አበባ ሀሌሉያ ሆስፒታል በህክምና ላይ እንዳሉ ነው ከዚህ ዓለም ድካም ያረፉት።

የብፁዕነታቸውን የሽኝት መርሐ ግብር በተመለከተ በቋሚ ሲኖዶስ ዉሳኔ እንደተላለፈ የሚታወቅ መሆኑም ተገልጿል።

ወንድሞቻችን እንደእህቶቻችን በ Brazil Human hair እያጌጡ ነው
24/09/2023

ወንድሞቻችን እንደእህቶቻችን በ Brazil Human hair እያጌጡ ነው

21/09/2023

መሶብ ባህላዊ ባንድ

19/09/2023

🙏

WORLD RECORD 14:00.21!!! History in Oregon from Gudaf Tsegay as she smashes Faith Kipyegon's world 5000m record of 14:05...
17/09/2023

WORLD RECORD

14:00.21!!!

History in Oregon from Gudaf Tsegay as she smashes Faith Kipyegon's world 5000m record of 14:05.20 🔥

Speechless 🤯

የተከለከለው የኢትዮጵያ ታሪክ የተሰኘ መጽሀፍ     ተመረቀ።የተከለከለው የኢትዮጵያ ታሪክ የተሰኘው በአሸናፊ ፈንቴ የተጻፈው ጥናታዊ የታሪክ መጽሐፍ መስከረም 5/2016 ዓ.ም በሀገር ፍቅር ...
17/09/2023

የተከለከለው የኢትዮጵያ ታሪክ የተሰኘ መጽሀፍ ተመረቀ።

የተከለከለው የኢትዮጵያ ታሪክ የተሰኘው በአሸናፊ ፈንቴ የተጻፈው ጥናታዊ የታሪክ መጽሐፍ መስከረም 5/2016 ዓ.ም በሀገር ፍቅር ትያትር አዳራሽ በድምቀት ተመረቀ፡፡

በመጽሐፉ ምረቃ ስነስርአት ላይ ረዳት ፕሮፌሰር መኩሪያ መካሻ፣ዶክተር አለማየሁ አረዳ ስለ መጽሀፉ ዳሰሳ አቅርበዋል በተጨማሪም መጽሐፉ ይዞአቸው የመጡትን አዳዲስ የታሪክ ግኝቶች እና ሙግቶች አስመልክቶ በባለሙያዎች የመጽሐፍ ዳሰሳ፣ልዩ የኪነ-ጥበብ ዝግጅቶች፣ቅንጭብ ትረካዎች እና ሌሎች ዝግጅቶችም ቀርበዋል፡፡

መጽሐፉ ትኩረቱን ያደረገው የመካከለኛው ክፍለ ዘመን በተለይም ደግሞ ከ1133 እስከ 1333 ዓ.ም የነበሩት ሁለት መቶ ዓመታት በታሪክ ጥናት ከመረጃ እጥረት አንጻር "የጨለማው ዘመን" እየተባለ በሚጠራው ዘመን ውስጥ የሚካተቱ ሲሆን መጽሀፉ የኢትዮጵያ ታሪክ ዘርፈ-ብዙ (Multi Disciplinary) የጥናት ስልትን ተከትሏል፡፡

የተከለከለው የኢትዮጵያ ታሪክን ጨምሮ ሌሎች ሶስት መጽሀፍትን ለመጻፍ ላለፉት 16 ዓመታት ብዙ ጥናቶች እና በቂ ጊዜ ተወስዶበት የተሠራ ምርምር መሆኑን እና በቀጣይም ከዚህ የቀጠሉ ሶስት እትሞች እንደሚቀሩም የመጽሀፉ ደራሲ አቶ አሸናፊ ፈንቴ አስረድተዋል።

ደራሲው መጽሀፉንም ለመጻፍ ከአንድ ሺህ በላይ ማጣቀሻዎችን ተጠቅመዋል፡፡

በዚህም የአርኪዮሎጂ፣ የአንትሮፖሎጂ፣ የፖፒውሌሽን ጀነቲክስ፣ የታሪክ፣ የብራና ምንጮች እና ሳይንሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች (ባይብል ስኮላርሽፕ) በስፋት ሥራ ላይ ውሏል፡፡

በተለይም ፖፒውሌሽን ጀነቲክስ የተባለው የዘመናችን ትንግርታዊ ሳይንስ በኢትዮጵያ ቅድመ-ታሪክ እና ጥንታዊ ታሪክ ላይ ሥራ ላይ ውሏል፡፡

ይህ የምረቃ ዝግጅት ብራና ማስታወቂያ ሃ/የተ/የግ/ማህበር አስተባብሮታል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከአዲስ አበባ ኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እውቅና ተሰጥቷቸዋል::ከንቲባ አዳነች አቤቤ በከተማችን አዲስ አበባ ሰላም እና አብሮነት እንዲጎለብት ፣ በተለያዩ ሰው ተኮር ስራዎ...
14/09/2023

ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከአዲስ አበባ ኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እውቅና ተሰጥቷቸዋል::

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በከተማችን አዲስ አበባ ሰላም እና አብሮነት እንዲጎለብት ፣ በተለያዩ ሰው ተኮር ስራዎች አመራሩንና ህዝቡን በማስተባበር ዝቅ ብለው የነዋሪውን ጥያቄ ለመመለስ እያደረጉት ላለው ተግባር እና ከሁሉም የሃይማኖር ተቋማት ጋር በቅርበት ፣ በእኩልነትና በፍትሃዊነት በመስራት ላሳዩት ቁርጠኝነት የአዲስ አበባ ኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ቦርድ እውቅና ሰጥቷቸዋል::

በእውቅና መርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ የኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ለሰጣቸው እውቅና ምስጋናቸውን አቅርበዋል::

10/09/2023
የኢትዮጵያ የቀድሞ ሰራዊት ድጋፍ  እና ልማት ማህበር  የትውልድ ቀንን እንዲሁም የዘመን መለወጫን  አስመልክቶ ለቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት አባላት(የማዕድ ማጋራት)ገንዘብ ድጋፍ አድርጓል።በማዕ...
10/09/2023

የኢትዮጵያ የቀድሞ ሰራዊት ድጋፍ እና ልማት ማህበር የትውልድ ቀንን እንዲሁም የዘመን መለወጫን አስመልክቶ ለቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት አባላት
(የማዕድ ማጋራት)ገንዘብ ድጋፍ አድርጓል።

በማዕድ ማጋራቱ ወቅት የቀድሞ ሰራዊት አባላት ማህበር ፕሬዝደንት የሆኑት 50 አለቃ ብርሃኑ አማረ እንደተናገሩት የቀድሞ ሰራዊት ትውልድን ለማስቀጠል ብዙ ዋጋ እንደከፈለና ይህን ታሳቢ በማድረግም ከ አንድ መቶ በላይ ሰዎች የ ድጋፍ እንደተደረገ ገልጸዋል።

በማዕድ ማጋራቱ ከተለያዮ አርቲስቶችና ተቋማት የገንዘብ አስተዋጽኦ አድርገዋል።

አሳዛኝ ዜና !ከሁለት ሳምንታት ፍለጋ በኋላ ፖሊስ የዮሐንስ ኪዳኔን አስክሬን በሳንፍራንሲስኮ የባህር ወሽመጥ ውሀ ላይ ተንሳፎ ማግኘቱን አስታውቋል😭😭😭😭************************...
07/09/2023

አሳዛኝ ዜና !
ከሁለት ሳምንታት ፍለጋ በኋላ ፖሊስ የዮሐንስ ኪዳኔን አስክሬን በሳንፍራንሲስኮ የባህር ወሽመጥ ውሀ ላይ ተንሳፎ ማግኘቱን አስታውቋል😭😭😭😭
*******************************************************
ማክሰኞ ነሐሴ 29/2023 ቀን ከሳን ፍራንሲስኮ የባህር ወሽመጥ ላይ በውሃ ውስጥ ምላሽ የማይሰጥ ሰው መታየቱን ጥቆማ ለመርማሪዎች ከደረሳቸው በኋላ አስክሬኑን ከውሀ ውስጥ ያወጡት ሲሆን የአስከሬን ምርመራው ውጤት አስከሬኑ የዮሐንስ ኪዳኔ መሆኑን አረጋግጧል።

የሞቱን መንስኤ ራስን ማጥፋት መሆኑን የማሪን ካውንቲ የሸሪፍ ጽህፈት ቤት ዛሬ ያስታወቀ ሲሆን የ22 አመቱ ወጣት የከባድ ጉልበት ጉዳት እና ውሀ ውስጥ መስጠም ለህይወቱ ማለፍ አስተዋፅኦ አድርጓል።

ዮሐንስ በቅርቡ ከኮርኔል ዩኒቨርስቲ ተመርቆ በታዋቂው ኔትፍሌክስ የሶፍትዌር ኢንጂነርነት ተቀጥሮ ለመስራት ከመጥፋቱ ሁለት ሳምንት በፊት ከኒውዮርክ መሄዱ ይታወቃል። ስልኮቹ እና የኪስ ቦርሳው ጎልደን ጌት ድልድይ አካባቢ ከጠፋ በኋላ ተገኝተው የነበረ ሲሆን ለመጨረሻ ግዜ የታየው ከሁለት ሳምንታት በፊት በኡበር ታክሲ ሲሳፈር ነው።

በትልቅ ተስፋ እና ፅናት ሲያፈላልጉት ለነበሩት ቤተሰቦቹ ፈጣሪ መፅናናቱን ይስጥ።

ቢጂአይ ኢትዮጵያ የስፖንሰርሺፕ ውል አቃረጠበሸራተን የአዲስ አመት ዋዜማ ኮንሰርት  አጋር ከሆኑት መካከል ቢጂአይ ኢትዮጵያ አንዱ የነበረ ሲሆን የህዝብ ጥያቄ መሠረት በማድረግ ኘሮግራሙን አጋ...
05/09/2023

ቢጂአይ ኢትዮጵያ የስፖንሰርሺፕ ውል አቃረጠ

በሸራተን የአዲስ አመት ዋዜማ ኮንሰርት አጋር ከሆኑት መካከል ቢጂአይ ኢትዮጵያ አንዱ የነበረ ሲሆን የህዝብ ጥያቄ መሠረት በማድረግ ኘሮግራሙን አጋርነት ሙሉ በሙሉ ያቋረጠ መሆኑን ዛሬ ማምሻውን በደረሠን መረጃ ለማወቅ ችለናል።

ከመቅደላ የተዘረፈ ቅርስ ለኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ተመለሰአርብ ነሐሴ 26 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) በመቅደላ አምባ በወቅቱ ከተዘረፉ ቅርሶች መካከል የቅዱስ ሚካኤል መስቀል እንደሆነና፤...
01/09/2023

ከመቅደላ የተዘረፈ ቅርስ ለኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ተመለሰ

አርብ ነሐሴ 26 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) በመቅደላ አምባ በወቅቱ ከተዘረፉ ቅርሶች መካከል የቅዱስ ሚካኤል መስቀል እንደሆነና፤ በወቅቱ ከመቅደላ የተወሰደ መሆኑን በእንግሊዘኛ የተከተበበት ቅርስ ሩት ኢማኑኤል ዛሬ ነሐሴ 26/2015 ለኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን አስረክበዋል።

በርክክቡ ወቅት ክብርት አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ፣ ዶ/ር አሉላ ፓንክረስ፣ ረ/ፕ አበባው አያሌው፣ ኩመራ ዋቅጅራ በተገኙበት ርክክብ መደረጉን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል።

አዲስ ማለዳ

በአባቷ ሱቅ ውስጥ ተቀጥረው በሚሰሩ  አራት ወንዶች በደቦ ከተደፈረች በኌላ በገመድ ተሰቅላ የተገደለች ፋጡማ ኡጋስ ይህች ነበረች። ወንጀሉ በሱማሌ ክልል በጅግጅጋ ከተማ ውስጥ ባለፈው እሁድ ...
31/08/2023

በአባቷ ሱቅ ውስጥ ተቀጥረው በሚሰሩ አራት ወንዶች በደቦ ከተደፈረች በኌላ በገመድ ተሰቅላ የተገደለች ፋጡማ ኡጋስ ይህች ነበረች። ወንጀሉ በሱማሌ ክልል በጅግጅጋ ከተማ ውስጥ ባለፈው እሁድ ነው የተፈጸመው። አባቷ ቢቢሲ ላይ ቀርቦ የፍትህ ያለ እያለ ነው። በየጥጉ፣ በየማህበረሰቡ ውስጥ አውሬ አውሬ ሞልቶናል። ሴት ከምድር ላይ የጠፋች ይመስል ይህችን አንድ ፍሬ ህጻን በደቦ ካሰቃዩአት በኋላ ወንጀሉን እንዳትናገር በገመድ ሰቅለው ገደሏት።

የሶማሌ ክልል መንግስት ወንጀል ፈጻሚዎቹ ላይ ትኩረት በማድረግ በቁጥጥር ስር በማዋል ህጋዊ እና አስተማሪ የሆነ እርምጃ ሊያደርግ ይገባል።

Gumaa Saqqataa Gem

5000 ሜትር ዳይመንድ ሊግ ወንዶች ውጤት 1ኛ ዮሚፍ ቀጄልቻ2ኛ ሰለሞን ባረጋ
31/08/2023

5000 ሜትር ዳይመንድ ሊግ ወንዶች ውጤት
1ኛ ዮሚፍ ቀጄልቻ
2ኛ ሰለሞን ባረጋ

በመዲናዋ ከባዕድ ነገር ጋር ተቀላቅሎ ለገበያ ሊቀርብ የነበረ አምስት ማዳበሪያ ቅይጥ ቂቤ በቁጥጥር ሥር ዋለበአዲስ አበባ ከተማ፣ ንፋስ ስልክ ላፎቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ልዩ ሥሙ ቻይና ...
31/08/2023

በመዲናዋ ከባዕድ ነገር ጋር ተቀላቅሎ ለገበያ ሊቀርብ የነበረ አምስት ማዳበሪያ ቅይጥ ቂቤ በቁጥጥር ሥር ዋለ

በአዲስ አበባ ከተማ፣ ንፋስ ስልክ ላፎቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ልዩ ሥሙ ቻይና ካምፕ ማርያም ሰፈር ተብሎ በሚጠራ አካባቢ፤ የኅብረተሰቡን ጤና ሊጎዳ በሚችል መልኩ ቅቤን ከባዕድ ነገር እና ካላስፈላጊ ምርቶች ጋር በመቀላቀል ለገበያ ሊቀርብ የነበረ አምስት ማዳበሪያ ቅይጥ ቂቤ በቁጥጥር ሥር መዋሉ ተገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በትላንትናው ዕለት ባካሂደው የገበያ ቅኝት ሥራ በቁጥጥር ሥር ካዋለው አምስት ማዳበሪያ ቅይጥ ቂቤ በተጨማሪ፤ 691 ኪሎ ለመቀላቀያ የሚውል የአትክል ቅቤ መያዙንም አስታውቋል፡፡

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ንፋስ ስልክ ላፎቶ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ፣ የጀሞና አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ጋር በቅንጅት ባደረገው የቁጥጥር ሥራ፤ በአካባቢው በአንድ ግለሰብ አማካኝነት ንጽሕናው በተጓደለ ቤትና ቁሳቁሶች ቅቤን ከተለያዩ የዘይት ምርቶችና ከባዕድ ነገር ጋር በመቀላቀል ወደ ገበያ ለማቅረብ ሲዘጋጅ በቁጥጥር ሥር መዋሉ ተነግሯል።

ምርቱ ከቁጥጥር ባለሙያዎች አልፎ ገብያ ላይ ቢውል፤ የኅብረተሰቡን ጤና አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ በተለይ በዓል ሲቃረብ ተመሳሳይ ሕገወጥ ድርጊቶች በስፋት የሚስተዋሉ በመሆኑ ኅብረተሰቡ በሚገዛቸው ምርቶች ላይ ከዚህ በፊት ከሚያውቀው የሽታ፣ የጣዕም፣ የቀለምና የመጠን ለውጥ እንዲለይ ተጠይቋል፡፡

ኅብረተሰቡ የተለየ ነገር ካስተዋለ በባለስልጣኑ ነጻ የስልክ መስመር 8482 በመደወል ወይም በአቅራቢያው ለሚገኙ ፖሊሲና የጤና ተቆጣጣሪ አካላት ማሳወቅ እንዳለበት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አሳስቧል።

አዲስ ማለዳ

በነዳጅ ምርቶች ላይ የተደረገው ጭማሪ ምን ያህል ነው ?ላለፉት ወራት ማለትም እስከ ትላንት ድረስ ቤንዚን በሊትር 69 ብር ከ52 ሳንቲም ሲሸጥ የነበረ ሲሆን ከዛሬ ጀምሮ ግን በሊትር 74 ብ...
29/08/2023

በነዳጅ ምርቶች ላይ የተደረገው ጭማሪ ምን ያህል ነው ?

ላለፉት ወራት ማለትም እስከ ትላንት ድረስ
ቤንዚን በሊትር 69 ብር ከ52 ሳንቲም ሲሸጥ የነበረ ሲሆን ከዛሬ ጀምሮ ግን በሊትር 74 ብር ከ85 ሳንቲም እንዲሸጥ ተወስኗል።

ነጭ ናፍጣ በሊትር 71 ብር ከ15 ሳንቲም ሲሸጥ የነበረ ሲሆን ወደ 76 ብር ከ34 ሳንቲም ከፍ ብሏል።

የቤንዚን እንዲሁም የነጭ ናፍጣ ላይ የደረገው የዋጋ ጭማሪ ከ5 ብር በላይ ነው።

ኬሮሲን በሊትር 71 ብር ከ15 ሳንቲም ሲሸጥ የነበረ ሲሆን ከ5 ብር በላይ ጭማሪ ተደርጎ በሊትር 76 ብር ከ34 ሳንቲም ገብቷል።

የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር 65 ብር ከ35 ሳንቲም የነበረው ከ3 ብር በላይ ጭማሪ ተደርጎ አሁን 68 ብር ከ58 ሳንቲም በሊትር ገብቷል።

ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 57 ብር ከ97 ሳንቲም የነበረው ከ4 ብር በላይ ጭማሪ ረደርጎ 62 ብር ከ22 ሳንቲም በሊትር ገብቷል።

ከባድ ጥቁር ናፍጣ ደግሞ በሊትር 56 ብር ከ63 ሳንቲም የነበረው 61 ብር ከ07 ሳንቲም ገብቷል።

ሚያዚያ ወር 2015 ላይ ጭማሪ ከተደረገ በኃላ እስከ ትላንት ድረስ የነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪ ሳይደረግ ባለበት እንዲቀጥል ተወስኖ የነበረ ሲሆን የዓለም የነዳጅ ዋጋ በመጨመሩ ምክንያት አሁን ላይ የነዳጅ ዋጋ መጨመር እንዳስፈለገ ተነግሯል።

" አዲሱ አልበሜ እንዳይሸጥ በፖሊስ ተከልክሏል ሰላም ሰላም እንዴት ናችሁ ! በትናትናው እለት እንደ አባቴ እወድሻለሁ የተሰኘው አዲሱ አልበሜ በአዲስ አበባ እንዳይሸጥ በፖሊስ ተከልክሏል እን...
29/08/2023

" አዲሱ አልበሜ እንዳይሸጥ በፖሊስ ተከልክሏል
ሰላም ሰላም እንዴት ናችሁ !

በትናትናው እለት እንደ አባቴ እወድሻለሁ የተሰኘው አዲሱ አልበሜ በአዲስ አበባ እንዳይሸጥ በፖሊስ ተከልክሏል እንዲህ ስለሆነ ለሀገሬ እና ለህዝቦቿ ያለኝ ፍቅር አይቀንስም እንደ አባቴ እወድሻለሁ።

አቡሽ ዘለቀ

ታቦታቱ ከጊዜያዊ መቃኞ ወደ መንበረ ክብራቸው እንደሚገቡ የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስታወቀ።============================== የአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኀኔዓለ...
28/08/2023

ታቦታቱ ከጊዜያዊ መቃኞ ወደ መንበረ ክብራቸው እንደሚገቡ የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስታወቀ።
==============================

የአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን ታሪካዊ ይዘቱን ጠብቆ ሕንጻ እድሳቱ ተጠናቆ የፊታችን አርብ ነሐሴ26/2015ዓ.ም በብጹዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተባርኮ ታቦታቱ ከጊዜያዊ መቃኞ ወደ መንበረ ክብራቸው እንደሚገቡ የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ዛሬ በሰጠው መግለጫ ገልጿል። የደብሩ ዋና አስተዳዳሪ ሊቀ ጉባኤ ቆሞስ አባ ሕሩይ የቤተመቅደሱ እድሳት አንድ ዓመት ከመንፈቅ የፈጀ ሲሆን ታሪካዊ ይዘቱን በጠበቀ መንገድ እድሳቱ እንደተጠናቀቀ ገልጸው የፊታችን አርብ ነሐሴ 26/2015ዓ.ም ከቀኑ ስምንት ሰዐት ጀምሮ ብጹአን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቤተመቅደሱን እንደሚባርኩ እና ሌሊት ስብሐተ እግዚአብሔር (ማኅሌት) ተቁሞ በበነጋታው ነሐሴ 27/2015ዓ.ም ታቦታቱ በመውጣት(በማንገሥ) ምእመኑን እንደሚባርኩ ገልጸዋል። የቤተመቅደስ እድሳቱን ምክንያት በማድረግ ከነሐሴ 26-28 ተከታታይ ለሦስት ቀናት የሚቆይ የሰርክ ጉባኤ መዘጋጀቱንና በዕለቱም መምህራነ ወንጌልና ዘማርያን እንደተጋበዙ የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ገልጿል።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምክትል ቴክኒክ ዳይሬክተር ከአውስትራሊያ ሳትመለስ ቀረች።የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የቴክኒክ ክፍል ምክትል ቴክኒክ ዳይሬክተር እና የሴቶች ልማት ባለሙያ ...
28/08/2023

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምክትል ቴክኒክ ዳይሬክተር ከአውስትራሊያ ሳትመለስ ቀረች።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የቴክኒክ ክፍል ምክትል ቴክኒክ ዳይሬክተር እና የሴቶች ልማት ባለሙያ አልማዝ ፍስሀ አውስትራሊያ መጥፏቷ ታውቋል።

ለትርታ ስፖርት ውስጥ አዋቂዎች ባደረሱት መረጃ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ ፣ የጽ/ቤት ሀላፊው አቶ ባህሩ ጥላሁን እና የሴቶች ልማት ባለሙያዋ አልማዝ ፍስሀ ከሴቶች የአለም ዋንጫ ፍፃሜ ጋር ተያይዞ ወደ አውስትራሊያ ተጉዘው እንደነበር ይታወሳል።

ይሁን እንጂ የፌዴሬሽኑ ምክትል ቴክኒክ ዳይሬክተር እና የሴቶች ልማት ባለሙያ አልማዝ ፍስሀ ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም አውስትራሊያ መቅረቷ ታውቋል። ከዚህ ቀደም ባለሙያዋ በፌዴሬሽኑ እገዳ ተጥሎባት እንደነበርና በደል ተፈፅሞብኛል ማለቷ አይዘነጋም። በፌዴሬሽኑ ወደ አሜሪካ ተጉዞ የነበረው የቀድሞው ቴክኒክ ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ፍራንኮ፣ እንዲሁም በአሜሪካ የብሄራዊ ቡድን ጉዞ ወቅት ትጥቅ ያዥ እና የቡድኑ ወጌሻ መጥፋታቸው ይታወሳል።

Afro addis infotainment

ለረዥም ዓመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ በግል እና በፓርቲ ደረጃ ተሳታፊ የነበሩት አቶ በቀለ ገርባ ከፓርቲያቸው ለቀው በአሜሪካ ጥገኝነት መጠየቃቸውን ለቢቢሲ ተናገሩ።BBCFidel post
28/08/2023

ለረዥም ዓመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ በግል እና በፓርቲ ደረጃ ተሳታፊ የነበሩት አቶ በቀለ ገርባ ከፓርቲያቸው ለቀው በአሜሪካ ጥገኝነት መጠየቃቸውን ለቢቢሲ ተናገሩ።

BBC

Fidel post

አትሌት ሰለሞን ባረጋ ከመኪና አደጋ ተረፈ‼አትሌት ሰለሞን ባረጋ ትላንት የጫካ ልምምዱን አጠናቆ ወደ ከተማ ሲመለስ በአዲስ አበባ ከተማ የካ ክፍለ ከተማ ውስጥ በሚገኘው ሾላ ገቢያ ውስጥ ሰለ...
27/08/2023

አትሌት ሰለሞን ባረጋ ከመኪና አደጋ ተረፈ‼

አትሌት ሰለሞን ባረጋ ትላንት የጫካ ልምምዱን አጠናቆ ወደ ከተማ ሲመለስ በአዲስ አበባ ከተማ የካ ክፍለ ከተማ ውስጥ በሚገኘው ሾላ ገቢያ ውስጥ ሰለሞን የሚያሽከረክራት መኪና ከሌላ መኪና ጋር የተጋጨ ሲሆን የአደጋው መንስኤ ቅድሚያ ባለመሰጣጠት የመጣ መሆኑ ተነግሯል።

በአደጋው ከስለሞን ጋር ከነበሩት ሁለት አትልቶች መጠነኛ ጉዳት ከማጋጠሙ ውጪ በአትሌት ሰለሞንም ሆኖ በሌሎች ሰዎች ላይ ምንም አይንት ጉዳት አልደረሰም።

አትሌት ሰለሞን ከቀናት በፊት የተመዘገበው ውጤት ከልፋታችን ጋር የማይመጣጠን ነው ከልቤም አዝኛለሁ በማለት ወደ ኢትዮጵያ መመለሱን ሀትሪክ ስፖርት ዘግቦ ነበር።
@ሀትሪክ ስፖርት
Getnet temesgen

አልተሳካም!የ5000 ሜትር የሴቶች ፍፃሜ ውድድር በኬንያ የበላይነት ተጠናቀቀ።ሁለተኛ ሲፋን ሀሰን ወጥታለች።ሶስተኛ ኬንያ፤ አምስት ፣ ስድስት ፣ ሰባት የኢትዮጵያ አትሌቶች ወጥተዋል።
26/08/2023

አልተሳካም!

የ5000 ሜትር የሴቶች ፍፃሜ ውድድር በኬንያ የበላይነት ተጠናቀቀ።

ሁለተኛ ሲፋን ሀሰን ወጥታለች።

ሶስተኛ ኬንያ፤ አምስት ፣ ስድስት ፣ ሰባት የኢትዮጵያ አትሌቶች ወጥተዋል።

5000ሜ ፍፃሜ ውድድር ጀምሯል ሀገራችን ለተጨማሪ ሜዳልያ የምትጠበቅበት የ5000ሜ ሴቶች ፍፃሜ ውድድር በአሁኑ ሰዓት መካሄዱን ጀምሯል።ሀገራችን ኢትዮጵያ በውድድሩ ፦- በጉዳፍ ፀጋይ፣ - በ...
26/08/2023

5000ሜ ፍፃሜ ውድድር ጀምሯል

ሀገራችን ለተጨማሪ ሜዳልያ የምትጠበቅበት የ5000ሜ ሴቶች ፍፃሜ ውድድር በአሁኑ ሰዓት መካሄዱን ጀምሯል።

ሀገራችን ኢትዮጵያ በውድድሩ ፦
- በጉዳፍ ፀጋይ፣
- በእጅጋየሁ ታዬ፣
- በመዲና ኢሳ፣
- በፍሬወይኒ ኃይሉ ተወክላለች።

በዚሁ ፤ የ5000 ሜትር ውድድር ላይ የኔዘርላንዷ ሯጭ ሲፋን ሀሰን ብርቱ ፉክክር ታደርጋለች ተብሎ ይጠበቃል።

መልካም ዕድል ለአትሌቶቻችን !

ውድ ኢትዮጲያዊያን     በተሳሳተ መረጃ  ብዠታ የፈጠረውን በፌደሬሽኑ የተሰጠው መግለጫ  ከተጠያቂነት ለመሸሽ እና ሙሉበሙሉ ውሸት እና ጥፋትን ላለመቀበል የተቀነባበረ በመሆኑን በማስረጃ አስ...
26/08/2023

ውድ ኢትዮጲያዊያን
በተሳሳተ መረጃ ብዠታ የፈጠረውን በፌደሬሽኑ የተሰጠው መግለጫ ከተጠያቂነት ለመሸሽ እና ሙሉበሙሉ ውሸት እና ጥፋትን ላለመቀበል የተቀነባበረ በመሆኑን በማስረጃ አስረድቼ ወደ ዛሬው መልክቴ አልፋለሁ፤

በ 19ኛው የአለም አትሌቲክስ ሻምፕዮና በሃንጋሪ ቡዳፔስት፤ በ 5ሺህ ሜትር ርቀት ሀገሬን ለማስጠራት ሰንደቋ ከፍ ብላ ሲውለበለብ ለማየት፤ ቀን ከሌሊት ከደከምኩበት ዉድድር አላግባብ በመዉጣቴ፤ ልቤ ተሰብሮ በእምባ በስሜት የታጀበ ሀዘኔን አካፍያቹሁ ነበር።
በዋናነት ሐዘኔን ዕጥፍ ድርብ ያደረገው በመጨረሻው ሰዓት በኔ ቦታ ሌላ ሯጭ ከመተካቱ ባሻገር፤

1. ለየትኛውም የውድድር ተግባር ተጠባባቂ አትሌት ወደ ውድድር ስፍራ ሄዶ አያውቅም ዘንድሮም ተጠባባቂ አልተወሰደም ለምሳሌ በ3000m መሰናክል ወንድም ሴትም በማራቶንም እንዲሁም እኔ እንኳን ተጠባባቂ ነዉ ካሉ እንኳን ለምንድነዉ ታድያ 10000m ከሮጡ በዃላ ነበር ጠርተዉን የወሰዱኝ ፤
2. በብቃቴ ታምኖ በቋሚ ተወዳዳሪነት በአለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተመዝግቤ ያንገት የመወዳደሪያና እስቴድየም የመግቢያና አክሬድሽን ካርድ ጭምር ተሰቶኝም ስለነበረ እንዲሁም የመወዳዳርያ ቁጥር በስሜ ከወጣ እና በእጄ ከተሰጠኝ በኋላ ነበር እንደዚህ አይነት በደል የተፈጸመብኝ

3. በተጨማሪም ፌዴሬሽኑን የመጨረሻ የሽኝት ቀንም ለያአንዳዱ አሰልጣኝ በፖስታ አሽጎዉ አትሌቶች የሚወዳደሩበት ፊልድ ደልድሎም ሰጥቶ ስለነበረና የኔስምም በ3 ተኛነት በሪሁን በተጠባባቂነት አስቀመጠዉ ነዉ በፖስታም አሽገዉ ለያንዳንዱ አሰልጣኝ ሲሰጠዉ የኔም አሰልጣኝ ተሰጦትም ስለነበረ ለኔም አሰልጣኜ አሳይቶኝ ስለነበረ ምንም ጥርጥር እንዳያድርብኝ ስላደረገኝ ነዉ፤

ይሄ ከታች የምትመለከቱት ሆቴል መግቢያ የወጣና በወቅቱ ባለንሳአት የወጣ አስተላለፍ ሲሆን ዋናዉን የመጨረሻዉን ከታች አስቀምጫዋለሁ፤

ዋናዉና የመጨረሻዉ ለአሰልጣኞች በፖስታ ታሽጎ የተሰጠዉ ሊስት ደሞ ይሄ ነዉ

እንደዉም አንድ ቀን እስኪቀረው ድረስ እንደ ምሮጥ ሙሉ እምነት ስለነበረኝ ትሬኒጌን ጭምር እየሰራሁ ስለነበር ነዉ በድንገት ያስደነገጡኝ ቁጥር ተሰጥቶኝ እያለ እንዴት እንደዚህ አይነት ነገር ይፈጠራል ብዬ ላስብ
ለዛም ነዉ ጥልቅ ሀዘን ዉስጥ የከተተኝ የፌዴሬሽኑን መግለጫ ግን እንደሰማችሁት ነዉ ፤

ይሁን እንጂ የሁላችሁም ምላሽ ህይወቴን በለተለየ መንገድ እንድመለከት አድርጎኛል። ለናንተ ምስጋናዬን በምንም መንገድ መግለጽም አልቻልኩም። ሁላችሁንም አመሰግናለሁ።

የተበላሸዉ ባይስተካከልም፣ የጨለመዉ ህልሜ ባይበራም፣ ኢትዮጲያን ወክለዉ ለሚሮጡ ጀግኖች ጓደኞቼ ምርጡን ዉጤት እንዲገጥማቸው እመኝላቸዋለሁ።

በኔ ኢ ፍትሀዊ ከዉድድር በመዉጣት ምክንያት ሀገርን የሚወክሉ አትሌቶች አዝነዉ ስለነበረና በተለይ አብሮኝ የሚሰራዉና አብሮኝ ሊሳተፍ የነበረዉ አትሌት ዮሚፎ ቀጀልቻ ና የማራቶን አትሌቶች ጥሩ ስሜት ዉስጥ ስላነበሩና በሰሙት ነገር ተረብሸዉም ስለነበረ አእምሮዋቸዉ እንዳይዝል ለፍጻሜዉ ዉድድር ሞራላቸዉ እንዳይነካ ሁላችንም በጋራ ልንደግፋቸዉ ይገባል፤
ምክንያቱም እነሱም ልክ እንደ እኔ እዚህ ቦታ ለመድረስ ብዙ ዋጋ በመክፈልና ብዙ ላብ በማፍሰስ ከባድ ጉዳቶችም ጭምር ተቋቁመዉ ነዉ ይሄ ዉድ እና ከባድ የሆነዉን ቦታ የተገኙት ቢያንስ የነሱ ዉጤት የኔም ህመም ስለሚያክምልኝ፤

የምንጊዜም የጀግንነት እና የታታሪነት ተምሳሌቶች ከሆኑት ከቀደምት ጀግኖች አትሌቶቻችን የተማርኩት ይህንኑ ነዉና። በችግርም በድሎትም ጊዜ ሀገርን አስቀድመዉ አስደምመዉናል።

በህይወት ዘመኔ ሁሉ ያልጠበኩት ሀዘን ቢያጋጥመኝም፤
እንደሁልጊዜዉ ሁሉ ጓደኞቼ በሪሁ፣ ሀጎስ እና ዮሚፍ ሲሮጡ ' ጥሩ የሆነ የቡድን ስራ ሰርተዉ ለነሱም ለሀገራችንም ጥሩ የሆነ ታሪክ ሰርተዉ እንደ ሚያኩሩንና ጥሩ እድል እንደ ሚገጥማቸዉ ልባዉ ምኞቴ ነዉ።

ድል ለአገሬ ልጆች!!

ከፍ ካለ ምስጋና ጋር
አትሌት ጥላሁን ኃይሌ
ነሐሴ 20/2015ዓ.ም

ያለምንም  ማስያዣ የብድር አገልግሎት መስጠት ሊጀምር መሆኑን ካቻ ዲጅታል ፋይናንሺያል ሰርቪስ አስታወቀ።ካቻ ዲጂታል ፋይናንሺያል ሰርቪስ አማ በዲጂታል አማራጭ የሚቀርቡ አነስተኛ ብድሮች ላይ...
26/08/2023

ያለምንም ማስያዣ የብድር አገልግሎት መስጠት ሊጀምር መሆኑን ካቻ ዲጅታል ፋይናንሺያል ሰርቪስ አስታወቀ።

ካቻ ዲጂታል ፋይናንሺያል ሰርቪስ አማ በዲጂታል አማራጭ የሚቀርቡ አነስተኛ ብድሮች ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት እና ምንም አይነት መያዣ የማይጠየቅባቸው የዲጂታል ብድር አገልግሎቶችን ለማስጀመር ከነሰብ ኢንተርናሽናል ባንክ እና ከግሎባል ባንክ ኦፍ ኢትዮጵያ ጋር ተፈራርሟል።ለሚቀጥሉት 5 ዓመታት ከካቻ ጋር በጋራ ይሰራሉ ተብሏል።

በፊርማ ሥነ ስርዓቱ ወቅት የካቻ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አብረሃም ጥላሁን፤ “ዲጂታል ብድር ግለሰቦችን እንዲሁም የጥቃቅን፣ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን የብድር አግልግሎት ተጠቃሚ በማድረግ፤ የኢኮኖሚ እድገትን እና የፋይናንስ አካታችነትን ለማስፋት ከፍተኛ አቅም እንዳለው እናምናለን።" ብለዋል።

አክለውም “በድምር ከ 3.5 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች ካላቸው ከኹለቱ ቦንኮች ጋር ያደረግነው በጋራ የመስራት ስምምነት፤ የፋይናንስ አካታችነትን በማስፋት እና የብድር አገልግሎትን ለመደበኛ ኢኮኖሚው ተደራሽ በማድረግ፤ የዋጋ ንረትን ለመከላከል በብሔራዊ ባንክ ለሚወሰዱ እርምጃዎች አወንታዊ አስተዋፅኦ ይኖረዋል።” ሲሉ ገልጸዋል።

የንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት አብርሃም ተስፋዬ በበኩላቸው፤ “እንደ ባንክ የረጅም ዓመታት ልምድን፣ የቁጥጥር ማዕቀፎችን፣ ጥልቅ ግንዛቤ እና ጠንካራ የደንበኛ መሰረት ወደዚህ አጋርነት እናመጣለን።" ብለዋል።

አክለውም "ሰፊውን የኢንዱስትሪ እውቀታችንን በካቻ ከሚቀርቡት አዳዲስ እና ፈጠራ የታከለባቸው የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶች ጋር በማጣመር ለመላው ኢትዮጵያዊያን አዳዲስ እድሎችን መክፈት እና የደንበኞቻችንን የፋይናንስ ፍላጎቶች ማሟላት ቀዳሚ ሥራችን እና የትኩረት አቅጣጫችን ይሆናል።” ሲሉም ተናግረዋል።

የግሎባል ባንክ ኦፍ ኢትዮጵያ ምክትል ፕሬዝዳንት ሳህለሚካኤል መኮንን በበኩላቸው፤ በጋራ የመስራት ስምምነቱ ባንኩ በተለየ መንገድ ቀርፆ ወደ ትግበራ ባስገባው የ5 ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ መሰረት ከካቻ ጋር በጋራ በዲጂታል አማራጭ የሚቀርቡ አነስተኛ ብድሮችን ወደ ገበያ በማስገባት የጥቃቅን፣ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች እድገትን በማጎልበት የባንኩን ዘላቂ እድገት ያረጋገጥበት እንደሚሆን ተናግረዋል።

አገልግሎቱን ለማግኘት ብድር ፈላጊዎች የባንኮቹ ደንበኞች መሆን ይጠበቅባቸዋል ተብሏል።

ካቻ ዲጂታል ፋይናንሺያል ሰርቪስ አ.ማ ከኹለቱ ባንኮች በተጨማሪ በቅርቡ ከሌሎች ባንኮች እና የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ጋር ተመሳሳይ ስምምነቶችን በመፈፀም እና በፍጥነት ወደ ትግበራ እንደሚገባ ተነግሯል።

አማራ ክልል ዛሬ የተሰጠው ሹመት     👇1.አቶ አብዱ ሁሴን የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር2.ዶክተር አህመዲን መሐመድ  በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማት ዘርፍ አስተ...
25/08/2023

አማራ ክልል ዛሬ የተሰጠው ሹመት
👇
1.አቶ አብዱ ሁሴን የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር
2.ዶክተር አህመዲን መሐመድ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ እና የከተማ እና መሰረተ ልማት ቢሮ ኅላፊ
3.ዶክተር ድረስ ሳህሉ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የገጠር ዘርፍ አስተባባሪ እና የግብርና ቢሮ ኅላፊ
4.ዶክተር ሙሉነሽ ደሴ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማእረግ የማሕበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኅላፊ
5.አቶ ደሳለኝ ጣሰው በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአስተዳደር ጉዳዮች አስተባባሪ እና የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኅላፊ
6.ዶክተር ጋሻው አወቀ የአማራ ክልል መንገድ ቢሮ ኅላፊ
7.አቶ ብርሃኑ ጎሽም የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ኅላፊ
8.ዶክተር መንገሻ ፈንታው የአማራ ክልል ኮምዩኒኬሽን ቢሮ ኅላፊ
9.ዶክተር ስቡህ ገበያው የአማራ ክልል ሥራ እና ስልጠና ቢሮ ኅላፊ
10.አቶ ክብረት አህመድ የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኅላፊ
11.አቶ አብዱልከሪም መንግሥቱ የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ኅላፊ
12.ዶክተር ደመቀ ቦሩ የአማራ ክልል ፕላን እና ልማት ቢሮ ኅላፊ

ከላይ የተጠቀሱት ተሿሚዎች በእጩነት የቀረቡ ሲሆን ሌሎቹ ተቋማት ባሉበት እንደሚቀጥሉ ርእሰ መሥተዳድሩ ገልጸዋል፡፡

የምክር ቤት አባላቱ በእጩ ተሿሚዎች ላይ ሰፊ ውይይት እና ምክክር ካደረጉ በኋላ ሹመታቸውን አጽድቀዋል፡፡
አሚኮ

አሸብር ካብታሙ አረፈ !የ " ገመና ቁጥር 1 "  "ገመና ቁጥር 2 " እና " መለከት " የቴሌቪዥን ድራማዎች ዳይሬክተር አሸብር ካብታሙ ዛሬ ነሐሴ 19 2015 ዓ.ም ጠዋት 1 ሰዓት አካባቢ...
25/08/2023

አሸብር ካብታሙ አረፈ !

የ " ገመና ቁጥር 1 " "ገመና ቁጥር 2 " እና " መለከት " የቴሌቪዥን ድራማዎች ዳይሬክተር አሸብር ካብታሙ ዛሬ ነሐሴ 19 2015 ዓ.ም ጠዋት 1 ሰዓት አካባቢ ከዚህ ዓለም በሞት ስለመለየቱ ተሰምቷል።

የፊልምና የድራማ ዳይሬክተር አሸብር ካብታሙ ለኢትዮጵያ ኪነጥበብ በርካታ ስራዎችን የሰራ ታላቅ ባለሙያ ነው።

በተለይ ገመና ድራማ መቼም የማይረሳ ድንቅ ስራው ነው።

መለከት ድራማም አሸብር ከሰራቸው ምርጥ ከሚባሉት ተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማዎች መካከል አንዱም ነው።

አሸብር ካብታሙ ለ14 ዓመታት " ችሎት " የተሰኘውን በህግ ዙሪያ የሚያጠነጥነውን አስተማሪ ድራማ ድራማ ዳይሬክት በማድረግ አሻራውን ያስቀመጠ ታላቅ ባለሙያ ነው።

አትሌት ጥላሁን ሀይሌ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰ !በ19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያን በ5000ሜ ይወክል የነበረው ጥላሁን ሀይሌ ዛሬ  ከሰዓት ወደ ኢትዮጵያ መመለሱ ታውቋል። አትሌቱ...
24/08/2023

አትሌት ጥላሁን ሀይሌ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰ !

በ19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያን በ5000ሜ ይወክል የነበረው ጥላሁን ሀይሌ ዛሬ ከሰዓት ወደ ኢትዮጵያ መመለሱ ታውቋል።

አትሌቱ ለወራት ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን ጋር ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቶ ወደ ሃንጋሪ ቢያመራም ከቡድኑ መቀነሱ ይታወሳል።

በዚህም ምክንያት አትሌት ጥላሁን ሀይሌ ከአሰልጣኙ ጋር ከተማከረ በኃላ ዛሬ ከሰዓት ወደ #ኢትዮጵያ ማቅናቱ ታውቋል።

አትሌቱ ከዝርዝሩ ወጪ መሆኑን ካረጋገጠ በኋላ በውሳኔው ማዘኑን እና ቅሬታውን በማህበራዊ ሚዲያ ካሰማ በኃላ የተለያዩ አስተያየቶች ሲሰነዘሩ ቆይተዋል።

ይሄም አትሌቱ ዜግነቱን #ይቀይራል የሚል ቢሆንም አትሌቱ ዜግነቱ መቀየር ሀሳቡም #እንደሌለው እና በቀጣይ ጠንክሮ በመስራት ኢትዮጵያን ወክሎ አቅሙን ማሳየት እንደሚፈልግ ለናሽናል ስፖርት ገልጿል።

@ Kidus Yoftahee

👉ረ/ኮሚሽነር አትሌት ደራርቱ ቱሉ ይቅርታ ጠየቀችየኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዜዳንት ደራርቱ ቱሉ ፤ አትሌት ጥላሁን ኃይሌን ይቅርታ ጠየቀች።ደራርቱ ፤ " ጥላሁን ስላዘንክ ፤ ስለተበሳ...
24/08/2023

👉ረ/ኮሚሽነር አትሌት ደራርቱ ቱሉ ይቅርታ ጠየቀች

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዜዳንት ደራርቱ ቱሉ ፤ አትሌት ጥላሁን ኃይሌን ይቅርታ ጠየቀች።

ደራርቱ ፤ " ጥላሁን ስላዘንክ ፤ ስለተበሳጨህ በጣም ይቅርታ " ያለች ሲሆን " ይቅርታ የምለው በጣም ስላለቀሰ ስላዘነ ነው ፤ ነገር ግን መብቱን አልነካንም ፤ እሱን አስወጥተን ማንንም አላስገባብም። ሁሉም ባላቸው ሰዓት እና በብቃታቸው ነው የገቡት " ብላለች።

ደራርቱ እንደ አመራር እና እንደ እናት በተፈጠረው ነገር አዝኛለሁ ፤ ይቅርታም እላለሁ ስትል ተናግራለች።

" የአትሌቱን መብት ነክተን አላስቀረነውም 4ኛ በመሆኑ ብቻ ነው ያስቀረነው " ስትልም አክላለች።

ውሳኔዎች ሲተላለፉ በኮሚቴ ተነጋግረን ለሀገር የሚበጀውን ነው ያለችው ደራርቱ እኔ ብቻዬን ማንም የማስገባትም ሆነ የማስወጣት መብት የለኝም ብላለች።

አትሌት ጥላሁን ኃይሌ በ5000 ሜትር ውድድር ተመርጦ ወደ ሀንጋሪ ከተጓዘ በኃላ ፤ ትላንት በውድድሩ ላይ እንደማይሳተፍ እና በሱ ምትክ በሪሁ አረጋዊ መካተቱን ሊያውቅ ችሏል።

በዚህም እጅግ ሀዘን ውስጥ የገባ ሲሆን " የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዜዳንት ደራርቱ የሰራችብኝን ግፍ የኢትዮጵያ ህዝብ ይፍረደኝ " ብሏል።

" የሀገሬን ባንዲራ ከፍ ለማድረግ ብዙ ውጣ ውረድ ስለፋ ስደክም ቆይቼ የተሻለ ብቃት ኖሮኝ ፌዴሬሽኑ በሰራብኝ ግፍ ተቀንሻለሁ " ያለ ሲሆን " አሰልጣኝ ሁሴን ሽቦ ነው ፌዴሬሽኑን እየመራ ያለው ማለት ይቻላል ልጄ ይሮጥልኛል ብሎ በሪሁ አራተኛ ወጥቶ ገብቶ እንዲወዳደር ተደርጓል " ሲል ቅሬታው አቅርቧል።

" ቀን እና ማታ በአጥንት እስክቀር ድረስ የለፋሁበት እንጀራዬን እንዲህ መደረጉን ህዝቡ ይወቅልኝ ፤ ፌዴሬሽኑ ውስጥ የሚሰራውን ግፍ ህዝብ ይወቅልኝ " ብሏል።

" ፌዴሬሽኑን የሚመሩት አትሌት የነበሩ ናቸው እነሱ ሲመጡት ውስጥ ያለው አሰራር ይሻሻላል ቢባልም ጭራሽ በነሱ ባሰ፤ ስም አለም ሚዲያውን እንቆጣጠራለን ታዋቂ ነን ፤ ህዝቡን ማሳመን እንችላለን ብለው ይሄን ሁሉ ግፍ የሚያደርጉት እነሱ ናቸው " ሲል አክሏል።

ይህን የአትሌቱን ቅሬታ በተመለከተ ዛሬ መግለጫ የሰጡት የፌዴሬሽን አመራሮች ምርጫው ብቃትን መሰረት ያደረገ ሀገርንም ይጠቅማል በሚል እንጂ ማንንም አስወጥቶ የማስገባት ጉዳይ አይደለም፤ በሪሁ የተሻለ ሰዓት ስላለው ብቃቱም ጥሩ ስለሆነ ነው የገባው ብለዋል።

አትሌት ጥላሁን ኃይሌ የማይወዳደር ከሆነ ለምን እንዲሄድ እንደተደረገ ሲገልፁም ፤ ምናልባት በሪሁ የሆነ ነገር ቢሆን የሱ መኖር አስፈላጊ ነው ፤ ተጠባባቂ አትሌት ሁኔም ይኖራል ይህ ድሮም የነበረ አሰራር ነው ሲሉ አስረድተዋል።

Tikvah

አሸዋ ቴክኖሎጂ ለሶስት(3) ወራት የሚቆይ የአክሲዎን ሽያጭ ጀመረ። አሸዋ ቴክኖሎጂ ሶሉሽን ከነሀሴ 20 እስከ ህዳር 16  2016 ዓ.ም የሚቆይ ልዩ የአክሲዮን ሽያጭ መጀመሩን ዛሬ በሰጠው ...
24/08/2023

አሸዋ ቴክኖሎጂ ለሶስት(3) ወራት የሚቆይ የአክሲዎን ሽያጭ ጀመረ።

አሸዋ ቴክኖሎጂ ሶሉሽን ከነሀሴ 20 እስከ ህዳር 16 2016 ዓ.ም የሚቆይ ልዩ የአክሲዮን ሽያጭ መጀመሩን ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቀ።

የአሸዋ ቴክኖሎጂ ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ዳንኤል በቀለ በሰጡት መግለጫ አሸዋ ቴክኖሎጂ ለማህበረሰቡ ዘመኑን የዋጁ ድንቅ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን በማቅረብ በአገራችን ላይ ያለዉን ዘልማዳዊ የቢዝነስ ሂደት በመቀየር ቢዝነስን ቀላል፣ ዘመናዊ ለማድረግ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

አሸዋ ቴክኖሎጂ በሁኑ ስአትም 10 የቦርድ አባላቶች ያሉት፣ ከ1500 በላይ ባለአክሲዮኖች ያሉት፣ 200 በላይ የበቁ ባለሙያዎችን ይዞ ቅርንጫፍ በኬንያ ከፍቶ፤ በመቶ ሺህ ተጠቃሚዎችን አፍርቶ፣ ብዙ ሶሉሽኖችን አፍርቶ፣ ፍቃድ ወስዶ በጣም ትልቅ ስራን እየሰራ ያለ ተቋም ነው፡፡ አሽዋ ኢ-ኮሜርስ፣ ኢ-ትምህርት፤ ሎጂስቲክስ፣ ስማርት ሶሉሽን እንደ ስማርት ኢአርፒ እና ዌብሳይት ቢውልደር እንደሰርቪስ ፤ የሶፍትዌር ግንባታ እና በአጠቃላይ በ 11 የመልቲ ቢሊዮን ብር ፕሮጀክቶች ቀርጾ በስራ ላይ የሚገኝ የቴክኖሎጂ ድርጅት ነው ፡፡

አቶ ዳንኤል በቀለ እንደተናገሩት በመጭው አምስት አመታት ውስጥ 7 ቢሊዮን ብር በአመት ገቢ ለማግኘት እየተሰራ መሆኑል አስረድተዋል።

በፕሮጀክቱ ውስጥ በሚሰሩ ስራዎች ላይ ልዩ ጥቅም የሚያስገኘውን አክሲዮን የሚገዙ ኢንቨስተሮች ላይ የሚገኘውን ትርፍ ለተከታታይ 4 አመት በየአመቱ 500 የሚያገኙ ይሆናል በሚል ብስራትን የያዘ ነዉ፡፡

ይህ ሲሆን ደግሞ አንድ ባለ አክሲዮን ወይም መነሻው 500ሺ ብር ሲገዛ በአጠቃላይ በድምሩ 6,910,752.25 የሚያገኝ ሲሆን ከ4 አመት በኃላ መደበኛ ባለአክሲዎን በመሆን የጠቅላላ ትርፍ ተካፋይ እንደሚሆን አቶ ዳንኤል አስረድተዋል ፡፡

የአክሲዮን ሽያጩን እስከ አምስት ሰዎች በጣምራ መግዛት እንደሚችሉም በመግለጫው ተጠቅሷል።

ጥላሁን ሀይሌ ላይ የአትሌቲክስ ፌደሬሽን ግፍ እየፈፀመ ነው‼️በ5 ሺ ሜትር ወንዶች ባስመዘገበው ምርጥ ሰአት ኢትዮጵያን እንዲወክል ወደ ሀንጋሪ ቡዳፔስት ያመራው አትሌት ጥላሁን ሀይሌ አትወዳ...
23/08/2023

ጥላሁን ሀይሌ ላይ የአትሌቲክስ ፌደሬሽን ግፍ እየፈፀመ ነው‼️

በ5 ሺ ሜትር ወንዶች ባስመዘገበው ምርጥ ሰአት ኢትዮጵያን እንዲወክል ወደ ሀንጋሪ ቡዳፔስት ያመራው አትሌት ጥላሁን ሀይሌ አትወዳደርም በሚል አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተገቢ ያልሆነ ውሳኔ እንዳስተላለፈበት ለትርታ ስፖርት ምንጮች ገልፀዋል።

በአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ5 ሺ ሜትር በዋናነት ጥላሁን ሀይሌ በቀለ ፣ ዮሚፍ ቀጀልቻ እና ሀጎስ ገብረህይወት እንዲካፈሉ የተመረጡ ቢሆንም ፤ በ10 ሺ ሜትር ተካፍሎ አራተኛ የወጣውን በሪሁ አረጋዊ በድጋሚ ለማሳተፍ ሲባል በ5 ሺ ሜትር ወንዶች ጥላሁን ሀይሌ እንዲቀነስ ተደርጓል። አትሌቱ በከፍተኛ ሀዘን ተውጦ እና በለቅሶ ለምን እንዲህ እንደተወሰነበት እነ ደራርቱ እና ገዛሀኝ አበራን ቢያናግርም ምላሽ አላገኘም ። ጉዳዮንም በቦታው ላሉት ለባህልና ስፖርት ሚንስቴር የስፖርት ዘርፍ ሀላፊ ለአምባሳደር መስፍን ቸርነት ገልፆላቸዋል ። ከሚመለከተው ጋር ተነጋግረው ውሳኔውን እንደሚያሳውቁት ገልፀውለታል። የ5 ሺ ሜትር የወንዶች ማጣሪያ ነገ ይደረጋል።



አትሌቱም በፌስቡክ ገፁ በቪድዮ የተፈፀመበት ግፍ በእንባ ገልፆ ድምፅ ሁኑኝ ብሏል።

ድርቤ ወልተጂ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።ኬንያዊቷ በአንደኝነት አጠናቃለች። ሲፋን ሀሰን ሶስተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች።እንኳን ደስ አለን
22/08/2023

ድርቤ ወልተጂ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።

ኬንያዊቷ በአንደኝነት አጠናቃለች።

ሲፋን ሀሰን ሶስተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች።

እንኳን ደስ አለን

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከመጪው ዓመት ጀምሮ የቅደመ ምረቃ ተማሪዎችን በውድድር ብቻ እንደሚቀበል ገለጸአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከመጪው 2016 ዓ.ም. ጀምሮ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎችን የሚቀበለው...
22/08/2023

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከመጪው ዓመት ጀምሮ የቅደመ ምረቃ ተማሪዎችን በውድድር ብቻ እንደሚቀበል ገለጸ

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከመጪው 2016 ዓ.ም. ጀምሮ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎችን የሚቀበለው በምደባ ሳይሆን በውድድር መሆኑን አስታወቀ። ዩኒቨርስቲው ክፍያ የሚፈጽሙ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎችን “በልዩ” ሁኔታ ለማስተማር እንዳቀደም ገልጿል።

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ይህንን ያስታወቀው የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ መሆኑን አስመልክቶ ዛሬ ማክሰኞ ነሐሴ 16፤ 2015 በዋናው ቅጥር ግቢ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው። መግለጫውን የሰጡት የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋሙ ራስ ገዝ ለመሆን ላለፉት ሁለት ዓመታት ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር ስር ያሉ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎችን ራስ ገዝ ለማድረግ የተዘጋጀው አዋጅ በተወካዮች ምክር ቤት የጸደቀው ባለፈው ግንቦት ወር ነበር። የዚህን አዋጅ መውጣት ተከትሎም አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ እንዲሆን ያስቻለው ደንብ፤ ከሶስት ሳምንት በፊት ሐምሌ 28፤ 2015 በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቋል።

የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት በዛሬው መግለጫቸው፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋሙ ወደ ራስ ገዝነት የሚያደርገውን ሽግግር “ሁለት ዓመት ባልሞላ” ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ማቀዱን አስታውቀዋል።

(ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

የጊዜ ባለቤት ጌታዬ መድሀኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ ክብሩን ሁሉ አንተ ጠቅልለህ ውሰድ🙏 Mekdes tsegaye
20/08/2023

የጊዜ ባለቤት ጌታዬ መድሀኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ ክብሩን ሁሉ አንተ ጠቅልለህ ውሰድ🙏

Mekdes tsegaye

ነሐሴ 15 በሀገር ፍቅር እንገናኝ #አንድ ለመንገድ
20/08/2023

ነሐሴ 15 በሀገር ፍቅር እንገናኝ
#አንድ ለመንገድ

https://youtu.be/V3oqmPGV9fs
10/05/2021

https://youtu.be/V3oqmPGV9fs

ወቅታዊ እና ጠቃሚ መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሰዎት Afta Media ሰብስክራይብ ያድርጉ፡፡በተጨማሪም በፌስቡ...

Address

Addis Ababa
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AFTA MEDIA አፍታ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share

Your Voice

Ethio Anchor Media ‘your voice’ Ethiopian multi-platform entertainment and media company ,Powered by its own proprietary technology We provide you with the latest breaking news, recent affairs, discussions with different prominent Ethiopian individuals and more.

is the go-to source for technology, digital culture and entertainment content for its dedicated and influential audience around the nation as well for the world.



You may also like