Ethiopian Media Network

Ethiopian Media Network እውነተኛ የመረጃ ምንጭ

ንግድ ባንክ የራሳቸው ያልሆነን ገንዘብ የወሰዱ ግለሰቦች እስከ ቅዳሜ ድረስ እንዲመልሱ አሳሰበየኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የራሳቸው ያልሆነን ገንዘብ የወሰዱ ወይም ወደተለያየ ሂሳቦች ያስተላለፉ ግ...
21/03/2024

ንግድ ባንክ የራሳቸው ያልሆነን ገንዘብ የወሰዱ ግለሰቦች እስከ ቅዳሜ ድረስ እንዲመልሱ አሳሰበ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የራሳቸው ያልሆነን ገንዘብ የወሰዱ ወይም ወደተለያየ ሂሳቦች ያስተላለፉ ግለሰቦች እስከ መጪው ቅዳሜ ድረስ በፈቃዳቸው እንዲመልሱ አሳስቧል፡፡

ሰሞኑን ባንኩ ካጋጠመው የሲስተም ችግር ጋር ተያይዞ የራሳቸው ያልሆነ ገንዘብ የወሰዱና ያልተገባ የገንዘብ እንቅስቃሴ ካከናወኑ ግለሰቦች መካከል ብዙዎች የተደረገላቸውን ጥሪ አክብረው ገንዘቡን ወደ ባንኩ ቅርንጫፎች እየቀረቡ እየመለሱ በመሆኑ ከስህተታቸው የመመለስ በጎ ምላሽነቱን እናደንቃለን ብሏል፡፡

ገንዘቡን ተመላሽ ያላደረጉ ግለሰቦችም እስከመጪው ቅዳሜ መጋቢት 14 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ በአቅራቢያቸው ወደሚገኝ የባንኩ ቅርንጫፍ በመቅረብ ተመላሽ እንዲያደርጉ የመጨረሻ ጥሪ አቅርቧል፡፡

ይሁን እንጂ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ገንዘቡን ተመላሽ በማያደርጉ ግለሰቦች ላይ ጠንካራ እርምጃ ለመውሰድ እንደሚገደድ ገልጿል፡፡

ከሕግ አካላት ጋር በመተባበር የግለሰቦችን ሥም ዝርዝር በየቅርንጫፎች እና እንደሁኔታው ግለሰቦቹ ሊታወቁ በሚችሉበት አካባቢ ይፋ በማድረግ ቀጣይ ሕጋዊ እርምጃዎች እንዲቀጥሉ እንደሚደረግም ነው ባንኩ የገለጸው፡፡

በእርምጃው መሰረት ቀርበው የማይመልሱ ከሆነ በሕጋዊ ሂደቱ ተገቢው ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ በድርጊቱ የተጠረጠሩትን ግለሰቦች ፎቶግራፍ እና ዝርዝር ማንነታቸውን የሚገልፁ መረጃዎች በብዙሀን መገናኛ መንገድ ለሕዝብ ይፋ የሚያደርግ መሆኑንም አሳስቧል፡፡

ከእርምጃዎች ጎን ለጎንም ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ የወሰዱትን ገንዘብ እስከ ቅዳሜ ተመላሽ የማያደርጉ ግለሰቦችን ከፍትህ አካላትና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመተባበር ተገቢውን የወንጀል፣ የፍትሐ ብሔርና አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ እንደሚያደርግ ባንኩ አሳስቧል፡፡

7.5 ሚልዮን ብር ወጭ የተደረገበት ሎጎ (አርማ) ለህዝብ ስናቀርብ በታላቅ ደስታ ነው።ሚድያው የደረሰበት ደረጃም ጭምር የሚመጥን ነው።
10/03/2024

7.5 ሚልዮን ብር ወጭ የተደረገበት ሎጎ (አርማ) ለህዝብ ስናቀርብ በታላቅ ደስታ ነው።

ሚድያው የደረሰበት ደረጃም ጭምር የሚመጥን ነው።

ወላይታ ሶዶ ከተማ እንግዶችን ለመቀበል በአዲስ መንፈስ ታድሳ፤ ብሩህ ተስፋ ሰንቃ እንዲህ ደምቃለች9ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም የምታዘጋጀው ወላይታ ሶዶ ከተማ አስፈላጊውን ዝግጅት በማጠናቀ...
13/02/2024

ወላይታ ሶዶ ከተማ እንግዶችን ለመቀበል በአዲስ መንፈስ ታድሳ፤ ብሩህ ተስፋ ሰንቃ እንዲህ ደምቃለች

9ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም የምታዘጋጀው ወላይታ ሶዶ ከተማ አስፈላጊውን ዝግጅት በማጠናቀቅ ላይ ትገኛለች።

ህብረብሔራዊቷ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአስተዳደርና የፖለቲካ ማዕከል የሆነችው ወላይታ ሶዶ ከተማ እንግዶቿን ለመቀበል ከወትሮ በበለጠ ሁኔታ አምራ ተውባ ደምቃለች።

የዳሞታ ጸዳል ነፋሻማ አየሯ፣ ለሁሉም ተስማሚ የሆነች የፍቅርና የሠላም ከተማ፣ እንግዳ አክባሪ እና ተቀባይ ህዝቦቿ እንግዶቻቸውን ለመቀበል እንዲህ ባማረ ሁኔታ ተዘጋጅታለች።

በከተማችን የሚገኙ አለምአቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎች ወደ ውቢቷ ወላይታ ሶዶ ከተማ የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅታቸውን ጨርሰዋል።

ለኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ለኦቦ ሽመልስ አብዲሳ የወላይታ ህዝብ ስጦታ አበረከተለኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ለኦቦ ሽመልስ አብዲሳ የወላይታ ህዝብ ስጦታ አበርክቷል።ስጦታው የንጉስ ...
28/11/2023

ለኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ለኦቦ ሽመልስ አብዲሳ የወላይታ ህዝብ ስጦታ አበረከተ

ለኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ለኦቦ ሽመልስ አብዲሳ የወላይታ ህዝብ ስጦታ አበርክቷል።

ስጦታው የንጉስ ካዎ ጦና እና በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ የሆነው የአጆራ መንትያ ፏፏት ሲሆን ስጦታውን የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ፣ የዞኑ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አሳምነው አይዛን ጨምሮ የሀገር ሽማግሌዎች በወላይታ ህዝብ ስም አበርክተዋል።

ለተደረገው ደማቅ አቀባበልና ለተወዳጁ ስጦታ ርዕሰ መስተዳድሩ ምስጋና አቅርበዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በወላይታ ሶዶ ከተማ በሚኖራቸው ቆይታ ከዕዳ ወደ ምንዳ የመንግስት አመራሮች ስልጠና ላይ በመገኘት የዕለቱን ማጠቃለያ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

"ጊፋታ" የወላይታ ህዝብ የማንነት መገለጫ የሆነ የህዝብ በዓል ነውጊፋታ አሮጌው ዓመት የሚሸኝበትና አዲስ ዓመት የሚቀበሉት የዘመን መለወጫ በዓል ትልቅ ቦታ ተሰጥቶ ከሚከበሩት በዓላት አንዱ ...
19/09/2023

"ጊፋታ" የወላይታ ህዝብ የማንነት መገለጫ የሆነ የህዝብ በዓል ነው

ጊፋታ አሮጌው ዓመት የሚሸኝበትና አዲስ ዓመት የሚቀበሉት የዘመን መለወጫ በዓል ትልቅ ቦታ ተሰጥቶ ከሚከበሩት በዓላት አንዱ ሲሆን በየአመቱ ጊፋታ ይከበራል።

በዓሉ ለማህበረሰቡ ያለው ፋይዳ የተለየ ሲሆን በተለይ የተኮራረፉት የተጣሉትና የተጋጩት ብሎም ደመኞች ጥላቸውን ይዘው ወደ አዲሱ አመት እንዳይሸጋግሩ ጥላቻና ኩርፊያ በፍቅር ተተክቶ ሰላምና ፍቅር እንዲሰፍን ሚናው ወደር የለውም።

በዓሉ ሁለት አላማዎችን ያነገበ ሲሆን በዋናነት አሮጌውን ዓመት በሰላም ላሸጋገረው ቤተሰብን ጎረቤትን አከባቢውንና አገርን በሙሉ ጠብቆ ላቆየው አምላክ እግዚአብሔር ምስጋና ውዳሴ ክብርና አድናቆትን የሚያቀርቡበት በዓል ነው።

በሌላ በኩል አዲሱ አመት የሰላም የደስታ የፍቅር የስኬት የድል እና የመተሳሰብ አመት እንዲሆን ለፈጣሪ እግዚአብሔር ፀሎት የሚያደርሱበት እና የሚማጽኑበት በዓልም ጭምር ነው።

ጊፋታ ሰዎች ብቻ ሳይሆኑ አእዋፋትና የቤት እንስሳትም ጭምር በጋራ የሚያከብሩት በዓል ነው፡፡ ምክንያቱም በጊፋታ ሰዎች በሬ አርደው ሥጋ እየበሉና እየጠጡ በዓሉን ሲያከብሩ የሰማይ ወፎችም ቅንጥብጣቢው ስለሚደርሳቸው ነው፡፡

በበዓሉ ወቅት ለቤት እንስሳት ከወትሮ በተለየ ሁኔታ የበዓል ወቅት እስከሚጠናቀቅ ድረስ የሚመገቡት በአሞሌ (aduwaa) የተለወሰ ልዩ ሳርና የእህል ዓይነት ይዘጋጃል፡፡ በመሆኑም ጊፋታ ለፍጥረት በሙሉ የደስታና የአዲስ ህይወት ጅማሮ እንደሆነም ይታመናል፡፡

የጊፋታን በዓል መቃረብ የሚያበስሩ የሰዎች የተለያዩ እንቅስቃሴዎች ደግሞ በየቤቱ እና በየገበያ ቦታዎች የሚሰሙ የወንዴ እና ሴቴ (Adiyaanne Indde karaabiyaa) ድምጾች፣ በየአካባቢው የሚሰሙ ባህላዊ ዘፈኖች፣ ሰዎች እርስ በርስ ″እንኳን ከጨለማ ወደ ብርሃን በሰላም አሻገረህ (Hashshu Xumaappe Poo’uwaa Saro Pinnasa) እየተባባሉ መመራረቅ ከብዙ በጥቂቱ የሚታዩ ናቸዉ፡፡

የወላይታ ህዝብ በአከባቢው መኖር ከጀመረ ወዲህ ሲወርድ ሲዋረድ ዛሬን የደረሰው ጊፋታ በዓል ዘንድሮም ካለፋት ጊዜያት በተለየ መልኩ በድምቀት ሊከበር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ተጠናቋል።

ዮ ዮ ጊፋታ!! Yoo yoo gifaataa !!

በወላይታ ዞን በባይራ ኮይሻ ወረዳ የሚገኝ ሰው ሰራሽ ታሪካዊ  ይህ ሰው ሰራሽ   ከወላይታ ሶዶ ከተማ በ30 ኪ ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ ታሪካዊ ስፍራን ነው።ሀገራችን ኢትዮጵያ በርካታ የተፈጥሮ...
16/08/2023

በወላይታ ዞን በባይራ ኮይሻ ወረዳ የሚገኝ ሰው ሰራሽ ታሪካዊ

ይህ ሰው ሰራሽ ከወላይታ ሶዶ ከተማ በ30 ኪ ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ ታሪካዊ ስፍራን ነው።

ሀገራችን ኢትዮጵያ በርካታ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ የቱሪስት መስዕብ ቦታዎች እንዳሉት ይታወቃል። በዋናነት ሰው ሰራሽ የመስዕብ ቦታዎች በተለያየ ጊዜ ለተለያየ አላማ ተብሎ የተሰሩ ስሆኑ በወቅቱ ለታለመለት አላማ ከዋሉ በኃላ ለቀጣይ ትውልድ የታሪክ ቦታና ቅርስ ከመሆኑም አልፎ በወቅቱ የነበሩ የአባቶቻችን ጥበብና ለአላማ ያላቸውን ፅናት የሚያሳይ ሆኖ ለዘመናት ይቆያል።

ከዚህም አልፎ ለአካባቢው የገቢ ምንጭ ሆኖ ሲያገለግሉም እናያለን። ከእነዚህ ሰው ሰራሽ የቱሪስት መስዕብ ቦታዎች አንዱ የሆነውና #በባይራ #ኮይሻ #ወረዳ በሴሬ ባላካ ቀበሌ ፑላሳ አምባ ላይ የሚገኘውን አንድ ታሪካዊ #ዋሻ እናስተዋውቃለን።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን ባይራ ኮይሻ ወረዳ በሴሬ ባላካ ቀበሌ በፑላሳ አምባ መንደር ከባህር ወለል #በ2,302 ሜትር ከፍታ ስፍራ ላይ የሚገኘው ሰው ሰራሽ የቱሪስት መስዕብ ቦታ የሆነው #የአሩጂያ #ዋሻ ታሪካዊ ቦታ ነው።

ይህ ዋሻ ከክርስቶስ ልደት በፊት የተቆፈረ እንደሆነና ዋሻው የተሰራበት የአሰራር ጥበብና በውስጡ ያሉ ክፍሎች እጅግ በጣም የሚደንቅ ናቸው።

በወቅቱ የነበሩ ሰዎች ልጆቻቸውንና ከብቶቻቸውን ከጠላት ለመጠበቅ፣ በጦርነት ድልን ለማግኘትና ለአደን ምቹ ቦታዎችን ለማግኘት በሚል ዓላማ የተሰራ እንደሆነ የታሪክ አዋቅዎች ይናገራሉ።

በአሩጂያ ንጉሰ ነገስታት ዘመን የነበሩ አባቶች ድንጋይን ከድንጋይ ጋር በማጋጨት እሳት አውጥቶ የተለያዩ የዱር እንስሳትን ቀንድ በመጠቀም የቆፈሩት ይህ አሩጂያ ዋሻ እጅግ ማራኪያ በርካታ ታሪኮችን ጠቅልሎ የያዘ እንደሆነ ይነገራል።

ይህ የአሩጂያ ዋሻ ሶስት መግቢያ በር ያሉት ስሆን በመሃል ያለው ትንሹ እንደ መስኮት እንደሚያገለግልና አንዳንደ ጠላትን አስቀድሞ ለመከላከል ይረዳ ዘንድ ውሻ እንደ ሚታሰር አባቶች ይናገራሉ።

ወደ ውስጥ ስንገባ ከ300 ሰው በላይ መያዝ የሚችል ሰፊ ሳሎን ያለው ስሆን በሁሉም አቅጣጫ የተለያዩ ክፍሎች አሉት። በጣም የሚገርመው በዚህ ዋሻ ውስጥ #ከ30-40 ደቂቃ መንገድ መጓዝ የሚያስችል ሁለት መግቢያዎች ያሉት ስሆን፣

የመጀሪያው ወደ አፋ ወረዳ ወደ ሚባልበት ስፍራ የሚወስድ እንደሆነና ሌላኛው ደግሞ አሁንም ወደ አፋ ወረዳ እንደሚያስወጣ የታሪክ አዋቅ አባቶች ይናገራሉ።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን ባይራ ኮይሻ ወረዳ የሚገኘውን የአሩጂያ ሰው ሰራሽ ዋሻ እስከ ቦታው ድረስ በመሄድ እንድትጎበኙና በታሪካዊ አሰራር እንዲትደነቁ ተጋብዛቿል በማለት የባይራ ኮይሻ ወረዳ ማህበራዊ ሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ዘግቧል።

የኮንሶ ዞን ሽግግር ምክር ቤት 6ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ማካሄድ ጀመረ። የዞኑ ምክር ቤት ምክትል አፌ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ገረመው አያኖ እንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ለምክር ቤ...
11/08/2023

የኮንሶ ዞን ሽግግር ምክር ቤት 6ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ማካሄድ ጀመረ።

የዞኑ ምክር ቤት ምክትል አፌ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ገረመው አያኖ እንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ለምክር ቤቱ ልዩ ልዩ አጀንዳዎች ቀርበው ይፀድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የህዝቦች አብሮነትና አንድነት ይበልጥ እንዲጠናከር ከከፋፋይ አጀንዳ ተላቀን አንዳች ለሌላችን ድርና ማግ፤ ዋልታና ማገር መሆን ይገባናል።ጨለማን የሚገፈው ብርሃን ነው፡፡ ድካምን የሚያቀለው እ...
07/08/2023

የህዝቦች አብሮነትና አንድነት ይበልጥ እንዲጠናከር ከከፋፋይ አጀንዳ ተላቀን አንዳች ለሌላችን ድርና ማግ፤ ዋልታና ማገር መሆን ይገባናል።

ጨለማን የሚገፈው ብርሃን ነው፡፡ ድካምን የሚያቀለው እረፍት ነው፡፡ ጥላቻን የሚያስወግደው ፍቅር ነው፡፡ ቂምንና ቁርሾን ማስወገድ የሚቻለው ደግሞ በይቅር ባይነት ነው፡፡

ሰሞኑ በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች የሚለቀቁ ጥላቻን ያነገቡ መረጃዎች ለዘመናት የቆየውን የህዝቦች አብሮነትንና እሴቶች ለመሸርሸር ታልሞና ታቅዶ እየተሰራጨ ያለ ቢሆንም ህዝብን ከህዝብ ጋር ለማጋጨት መሞከር ወንጀለኛ እንጂ ጀግና አያስብልም፡፡

ታዋቂው የጥቁሮች ሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ማርቲን ሉተር ኪንግ በአንድ ወቅት እንዲህ ሲል መናገሩ ይታወቃል፤ "Darkness cannot drive out darkness; only light can do that. Hate cannot drive out hate; only love can do that". “ጨለማን በጨለማ ሳይሆን በብርሀን፤ ጥላቻንም በጥላቻ ሳይሆን በፍቅር” ልንቀይር እንደምንችል ያሳያል፡፡

ታዲያ እውነታው ይህ ከሆነ እኛ እየሆንን ያለነው የትኛውን ነው? ጥላቻን በጥላቻ ወይስ ጥላቻን በፍቅር? ማንም ሊረዳው የሚገባው እውነታ ግን ጥላቻ የበለጠ ሰውን ከሰው እያራራቀ ወዳልተፈለገ መንገድ ይመራል እንጂ ሰላምና አንድነትን ከቶውንም ቢሆን አምጥቶ አያውቅም፡፡

ስለዚህ በሰዎች ዘንድ የቱንም ያህል ክብራችንን የሚነካ ማንነታችንን የሚያጠለሽ ነገር እንኳ ቢፈጠር ክፉን በክፉ መመለስ ሳይሆን መጥፎውን በደግነት ቀይረን እኛነታችንን የበለጠ በመልካምነት ልናሳይ ይገባናል፡፡ የጽንፈኛ ኃይሎች መጠቀሚያ እንዳንሆን ራሳችንን እንጠብቅ፡፡

አንዳንድ ጽንፈኞች በማህበራዊ ሚዲያ በህዝቦች መካከል ያለው የእርስ በእርስ ትስስርን ለማጠላሸት፣ ወንድማማችነትና እህተማማችነት ለመከፋፈል የሚያሰራጩትን በጋራ መታገልና መቃወም ያስፈልጋል፡፡

ጥላቻን በጥላቻ፤ ስድብን በስድብ ሳይሆን በፍቅርና በመተሳሰብ ማሸነፍ ይገባል፡፡ የህዝቦች አብርነትና አንድነት ከጥንት ጀምሮ አባቶቻችን እንደሰርገኛ ጤፍ ህብር ፈጥረው ያመጡት በጥቂት ሴረኞችና የፌስቡክ አርበኞች የሚሻክር አይደለም፡፡

ብልጽግና ፓርቲ ወንድማማችነትን መተክሉ አድርጎ ሲነሳ የሁሉም ችግሮች ማሰሪያ ውል እንደሆነ ስለሚያምን ነው፡፡ ማናቸውም ለፍትህ እና ለነፃነት የሚዳርጉ ትግሎች ፍሬያማ የሚሆኑትም በወንድማማችነት ዕሴት ውስጥ ብቻ ነው፡፡

የወንድማማችነት ዕሴት ባለበት ሁሉ አንዱ ሌላውን መረዳት አለ፤ ሆኖም ይህ እሴት በተሸረሸረ ቁጥር ደግሞ የሌላውን ሕመምና ፍላጐት መረዳት ከባድ ያደርገዋል፡፡

ሠላም እንዳያያዛችን ሁኔታ የሚወሰን እንጂ በየትኛውም ዓለም ስለተፈለገ ብቻ የሚገኝ ማህበራዊ ሀብት አይደለም፡፡ የመጠፋፋትና የመከፋፈል ስንክ-ሳሮች በብልጽግና ህክምና ይፈወሳሉ፡፡ ለዚህ ደግሞ እያንዳንችን የራሳችንን ድርሻ መወጣት ይኖርብናል፡፡

አዲሱ "የደቡብ ኢትዮጲያ ክልል" ሠላሙ የሰፈነበት፣ ህብረቱ እንደብረት የሚጠነክርበት፣ ፍቅር የሚጎለብትበት፣ ፍትህ የሚሰፍንበት፣ ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚረጋገጥበት፣ አብሮነትና ወንድማማችነት የሚጸናበት፣ መተሳሰብና አብሮነት የሚታይበት፣ አግላይነት እና ጽንፈኝነት ከሥር መሠረቱ የሚነቀልበትና የሚጠፋበት፣ እውነት የሚነግስበት እና ኢትዮጵያዊነት የሚያጸናበት እንዲሆን ሁሉም የበኩሉን አስተዋፆኦ ማበርከት ያስፈልጋል እንላለን፡፡

ዋልያዎቹ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የአፍሪካ ዞን ማጣሪያ በምድብ አንድ ተደልድለዋል ✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️አዲስ አበባ ሐምሌ 6/2015 ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2026 በሚካ...
13/07/2023

ዋልያዎቹ በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የአፍሪካ ዞን ማጣሪያ በምድብ አንድ ተደልድለዋል
✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️
አዲስ አበባ ሐምሌ 6/2015 ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2026 በሚካሄደው 23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የአፍሪካ ዞን ማጣሪያ በምድብ አንድ ተደልድላች።

የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን (ካፍ) የዓለም ዋንጫ የአፍሪካ ማጣሪያ የምድብ ድልድል ማምሻውን በኮትዲቭዋር አቢጃን ዛሬ ይፋ አድርጓል።

በዚህም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በምድብ አንድ ከግብፅ፣ ቡርኪና ፋሶ፣ ጊኒ ቢሳው፣ ሴራሊዮን እና ጂቡቲ ጋር ተደልድሏል።

54 የአፍሪካ አገራት በማጣሪያው በዘጠኝ ምድብ ተደልድለው የማጣሪያ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እ.እ.አ 2026 በአሜሪካ፣ሜክሲኮ እና ካናዳ ጣምራ አዘጋጅነት ይካሄዳል።

በዓለም ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ 48 አገራት ይሳተፋሉ።

ዓለም አቀፋ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) አፍሪካ በዓለም ዋንጫው የምታሳትፈው አገራት ቁጥር ከአምስት ወደ ዘጠኝ ከፍ አድርጓል።

ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳዉ እና ሌሎች የፌደራልና የደቡብ ክልል ከፍተኛ አመራሮች የተለያዩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶችን አስጀመሩ✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️የፌደራልና የደቡ...
13/07/2023

ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳዉ እና ሌሎች የፌደራልና የደቡብ ክልል ከፍተኛ አመራሮች የተለያዩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶችን አስጀመሩ
✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️
የፌደራልና የደቡብ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ የክረምት የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን አስጀመሩ።

በማብሰሪያ ፕሮግራሙ የደም ልገሳ፣የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስና የችግኝ ተከላ ተካሂዷል።

መሰል የበጎ ተግባር ስራዎች በሁሉም አካባቢ ተጠናክሮ እንዲቀጥል መልእክት ተላልፏል።

በዱራሜ ከተማ ኅብረተሰቡን ተጠቃሚ ያሚያድርጉ የተለያዩ ልማት ፕሮጀክቶች ተመረቁ ✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️በከምባታ ጠንባሮ ዞን ዱራሜ ከተማ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወ...
09/07/2023

በዱራሜ ከተማ ኅብረተሰቡን ተጠቃሚ ያሚያድርጉ የተለያዩ ልማት ፕሮጀክቶች ተመረቁ
✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️
በከምባታ ጠንባሮ ዞን ዱራሜ ከተማ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ እና ኅብረተሰቡን ተጠቃሚ ያሚያድርጉ አምስት ልማት ፕሮጀክቶች በዛሬው ዕለት ተመርቀዋል።

ፕሮጀክቶቹ ለወጣቶች የሚተላለፉ የንግድ ቤቶች፣ የሕዝብ መድኃኒት ቤት፣ የእሳት አደጋ መከላከያ፣ የካንባታ ማኅበረሰብ ቴሌቪዥን ጣቢያ እና አደባባይ ናቸው።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የካንባታ ጠንባሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ መለሰ አጭሶ፣ የደቡብ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ፋጤ ሰርሞሎ እና ሌሎችም የክልል እና የዞን የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

ፕሮጀክቶቹ በርካታ ወጣቶችን ወደ ሥራ በማስገባት ተጠቃሚ የሚያደርጉ እንደሚሆኑ ተመላክቷል።

09/07/2023

Welcome to Wolaita s**o እንኳን ወላይታ ሶዶ ደህና መጡ
✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️
ወላይታ ሶዶ ባሁኑ ጊዜ በፈጣን እድገት ላይ የሚትገኝ ምርጥ ከሀገራችን ከተሞች አንዱዋ ነች።

ከተማዋ ለኑሮ እጅግ ተስማሚ ናት። አየሯ ወይና ደጋ ሆኖ ለመኖርም ሆነ ለመስራት እጅግ በጣም አመቺ ከተማ ናት።
ወላይታ ሶዶ ባለሰባት በር ከተማ ነች።

ኢትዮጵያን ለማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች በነፃነት የሚጓጓዙበት ባለሰባት በር መንገዶችም⏬

1. ከዎላይታ ሶዶ-ዋካ-ታርጫ-ጭዳ-ጅማና ከጭዳ- አመያ- ቦንጋ ኮንክሪት አስፋልት መንገድ ያላት

2. ከዎላይታ ሶዶ- ሠላምበር- ሳውላ-ቡልቂ-ላስካ ኮንክሪት አስፋልት ያላት እና ከዎላይታ ሶዶ- ሠላምበር- ሳውላ-ጅንካ አማራጭ መንገድ ያላት

3. ከዎላይታ ሶዶ- ሁምቦ-አርባምንጭ- ካራት-ጂንካ-ሳላማጎ-ሚዛን አማን የሚያገናኝ ኮንክሪት አስፋልት መንገድ ያላት

4. ከዎላይታ ሶዶ-ባደሣ-ሞሮቾ-ዲላ-ሞያሌ -ናይሮቢ ኮንክሪት አስፋልት መንገድ ያላት (ከዎላይታ ሶዶ-ባደሣ-ሞሮቾ-ሐዋሳ)

5. ከዎላይታ ሶዶ- ቦዲት-ሾኔ- ሀላባ ቁሊቶ- ሻሼመኔ- ዝዋይ- አዲስ አበባ (ከዎላይታ ሶዶ- ቦዲት-ሾኔ- ሀላባ ቁሊቶ- ሻሼመኔ-ሐዋሳ)

6. ከዎላይታ ሶዶ-አረካ-ሆሳዕና -ወራቤ -ቡታጅራ -ሰበታ አስፋልት መንገድ ያላት ናት።

7 .ዎላይታ ሶዶ- ጉልጉላ -ሆብቻ- ዲላ ጌዲኦ- ሞያሌ- ኬኒያ

በእነዚህ በሮች አማካኝነት ስፈልጉ ምርትዎን ማስገባት አሊያም ማስወጣት መብትዎ በእጅዎ ነው። በአጭር ጊዜ ትርፋማ የመሆን እድል በጣም ሰፊ ነው። ይህንን ደግሞ ወደ ከተማዋ ስመጡ በተግባር የሚያዩት ነገር ነውና ይምጡ ይጎብኙ ያትርፉ ይኑሩበት።

አሁን ላይ በሀገራችን ታዋቂ የሆኑ ግለሰቦች የአይን ማረፍያ ሆናለች። ለአብነትም ያክል ሌዊ ሆቴል እና ሪዞርት ሥራ ጀምሯል። ቀጥሎ ሻለቃ ኃይለ ገብረስላሴም ባለስድስት ኮከብ ሆቴልና ሪዞርት ግንባታውን የተጠናቀቀ ስሆን በቅርቡ ሥራ ይጀምራል።

ሌሎች ባለሀብቶችም በውብቷ ወላይታ ሶዶ የእንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው እየሰሩ ይገኛሉ። እናም እርስዎም ይምጡና እንቨስት ያድርጉ ራስዎትን ይለውጡ ሀገርንም ይለውጡ!!!

ከህዝብ አንጻር የወላይታ ህዝብ ራሱን በኢትዮጵያዊነት የሚያይ ስለሆነ ከበርካታ የሀገራችን ብሄር ብሄረሰቦች ጋር አብሮ የኖረ ህዝብ ነው።

እነዚህ ብሄር ብሄረሰቦች ለአንድም ሰከንድ እንኳን በጎሪጥ ያዬ የለም። እናም የወላይታ ህዝብ ፍቅር ማርኳቸው ሙሉ ኑሯቸውን እዛው ያደረጉት እጅግ በጣም ብዙ ናቸው።

ባጠቃላይ የወላይታ ህዝብ ሥራ ወዳድ ህዝብ ስለሆነ እዛው እንቨስት በማድረግዎ ምንም ጸጸት አይሰማዎትም። ይምጡ ይጎብኙ ያትርፉ ይኑሩ።

ኑ Invest In Wolaita, Ethiopia🙏
ሰላም ለሀገራችን🙏🇪🇹
Ethiopian Media Network

የሱዳን ተፋላሚ ሀይሎችን ለማደራደር መሪዎች አዲስ አበባ ገብተዋል✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️የሱዳንን የርስ በርስ ግጭት ለመፍታት ተፋላሚ ሀይሎችን ለማደራደር በነገው እለት በአዲ...
09/07/2023

የሱዳን ተፋላሚ ሀይሎችን ለማደራደር መሪዎች አዲስ አበባ ገብተዋል
✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️
የሱዳንን የርስ በርስ ግጭት ለመፍታት ተፋላሚ ሀይሎችን ለማደራደር በነገው እለት በአዲስ አበባ በመሪዎች ደረጃ ውይይት ይካሄዳል።

በዚህ ውይይት የሚሳተፉ የተለያዩ አገራት መሪዎች እና የዓለምአቀፍ ተቋማት መሪዎች ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል።

ከመሪዎቹ መካከልም የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ የጅቡቲው የውጭ ጉዳይና አለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር መሀመድ አሊ ይገኙበታል።

መሪዎቹ አዲስ አበባ ሲገቡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ሰኔ አምስት 2015 ዓ.ም በጂቡቲ በተደረገው የኢጋድ መደበኛ የመሪዎች ጉባዔ ላይ ኢጋድ የሱዳንን ግጭት እንዲያሸማግሉ የኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ጅቡቲና ደቡብ ሱዳን መሪዎች መሰየሙ ይታወቃል፡፡

የሰላም ድርድሩም በአዲስ አበባ እንዲሆን ውሳኔ ማስተላለፉ ይታወሳል፡፡

ከሁለት ሳምንት በፊት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለጹት፣ኢጋድ ኢትዮጵያን ጨምሮ አራት አገራት ለሱዳን መፍትሄ እንዲያፈላልጉ ወክልና ሰጥቷል፤ የሰላም ሂደት ድርድሩም በአዲስ አበባ እንዲካሄድ ወሳኔ ተላልፏል፤ ይህ ታሪካዊ ውሳኔ ተደርጎ ይወሰዳል ማለታቸው አይዘነጋም።

የተለያዩ የአለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡት ለአራት ወራት ያህል የዘለቀው ግጭት የሱዳን ህዝብን ስጋት ውስጥ ጥሏል። የአገልግሎት መስጫ ተቋማት በሚፈለገው ልክ አገልግሎት እየሰጡ አይደለም፡፡ እንዲሁም ከዋናው ከተማ በመስፋፋት ወደ ሌሎች ከተሞች መዛመቱን እየዘገቡ ይገኛሉ።

በግጭቱ በርካታ ዜጎች ህይወታቸውን ሲያጡ ከሶስት ሚሊየን በላይ ሱዳናዊያን ወደ ጎረቤት ሀገራት በተለይ ወደ ኢትዮጵያ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በግዜያዊ መጠለያዎች ይገኛሉ።

ሐምሌ 2 ቀን 2015 ዓ.ም
በሞገስ ጸጋዬ

ውቧ፣ ባለ 7 በሯ እና ሙሹራዋ ወላይታ ሶዶ ከተማ✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️የወላይታ ዞን ዋና ከተማ የሆነችው ወላይታ ሶዶ በ1887 ዓ/ም ተቆረቆረች ፡፡ወላይታ ሶዶ ስያሜዋን ያ...
09/07/2023

ውቧ፣ ባለ 7 በሯ እና ሙሹራዋ ወላይታ ሶዶ ከተማ
✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️
የወላይታ ዞን ዋና ከተማ የሆነችው ወላይታ ሶዶ በ1887 ዓ/ም ተቆረቆረች ፡፡

ወላይታ ሶዶ ስያሜዋን ያገኘችው ከ150 ዓመታት በፊት በአከባቢው ይኖሩ ከነበሩ "ሞቼና ቦራጎ ሶዶ" ከተባሉ አንድ ታዋቂ ነጋዴ ስምና ከተማዋ አሁን በምትገኝበት አቅራቢያ ይገኝ ከነበረው "ሶዷ ሹቻ" ከሚባለው ሲሆን ትርጓሜውም "የሶዶ ድንጋይ" ተብሎ ከሚታወቅ ትልቅ የድንጋይ አለት የተወሰደ እንደሆነ ይነገርለታል፡፡

ውቧ ወላይታ ሶዶ ከተማ ከአዲስ አበባ በሻሸመኔ 390 ኪ.ሜ፤ በቡታጅራ ሆሳዕና 329 ኪ.ሜ በደቡብ ምዕራብ አቅጣጫ እንዲሁም ከሐዋሳ 167 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች ፡፡ 16 ሺ 164 ሄክታር ላይ ነው ከተማዋ ያረፈችው፡፡የመልክዓ ምድር አቀማመጡ ከባህር ጠለል በላይ 1784-2346 ኪ.ሜ ከፍታ ላይ ትገኛለች፡፡

ወላይታ ሶዶ ከተማ በአዲሱ መዋቅራዊ እና አስተዳደራዊ ፕላን የቆዳ ስፋቷ 17 ሺ 164 ሄክታር ይሸፍናል፡፡ በክልሉ ትልቁ ግብር ከፋይና ከፍተኛ ገቢ የሚሰበስቢባት ከተማ ነች።

በደቡብ ክልል ካሉ ከተሞች በከፍተኛ ዕድገትና ለውጥ ጎዳና የምትገኘው ውቧ ወላይታ ሶዶ ከተማ በርካታ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴዎች የሚደረጉባት 7 መግቢያና መውጫ በሮች ባለቤት ነች፡፡

ወላይታ ሶዶን ከሌሎች አጎራባች ከተሞች ያስተሳሰሯት ዋና ዋና መንገዶቿም ከሶዶ ሻሸመኔ አዲስ አበባ፣ ከሶዶ አርባምንጭ ጂንካ፣ ከሶዶ ጎፋ ሳውላ፣ ከሶዶ ታርጫ ጅማ፣ ከሶዶ ቢጣና ሞሮቾ ሐዋሳ፣ ከሶዶ ሆሳዕና አዲስ አበባ እና ከሶዶ ጉልጉላ ዲላ ናቸው ፡፡

በአሁኑ ጊዜ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ተቻችሎ፤ ተከባብሮና ተፈቃቅሮ የሚኖሩባት የብሔር ብሔረሰቦች ከተማ ናት፡፡በሆቴልና ቱሪዝም፤ በኢንዱስትሪ፤ በማህበራዊ አገልግሎትና በከተማ ግብርና በከፍተኛ ሁኔታ ኢንቨስት ለማድረግ ምቹ አቅም አላት፡፡

የወላይታ ሶዶ ከተማ ሻኛ በመባል የሚታወቀው ዳሞታ ተራራ የከተማው ትልቅ መስህብ ነው፡፡ በተፈጥሮ አምራና ተውባ በልምላሜ ያጌጠች ከተማ ናት።

ይችን ውብ ከተማ መጣችሁ ኢንቨስት እንድታደርጉና እንድትጎበኙ ከተማ አስተዳደሩ ጥሪ ያቀርባል።

ይቀጥላል...

ስለ ጊቤ 3 ምን ያህል ያውቃሉ⁉️✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️ ግልገል ጊቤ 3 የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የሚገኝበትን መቀመጫ እነሆ !! የግልገል ጊቤ 3 የኤሌክትሪክ ኃ...
08/07/2023

ስለ ጊቤ 3 ምን ያህል ያውቃሉ⁉️
✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️
ግልገል ጊቤ 3 የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የሚገኝበትን መቀመጫ እነሆ !!

የግልገል ጊቤ 3 የኤሌክትሪክ ኃይል ፕሮጀክት በደቡብ ብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት በወላይታ ዞን, በኪንዶ ዲዳዬ ወረዳ ውስጥ ይገኛል።

ይህ ኃይል ማመንጫ ጣቢያው ከአዲስ አበባ በስተደቡብ 470 ኪሎ ሜትር ገደማ በኪንዶ ዲዳዬ ወረዳ በወላይታ ዞን እና በዳውሮ ዞን ድንበሮች መካከል ይገኛል። ከግልገል ጊቤ ዳግማዊ ሃይል ማመንጫ ጣቢያ 155 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው የኦሞ ወንዝ የታችኛው ኮርስ ላይ ይገኛል። ፕሮጀክቱ በ240 ሜትር ከፍ ያለ አለት የተሞላ ግድብ 10 ሜትር ስፋት ያለው እና 630 ሜትር ርዝመት ያለው ግድብ አለው።

ግልገል ጊቤ 3 ግድብ በዳውሮ ዞን እና በወላይታ ዞን በኦሞ ወንዝ ላይ ከተያያዘው የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጋር 243 ሜትር ከፍታ ያለው ሮለር የታመቀ የኮንክሪት ግድብ ነው። በደቡብ ብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል በዳውሮ እና በወላይታ ዞን 62 ኪሎ ሜትር (39 ማይል) አካባቢ ይገኛል። በ1870 ሜጋ ዋት (MW) ገደማ የኃይል ማመንጫ በአፍሪካ ውስጥ ትልቁ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ፋብሪካ ነው ፣ ስለሆነም በ2007 ከነበረው 814 ሜጋ ዋት ውስጥ በኢትዮጵያ ውስጥ የተጫነውን አጠቃላይ አቅም በእጥፍ ይጨምራል። [1]

የጊቤ ሶስት ግድብ የጊቤ ካሴድ አካል ነው ፣ ነባር የጊቤ 1 ግድብ 184 ሜጋ ዋት(MW) እና ጊቤ 2 የኃይል ማመንጫ 420 ሜጋ ዋት(MW) እንዲሁም ጊቤ አራተኛ/ ኮንታ ኮይሻ/ 1472 ሜጋ ዋት(MW) እና ጊቤን ጨምሮ ተከታታይ ግድቦች VI 560 ሜጋ ዋት(MW) ግድቦች። ነባሮቹ ግድቦች በባለቤትነት የሚተዳደሩት በመንግስት ባለቤትነት በተያዘው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እንዲሁም የጊቤ ሶስት ግድብ ደንበኛ ነው።

ስለዚህ ግልገል ጊቤ 3 የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት 1870 ሜጋ ዋት (MW) የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በአፍሪካ ውስጥ ትልቁ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ በመሆን የሚገኝበት ትክክለኛው መቀመጫ በደቡብ ብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት ፣ በወላይታ ዞን, በኪንዶ ዲዳዬ ወረዳ ነው።

የኮንሶ ህዝብ በተፈጥሮና በሰዉ ሰራሽ አደጋ በድርቅ በተጎዳበት ወቅት ከጎናቸን ለነበረዉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለከተማዉ ህዝብ ምስጋናችንን በከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት በመገኘት አ...
08/07/2023

የኮንሶ ህዝብ በተፈጥሮና በሰዉ ሰራሽ አደጋ በድርቅ በተጎዳበት ወቅት ከጎናቸን ለነበረዉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለከተማዉ ህዝብ ምስጋናችንን በከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት በመገኘት አቅርበናል።

የኮንሶ ዞን በተከሰተዉ የሰዉ ሰራሽና የተፈጠሮ አደጋ ለጉዳት ለተዳረገዉ ህዝባችን ጉዳታችንን እንደ ጉዳታቸዉ ቆጥረዉ ድጋፍ ላደረጉልን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና ለከተማዉ ነዋሪ የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች፣ የአገር ሽማግሌዎች እና የህዝብ ተወካዮች በጋራ በመሆን በከተማ አስተዳደሩ ም/ቤት በመገኘት ምስጋናችንን አቅርበናል።

እንዲህ እርስ በርሳችን ስንተባበር የማንሻገረዉ መከራ፣ የማናልፈዉ ችግር አይኖርም። እናመሰግናለን።

የዓባይ ግድብ ግንባታ አሁናዊ ገጽታ በፎቶ‼️
08/07/2023

የዓባይ ግድብ ግንባታ አሁናዊ ገጽታ በፎቶ‼️

በወላይታ ዞን ወጣት አጃዬ ማጆር የሠራት ሞተር KTM-690 የብዙዎችን ትኩረት ስባለች ✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️በወላይታ ዞን በአረካ ከተማ ወጣት ፈጣራ ባለቤት አጃዬ ማጆር የ...
08/07/2023

በወላይታ ዞን ወጣት አጃዬ ማጆር የሠራት ሞተር KTM-690 የብዙዎችን ትኩረት ስባለች
✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️
በወላይታ ዞን በአረካ ከተማ ወጣት ፈጣራ ባለቤት አጃዬ ማጆር የተሠራው ሞተር የብዙዎችን ትኩረት ስቧል፡፡

ወጣቱ ከዚህ ቀደም የራሱን ሞዴል መኪና መሥራቱና ለዚህም የፈጠራ ባለቤትነት ከኢትዮጵያ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒሰቴር የድጋፍና እውቅና ማገኘቱ ይታወሳል።

አሁን ደግሞ እጅግ በጣም ፈጣን፣ ነዳጅ ቆጣቢ፣ ብዙ ኪሎ ሜትሮችን መጓዝ የሚችል KTM-690 የሚል ስያሜ የተሰጣት፥ ባለ ራዳይተር ሞተር ሳይክል ሰርቶ ለአገልግሎት አብቅቷል፡፡

የወጣቱ ፈጠራ የሆነው KMT 690 የተባለው ሞተር ረዥም ኪሎሜትር የመጓዝ አቅም ያለው ብቻ ሳይሆን፥ ለወታደራዊና ለሀገር አቋራጭ ተጓዥ ቱርስቶች፣ መኪኖች መግባት በማይችሉበት አስቸጋሪ ቦታዎች ላይ ጭምር መጓዝ የሚችል አቅም ያለው መሆኑን ጠቅሶ፥ ሞተሩን ለመሥራት ከ2 መቶ ሺ ብር በላይ ወጪ እንዳደረገ ተናግሯል።

KTM-690 የተባለው አዲስ ፈጠራ ሥራ የሆነው ሞተር በሰዓት ከመቶ ኪ.ሜ በላይ መጓዝ የሚችል፣ ስድስት ማርሽ ያለው ሲሆን ሦስት መቶ ሲሲ እንደሆነም ወጣቱ አሰረድቷል።

የመኪና፣ የሞተር ጥገናና የማሳመር ስራ እየሰራ የሚገኘው ወጣቱ የፈጠራ ባለቤት፥ ለመንግስታዊና ለግለሰቦች ሞተሩን በ250ሺህ ብር ለሽያጭ እንደሚያቀርብ ተናግሯል።

KTM-690 ሞዴል በውጭ አገር ባለው ገበያ እስከ 13ሺ 500 ዶላር (ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ) የሚሸጥ ሲሆን ሞተሩን በሀገር ውስጥ በማምረት የውጭ ምንዛሪ ማስቀረት እንደሚቻል ተናግሯል።

በአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የአውቶቡስ ትምህርት ክፍል ተጠሪ ላጵሶ ቶማስ እንደገለፁት፥ በሞተሩ ላይ የተገጠመው ቴርሞስታትክ ባልብና (termo static valb) እና ራዲያተር ሞተሩ ቶሎ እንዳይሞቅና ረዥም መንገድ እንዲጓዝ አቅም እንደሚሆን ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።

በሻንጣ ውስጥ ተደብቆ አውሮፓ የገባው አፍሪካዊ ሸረሪት የመኖሪያ ፍቃድ ተሰጠው✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️በሻንጣ ውስጥ ተደብቆ አውሮፓ የገባው አፍሪካዊ ሸረሪት የመኖሪያ ፍቃድ እ...
07/07/2023

በሻንጣ ውስጥ ተደብቆ አውሮፓ የገባው አፍሪካዊ ሸረሪት የመኖሪያ ፍቃድ ተሰጠው
✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️
በሻንጣ ውስጥ ተደብቆ አውሮፓ የገባው አፍሪካዊ ሸረሪት የመኖሪያ ፍቃድ እንደተሰጠው ተሰምቷል።

በግዙፍነታቸው ከሚታወቁት ‘አፍሪካን ሀንትስማን’ የተሰኙ የሸረሪት ዝርያዎች አንዱ ስኮትላንድ ኢዲንበርግ ከተማ ውስጥ መገኘቱ የበርካቶችን ትኩረት እንዲስብ አድርጎታል።

10 ሳንቲ ሜትር ያክል ርዝመት ያለው ይህ ሸረሪት ባህር ተሻግሮ ስኮትላንድ የተገኘው ለስራ ጉዳይ አፍሪካ ሰነባብተው በተመለሱ ሰዎች ሻንጣ ውስጥ ተደብቆ ሳይሆን እንዳልቀረ ተገምቷል።

ከመኖሪያ ቀዬው ብዙ ሺህ ኬሎ ሜትሮችን አቆራርጦ አውሮፓ ምድር የተገኘው ሸረሪት በስኮትላንዳውያን የእንስሳት ጤና ክብካቤ ባለሙያዎች እጅ እንዲገባ የተደረገ ሲሆን፤ በአንድ የእንስሳት መጠለያ ስፍራ በጥገኝነት የመኖር ፍቃድም ተሰጥቶታል።

ሸረሪቱ በቀሪ ዘመኑ ደህንነቱ በሙያተኛ እየተጠበቀለት በደስታ እንዲኖር እንደሚደረግም ነው ስኮትላንዳውያኑ የእንስሳት ጤና ክብካቤ ባለሙያዎች የተናገሩት።

በአፍሪካ፣ እስያና አውስትራሊያ ባሉ ሞቃታማ ስፍራዎች እንደሚገኙ የሚነገርላቸው ‘ሀንትስማን’ ሸረሪቶች በእግሮቻቸው ግዝፈት ከዓለም አንደኛ ከመሆናቸው በተጨማሪ በፍጥነታቸውና በዝላያቸው ተለይተው ይታወቃሉ።

ሸረሪቶቹ በተሟላ የዕድገታቸው ወቅት እስከ 28 ሳንቲ ሜትር የሚደርስ ርዝማኔ አላቸው።

ሸረሪቶቹ በተፈጥሮ መርዛማ ቢሆኑም የመናደፍ ፍላጎት እምብዛም የላቸውም፤ በመሆኑም የሰው ልጆችን ለከፋ አደጋ የሚዳርጉ አይደሉም ሲል በድረገጹ ያስነበበው ቢቢሲ ነው።

አዳማ➖ኢትዮጵያ✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️በአዳማ ከተማ የከተማዋ እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ በቀን 24/7 ሠዓት በደህንነት ካሜራ ቅኝት የሚደረግባት ከተማ ሆናለች።
07/07/2023

አዳማ➖ኢትዮጵያ
✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️
በአዳማ ከተማ የከተማዋ እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ በቀን 24/7 ሠዓት በደህንነት ካሜራ ቅኝት የሚደረግባት ከተማ ሆናለች።

አርባምንጭ ከተማ ወደ ከፍተኛ ሊግ ወርዷል!✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️2014 ላይ ዳግም ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተመልሶ ሲሳተፍ የነበረው አርባምንጭ ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ...
06/07/2023

አርባምንጭ ከተማ ወደ ከፍተኛ ሊግ ወርዷል!
✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️
2014 ላይ ዳግም ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተመልሶ ሲሳተፍ የነበረው አርባምንጭ ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ለገጣፎ ለገዳዲን ተከትሎ ከሁለት ተከታታይ የተሳትፎ ዓመታት በኋላ ወደ ከፍተኛ ሊግ መውረዱ ተረጋግጧል።

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ በፌዴሬሽን ም/ቤት የሰጡት አስተያየት✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️በህዝበ ውሳኔው ተፈጽመዋል ከተባሉ የህግ ጥሰቶች መካከል አመራሮች ...
06/07/2023

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ በፌዴሬሽን ም/ቤት የሰጡት አስተያየት
✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️
በህዝበ ውሳኔው ተፈጽመዋል ከተባሉ የህግ ጥሰቶች መካከል አመራሮች ተቀብለው “ማረም ያለባቸው ነገሮች” መኖራቸውን የጠቀሱት ዋና አስተዳዳሪው፤ ሆኖም ከዚህ ጋር በተያያዘ በዞኑ በቁጥጥር ስር የዋሉት አብዛኛዎቹ የምርጫ አስፈጻሚዎች መሆናቸው መዘንጋት እንደሌለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።

በወላይታ ዞን በድጋሚ ህዝበ ውሳኔ በተደረገበት ወቅት ከመታወቂያ ካርድ ጋር በተያያዘ ምርጫ ቦርድ የወሰደው እርምጃ፤ “በስውር” ለምርጫ አስፈጻሚዎች የተላለፈ መሆኑን አንስተውም ወቀሳ አሰምተዋል።

ይህ አሰራር ቦርዱ “ቀድሞ ያላስተዋወቀው” መሆኑን የጠቀሱት አቶ አክሊሉ፤ አሰራሩ የመጣው “ህዝብ በነቂስ ወጥቶ ድምጽ መስጠት ከጀመረ” እና “ከረፋዱ አራት ሰዓት በኋላ” መሆኑንም ተናግረዋል።

በዚህም ምክንያት አንዳንድ መራጮች “ከሰልፍም ጭምር እንዲበተኑ” ተደርገዋል ሲሉ ወንጅለዋል። “ምርጫ የማስፈጸም ሚና ተሰጥቶት የመጣ ምርጫ ቦርድ፤ የመራጩን የመምረጥ መብት የተጋፋ አይነት ሆኖ አይተናል። ይሄ መታረም አለበት ብዬ አስባለሁ።

ምናልባትም በቂ ማብራሪያ በዚህ ዙሪያ ቢሰጥ ጥሩ ይመስለኛል” ሲሉ አስተየታቸውን ሰጥተዋል።

04/07/2023

ገበታ ለትውልድ ዐርባ ምንጭ

Dine for Generations Arbaminch

ጠቅላይ ሚኒስተር ዶክተር ዐቢይ  አሕመድ አርባምንጭ ከተማ ገቡ✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️ጠቅላይ ሚኒስተር ዶክተር ዐቢይ  አሕመድ ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክትን ለማስጀመር አርባምንጭ...
03/07/2023

ጠቅላይ ሚኒስተር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ አርባምንጭ ከተማ ገቡ
✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️
ጠቅላይ ሚኒስተር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክትን ለማስጀመር አርባምንጭ ከተማ ገቡ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ አርባምንጭ ከተማ ሲደርሱ የጋሞ አባቶችና የከተማ ነዋሪዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

በአርባምንጭ ቆይታቸው የገበታ ለትውልድ የኮንፍረንስ ሪዞርት ፕሮጀክት በይፋ ያስጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጌዲኦ ዞን በነበራቸው ቆይታ እንደ አረንጓዴ ዐሻራችን ካሉ የልማት ሥራዎች ጎን ለጎን የጋራ ሰላማችንን ለማጎልበት የበለጠ ተባብረን መሥራት ይኖርብናል ማለታቸው ይታወሳል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት የ“ደቡብ ኢትዮጵያ” ክልልን ለመመስረት የተካሄደውን ህዝበ ውሳኔ ውጤት ሊያጸድቅ ነው   ✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️የፌደሬሽን ምክር ቤት በመጪው ሳምንት ማ...
01/07/2023

የፌዴሬሽን ምክር ቤት የ“ደቡብ ኢትዮጵያ” ክልልን ለመመስረት የተካሄደውን ህዝበ ውሳኔ ውጤት ሊያጸድቅ ነው
✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️
የፌደሬሽን ምክር ቤት በመጪው ሳምንት ማክሰኞ እና ረቡዕ በሚያደርገው መደበኛ ስብሰባው፤ “ደቡብ ኢትዮጵያ” የሚል ስያሜ የተሰጠውን ክልል ለመመስረት የተካሄደውን ህዝበ ውሳኔ ውጤት እንደሚያጸድቅ የምክር ቤቱ ምንጮች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የህዝበ ውሳኔውን አጠቃላይ ሪፖርት ከነገ በስቲያ ሰኞ ሰኔ 26፤ 2015 ለፌደሬሽን ምክር ቤት በጹሁፍ ያቀርባል ተብሏል።

የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት፤ ከማንነት እና ራስን በራስ ከማስተዳደር ጋር በተያያዙ የሚነሱ ጥያቄዎችን የመመልከት ስልጣን የሰጠው ለፌደሬሽን ምክር ቤት ነው። የፌዴሬሽን ምክር ቤትን ስልጣን እና ተግባር ለመዘርዘር የወጣው አዋጅ፤ ምክር ቤቱ የህዝብ ፍላጎትን በህዝበ ውሳኔ እንዲረጋገጥ የማድረግ ኃላፊነትንም ሰጥቶታል።

በምርጫ ቦርድ የተከናወነውን ህዝበ ውሳኔ ውጤት የማጽደቅ ኃላፊነት በአዋጅ የተሰጠውም ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ነው። በመጪው ማክሰኞ ሰኔ 27፤ 2015 ከሰዓት በኋላ ተጀምሮ በማግስቱ በሚቀጥለው የምክር ቤቱ ስብሰባ ላይ፤ ምርጫ ቦርድ “የደቡብ ኢትዮጵያ” ክልል ህዝበ ውሳኔ ሪፖርትን በንባብ እንዲያቀርብ ቀጠሮ መያዙን የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ምንጮች ገልጸዋል።

Ethiopian Media Network

01/07/2023

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተሳተፉበት የእግር ኳስ ጨዋታ
✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️
ሙሉ ጨዋታውን ይመልከቱ

የወረዳ ዋና ስራ አስፈጻሚና ምክትላቸው የሙስና ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ ተያዙ✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️በጉለሌ ክፍለ ከተማ የወረዳ 03 ዋና ስራ አስፈጻሚና ምክትላቸው በመስሪያ...
29/06/2023

የወረዳ ዋና ስራ አስፈጻሚና ምክትላቸው የሙስና ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ ተያዙ
✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️
በጉለሌ ክፍለ ከተማ የወረዳ 03 ዋና ስራ አስፈጻሚና ምክትላቸው በመስሪያ ቦታ አሰጣጥ ተደራድረው የሙስና ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፈንጅ መያዙን የጉለሌ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

የጉለሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ረ/ኮሚሽነር ፋሳካ ፈንታ እንደገለጹት በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 3 ከስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ብሎክን መሰረት በማድረግ የተፈጠረ የስራ እድል ላይ ከተጠቃሚ ወላጅ ጋር የተሻለ የመስሪያ ቦታ በጉንድሽ የመስሪያ ቦታ እናሰጣለን በማለት የተጠቃሚዋን ወላጅ አባት ብር ካልሰጠኸን ልጅህን ከስልጠና እናወጣታለን፣ የስራ እድልም አይፈጠርላትም በማለት ወላጅ አባቷን በማስፈራራት ልዩ ስሙ 6 ኪሎ አከባቢ ልዩ አዲስ ሆቴል 50,000 (ሀምሳ ሺህ ብር) ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል።

እጅ ከፍንጅ የተያዙት ግለሰቦች 1ኛ የጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 3 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አያናው አስራት እና 2ኛ የወረዳው ምክትል ስራ አስፈጻሚና የስራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ እዮብ አፈወርቅ 5000 ብር ዛሬ ከቀኑ 10:30 ሰዓት ሲቀባበሉ ክትትል በማድረግ ገንዘብ ሲቀበሉ በጸጥታ ሃይላችን እጅ ከፍንጅ ተይዘው ወደ ፖሊስ ጣቢያ ገብተው ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገባቸው ይገኛሉ።

የክ/ከተማው ፖሊስ መምሪያ በመልዕክቲቸው፣ የከተማችን ነዋሪ በየትኛውም የመንግስት ተቋም ለሚሰጡ አገልግሎቶች ሙስና ለመቀበል የሚጠይቁና የሚቀበሉ ማናቸውንም አካላት በመጠቆም ተባባሪ እንዲሆን ጥሪ አስተላልፈዋል።

የክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ መታሰቢያሐውልት ተመረቀ✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️በአዲስ አበባ ከተማ ጋርመንት አካባቢ ባለው አደባባይ የተገነባው የክቡር ዶክተር አርቲስት አሊ ...
25/06/2023

የክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ መታሰቢያሐውልት ተመረቀ
✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️
በአዲስ አበባ ከተማ ጋርመንት አካባቢ ባለው አደባባይ የተገነባው የክቡር ዶክተር አርቲስት አሊ ቢራ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ፡፡

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ፣ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ፣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃርን ጨምሮ የአርቲስቱ ቤተሰቦች እና ወዳጆች ተገኝተዋል፡፡

የቦዲ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ የሆነው የ"ኬኤል" በዓል እየተከበረ ነው✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️የቦዲ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ የሆነው የ"ኬኤል" በዓል በደቡብ ኦሞ ዞን ሳላማ...
24/06/2023

የቦዲ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ የሆነው የ"ኬኤል" በዓል እየተከበረ ነው
✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️
የቦዲ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ የሆነው የ"ኬኤል" በዓል በደቡብ ኦሞ ዞን ሳላማጎ ወረዳ ላይ እየተከበረ ነው።

በዚህ ክብረበዓል ላይ የተለያዩ ባህላዊ ክዋኔዎች በመከናወን ላይ ናቸው።

የሣላማጎ ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ስልጣኑ ሉችኮሩ እንደገለጹት፣ የዘንድሮው የ“ኬኤል” ክብረ በዓል እየተደረገ ያለው በቦዲ እና በዲኔ ብሔረሰቦች መካከል ተከስቶ የነበረው ግጭት በእርቀ ሰላም በተፈታበት ማግስት በመሆኑ ለየት ያደርገዋል።

ግጭቱ በሰላም ሊፈታ የቻለው በሁለቱ ብሔረሰቦች ባላባቶች እና ሽማግሌዎች ጥረት መሆኑንም ጠቅሰዋል።

"ኬኤል" የአንድነት የሰላምና የፍቅር መገለጫ መሆኑን ያብራሩት ኃላፊው፣ ይህንን በዓል ሁሉም ኢትዮጵያዊ እንዲጎበኘው ጥሪ አቅርበዋል።

በዚህ ክብረ በዓል ላይ ከስድስት ወር ላላነሰ ጊዜ የከብት ወተት እና ደም ብቻ ሲቀለቡ የቆዩ ወንዶች የውፍረት ውድድር በማድረግ ላይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም ያካሄደውን የወላይታ ዞን ህዝበ ውሳኔ የጊዜያዊ ውጤቱን ይፋ አደረገ✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ...
24/06/2023

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም ያካሄደውን የወላይታ ዞን ህዝበ ውሳኔ የጊዜያዊ ውጤቱን ይፋ አደረገ
✳️〰️〰️〰️〰️〰️➰〰️〰️〰️〰️〰️✳️
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በ1,812 ምርጫ ጣቢያዎች ላይ ያስፈጸመውንና 849,896 መራጮች ድምፅ የሰጡበትን የወላይታ ዞን የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ የውጤት ማዳመሩን ሥራ በዞኑ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሲያከናወን መቆየቱ ይታወቃል።

በዛሬውም ዕለት ቦርዱ የውጤት የማመሳከሩንና የማዳመሩን ሥራ በማጠናቀቅ በዞን ደረጃ የጊዜያዊ ውጤቱን ይፋ አድርጓል።

ኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ

Address

Arbaminch
S**o
GOVERNMENTAFFAIRS

Telephone

+251952634183

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian Media Network:

Videos

Share