07/09/2020 ልብ በሉ! አንድነት ሁሌም አትራፊ ነዉ! ህወሀት የክፍፍል ሴራዉን በቤንሸንጉል፣ በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ላይ ለማስፋት ይታትራል! ይህ ፎቶ የከፋፋይ የግጭት ነጋዴዎቹን ስኳር እና ግፊት እንዳይጨምር ያሰጋል!
29/08/2020 : የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አዲሱን የፌዴራል ፖሊስ የደንብ ልብስ በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጓል! የፌዴራል ፖሊስን የደንብ ልብስን በአዲስ መቀየር ያስፈለገበት ምክንያት ልብሱ ለረጅም ዓመታት አገልግሎት ላይ በመቆየቱ መሆኑን የደንብ ልብሱን ይፋ ያደረጉት የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል እንደሻው ጣሰው ገልጸዋል።