Boditti Town Gov't Communication Affairs Office የቦ/ከ/መ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Sodo
  • Boditti Town Gov't Communication Affairs Office የቦ/ከ/መ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

Boditti Town Gov't Communication Affairs Office የቦ/ከ/መ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት Non Profit Make Page
To build Social Interaction Among Different nations

በ 2.4  ሚሊዮን ብር በIOM UN MIGRATION ድጋፍ እየተገነባ ያለው የገበያ ማዕከል ያለበት ደረጃ በከተማ አስተባባሪ አካላት ጉብኝት ተደርጓል ።ጥቅምት 17/02/2015 ዓ.ም  በቦዲ...
27/10/2022

በ 2.4 ሚሊዮን ብር በIOM UN MIGRATION ድጋፍ እየተገነባ ያለው የገበያ ማዕከል ያለበት ደረጃ በከተማ አስተባባሪ አካላት ጉብኝት ተደርጓል ።

ጥቅምት 17/02/2015 ዓ.ም በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር በ IOM UN MIGRATION ድጋፍ በ 2.4 ሚሊዮን ብር ወጪ እየተሰራ ወደ መጨረሻው ምዕራፍ የደረሰው የገበያ ማዕከል ያለበት ደረጃ በከተማ አስተባባሪ አካላት ጉብኝት ተደርጓል ።

በጉብኝቱ ወቅት የቦዲቲ ከተማ ከንቲባ አቶ ደስታ ዳና:ከ IOM UN MIGRATION ድርጅት የግንባታ ስራውን የተረከበው YENOL CONSTRACTION ግንባታውን ወደ መጨረሻ ምዕራፍ ማድረሱንና ጨርሶ ለማስረከብ እያደረገ ያለውን ጥረት በማድነቅ በቀጣይ ርክክብ ለማድረግ የሚያስችሉ ውስን ስራዎች በፍጥነት ሊጠናቀቁ እንዲሚገባ አሳስበዋል።

የግንባታ ሂደቱን በቅርበት በገንዘብ ከመደገፍ ውጭ ግንባታው ተጠናቆ ርክክብ እንዲደረግ ክትትል እያደረጉ ያሉ የድርጅቱ ተወካዮችና የከተማው ኮንስትራክሽን ዘርፍ ባለሙያዎች ዕውቅና ያስፈልጋቸዋል ሲሉም ገልፀዋል።

ድርጅቱ የሰራው መልካም ስራ በከተማችን ዕድገት ላይ የራሱ የሆነ አዎንታዊ አሻራ ከማሳረፉ በላይ የስራ አጥነት ቁጥር የሚቀንስ እንደሆነም አቶ ደስታ አክለው ገልፀዋል ።

የገባያ ማዕከሉ ከስደት ተመላሽ ለሆኑ ሴቶች ታልሞ የተገነባ ሲሆን ግንባታው ተጠናቆ ርክክብ ሲደረግ ለታለመለት ዓላማ የማዋል ስራ እንደሚሰራ የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽ/ቤት ኃላፊና ም/ከንቲባ አቶ በረከት በላይነህ አሳውቀዋል ።

" በደም የተከበረ በላብ የታሠረ ዘላቂ ሠላምና ቀጣይነት ያለው ዕድገት ማረጋገጥ " በሚል መሪ ቃል በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
27/10/2022

" በደም የተከበረ በላብ የታሠረ ዘላቂ ሠላምና ቀጣይነት ያለው ዕድገት ማረጋገጥ " በሚል መሪ ቃል በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

በመኸር እርሻ ከ512 ሺህ በላይ ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ አቅዶ እየሰራ መሆኑን በወላይታ ዞን የዳሞት ጋሌ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አስታወቀቦዲቲ፣ጥቅምት 14/2015 በመኸር እርሻ ከ512 ሺህ...
24/10/2022

በመኸር እርሻ ከ512 ሺህ በላይ ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ አቅዶ እየሰራ መሆኑን በወላይታ ዞን የዳሞት ጋሌ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አስታወቀ

ቦዲቲ፣ጥቅምት 14/2015 በመኸር እርሻ ከ512 ሺህ በላይ ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ አቅዶ እየሰራ መሆኑን በወላይታ ዞን የዳሞት ጋሌ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አስታውቋል።

የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ከድህነት ለመላቀቅ ከጀመሩት የመኸር ሥራዎች የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁ የወረዳው አርሶ አደሮች ተናገሩ።

ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ የመጣውን የምርታማነት ችግር፣ የዋጋ ንረት፣ ከውጭ ሀገር የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ምርት ለመተካት እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንደ ሀገር ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።

የወረዳው አርሶ አደሮች በአየር መዛባት፣ በዝናብ መቆራረጥ እና በበሽታ ምክንያት በበልግ እርሻ ወቅት ያጡትን ምርት በመኸር ለማግኘትና በምግብ ራሳቸውን ለመቻል በሰሩት ስራ የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁ ነው የቸናገሩት።

የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ድህነትን ለማስወገድ አዳድስ ቴክኖሎጅዎችን ተግባራዊ ለማድረግ በትኩረት እየሰሩ መሆናቸውንም አርሶ አደሮቹ ገልጸዋል።

ከዘንድሮ መኸር እርሻ የተሻለ ምርት ለማግኘት ከ6200 ሄክታር በላይ ማሳ በተለያዩ ሰብሎች የተሸፈነ ሲሆን ለእነዚህ ሰብሎች የሚውሉ እና ምርታማነትን ከፍ የሚያደርጉ ግብአቶች በጊዜ ማቅረብ መቻሉን የዳሞት ጋሌ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ዋና ኃላፊ ኤፍረም ያዕቆብ ተናገሩ።

እንደ ሀገር የተያዘውን የብልጽግና ጉዞውን ዕውን ለማድረግና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንደ ወረዳው በግብርና ዘርፎች የተሰሩ ስራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን አቶ ኤፍሬም ገልጸዋል።

እንደ ለገር የተያዘውን የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በመኸር የተሰሩ ሥራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን

በመኸር እርሻ ከ6200 ሄክታር በላይ ማሳ በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች በመሸፈን ከ512 ሺህ በላይ ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑንም አቶ ኤፍሬም አስታውቀዋል ሲል ዓ/ም (ወቴቪ) ዘግቧል።

የወላይታ ዞን ከፍተኛ አመራሮች በአረካ ከተማ በገበያ ማዕከል የተነሳው ድንገተኛ እሳት አደጋ ያደረሰውን ጉዳት በስፍራው በመገኘት ጎበኙቦዲቲ ፤ ጥቅምት 14/2015 የወላይታ ዞን የመንግስት ...
24/10/2022

የወላይታ ዞን ከፍተኛ አመራሮች በአረካ ከተማ በገበያ ማዕከል የተነሳው ድንገተኛ እሳት አደጋ ያደረሰውን ጉዳት በስፍራው በመገኘት ጎበኙ

ቦዲቲ ፤ ጥቅምት 14/2015 የወላይታ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ዮሐንስ በየነን ጨምሮ ሌሎች የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች በአረካ ከተማ በገበያ ማዕከል የተነሳው ድንገተኛ እሳት አደጋ ያደረሰውን ጉዳት ተመልከተዋል።

እሳት አደጋው በቀን 12/2/2015 ዓ/ም ቅዳሜ ማታ ከምሽቱ በግምት 2.30 ገደማ አከባቢ የተነሳ ሲሆን በአደጋው ከ100 ሼዶች በላይ ማውደሙን ተገልጿል።

ከፍተኛ አመራሮች በገበያ ማዕከል የተነሳው ድንገተኛ እሳት አደጋው ያደረሰውን ጉዳት ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

የእሳት አደጋው በንብረት ላይ ያደረሰውን ጉዳት የተመለከቱት የወላይታ ዞን ከፍተኛ የመንግስት ስራ ኃላፊዎች ጉዳት ለደረሰባቸውን ወገኖች ማዘናቸውን ገልጸዋል፡፡

የእሳት አደጋው ከዚህም በላይ ወደ ሌሎች አከባቢዎች እንዳይዛመት ህብረተሰቡ ያሳየዉ ርብርብ ምስጋናዉን አቅርበዋል፡፡

የዘገበው የከተማው ህዝብ ግንኙነትና ማህበራዊ ሚዲያ ዘርፍ ነው

የወቅታዊ ሁኔታ መረጃየኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ቁልፍ የሚባሉ የትግራይ ከተሞችን መቆጣጠሩን ቀጥሏል።ይህንን ሲያደርግም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በከተሞች ውጊያ ሳይደረግ የህወሓትን ወታደ...
24/10/2022

የወቅታዊ ሁኔታ መረጃ

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ቁልፍ የሚባሉ የትግራይ ከተሞችን መቆጣጠሩን ቀጥሏል።

ይህንን ሲያደርግም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በከተሞች ውጊያ ሳይደረግ የህወሓትን ወታደራዊ ዐቅም ለማሽመድመድ የሚያስችል ስልት ተጠቅሟል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ከሰብአዊ የእርዳታ ተቋማት ጋር በመቀናጀት በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ሰብአዊ እርዳታ እንዲደርስ እየሠራ ይገኛል።

የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት በእነዚህ አካባቢዎች አገልግሎት ለመጀመር የሚያስችል ዝግጅት እንዲያፋጥኑ እያደረገ ነው።

ከየአካባቢው ማኅበረሰብ ጋር በመነጋገር ሕዝባዊ አስተዳደር የሚቋቋምበትንና ማኅበራዊ አገልግሎቶች የሚጀምሩበትን መንገድ እያመቻቸ ይገኛል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በአፍሪካ ኅብረት በኩል በደቡብ አፍሪካ በሚደረገው የሰላም ንግግር የሚሳተፍ ይሆናል።

አጋጣሚውንም የሰላም ንግግሩን ግጭቱን በሰላም ለመፍታት የሚቻልበት ዕድል አድርጎ ይመለከተዋል።

በመከላከያ ኃይላችን መሥዋዕትነት እየተስተካከለ የመጣውን ሁኔታ የበለጠ ለማጠናከር ምቹ አጋጣሚ የሚፈጥር አድርጎ ይወስደዋል።

በሰላም ንግግሩ ላይ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ የልዑካን ቡድን ዛሬ ጠዋት ወደ ደቡብ አፍሪካ አምርቷል።

ጥቅምት 14 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

በዎላይታ ዞን አረካ ከተማ በገበያ ማዕከል ድንገተኛ የእሳት ቃጠሎ በመንግስት እና በህብረተሰብ ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገለፀ።ከከተማው በዛሬው ምሽት ከሌሊቱ  2:30 ገደማ በገበያ ማዕከ...
23/10/2022

በዎላይታ ዞን አረካ ከተማ በገበያ ማዕከል ድንገተኛ የእሳት ቃጠሎ በመንግስት እና በህብረተሰብ ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገለፀ።

ከከተማው በዛሬው ምሽት ከሌሊቱ 2:30 ገደማ በገበያ ማዕከል የተነሣው የእሳት ቃጠሎ በመንግስትና በህብረተሰብ ትግል መቆጣጠር መቻሉ ተነግሯል።

የእሳት አደጋው መንሰኤው ባይታወቅም እሳቱን ለማጥፋት የዎላይታ ሶዶ ከተማ የእሳት ማጥፊያ ብርገድ እንዲሁም መላው የከተማችን ነዋሪ ህዝብ ባደረጉት ርብርብ እሳቱን ለመቆጣጠር ተችሏል።

የአደጋው መንስኤውና የደረሰው ጉዳት መጠን በመጣራት ላይ ሲሆን ለመቆጣጠር የተባበሩትን ሁሉ የከተማ አስተዳደሩ ልባዊ ምስጋናውን ያቀርባል ስል የከተማው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ዘግቧል።

"ስፖርትን በሁሉም ዘርፍ ሕዝባዊ መሠረት ለማስያዝ ትኩረት ይደረጋል !":-  አቶ አክሊሉ ለማ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳደርና የዞኑ ስፖርት ም/ቤት ሰብሳቢበ2014 የተሻለ ድጋፍ ያደረጉና ው...
23/10/2022

"ስፖርትን በሁሉም ዘርፍ ሕዝባዊ መሠረት ለማስያዝ ትኩረት ይደረጋል !":- አቶ አክሊሉ ለማ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳደርና የዞኑ ስፖርት ም/ቤት ሰብሳቢ

በ2014 የተሻለ ድጋፍ ያደረጉና ውጤት ላስመዘገቡት ለግል ሃብቶችና ተቋማት የዋንጫ ሽልማትና ምስክር ወረቀት የዞኑ ስፖርት ምክር ቤት አበረከተ።

ቦዲቲ ጥቅምት 12/2015 ዓም

የወላይታ ዞን ስፖርት ምክር ቤት በ2014 አፈጻጸምና በ2015 በጀት ዓመትየሥራና የበጀት ዕቅድ ዙሪያ የ16ኛ ጠቅላላ መደበኛ ጉባኤ ተካሂዷል ።

አቶ አክሊሉ ለማ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳደርና የዞኑ ስፖርት ም/ቤት ሰብሳቢ የስፖርት ውድድሮች በመንግሥት ትከሻው ላይ ብቻ ሳይሆን ሕብረተሰቡን በማነቃነቅ ሕዝባዊ መሠረት እንዲይዝ በቀጣዩ ልዩ ትኩረት እንደሚደረግ ጠቁመዋል

የስፖርት ምክር ቤቱ ማስተካከል ባለባቸው ሃሳቦችና በቀጣይ ስፖርታዊ ክንውኖች በማሳደግ በዞን ደረጃ ከ18 በላይ ስፖርታዊ ውድድር ዓይነቶች እንደሚሳተፉ አቶ አክሊሉ ለማ ተናግረዋል ።

ስፖርት ሕዝባዊ መሠረት ለማስያዝ የሚደረጉ ርብርብ በማጠናከር የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታ ከማመቻቸት አኳያ በየአካባቢ ያለው ሁኔታ በማጤን የተሻለ ሥራ መሰራት እንደሚገባ አቶ አክሊሉ አሳስበዋል ።

በወላይታ ዞን ውስጥ መረብ ኳስ ሁሉም ቦታ የሚዘውተር ሕዝባዊ መሠረት ያለው በሆንም
በእግር ኳስ ላይ በልዩ ሁኔታ የድቻ ስፖርት ክለብ በኩል ያለው ተሳትፎ ታዳግ ኃይል በማፍራት የሚመገብ ከመሆኑም ባሸገር ከታዳጊ እስከ ውጪ በባርሴሎና ቢ ቡድን የገቡበት ዕድል መፍጠሩንና ስምንት ታዳጊዎች በጀርመን አካዳሚ መቀላቀላቸውን አቶ አክሊሉ ለማ ጠቁመዋል ።

የዞኑ ስፖርት ም/ቤት ሰብሳቢ እንዳስረዱት በቦክስ ፣እጅ ኳስ፣ አትሌትክስ እንዲሁም በባህላዊ ስፖርት ዘርፍ በቂ ሥራ አለመስራቱ የጠቆሙት አቶ አክሊሉ በመረብና በእግር ኳስ ከሞላ ጎደል አበረታች ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል።

በዞኑ ውስጥ ያሉ ባለሃብቶች፣ ግለሰቦችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፏቸውን ለዞኑ ስፖርት ዕድገት ከውትሮ በተሻለ መንገድ የመደገፈና የማበረታታት ሥራ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ

አቶ ታደሰ ተክሌ የወላይታ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊና የስፖርት ም/ቤት ም/ሰብሳቢ የዞናችን ስፖርት አብዮት ከዳር ለማድረስ በሚፈልገው ልክ ውጤት ለማምጣት ጊዜ የሚጠይቅ መሆኑን ጠቁመዋል።

በዞኑ ስፖርት ለኢኮኖሚ፣ ለማህበራዊና ለፖለቲካ መረጋጋት ለሰላም እሴቶች ከሚሰጠው ፋይዳ ባሻገር ለፍቅር አብሮነት ለአንድነት፣ ለዕድገትና ለውጥ የማይተካ ሚና እንዳለው የወላይታ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ታደሴ ተክሌ አስታውቀዋል።

አቶ አኮዬ ገካ የወላይታ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ምክትልና ስፖርት ዘርፍ ኃላፊ እንዲሁም የዞኑ ስፖርት ም/ቤት ጸሐፊ በሁሉም ስፖርት ዘርፍ የሚገኘውን ወጤትና ጥቅም የላቀ ለማድረግ የገቢ መጠንን ማሳደግ ቁልፍ ጉዳይ ስለሆነ ውጤትን የሚመጥን አሰልጣኝ በመምረጥ የስፖርት ዘርፍ አቅምን የሚያደከሙ ቁልፍ ጉዳዮችን በመለየት በየዘርፉ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ አስረድተዋል ።

የ2014 አፈጻጸም በመገምገምና የ2015 በጀት ዓመት የሥራና በጀት ዕቅድ ላይ የስፖርቱ ምክር ቤቱ በመወያየት አጽድቋል ።

በ2014 የተሻለ ድጋፍ ያደረጉና ውጤት ላስመዘገቡት ለአሰልጣኞች ፣ ለግል ሃብቶችና ተቋማት ምስክር ወረቀት የዞኑ ስፖርት ምክር ቤት

የተሻለ ድጋፍና ውጤት በማምጣት የዋንጫ ሽልማት ያገኙት ባለሃብቶች
:- ለአቶ አበበ ዘለቀ ልጅ ወ/ሮ ትዕግሥት ዘለቀ፣ለአቶ ሙሴ ጳውሎስ እና ለአቶ ፈለቀ ፋንታ የዋንጫ ሽልማትና ምስክር ወረቀት የዞኑ ስፖርት ምክር ቤት አበረከተ።

በ2014 አፈጻጸም የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ የዋንጫ ተሸላሚ ወረዳዎችና ከተማ አሰተዳደር
1ኛ አረካ ከተማ አስተዳደር
2ኛ ሁምቦ ወረዳ አስተዳደር እና
3ኛ የገሱባ ከተማ አስተዳደር በስፖርት ም//ቤት ደረጃ ተሸላሚ ሆነዋል ።

በጉባኤው ማጠቃለያ የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡት የዋንጫ ሽልማትና ምስክር ወረቀት የዞኑ ስፖርት ምክር ቤት ያበረከተ ሰሆን የዞኑ የካቢኔ አባላት፣ የወረዳና ከተማ አስተዳዳሪዎች እና የዘርፉ አመራሮች እንዲሁም የምክር ቤቱ አባላት ተሳታፊ ሆነዋል።
(ወ/ዞ/መ/ኮ/ጉ/መምሪያ)

 #ታላቅ የምስራች ለቦዲቲ ከተማ ህብረተሰብ በሙሉ ፥ የቅዳሜ እና እሁድ ገበያ በይፋ ስራ ጀመረጥቅምት 12/2015 ዓ.ም በወላይታ ዞን በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር   የገበያ ሁኔታን ለማረጋጋት...
22/10/2022

#ታላቅ የምስራች ለቦዲቲ ከተማ ህብረተሰብ በሙሉ ፥ የቅዳሜ እና እሁድ ገበያ በይፋ ስራ ጀመረ

ጥቅምት 12/2015 ዓ.ም በወላይታ ዞን በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር የገበያ ሁኔታን ለማረጋጋት የቅዳሜ እና እሁድ ገበያ ስራ መጀመሩን የቦዲቲ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት አስታውቋል ።

ለገበያው የሚቀርቡ ምርቶች ቀጥታ ከአምራች ጓሮ የሚመጡ ሲሆን ለሸማች ህብረተሰብም የኑሮ ደረጃን ባገናዘበ መልኩ በቅናሽ ዋጋ እንደሚሸጥ የቦዲቲ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ እንድሪያስ ጉንታ ገልጿል ።

በወላይታ ዞን በበሰልፉ እየተንፀባረቁ ካሉ መልእክቶች ጥቂቱ፤👉የትግራይ ሕዝብ ወገናችን ነዉ፤ ጁንታዉ ጠላታችን ነው!👉 ህወሃት የችግሩ ምንጭ ነው!👉  ሉዓላዊነታችንን አክብሩ!👉  ህወሃት ቅጥ...
22/10/2022

በወላይታ ዞን በበሰልፉ እየተንፀባረቁ ካሉ መልእክቶች ጥቂቱ፤

👉የትግራይ ሕዝብ ወገናችን ነዉ፤ ጁንታዉ ጠላታችን ነው!
👉 ህወሃት የችግሩ ምንጭ ነው!
👉 ሉዓላዊነታችንን አክብሩ!
👉 ህወሃት ቅጥረኛ ነው!
👉 በድርድር ሥም ሰቆቃችንንና የህወሃት ዕድሜን ማራዘም ይብቃ!
👉 በዉክልና ጦርነት መጠቃት ይብቃ!
👉 ለህወሀት 4ኛ ዙር ጥቃት ዕድል መስጠት አይገባም!

ለኢትዮጵያ እቆማለሁ ድምፄን አሰማለሁ!!በወላይታ ሶዶ ከተማ ለሚካሄደው ታላቅ ህዝባዊ ሰልፍ ለመታደም የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ልዑካን ሁለገብ ስታዲየም እየገባ ነው፡፡
22/10/2022

ለኢትዮጵያ እቆማለሁ ድምፄን አሰማለሁ!!

በወላይታ ሶዶ ከተማ ለሚካሄደው ታላቅ ህዝባዊ ሰልፍ ለመታደም የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ልዑካን ሁለገብ ስታዲየም እየገባ ነው፡፡

የቦዲቲ ከተማ ነዋሪዎች  አሸባሪውን ህወሓትና የውጭ ጣልቃ ገብነትን ለመቃወም በተዘጋጀው ህዝባዊ ሰልፍ ላይ ድምጻቸው ለማሰማት ወደ ወላይታ መዲና ሶዶ ከተማ መንቀሳቀስ ጀምረዋል።
22/10/2022

የቦዲቲ ከተማ ነዋሪዎች አሸባሪውን ህወሓትና የውጭ ጣልቃ ገብነትን ለመቃወም በተዘጋጀው ህዝባዊ ሰልፍ ላይ ድምጻቸው ለማሰማት ወደ ወላይታ መዲና ሶዶ ከተማ መንቀሳቀስ ጀምረዋል።

በወላይታ ዞን በነገው ዕለት ለሚካሄደው ሰልፍ ዝግጅት ማጠናቀቁን ተገለጸ ቦዲቲ ፤ ጥቅምት 11/2015 በወላይታ ዞን በነገው ዕለት ለሚካሄደው ታላቅ ህዝባዊ ሰልፍ ዝግጅት ማጠናቀቁን የሰልፉ ...
21/10/2022

በወላይታ ዞን በነገው ዕለት ለሚካሄደው ሰልፍ ዝግጅት ማጠናቀቁን ተገለጸ

ቦዲቲ ፤ ጥቅምት 11/2015 በወላይታ ዞን በነገው ዕለት ለሚካሄደው ታላቅ ህዝባዊ ሰልፍ ዝግጅት ማጠናቀቁን የሰልፉ አስተባባሪ ኮሚቴ አስታውቋል።

በነገው ዕለት ለሚደረገው ታሪካዊ ሰልፍ ሁሉም ህብረተሰብ ክፍሎች በነቂስ በመውጣት የምዕራባውያንን ጣልቃ ገብነትን ከፍ ባለ ድምፅ ማውገዝና ለመንግስታችን ያለውን አጋርነታችንን ማሳየት አለብን።

ሰልፉ ከማለዳው 12:00 ጀምሮ በወላይታ ሶዶ ከተማ ስታዲየም ይካሄዳል።

በሰልፉ ላይ በመገኘት ለሀገር ድምጽ በመሆን ታሪካዊ ኃላፊነታችንን መውጣት ያስፈልጋል።

ማሳሰቢያ ፦ ለቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች በሙሉበቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ከነገ :ማለትም ከቀን 12/02/2015 (ቅዳሜ ) ጀምሮ እስከ ቀን 14/022015 ዓ.ም(ሰኞ) ድረስ በጥገና ም...
21/10/2022

ማሳሰቢያ ፦ ለቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች በሙሉ

በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ከነገ :ማለትም ከቀን 12/02/2015 (ቅዳሜ ) ጀምሮ እስከ ቀን 14/022015 ዓ.ም(ሰኞ) ድረስ በጥገና ምክንያት #የውሃ መቆራረጥ ስለሚኖር ከወዲው አስፈላጊው ቅድመ ጥንቃቄ እንዲወስድ የቦዲቲ ከተማ ውሃ ልማት ጽ/ቤት ያሳስባል ።

አይቀርም!ነገ ጥቅምት 12/2015 ዓ.ም ቅዳሜ ማለዳ ልክ 12:00 ሰዓት ታላቅ ህዝባዊ ሰልፍ በወላይታ ሶዶ ከተማ ሁለገብ ስታዲየም ይካሄዳል!!የሰልፉም ዓላማ አገራችን ያለችበትን ነባራዊ ሁ...
21/10/2022

አይቀርም!

ነገ ጥቅምት 12/2015 ዓ.ም ቅዳሜ ማለዳ ልክ 12:00 ሰዓት ታላቅ ህዝባዊ ሰልፍ በወላይታ ሶዶ ከተማ ሁለገብ ስታዲየም ይካሄዳል!!

የሰልፉም ዓላማ አገራችን ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅና ለአገራችን ሉአላዊነትና የግዛት አንድነት መከበር ከዜጎች የሚጠበቀውን ማንኛውንም መስዋዕትነት በመክፈል ከመንግስታችን ጎን መቆማችንን ለማረጋገጥ የሚደረግ የድጋፍ ሰልፍ ነው።

በቁጥር የበዙ ላሞችን በአንድ ቤት ከማርባት ይልቅ ዘመናዊ እና በምርታማነት የታወቁ ጥቂት ላሞችን ማርባት  ውጤታማ እንደሚያደርግ የቦዲቲ ከተማ  የመንግስት ረዳት ተጠሪ ወ/ት እመቤት ጥላሁን...
21/10/2022

በቁጥር የበዙ ላሞችን በአንድ ቤት ከማርባት ይልቅ ዘመናዊ እና በምርታማነት የታወቁ ጥቂት ላሞችን ማርባት ውጤታማ እንደሚያደርግ የቦዲቲ ከተማ የመንግስት ረዳት ተጠሪ ወ/ት እመቤት ጥላሁን ገለፁ

ጥቅምት 11/2015 በወላይታ ዞን በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር በዳ/ጋሌ እንስሳት ክንኒክ ሦስተኛ ዙር የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ ወይም ስንክሮናይዘሽን ስራ በደመቀ ሁኔታ መጀመሩን የቦዲቲ ከተማ ግብርና ጽ/ቤት አስታውቋል ።

ሦስተኛ ዙር የስንክሮናይዘሽን መርሐግብር በይፋ ያስጀመሩት የቦዲቲ ከተማ የመንግስት ረዳት ተጠሪ ወ/ሪት እመቤት ጥላሁን በንግግራቸው በቁጥር የበዙ ላሞችን በአንድ ቤት ከማርባት ይልቅ ዘመናዊ እና በምርታማነት የታወቁ ጥቂት ላሞችን ማርባት የተሻለ ውጤት እንድናገኝ ያስችላል ብለው ህብረተሰቡ ከብዛት ይልቅ በጥራት ላይ ትኩረት እንዲያደርግ አሳስበዋል ።

የቦዲቲ ከተማ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወርቁ አንጁሎ ህብረተሰቡ ይህን መልካም አጋጣሚ እንድጠቀም ባለሙያው በችግሮች ሳይበገር መስዋዕትነት ከፍሎ እንደምሰራ እምነታቸውን አስቀምጠዋል ።

አቶ ወርቁ አክለው የአከባቢው ህብረተሰብም የደረሱ ላሞችን ወደ ጤና ኬላው በማምጣት ትብብር ያድርግ ብለዋል።

ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ "በወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ "አገራችንን ከዓለም አቀፍ ተጽዕኖ በመታደግ ወደንና ፈቅደን በምንከፍለው መስዋዕትነት ሉዐላዊነታችንንና የግዛት አንድነታችንን እናስከብራለን"!!...
20/10/2022

ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ "በወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ "አገራችንን ከዓለም አቀፍ ተጽዕኖ በመታደግ ወደንና ፈቅደን በምንከፍለው መስዋዕትነት ሉዐላዊነታችንንና የግዛት አንድነታችንን እናስከብራለን"!!! በሚል መሪ ቃል ቅዳሜ ጥቅምት 12/2015 ዓ.ም ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እንደሚካሄድ የሰልፉ አስተባባሪ ኮሚቴ አስታወቀ
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
የሠልፉ ዋና ዓላማ አገራችን ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅና ለአገራችን ሉአላዊነትና የግዛት አንድነት መከበር ከዜጎች የሚጠበቀውን ማንኛውንም መስዋዕትነት በመክፈል ከመንግስታችን ጎን መቆማችንን ለማረጋገጥ ነው ሲሉ አስተባባሪ ኮሚቴ አስታውቀዋል፡፡

"አገራችንን ከዓለም አቀፍ ተጽዕኖ በመታደግ ወደንና ፈቅደን በምንከፍለው መስዋዕትነት ሉዐላዊነታችንንና የግዛት አንድነታችንን እናስከብራለን" በሚል መሪ ቃል አሸባሪው የህወሓት ቡድን ለ3ኛ ጊዜ የሠላም አማራጮችን በመዝጋት የጀመረውን አስገዳጅ ጦርነት ለመቀልበስና የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ለሚያደርጉት ድንቅ ተጋድሎ የወላይታ ህዝብና አስተዳደር ደጀን መሆኑንም የሚያሳይበት መድረክ መሆኑንም ኮሚቴው ገልጿል ።

የድጋፍ ሠልፉ በወላይታ ሶዶ ከተማ የፊታችን ቅዳሜ ጥቅምት 12/2015 ዓ.ም ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ በወላይታ ሶዶ ከተማ ባለው ሁለገብ ስታዲየም በወላይታ ዞን የሚገኙ ነዋሪዎች በነቂስ በመውጣት እንደሚሳተፉበት ተጠቁሟል ።

ኢትዮጵያ በሁሌንተናዊ መልኩ ቀና የማለትና ተወዳዳሪ የመሆን ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ ያላስደሰታቸውና በለውጡ ሂደት ጥቅማቸው የተነካባቸው አሸባሪው የህወሓት ቡድንና መሰል አቋም ያላቸው ሀይሎች በጋላቢዎቻቸው ምዕራባዊያን ሀይሎች ዓለም አቀፍ ሚዲያዎቻቸዉን በመጠቀም ለውጡን ለመቀልበስ፣ የሀገር ሉአላዊነትና የሀገራችንን የግዛት አንድነት ለማፍረስ የከፈቱብን የሽብር ጦርነትና ሀሰተኛ ፕሮፓጋንዳቸውን በፅኑ የሚያወግዝ ሰልፍ እንደሆነም የሰልፉ ኮሚቴ አክሏል ።

የወላይታ ዞን ህዝብና መንግሥት በሀገራችን ላይ አሸባሪው ህወሓት በሁለት ዙሮች የጀመረውን ጥቃት ከመንግሥት ጎን በመቆም አክሽፈናል አሁንም ይህ እኩይ ቡድን ለ3ኛ ጊዜ የቀረበለትን የሠላም ጥሪ በመርገጥ የከፈተውን ጦርነት በጥምር ጦራችን ድል ነስተን የኢትዮጵያን ብልፅግና እንደሚናረጋግጥ በድጋፉ ለማሳየት ነዉ ብለዋል።

!

ወ/ሶዶ ጥቅምት 10/ 2015 ዓ.ም (ወ/ዞ/መ/ኮ/ጉ/መምሪያ)

ከግል ጥቅም ይልቅ የዜጎችን ሁለንተናዊ ጥቅም ለማስከበር ጤናማ የንግድ ስርዓት መዘርጋት ያስፈልጋል ።አቶ ደስታ ዳና ጥቅምት 10/02/2015 ዓ.ም በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር የንግድና ገበያ ...
20/10/2022

ከግል ጥቅም ይልቅ የዜጎችን ሁለንተናዊ ጥቅም ለማስከበር ጤናማ የንግድ ስርዓት መዘርጋት ያስፈልጋል ።አቶ ደስታ ዳና

ጥቅምት 10/02/2015 ዓ.ም በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር የንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት የ2014 ዓ.ም ክንውን ሪፖርት እና የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ ክንውን ላይ ምክክር ተደርጓል።

አቶ ደስታ ዳና የቦዲቲ ከተማ ከንቲባ ፦ በገበያ ስርዓት ውስጥ የሚስተዋሉ መጠነ ሰፊ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ጠንካራ የንግድ ስርዓት መዘርጋት እንደሚሻ ገልፀዋል ።

የንግድ ስርዓት በአግባቡ ካልተዘረጋ የገበያን አላስፈላጊ አለመረጋጋት መቆጣጠር እጅግ ከባድ ይሆናል። ስለሆነም ከግል ጥቅም ይልቅ የዜጎችን ሁለንተናዊ ጥቅም ለማስከበርና ጤናማ የንግድ ስርዓት ለመዘርጋት በቅንነትና በታማኝነት መትጋት እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል ።

ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ሳይኖራቸው በከተማ ውስጥ ባልተገባ ቦታ ያልተገባ ግብይት በማድረግ ያልተፈለገ የዋጋ ንረት እንዲኖርና ህጋዊ የሆኑ የንግዱ ማህበረሰቦች ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንዲፈጠር የሚያደርጉ ህገወጥ ነጋዴዎችን ለይቶ ወደ ትክክለኛው መስመር እንዲገቡ የማድረግ ስራም በጥንቃቄ ፣በፍጥነት ሊሰራ ይገባልም ብለዋል።

ከዚህ ቀደም የነበሩ ውስንነቶች በአዳዲስ አሠራሮች ሊቀረፉ እና መፍትሔ ሊበጅላቸው ያስፈልጋል ። ህብረተሰቡን ፣ የንግዱ ማህበረሰብን እና ሌሎች አካላትን የሚያማርሩ የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ስር ነቀል ለውጥ በማድረግ የሚታይና ሁሉም የሚመሰክረው ለውጥ ሊመዘገብ እንደሚገባም ገልፀዋል ።

አቶ ደስታ ዳና አክለውም የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እና ህገወጥነትን ለመታገል ተግባራትን ለቅሞ በጋራ መምራት ያስፈልጋል ሲሉም ገልፀዋል ።

አቶ ወንድሙ ዎርሲሶ የወላይታ ዞ/ን/ገ/ል/መ ኃላፊ ፦ መንግስት የህብረተሰቡን ችግር ለመቅረፍ በተለያዩ መንገዶች የሚያስገቧቸው በድጎማ የሚገቡ የፍጆታ ዕቃዎች ለህብረተሰቡ በአግባቡ ሊዳረሱ ይገባል ብለዋል።

ከነዳጅ ግብይት ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮች በደንብና መመሪያ መሠረት ዕልባት እንዲያገኙና ከማደያ ውጭ የሚደረጉ ህገወጥ የነዳጅ ግብይቶች እንዲቆሙ ባለድርሻ አካላት አሠራርን ተከትሎ እንዲሰራ አሳስበዋል።

የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ያስችል ዘንድ የሰንበት ግብይት ማስጀመርና ለተግባራዊነቱ መጣር እንደሚያስፈልግ ገልፀው በቀጣይ የገበያ ሁኔታ ለማረጋጋት ቅንጅታዊ አሠራሮች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልፀዋል።

አቶ እንድርያስ ጉንታ የቦዲቲ ከተማ ን/ገ/ል/ጽ/ቤት ኃላፊ በበኩላቸው ፦ ፍትሐዊ የንግድ አሰራርና ዘመናዊ የግብይት ስርዓትን በመዘርጋትና መልካም አስተዳደርን በማስፈን የንግዱ ማህበረሰብና የሸማቹን ህብረተሰብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በበጀት ዓመቱ ትኩረት ተሰጥቶት ይ:ሰራል ብለዋል።

በንግድ ስርዓት ውስጥ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት በተለያዩ የፍጆታና ሌሎች ነገሮች ላይ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ ህብረተሰቡን ላልተፈለገ ኪሳራ በሚዳርጉ ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ እርምጃ ለመውሰድ በሚያስችል ቁመና ላይ ጽ/ቤታቸው እንደሚገኝ የገለፁት አቶ እንድርያስ ባለድርሻ አካላት ከጎናቸው እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።

በምክክር መድረኩ ላይ የዞን ን/ገ/ል/መመሪያ ኃላፊና ባለሙያዎች ፣የከተማ አስተባባሪ አካላት ፣አጠቃላይ የከተማ አመራሮች ፣የጽ/ቤቱ ማኔጅመንት አካላት፣የጽ/ቤቱ ባለሙያዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል ።

ህገወጥነትን ለመታገል በቁርጠኝነት ትግል ማድረግ እንደሚያስፈልግ ተገለፀ።ቦዲቲ፤ጥቅምት፤9/2015 በወላይታ ዞን በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር አጠቃላይ ተግባራት ያሉበት ደረጃ ተገምግሟል። አቶ ደ...
19/10/2022

ህገወጥነትን ለመታገል በቁርጠኝነት ትግል ማድረግ እንደሚያስፈልግ ተገለፀ።

ቦዲቲ፤ጥቅምት፤9/2015 በወላይታ ዞን በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር አጠቃላይ ተግባራት ያሉበት ደረጃ ተገምግሟል።

አቶ ደስታ ዳና የቦዲቲ ከተማ ከንቲባ : ህገወጥነትን ለመታገል በቁርጠኝነት ትግል ማድረግ አስፈላጊ ነው ።ሁሉም ተግባር ሊመራ የሚገባው በአሠራር ነው ሰለሆነም በከተማችን ውስጥ የሚሰሩ እያንዳንዳቸው ተግባራት መንግስት በዘረጋው አሠራር መሠረት ሊተገበር ያስፈልጋል በማለት ይህን ለማስፈፀም በየተቋማቱ የተሰየሙ ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን በአግግባቡ መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የንግድ አካባቢዮች ለተጠቃሚዮችና ለከተማው ነዋሪ የጤና ጠንቅ እንዳይሆኑ ውሃ መድፊያ፣መፀዳጃ ቤትና ሌሎች መሠረታዊ ነገሮችን ማሟላት ለማይችሉ የንግድ ተቋማት የምግብ ዝግጅት የንግድ ፈቃድ መስጠት ተገቢ እንዳልሆነ የገለፁት ክቡር ከንቲባው በቀጣይ የፀዳ ውብ እና ማራኪ ከተማ ለመፍጠር የከተማ ገፅታ በሚያበላሹ የግልና የድርጅት ተቋማት ላይ ጥብቅ እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል።

ከተማችን ዘርፈ ብዙ ለውጥ ያስፈልጋታል።ለውጥ እንዲመጣ ችግሮች ተለይተው ለችግሮች ብቁ መፍትሔ ሊሰጥባቸው ይገባል።አስተማማኝ ለውጥ እንዲመዘገብ ደግሞ እጅ ለእጅ ተያይዞ በህግና ደምብ ማዕቀፍ ውስጥ ሆኖ ተግባራት ተፈጻሚነት ሊያገኙ ያስፈልጋል ።

አቶ ደስታ ዳና አክለውም የኢንቨስትመንት መሬት የወሰዱ ባለሀብቶች ወደስራ የሚገቡበት ሁኔታ እንዲፈጠርና የስራ ዕድል ከመፍጠር አኳያ ያላቸውን ሚና በአግባቡ በሚወጡበት ሁኔታ የከተማ አስተዳደሩ በትኩረት ይሰራል ብለዋል ።

የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ጌታሁን ዳና:የከተማችንን ዕድገት በሚፈለገው ልክ ለማሳደግ አመራሩ የተሰጠውን ተልዐኮ በአግባቡና በፓርቲ ዲስፕሊን መምራት እንዳለበት ገልፅዋል ።

የገቢ አማራጮችን አሟጦ መጠቀምና የገቢ ስወራን የመታገል ስራ በትኩረት ሊመራ እንዳለበት የገለፁት አቶ ጌታሁን ፣ ከባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅታዊ አሰራር አጠናክሮ መስራት ገቢን በአግባቡ መሰብሰብ ወሳኝ እንደሆነ አስረድተዋል ።

ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት የአገልግሎት አሰጣጥና በሌሎች ጽ/ቤቱ በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ላይ ስር ነቀል ለውጥ ለማምጣት መትጋት እንደሚገባም አሳስበዋል።

ከኢንተርፕራይዝ ጽ/ቤት አንፃር በ2015 ዓ.ም የወጣቱን ስራ ዕድል ፈጠራ ከልየታ ባሻገር ወጣቱን ወደ ስራ ማስገባት ላይ በትኩረት መስራት፣ እንዲሁም ወጣቶች በአዳዲስ የስራ መስክ እንዲሰማሩ የግንዛቤ ስራ መስጠት እንዳለበት ጠቅሰዋል።

በተጨማሪም የጤና ሥራ ፣ የትምህርት ስራ
፣የገበያ ሁኔታና የዋጋ ጭማሪ መቆጣጠር፣ የኑሮ ውድነት ለመቀነስ የከተማን ግብርና አጠናክሮ መስራትና የበጋ መስኖ ተግባርን በታቀደው ልክ መምራት አስፈላጊ እንደሆነ የመንግስት ዋና ተጠሪው አክለው ገልፀዋል።

አቶ በረከት በላይነህ የኢንተርፕራይዝ እና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ እና የከተማው ም/ከንቲባ :ስራ አጥ ወጣቶችን ህግና ደንቡን ጠብቆ በአግባቡ በማህበር አደራጅቶ ወደ ሥራ ማስገባት ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ እንደሆነ ጠቅሰው በተለይ በኮንስትራክሽን ዘርፍ ደረጃ 9 እና ኮብልስቶን ማህበር አደረጃጀት መመሪያ መሰረት አድርጎ በአዲስ መልክ ይዋቀራል ብለዋል።

የፀጥታ ስራ ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ተሰጥቶት ሊሰራ የሚገባ እንደሆነና ከወንጀል ነፃ የሆኑ ቀጠናን የማስመረቅ ስራን በተገቢው መስራት እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል።

በ100 ሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች የስራ እድል ተጠቃሚ ሆነዋል- አቶ እርስቱ ይርዳው ቦዲቲ ፣ ጥቅምት 9፣ 2015 የስራና ክህሎት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል በደቡብ ክልል ከሚገኙ የካቢኔ...
19/10/2022

በ100 ሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች የስራ እድል ተጠቃሚ ሆነዋል- አቶ እርስቱ ይርዳው

ቦዲቲ ፣ ጥቅምት 9፣ 2015 የስራና ክህሎት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል በደቡብ ክልል ከሚገኙ የካቢኔ አባላት ጋር በሚኒስትር መስሪያ ቤቱ በአዲሱ የዘርፉ እሳቤ ላይ በሀዋሳ ምክክር እያደረጉ ነው

የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እርስቱ ይርዳው በምክክር መድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ በአጭር ጊዜ ተደራጅቶ በአዲስ አስተሳሰብ ሁሉንም የዘርፍ ስራዎች በተቀናጀ መንገድ ወደ ውጤት መቀየር የሚያስችል አአራር መዘርጋቱን አድንቀዋል።

በብዙ ችግሮች ውስጥ ሆነን መሰናክሎች ቢያጋጥሙንም ፈተናዎችን እየተሻገርን ለወጣቶች የስራ እድል በመፍጠር ኢኮኖሚያችንን ማሳደግ የሚያስችል ጉዞ ቀጥለናል ሲሉም አውስተዋል።

በችግር ውስጥ እያለፉ ተቋም መገንባት፣ስራ መፍጠር፣ኢንቨስትመንት ማስፋፋት፣ወጣቶች ሀገራቸውን በደማቸው የሚያስከብሩ ብቻ ሳይሆን ሰርተው ከራሳቸው አልፈው ለወገናቸውም እንደሚተርፉ ማየት ችለናል ብለዋል።

ክልሉ ባለፈው በጀት ዓመት ባጋጠሙ ችግሮች ሳይንበረከክ ለወጣቶች የስራ እድል መፍጠር አብይ ጉዳይ በማድረግ ሲሰራ እንደነበር የተናገሩት ርዕሰ መስተዳድሩ ለረጅም ጊዜ ግንባታቸው ሲጓተቱ የነበሩ የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን በማጠናቀቅ ስራ ፈጣሪ የሆነ ዜጋ ማፍራት እንዲቻል ጥረት መደረጉን ጠቁመዋል።

የነበሩት ማሰልጠኛ ተቋማት ሰልጣኞችን የመቀበል አቅማቸውን እንዲያሳድጉ እና የስራ እድል መፍጠር በሚቻልባቸው እድሎች ላይ እንዲያተኩሩ መሰራቱን አስረድተዋል።

በክልሉ የታሰበውን ያህል ባይሆንም በገጠር እና በከተማ በ100 ሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች በማህበር ተደራጅተው ስራ እንዲፈጥሩ መደረጉንም ተናግረዋል።

የስራና ክህሎት ሚኒስትሯ ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል በበኩላቸዉ ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ባለፈው አመት ከተቋቋመ ወዲህ በዘርፉ ለውጥ ለማምጣት ጥረት ሲያደርግ እንደነበር ተናግረዋል።

ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ በዘርፉ መሻሻል ስላለባቸው ጉዳዮች ዝርዝር እቅድ በማዘጋጀት የበርካታ አካላትን ተሳትፎ ማካተቱን ጠቁመዋል።

ካለው ነባራዊ ሁኔታ አንጻር ለክልሎች ምን አይነት ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባ እንዲሁም ከካቢኔ አባላት የተሟላ ተግባቦት በመፍጠር በቀጣይ ውጤታማ ስራ መስራት የሚያስችል አሰራር ለመዘርጋት ነው ብለዋል።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የክህሎት ልማት፣የስራ እድል ፈጠራ እና የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳዮችን በአንድ ላይ በማስተሳሰር እየተንቀሳቀሰ ነው ሲሉም አብራርተዋል።

ከዚህ ቀደም 10 የተለያየ ቦታ ላይ ተደራጅተው የነበሩ ተቋማትን አሰባስቦ ወጥ ወደሆነ ሚኒስትር መስሪያ ቤት መቀየር የሚያስችል ስራዎችን ሲያከናዉን መቆየቱን ሚኒስትሯ አብራርተዋል።

በአገር አቀፍ ደረጃ 2 ሚሊየን ገደማ ወጣቶ በቴክኒክና ሙያ ስርዓቱ እንዲያልፉ ይደረጋል ያሉት ሚኒስትሯ ይህንን ሀይል ስልጠና በመስጠት ብቻ ወደ ስራ ማስገባት በራሱ ግብ አይደለም ብለዋል።

እናም ወጣቶችን በአስተሳሰብ እንዲልቁ በማድረግ ያገኙትን እድል ሀብት ማፍረራት እንዲችሉ መስራት ይገባል ሲሉም አውስተዋል።

አዲሱ እሳቤ አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ወደ መልካም እድል መቀየር ታሳቢ ያደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል ።

በመድረኩ በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጥላሁን ከበደን ጨምሮ የክልሉ መንግስት የካቢኔ አባላት እና ሌሎችም ተገኝተዋል ።

#የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ

ለዞናችን ብሎም ለሃገራችን ብልጽግና አስተዋጽኦ ሊያደርጉ የሚችሉ ጠንካራ ተቋማትን መገንባት ያስፈልጋል፦ አቶ መስፍን ዳዊትቦዲቲ ፤ጥቅምት 9/2015 ለዞናችን ብሎም ለሃገራችን ብልጽግና አስተ...
19/10/2022

ለዞናችን ብሎም ለሃገራችን ብልጽግና አስተዋጽኦ ሊያደርጉ የሚችሉ ጠንካራ ተቋማትን መገንባት ያስፈልጋል፦ አቶ መስፍን ዳዊት

ቦዲቲ ፤ጥቅምት 9/2015 ለዞናችን ብሎም ለሃገራችን ብልጽግና አስተዋጽኦ ሊያደርጉ የሚችሉ ጠንካራ ተቋማትን መገንባት እንደሚያስፈልግ የወላይታ ዞን ም/አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ዳዊት አሳሰቡ።

የወላይታ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት መምሪያ የ2014 ተግባር አፈጻጸም ግምገማና የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

የወላይታ ዞን ም/አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ዳዊት በመድረኩ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት በአገልጋይነት ስሜት የተሟላ ቀልጣፋ መንግስታዊ አገልግሎት ተቋም መፍጠር አለብን ብለዋል።

በመንግስት ተቋማት ሥር የሰደዱ ችግሮችን ለማስወገድ በጠንካራ መሠረት ላይ የሚቆሙ ዘላቂ የሆነ የመፈጸምና የማስፈፀም አቅማ ያለው ተቋም መገንባት እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል።

ለሃገራችን ብልጽግናና ለዜጎች እርካታ አስተዋጽኦ የሚያድርጉ ጠንካራ ተቋማት መገንባት ዋነኛ ቁልፍ ስራ ሊሆን እንደሚገባም አመላክተዋል።

ከሰው ሀብት ልማት ረገድ በቅጥር፣ በዝውውርና በደረጃ ዕድገት ዙሪያ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥ አሰራሮችን ማረም ያስፈልጋል ሲሉም አሳስበዋል።

የወላይታ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት መምሪያ በዛብህ ዛዛ በበኩላቸው በጀት ዓመቱ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ቀልጣፋ እንዲሆን በትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም አስታውቀዋል።

አቅደን እንሰራለን፤ በውጤት አጅበን ለተሻለ ውጤት በማስመዝገብ የተገልጋይ እርካታን ለማረጋገጥ እንደሚተጋ መምሪያው ገልጿል።

መምሪያው በ2014 የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ መዋቅሮች የዕውቅና ሽልማት እንደሚያበረክት አስታውቋል።

በመድረኩ የዞኑ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ዮሐንስ ቀየነን ጨምሮ አጠቃላይ አመራር፣ የወረዳና ከተማ አስተዳዳሪዎች፣ የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም የመምሪያው ማኔጅመንት አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የኀብረት ሥራ ማህበራት ለማህበረሰቡ የሚያበረክተው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ ገለጹቦዲቲ ፤ጥቅምት 8/2015 የወላይታ ዞን የኀብረት ሥራ ጽ/ቤት ዓ...
18/10/2022

የኀብረት ሥራ ማህበራት ለማህበረሰቡ የሚያበረክተው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ ገለጹ

ቦዲቲ ፤ጥቅምት 8/2015 የወላይታ ዞን የኀብረት ሥራ ጽ/ቤት ዓመታዊ ጉባኤ እና የዳሞታ ወላይታ ገበሬዎች ኀብረት ሥራ ዩኒየን የምግብ ዘይት ፋብሪካ ለማቋቋም የሚያስችል ካፒታል ማሳደጊያ ንቅናቄ መድረክ አካሂዷል።

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ እንደገለጹት የኀብረት ስራ ማህበራት በኢኮኖሚያዊ፣ በማህበራዊና በፖለቲካዊ መስተጋብር ለማህበረሰቡ የሚሰጠው ፈይዳ ከፍተኛ ነው ብለዋል።

በዞኑ ባለፉት ዓመት ኅብረት ስራ ማህበራትን ከማደራጀት ባለፈ ለህብረተሰቡ ያበረከተው አስተዋፅኦ አነስተኛ መሆኑን የጠቆሙት ዋና አስተዳዳሪው ለዚህም ዘርፉ ትኩረት አለመሰጠቱን ያመለክታል ብለዋል።

ማህበራትን ማጠናከር ያስፈልጋል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ማህበራት ሲጠናከሩ ህብረተሰብ በተጨባጭ በኢኮኖሚ ተጠቃሚ የሚያደርግ ዘርፍ ነው ብለዋል።

የግል ባለሀብቶችና ስግብግብ ነጋዴዎች በዋጋ ንረት ላይ የሚያደርጉትን አሉታዊ ተጽዕኖ ለመቅረፍና ገበያን ለማረጋጋት የኅብረት ስራ ማህበራት ላቅ ያለ ድርሻ እንዳላቸው አስረድተዋል።

አያይዘውም የግብይት ስርዓቱን ጤናማ ለማድረግ ትልቅ አቅም እንዳለው የጠቆሙት ዋና አስተዳዳሪው የጋራ የሆኑ እሴቶችን ለማሳደግና አብሮነትን ለማጎልበት አቅም ይፈጥራል ሲሉም አስገንዝበዋል።

የዳሞታ ወላይታ ዩኒየኑ የዘይት ፋብርካ ለማቋቋም የጀመረው ዓለማ እውን እንዲሆን ህብረተሰቡን በማሳተፍና በማነቃቃት የባለድርሻዎች ርብርብ ከወትሮ በተለየ መልኩ እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል።

ሁሉንም ህብረተሰብ ክፍሎችን የኅብረት ስራ ማህበር አባል እንዲሆኑ በማድርግ የማህበራት የውስጥ አቅም ማሳደግና ተደራሽ እንዲሆን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ መስራት እንደሚገባም አሳስበዋል።

የማህበራት ደህንነትን በአስተማማኝ ሁኔታ ለማስጠበቅና ህዝባዊ ውግንና እንዲኖር የኦዲት ስራን ማዘመን እንደሚገባም አመላክተዋል።

የአፈር ማዳበሪያ ስርጭት ላይ የነበሩ ጉድለቶችን ለማረም ልዩ ትኩረት መስጠት እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል።

የዞኑ የኀብረት ሥራ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት ሳሙኤል በበኩላቸው የዘርፉ ግቦቻችንንና የትኩረት መስኮቻችንን በመለየት በበጀት ዓመቱ የህዝባችን ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል።

ማህበራት ማጠናከርና ማደራጀት ለህብረተሰቡ የሚሰጠው ፋይዳ ከፍተኛ ነው ያሉት ወ/ሮ ሰላማዊት ከወትሮ በተሻለና በዘመነ ሥርዓት እንዲጠብቁ ተገቢውን ክትትል ማድረግ እንደሚያስፈልግም አመላክተዋል።

በማህበራት ዘንድ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን የሚፈጽሙ አካላት ላይ በህግ አግባብ ተጠያቂ እንዲሆኑ በማድረግ የማህበራትን ሀብት ከምዝበራ መታደግ እንደሚገባም አሳስበዋል።

ጽ/ቤቱ በ2014 የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ መዋቅሮች የማበረታቻ ሽልማት ዋንጫና ሰርተፊኬት አበርክቷል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ የጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ጌዲዮ፣ ኮንሶና፣ ደቡብ ኦሞ ዞኖች እንዲሁም የቡርጂ፣ አማሮ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ፣ አሌ ልዩ ወረዳዎች የሚካ...
18/10/2022

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ የጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ጌዲዮ፣ ኮንሶና፣ ደቡብ ኦሞ ዞኖች እንዲሁም የቡርጂ፣ አማሮ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ፣ አሌ ልዩ ወረዳዎች የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ በተመለከተ ለመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞች ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል።

በመሆኑም ከታች የተጠቀሱትን መሥፈርቶች የምታሟሉ ብዙኃን መገናኛ አካላት ረዕቡ ጥቅምት 9 ቀን 2015 ዓ.ም. ከቀኑ 8:00 ሰዓት ላይ አትላስ በሚገኘው ዋሽንግተን ሆቴል ተገኝታችሁ መዘገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

•በኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ባለሥልጣን የተመዘገበ የብዙኃን መገናኛ ተቋም መሆን፣
•የመጡበትን ብዙኃን መገናኛ መታወቂያ መያዝ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
ጥቅምት 8 ቀን 2015 ዓ.ም.

በትግራይ ክልል የሰብዓዊ አቅርቦት እና አገልግሎት ማስጀመርን በተመለከተ ከመንግሥት ኮሙኒኬሽን የተሰጠ መግለጫ የሰብአዊ ርዳታ አቅርቦትንና መሠረታዊ አገልግሎቶችን ስለማስቀጠል የተሰጠ መግለጫ...
18/10/2022

በትግራይ ክልል የሰብዓዊ አቅርቦት እና አገልግሎት ማስጀመርን በተመለከተ ከመንግሥት ኮሙኒኬሽን የተሰጠ መግለጫ

የሰብአዊ ርዳታ አቅርቦትንና መሠረታዊ አገልግሎቶችን ስለማስቀጠል የተሰጠ መግለጫ
**************

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የተወሰኑ የትግራይ ክልል ከተሞችን መቆጣጠሩ ይታወቃል።

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በቅርቡ ባወጣው መግለጫ፣ የኢትዮጵያ ሠራዊት ከተሞች የጦርነት ቦታ እንዳይሆኑ የሚያደርግ የጥንቃቄ አካሄድ እንደሚከተል መግለጡ ይታወሳል።

የመከላከያ ሠራዊት በከተሞች ጦርነት እንዳይደረግ የተከተለው ጥብቅ ዲሲፕሊን፣ በሲቪሎች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ አድርጓል። የኢትዮጵያ መከላከያ በከተሞች ውስጥ ምንም ዓይነት ጦርነት ሳያካሂድ ሽሬን፣ አላማጣና ኮረም ከተሞችን ለመቆጣጠር ችሏል።

ይህ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የተከተለው ጥብቅ ወታደራዊ ዲሲፕሊን፣ የሕወሐትን ፕሮፓጋንዳ ሲያስተጋቡ የነበሩ አካላትን ሟርት ያመከነ ነው።

ከልዩ ልዩ የርዳታ ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት፣ መከላከያ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ርዳታ በተሣለጠ መንገድ እንዲደርስ የኢትዮጵያ መንግሥት በቂ ዝግጅት አድርጓል። ይሄም የሽሬ አውሮፕላን ማረፊያን ተጠቅሞ ርዳታ ማድረስን ይጨምራል።

መንግሥት ከሰብአዊ የርዳታ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ሰብአዊ ርዳታ የሚደርስባቸውን መንገዶች እያስፋፋ ነው። በተቀናጀ መንገድ በሰሜን ጎንደር በኩል ወደ ሽሬ የሚወስደውን እና ከኮምቦልቻ - ደሴ- ወልድያ- ቆቦ- አላማጣ ያለውን መንገድ ለመክፈት እየሠራ ነው።

ይሄንን ሥራ የሚያሣልጥ ኮሚቴ ከሚመለከታቸው አካላት ተወጣጥቶ ሥራ ጀምሯል። እነዚህ ሥራዎች ቴክኒካዊ የሆኑ ጥናቶችን እና ግጭት በነበረባቸው አካባቢዎች አገልግሎቶችን ለማስጀመር የሚያስችሉ መሠረታዊ ሥራዎችን ይጨምራል።

ጥቅምት 8 ቀን 2015 ዓ.ም

አዲስ አበባ

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

አርሶአደሮች በበጋ መስኖ እርሻ ልማት ሥራ የተሻለ ምርት እንዲያገኙ ልዩ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ የወላይታ ዞን የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ አሳሰቡ ቦዲቲ ፤መሰከረም 8/2015...
18/10/2022

አርሶአደሮች በበጋ መስኖ እርሻ ልማት ሥራ የተሻለ ምርት እንዲያገኙ ልዩ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ የወላይታ ዞን የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ አሳሰቡ

ቦዲቲ ፤መሰከረም 8/2015 ዓ.ም በወላይታ ዞን በድጉና ፋንጎ ወረዳ በብላቴ ጫርቾ ቀበሌ የበጋ መሰኖ ሰንዴ ልማት ቅድም ዝግጅት ሥራ ያለበት ደረጃ የወላይታ ዞን የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ የመስክ ምልከታ ጉብኘት አድርገዋል።

በጉብኝቱ ወቅት የወላይታ ዞን የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ እንዳሉት መንግሥት የግብርና ስራን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን በመጨመር የምግብ ዋስትናን በዘላቂነት ለማረጋገጥ አቅዶ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

አያይዘውም በእጃችን ያለው ሀብትን በአግባቡ ተጠቅመን የበጋ መስኖ ስንዴን በማልማት የአርሶአደሩን ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥና መትጋት አለብን ሲሉም አመላክተዋል።

አርሶአደሮች በምግብ ራሳቸውን ችለው ምርታቸውን ለገበያ እስከሚያቀርቡ ድረስ ከአመራሩና ባለሙያው የሚደረገውን ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

የድጉና ፋንጎ ወረዳ ም/አሰተዳደርና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማርቆስ ኡሹላ በበኩላቸው በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት 690 ሄክታር ማሳን በማልማት ከ24 ሺህ በላይ ኩንታል ምርት ለማግኘት ወደ ተግባር መገባቱን አስታውቋል።

የ2014 ዓ.ም የበጋ ስንዴ ልማት ብዙ ልምድ ያገኘንበት ነው ያሉት አቶ ማርቆስ በዚህ ዓመት በትልቅ ተነሳሽነት እና ቁርጠኝነት ብዙ ምርት ለማግኘት በትኩረት እንደሚሰራም አስታውቀዋል።

በበጋ መሰኖ ሰንዴ ልማት አምና በቁጭት የተጀመረው በብዙ ድል የታጀበ በመሆኑም አርሶአደሮቻችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏልም ብለዋል።

ያለንን አቅም አሟጠን በመጠቀም ከአምናው ይበልጥ ተጠቃሚ ለመሆን በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ የወረዳው አርሶ አደሮች ተናግረዋል።

በጉብኘቱ የወላይታ ዞን ረዳት የመንግሰት ተጠሪ ክብር አቶ ሳሙኤል ፎላን ጨምሮ የድጉና ፋንጎ ወረዳ አሰተባባሪ አካላት፣ የቀበሌ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊና አጠቃላይ የቀበሌ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የዘገባው የወረዳው ህዝብ ግንኙነትና ማህበራዊ ሚዲያ ዘርፍ ነው

"በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ግጭት ከቁጥጥር ውጪ የወጣ ነገር የለም!!" - አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን “በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ግጭት ከቁጥጥር ውጪ የወጣ ነገር የለም፤ ሁሉም ነገር በታ...
18/10/2022

"በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ግጭት ከቁጥጥር ውጪ የወጣ ነገር የለም!!" - አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን

“በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ግጭት ከቁጥጥር ውጪ የወጣ ነገር የለም፤ ሁሉም ነገር በታቀደው መሰረት እየሄደ ነው” ሲሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ገለጹ።

መንግስት የአፍሪካ ሕብረት የሰላም ውይይቱ የሚካሄድበትን ቀን እስኪያሳውቅ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል ብለዋል።

“አንዳንዶች በሰሜን ኢትዮጵያ የተፈጠረው ግጭት ከቁጥጥር ውጪ ሆኗል በሚል እየተጠቀሙበት ያለው አገላለጽ ከእውነት የራቀ ነው” ሲሉ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።

“ግጭቱ ወደ አማራና አፋር ክልሎች ተስፋፍቶ ነበር አሁን ያ ነገር የለም፤ የመከላከል እርምጃው በታሰበው መልኩ እየሄደ ይገኛል” ነው ያሉት።

የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦትና አገልግሎትን እንደሚጀመር ነው አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በመልዕክታቸው የጠቆሙት።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ትናንት በሰጡት መግለጫ “በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ከቁጥጥር ውጪ እየሆነ ነው” በሚል ከእውነታ የራቀ አስተያየት መስጠታቸውን ጠቅሰዋል።

የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ትናንት ባወጣው መግለጫ መንግስት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ለማስከበር በትግራይ ክልል የሚገኙ የአውሮፕላን ማረፊያዎችን፣ የፌዴራል ተቋማትንና ታላላቅ መሠረተ ልማቶችን የግድ ለመጠበቅ እንደሚገደድ መግለጹ ይታወሳል።

ከዚህም ባሻገር በመንግሥት ቁጥጥር ስር በሆኑ አካባቢዎች ሰብአዊ እርዳታ በተሻለ መንገድ መቅረብ እንዲችልና የእርዳታ ሠራተኞች ደህንነት የተጠበቀ እንዲሆን መንግሥት ከእርዳታ ድርጅቶች ጋር አብሮ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን በመግለጫው አመልክቷል።

የኀብረት ሥራ ማህበራትን ማደራጀትና ማጠናከር ለሀገራቱ ኢኮኖሚያዊ ዕድገትና ለኢንዱስትሪ ሽግግር ወሳኝ ነው፦ ወ/ሮ ሰላማዊት ሳሙኤል ቦዲቲ ፤ ጥቅምት 8/2015 የኀብረት ሥራ ማህበራትን ማደ...
18/10/2022

የኀብረት ሥራ ማህበራትን ማደራጀትና ማጠናከር ለሀገራቱ ኢኮኖሚያዊ ዕድገትና ለኢንዱስትሪ ሽግግር ወሳኝ ነው፦ ወ/ሮ ሰላማዊት ሳሙኤል

ቦዲቲ ፤ ጥቅምት 8/2015 የኀብረት ሥራ ማህበራትን ማደራጀትና ማጠናከር ለሀገራቱ ኢኮኖሚያዊ ዕድገትና ለኢንዱስትሪ ሽግግር ወሳኝ መሆኑን የዞኑ የኀብረት ሥራ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት ሳሙኤል ገለጹ።

የወላይታ ዞን የኀብረት ሥራ ጽ/ቤት ዓመታዊ ጉባኤ እና የዳሞታ የወላይታ ገበሬዎች ኀብረት ሥራ ዩኒየን የምግብ ዘይት ፋብሪካ ለማቋቋም የሚያስችል ካፒታል ማሳደግያ ንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ መልዕክት ያስተላለፉት የዞኑ የኀብረት ሥራ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት ሳሙኤል እንዳሉት የኀብረት ሥራ ማህበራትን ማጠናከር ለኢንዱስትሪ ሽግግር መሠረት ነው ብለዋል።

የአርሶአደሩን ምርትና ምርታማነቱን ለማሳደግ የግብዓት አቅርቦት በፍታሃዊነት ማቅረብ ትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ገልጸዋል።

ገበያን ለማረጋጋት ለዘርፉ ቁልፍ ተግባር ነው ያሉት ወ/ሮ ሰላማዊት በዚህም ታቅዶ የተሻለ እንቅስቃሴ መደረጉንም አስታውቀዋል።

የማህበራት ድህነትን በማረጋገጥና ያለባቸውን ዘርፈ ብዙ ችግሮች በመቅረፍና አቅማቸውን በማጎልበት አባላት ተጠቃሚ እንዲሆኑ በትኩረት እንደሚሰራም አስገንዝበዋል።

በ2015 የዘርፉን ተግባርን ለማሳለጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት እና ማህበራትን በማነቃቃት ለተሻለ ውጤት እንተጋለን ብለዋል።

በመድረኩ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማን ጨምሮ የዞኑ አጠቃላይ አመራር፣ የወረዳና ከተማ አስተዳዳሪዎች፣ ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።

አሰልጣኝ ስዩም ከበደ የሲዳማ ቡና አሰልጣኝ ሆነው ተሾሙቦዲቲ ፣ ጥቅምት 8፣ 2015  አሰልጣኝ ስዩም ከበደ የሲዳማ ቡና ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል፡፡  በ2013 የኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪ...
18/10/2022

አሰልጣኝ ስዩም ከበደ የሲዳማ ቡና አሰልጣኝ ሆነው ተሾሙ

ቦዲቲ ፣ ጥቅምት 8፣ 2015 አሰልጣኝ ስዩም ከበደ የሲዳማ ቡና ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሾመዋል፡፡

በ2013 የኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪሚየር ሊግ ፋሲል ከነማን ለሻምፒዮናነት ያበቁት አሰልጣኝ ስዩም ከበደ በዘንድሮው የውድድር አመት አስከፊ የሚባል አጀማመር ላይ የሚገኘውን ሲዳማ ቡናን በዋና አሰልጣኝነት ተረክበዋል፡፡

በዘንድሮ የዝውውር መስኮት ከፍተኛ እንቅስቃሴ በማድረግ አዳዲስ ተጫዋችን ማስፈረም የቻለው ሲዳማ ቡና የሚጠበቀውን ውጤት ማግኘት አልቻለም፡፡

እስካሁን ባደረጋቸው ሦስት ጨዋታዎች ከድሬዳዋ ከተማ 2 ለ 2 ሲለያይ በሀድያ ሆሳዕና 4 ለ1 እንዲሁም በፈረሰኞቹ ደግሞ የ5 ለ 1 ሽንፈትን አስተናግዷል፡፡

ክለቡ በሶስት ጨዋታዎች ማግኘት ከነበረበት 9 ነጥብ ውስጥ 1 ነጥብ ብቻ በማስመዝግብ የሊጉ ግርጌ ላይ ይገኛል፡፡

(ኤፍ ቢ ሲ)

በብልጽግና ፓርቲ የሚመራዉ መንግስት የትምህርት ጥራትን እና ተገቢነትን በሁሉም ደረጃ በማሻሻል ሁሉም ህጻናትና ወጣቶች ሙሉ አቅማቸውን እንዲጠቀሙ የሚያስችል የትምህርት ሥርዓት እንዲኖር ተግቶ...
18/10/2022

በብልጽግና ፓርቲ የሚመራዉ መንግስት የትምህርት ጥራትን እና ተገቢነትን በሁሉም ደረጃ በማሻሻል ሁሉም ህጻናትና ወጣቶች ሙሉ አቅማቸውን እንዲጠቀሙ የሚያስችል የትምህርት ሥርዓት እንዲኖር ተግቶ ይሠራል፡፡

የሀገራችን ሥርዓተ-ትምህርት፣ የማስተማር ስነ-ዘዴው፣ የማስተማሪያ እና የመማሪያ ቁሳቁሶች እና ግምገማ ስርዓቶቹ እንዲሻሻሉ እና ከገበያው ፍላጎት ጋር የተጣጣሙ እንዲሆኑ በማድረግ ሁሉም የሀገራችን ተማሪዎች ከፍተኛ አፈፃፀም ካላቸው ዓለም አቀፍ ሥርዓቶች ጋር የሚነፃፀሩ ከፍተኛ የትምህርት ደረጃ ውጤቶችን ማስመዝገብ የሚችሉበት የትምህርት ሥርዓት እንዲኖር ለማድረግ የተጀመረው እንቅስቃሴ የሁሉንም አካላት ጥረት ይጠይቃል፡፡

ለ12ኛ ክፍል የሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች መልካም የፈተና ጊዜ፣

አፍሪካ የሠላም እና የደኅንነት ተግዳሮቶቿን በራሷ መፍታት አለባት - ኃይለማሪያም ደሳለኝቦዲቲ ፡ ጥቅምት 07/2015 አፍሪካ ለሠላም እና ደኅንነት ተግዳሮቶች ከውጭ መፍትሄ ከመሻት አስቀድማ...
18/10/2022

አፍሪካ የሠላም እና የደኅንነት ተግዳሮቶቿን በራሷ መፍታት አለባት - ኃይለማሪያም ደሳለኝ

ቦዲቲ ፡ ጥቅምት 07/2015 አፍሪካ ለሠላም እና ደኅንነት ተግዳሮቶች ከውጭ መፍትሄ ከመሻት አስቀድማ በራሷ ለመፍታት መሥራት እንዳለባት የኢፌዴሪ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ገለጹ፡፡

ትናንት የተጠናቀቀው የጣና ፎረም “የአኅጉሪቷ ሠላምና ደኅንነት እንዲረጋገጥ ምላሽ የመስጠት ዐቅም” በሚል ግልጽ የፓናል ውይይት አካሂዷል፡፡

አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ አፍሪካ የመንግስት አስተዳደር ለማስተካከል፣ ብዝሃነትን ለመቀበል እና የራስን ሥልጣን ለማራዘም ቅድሚያ ከመስጠት ይልቅ የዜጎችን ደኅንነት ለማረጋገጥ መሥራት አለባት ብለዋል።

አፍሪካ የምታደርጋቸው የትብብር ስምምነቶችም አፍሪካውያን ለአፍሪካዊ ችግሮች መፍትሄ እንዳይሆኑ የሚከለክል መሆን የለበትም ማለታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

አፍሪካ ከሌሎች ጋር የሚኖራት አጋርነትም ፍትሃዊ እና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ያማከለ መሆን እንዳለበት አመላክተዋል፡፡

እንደ ኤፍቢሲ ዘገባ በፓናል ውይይቱ የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ በአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር፣ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሀና ቴት፣ በአውሮፓ ኅብረት የአፍሪካ ቀንድ ተወካይ ዶክተር አኔት ዌበር እና የአፍሪካ ኅብረት የፖለቲካ ጉዳዮች የሆኑት ባንኮሌ አዴኦዬ ተካፍለዋል፡፡

በጣና ፎረም የመዝጊያ መርሐ-ግብር ላይ በኬኔት ኦሞጄ የተጻፈው “ፊዚቢሊቲ ኦፍ ካፒታሊዝም ኢን አፍሪካ” የተሰኘ የመፅሃፍ ምርቃት እና ሌሎች ሁለት ዝግጅቶች ተካሂደው የ2022 ፎረም ተጠናቋል ሲል (ደሬቴድ) ዘግቧል።

ሀገራችን የምግብ ዋስትናዋን አረጋግጣ በዓለም ገበያ በምርቶቿ መሳተፏ የሩቅ ጊዜ ህልም ሳይሆን፤ እየቀረበ የሚገኝ የጥረት ውጤት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ቦዲቲ ፡ ጥቅምት...
17/10/2022

ሀገራችን የምግብ ዋስትናዋን አረጋግጣ በዓለም ገበያ በምርቶቿ መሳተፏ የሩቅ ጊዜ ህልም ሳይሆን፤ እየቀረበ የሚገኝ የጥረት ውጤት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ

ቦዲቲ ፡ ጥቅምት 07/2015 ሀገራችን የምግብ ዋስትናዋን አረጋግጣ በዓለም ገበያ በምርቶቿ መሳተፏ የሩቅ ጊዜ ህልም ሳይሆን፤ እየቀረበ የሚገኝ የጥረት ውጤት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ገለፁ።

በአማራ ክልል ምርታማነትን ለማሳደግ በሚካሄደው ርብርብ፣ አኩሪ አተርን ለማምረት ሰፊ ዕቅድ ተይዞ እየተሠራ መሆኑንም አንስተዋል።

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በ38,000 ሄክታር ላይ ያረፈውን የኩታ ገጠም ምርት ተመልክተዋል። በጠገዴ ወረዳዋ አዲስ ዓለምም በኩታ ገጠም 1,200 ሄክታር ላይ የተመረተውን አኩሪ አተር የጎበኙ ሲሆን ያስገኙት ምርት በእጅጉ አበረታች ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በይፋዊ ማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አስፍረዋል።

በስንዴ አምራችነት ያገኘነውን አስደሳች ውጤት በሌሎች ምርቶችም እንደሚቀጥል ያመላክታል ነው ያሉት።

የቦዲቲ ከተማ መሐል ቀበሌ ምክር ቤት የ2015 ዓ.ም መደበኛ ጉባኤ አካሄደጥቅምት 7/2015 ዓ.ም በወላይታ ዞን በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር የመሐል ቀበሌ ምክር ቤት የ2015 ዓ.ም መደበኛ ጉ...
17/10/2022

የቦዲቲ ከተማ መሐል ቀበሌ ምክር ቤት የ2015 ዓ.ም መደበኛ ጉባኤ አካሄደ

ጥቅምት 7/2015 ዓ.ም በወላይታ ዞን በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር የመሐል ቀበሌ ምክር ቤት የ2015 ዓ.ም መደበኛ ጉባኤ አካሂደዋል ።

በምክር ቤቱ መደበኛ ጉባኤ የ2015 ዓ.ም የመስከረም ወር አጠቃላይ ዕቅድ ክንውን ፡ የአፈጉባኤ ዕቅድ ክንውን ፡ የአስፈጻሚ ዕቅድ ክንውን እና የቋሚ ኮሚቴ ዕቅድ ክንውን የቀረበ ሲሆን ግምገማ ተደርጎበት መጽደቅ ችሏል።

በተጨማሪም ምክር ቤቱ ለአባላት በጎጂ ልማዳዊ ድርጊት እና በህፃናት ጥቃት ተጋላጭነትን ለማስወገድ የሚያስችል የግዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተስጥቶ ውይይትም ተደርጓል ።

የቦዲቲ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ የሴቶች ሊግ አደረጃጀት አቅመ ደካማ  ለሆኑ ቤተሰቦች የበሶ ዱቄት ድጋፍ አደረጉ ጥቅምት 7/2015 ዓ.ም በወላይታ ዞን የቦዲቲ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ የሴቶች ሊ...
17/10/2022

የቦዲቲ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ የሴቶች ሊግ አደረጃጀት አቅመ ደካማ ለሆኑ ቤተሰቦች የበሶ ዱቄት ድጋፍ አደረጉ

ጥቅምት 7/2015 ዓ.ም በወላይታ ዞን የቦዲቲ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ የሴቶች ሊግ አደረጃጀት ለአቅመ ደካማ ለሆኑ ነፍሰጡርና ለወለዱ እናቶች እንዲሁም ለመከላከያ ሠራዊት ቤተሰቦች የበሶ ዱቄት ድጋፍ አድርገዋል ።

በቦታው ተገኝተው ድጋፍ ያደረጉት የቦዲቲ ከተማ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ት እመቤት ጥላሁን ፡ ይህን ድጋፍ የከተማ ህብረተሰብን አስተባብረው ያዘጋጁትን የብልፅግና ፓርቲ የሴቶች ሊግ አደረጃጀቶችን አመስግነው በቀጣይም አቅም የሌላቸው አረጋዊያንን የመርዳት ፣ የተራቡትን የማብላት እና የታረዙትን የማልበስ ስራን አደረጃጀቶቹ አጠናክረው እንድቀጥሉ አሳስበዋል ።

"በደማችን ያስከበርናትን ሰንደቅ ዓላማ በላባችን ከፍ እናደርጋታለን!" - የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት 15ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን ዛሬ በመላው ኢትዮጵያ ተከብሮ ይውላል፡፡ ቀኑን ስናከብ...
17/10/2022

"በደማችን ያስከበርናትን ሰንደቅ ዓላማ በላባችን ከፍ እናደርጋታለን!" - የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

15ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን ዛሬ በመላው ኢትዮጵያ ተከብሮ ይውላል፡፡ ቀኑን ስናከብር በደም ጠብቀን ያቆያናትን ሀገራችንን በደማችን እና በላባችን እያጸናን ነው፡፡ ሰንደቅ ዓላማ የሀገር ምልክት ነው። ይሄንን ዓርማ ይዘው ጀግኖች መሥዋዕትነት ከፍለዋል። በዓለም አደባባይ አሸንፈዋል። ይህ ሰንደቅ ዓላም ከልጅ እስከ ዐዋቂ ልብ ውስጥ የማይፋቅ ማኅተም አሳርፏል።

የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የትናንት የጋራ ታሪካችንን፤ የዛሬ ጥረታችንን እና የነገ ተስፋችንን እንዲሁም ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን አጣምሮ የያዘ የክብራችን እና የማንነታችን ማኅተም ነው፡፡

ሀገራችን ኢትዮጵያ በዘመናት ሂደት ሰንደቅ ዓላማዋን አንግበው ለሉዓላዊነቷ እና ለአንድነቷ የተዋደቁ የጀግኖች ልጆች እናት ናት፡፡ አሁን ባለንበት ዘመንም ቢሆን ሰንደቅ ዓላማዋን አንግቦ፣ ኢትዮጵያን ሊያፈርሱ የተነሡ ጠላቶቿን አሳፍሮ የሚመልስ ትውልድ ያላት፣ የእልፍ ጥቁር አንበሶች ምድር ናት፡፡ የቅርብ እና የሩቅ ጠላቶቻችን ከሀገር ውስጥ ባንዳ አሸባሪዎች ጋር ተባብረው ኢትዮጵያን ለመበታተን መሄድ እስከሚችሉት ድረስ ተጉዘዋል፡፡ ሆኖም በልጆቿ ደምና ብርታት ምኞታቸዉ ቅዠት ሆኖ ቀርቷል፡፡ እኛ ካልመራናት ትፍረስ ብለው፣ በየአካባቢው ግጭት ጠንሰሰው፣ ጠብን ስፖንሰር አድረገው ሕዝባችንን ተስፋ ለማስቆረጥ ያልፈነቀሉት ድንጋይ የለም፡፡

እያንዳንዱ የሀገር ብተና ሤራቸው ተራ በተራ ሲከሽፍባቸው ደግሞ ሀገር ጠባቂ መከላከያ ሠራዊታችንን በሌሊት አጥቅተው ጦርነት ከፍተውብናል፡፡ ይህ ሁሉ ወጥመድ ግን ለሰንደቃቸው ክብር በሚሠዉ ጀግኖች የኢትዮጵያ ልጆች የጋራ ርብርብ ከግቡ ሳይደርስ መክኖ
ቀርቷል፡፡

በተለይም የሀገር መከላከያ ሠራዊታችን እና የክልል የጸጥታ ኃይሎች በሀገራችን ላይ ጦርነት የከፈቱ አሸባሪዎችን ድል ነሥተው፤ ሀገራቸውን ከመፍረስ ታድገዋል፡፡ በደማቸው ሰንደቅ ዓላማችንን አስከብረዋል፡፡

ጠላቶቻችን ጦርነት የከፈቱብን ሁሉንም ትኩረታችንን ወደ ጦር ግንባር አድርገን በሌሎች ዘርፎች ሽባ እንድንሆን አስበው ነበር፡፡ ዓላማቸው ኢትዮጵያን አዳክሞ ማፍረስ ነበር፡፡ ነገር ግን ይህ ዓላማቸው በቁርጥ ቀን ልጆቿ ብርታትና እና በሕዝባችን ድጋፍ ሳይሳካ ቀርቷል፡፡ “በደማችን እየጠበቅን በላባችን እናጸናለን” በሚል ዕሳቤ፤ የኢትዮጵያ ልጆች ከጫፍ እስከ ጫፍ በአንድ እጃቸው እያረሱ፤ በሌላኛው እጃቸው እየተኮሱ ሀገራቸውን እየገነቡ ነው። በአንድ በኩል ከጠላት እየተከላከሉ፣ በሌላ በኩል የሰብል ምርታቸውን በብዙ እጥፍ አሳድገዋል፡፡ በዚህ ሂደትም ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ የግብርና ምርቶችን በማምረት፤ እንደ ሕዳሴ ግድብ ያሉ የተጀመሩ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን ወደላቀ ምዕራፍ በማድረስ እና ሌሎቹንም በማጠናቀቅ ሕዝባችንን ተስፋ ሊያስቆርጡ የተነሡ ጠላቶቿን ተስፋ አስቆርጣለች፡፡ በዚህም የሀገር ክብርና ሰንደቅ ዓላማችን ከፍ እንዲል ተደርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ እና መንግሥት የልማት ሥራዎችን እያጧጧፉ ጎን ለጎን የተከፈተባቸውን ጦርነት ሲመክቱ፤ ዐዋቂ እና ወጣት አትሌቶቻችን ደግሞ በዓለም አደባባይ በሀገር ፍቅር ስሜት ተናበው የሀገራቸውን አሸናፊነት ለወዳጅም ለጠላትም ዐውጀዋል፡፡ ሰንደቅ ዓላማችንን ከፍ አድርገው አውለብልበዋል፡፡ ከሀገር አልፈው የአፍሪካ ኩራት ሆነዋል፡፡

ኢትዮጵያችን በብዙ ፈተና በተወጠረችበት በዚህ ወቅት ጠላቶቿን እየመከተች የልማት ሥራዎችን በታላቅ ስኬት ቀጥላበታለች፡፡ የምግብ ሉዓላዊነት ሳይኖር የሀገር ሉዓላዊነትን ማስከበር ከባድ ነው። በልመና ስንዴ የሰንደቅ ዓላማ ክብርን በዘላቂነት ማረጋገጥ አዳጋች ነው። ጀግኖቻችን በጦር ግንባር በደም ያስከበሯትን ሰንደቅ ዓላማ፤ በልማት ትግል በላባችን ከፍ ለማድረግ፣ ሁሉም በተሠማራበት መስክ የበኩሉን መወጣት ይኖርበታል፡፡

ጥቅምት 7 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

Address

Boditti
S**o

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Boditti Town Gov't Communication Affairs Office የቦ/ከ/መ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share