Wondmeneh Fikadu

Wondmeneh Fikadu Humanity

03/08/2023

ከአዲስአበባ ወደ ጎጃም የሚያስገባው የአባይ በርሃ በደጀን ፋኖዎች ሙሉ በሙሉ ተዘግቷል!

ሼር  ሼር  ሼርደብረ ማርቆስ ከተማ ፖሊስ ጣቢያዎች እና የብልፅግና አስተዳደር ቢሮዎች በህዝብ ቁጥጥር ውስጥ ገቡ።ህዝቡ በከፍተኛ መነቃቃት እና ወኔ እየተቆጣጠራቸው ነው።
02/08/2023

ሼር ሼር ሼር

ደብረ ማርቆስ ከተማ ፖሊስ ጣቢያዎች እና የብልፅግና አስተዳደር ቢሮዎች በህዝብ ቁጥጥር ውስጥ ገቡ።

ህዝቡ በከፍተኛ መነቃቃት እና ወኔ እየተቆጣጠራቸው ነው።

እኔም ፋኖ ነኝ ዘመቻ ተጀምሯል‼️         እኔም ፋኖ ነኝ የሚለው የማህበራዊ ዘመቻ ሁሉም በያለበት በመሆን በግል ፣በቡድን በመሆን "እኔም ፋኖ ነኝ " የሚል በሁሉም የማህበራዊ ትስስር ...
02/08/2023

እኔም ፋኖ ነኝ ዘመቻ ተጀምሯል‼️



እኔም ፋኖ ነኝ የሚለው የማህበራዊ ዘመቻ ሁሉም በያለበት በመሆን በግል ፣በቡድን በመሆን "እኔም ፋኖ ነኝ " የሚል በሁሉም የማህበራዊ ትስስር ገፆች ማለትም ፦በፌስቡክ ፣በቲክ ቶክ ፣ቲዊተር ፣በቴሌግራም ወዘተ አጫጫር ቪዲዮ እና አጭር መልዕክት በማስቀመጥ ለደም ዋጋ እየከፈለ ለሚገኘው የአማራ ፋኖ ፍፁም አጋርነታችንና አንድነታችን ከአሁኑ ሰዓት ጀምሮ ማስተላለፍ አለብን ።

ይህንን መልዕክት በግል ገፃችን እና ለሌሎች የአማራ የሚዲያ ተቋማትና ባለሙያዎች በማድረስ እንሳተፍ በማለት የአማራ ወጣቶች ማህበር የከበረ ጥሪውን ያስተላልፋል ።

ድል ለአማራ ፋኖ‼️
ድል ለአማራ ህዝብ‼️

የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና ከተማ ደብረ ማርቆስ መውጫ መግቢያ መንገዷቿን ዘጋችአሁን ከረፈደ "ወንድሞቻችን እየተዋደቁ የምን ስራ ነው?፤የምን መፍዘዝ ነው?" በሚል ነው ነጋዴው ሱቁን እየዘጋ፣ሰ...
02/08/2023

የምስራቅ ጎጃም ዞን ዋና ከተማ ደብረ ማርቆስ መውጫ መግቢያ መንገዷቿን ዘጋች

አሁን ከረፈደ "ወንድሞቻችን እየተዋደቁ የምን ስራ ነው?፤የምን መፍዘዝ ነው?" በሚል ነው ነጋዴው ሱቁን እየዘጋ፣ሰራተኛው ቢሮውን እየዘጋ ትግሉን የተቀላቀለው።

የደብረ ማርቆስ ህዝብ ለሁሉም የአማራ ከተሞች ትግሉን እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርበዋል።

አሰቸኳይ  ጥሪ ለ #ጎጃም ዳሞት ህዝብ በሙሉ!!አሸባሪው እና ኦነግ መራሹ  ሀይል በደጋ ዳሞት አማራ ላይ ይፋዊ ጦርነት ከፍቶብናል ሰለሆነም  ፍ /ሰላም ፡ጅጋ፡ደምበጫ፡አማኑኤል በተጠንቀቅ እ...
01/08/2023

አሰቸኳይ ጥሪ ለ #ጎጃም ዳሞት ህዝብ በሙሉ!!

አሸባሪው እና ኦነግ መራሹ ሀይል በደጋ ዳሞት አማራ ላይ ይፋዊ ጦርነት ከፍቶብናል ሰለሆነም ፍ /ሰላም ፡ጅጋ፡ደምበጫ፡አማኑኤል በተጠንቀቅ እንድንቆም እና ለወንድም ህዝባችን ደጋ ዳሞት ጋሻ መከታ እንሆነው ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን
ጎጃም ካለፉት የጦርነት ቦታዎች ሳይነካ ሳይወረር መቅረቱ ቁጭት የፈጠረበት አሸባሪው የአብይ አህመድ ጦር የጎጃምን አማራ ለማንበርከክ ብሎም የአማራን ህዝብ እረፍት ለመንሳት ማረሰ እንዳንችል ማዳበሪያ ክልከላ ብሎም ሰላም አዳሪውን ህዝባችንን ሰላም መንሳት በ ኢኮኖሚ ማሺመድመድ በ አጠቃላይ ሚሰጥራዊ የአማራር ዘር ለማጥፋት ብሎም ኢትዮጵጵያን ለማፍረሰ ቀን ከሌት እየተንተፋተፈ ይገኛል።
ይህን ሀይል ማጥፋት መታገል ግዴታ ነው።
መላው የአማራ ህዝብ ከጎናችን እንዲሰለፍ
ጥሪያችንን እናሰተላልፋለን።

የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ በጸሎት ተጀመረ።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በክልል ትግራይ ባሉ አህጉረ ስብከት ለመንፈሳዊ አገልግሎት ተመድበው ...
01/08/2023

የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ በጸሎት ተጀመረ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በክልል ትግራይ ባሉ አህጉረ ስብከት ለመንፈሳዊ አገልግሎት ተመድበው የነበሩ አራት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ሐምሌ ፲፮ እና ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ/ም በፈጸሟቸው የቀኖና ቤተክርስቲያን እና የሕግጋተ ቤተክርስቲያን ጥሰቶች ዙሪያ ለመወያየትና ሕግጋተ ቤተክርስቲያንን መሠረት ያደረጉ ውሳኔዎችን ለማሳለፍ ጉባኤውን በጸሎት ጀመረ።

ሕገወጥ ድርጊቱ መፈጸሙን ተከትሎ በቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት በኩል የተጠራውን አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ ለመጀመር ዛሬ ሐምሌ ፳፭ ቀን ፳፻፲፭ ዓ/ም በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ቀኖና ቤተክርስቲያንና ሕገ ቤተክርስቲያን በሚያዘው ሥርዓት መሠረት የመክፈቻ ጸሎቱ ደርሷል።

የመክፈቻ ጸሎቱ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የተመራ ሲሆን በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ባሉ አህጉረ ስብከቶች ተመድበው የቤተክርስቲያንን አገልግሎት የሚመሩ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተገኝተዋል።

የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ባወጣው የድርጊት መርሐ ግብር መሠረት ዛሬ በጸሎት የተጀመረው የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልአተ ጉባኤ ነገ ሐምሌ ፳፮ ቀን ፳፻፲፭ ዓ/ም ጠዋት 2:30 ሰዓት በተያዙት አጀንዳዎች ላይ በመወያየት የቤተክርስቲያናችንን ቀኖናትና ሕግጋት የሚያስከብሩ ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል።

ሰበር ዜና!የላስታ አውራጃ ፋኖ ለሰዓታት ባደረገው ውግያ የላሊበላ አየር መንገድን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠረ።
01/08/2023

ሰበር ዜና!

የላስታ አውራጃ ፋኖ ለሰዓታት ባደረገው ውግያ የላሊበላ አየር መንገድን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠረ።

የአማራ ሕዝባዊ ግንባር በDC የተሳካ ውይይት አደረገ  በአዲስ አስተሳሰብ፣ በጠራ ራእይ፣ ተፈትኖ ባለፈ መሪ እየተመራ ጉዞውን የቀጠለው የአማራ ህዝባዊ ግንባር በትናንትናው ዕለት በአሜሪካ ዋ...
31/07/2023

የአማራ ሕዝባዊ ግንባር በDC የተሳካ ውይይት አደረገ

በአዲስ አስተሳሰብ፣ በጠራ ራእይ፣ ተፈትኖ ባለፈ መሪ እየተመራ ጉዞውን የቀጠለው የአማራ ህዝባዊ ግንባር በትናንትናው ዕለት በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ የተሳካ ህዝባዊ ውይይት አካሄዷል።

በአሜሪካ የመጀመሪያውን የአዳራሽ ስብሰባ የአለም ፖለቲካ በሚዘወርባት በዋሽንግተን ዲሲ በተሳካ ሁኔታ አድርጓል።

የአማራ ህዝባዊ ግንባር በተመሰረተ አጭር ጊዜ ውስጥ ዕጅግ ከፍተኛ ልምድ ባላቸው ሙሁራን ልጆቹ በእስራኤል፣በአውሮፓ በጀርመን፣በአሜሪካ እና በተለያዩ አካባቢዎች የተሳካ ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ ይገኛል።በአገር ውስጥም ይሁን በውጭ ከፍተኛ ቅቡልነትን ያተረፈው የአማራ ህዝባዊ ግንባር ለአማራ ህዝብ ነፃ መውጣት የሚያደርገውን ትግል ከጊዜ ወደ ጊዜ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ ሲሆን በርካታ ተሽከርካሪዎች ወድሙበኮሎኔል ፈንታው ሙሀባና በኮሎኔል ሞገስ ዘገየ የሚመራው ፋኖ በሰሜን ወሎ ሳንቃ ላይ በአብይ አህመድ/ኦነግ ጦር ላ...
31/07/2023

ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ ሲሆን በርካታ ተሽከርካሪዎች ወድሙ

በኮሎኔል ፈንታው ሙሀባና በኮሎኔል ሞገስ ዘገየ የሚመራው ፋኖ በሰሜን ወሎ ሳንቃ ላይ በአብይ አህመድ/ኦነግ ጦር ላይ በወሰዱት ድንገታዊ ጥቃት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ተሽከርካሪዎች ከጥቅም ውጭ ሆነዋል።

በተጨማሪም በርካታ የአገዛዙ ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ ሆኗል ሲሉ ምንጮች ከስፍራው አድርሰውናል ።

ፋኖዎችም በርካታ የትጥቅ መሳሪያዎችን መመረካቸውን እና ቀሪው የአገዛዙ ሀይል እግሬ አውጭኝ በማለት ፈርጥጧል ሲሉ ገልጸዋል።

©ወግደረስ ጤናው

አፄ ፋሲለደስ ሻለቃ ተመሰረተ‼️የአማራ ፋኖ በጎንደር ቴውድሮስ ብርጌድ አፄ   ፋሲልደስ ሻለቃ በዛሬው ዕለት ሃምሌ 23/2015 ዓ/ም በይፋ ተመሰረተ።ይህንን ምስረታ አስመልክቶ ከዚህ ቀደም ...
30/07/2023

አፄ ፋሲለደስ ሻለቃ ተመሰረተ‼️

የአማራ ፋኖ በጎንደር ቴውድሮስ ብርጌድ አፄ ፋሲልደስ ሻለቃ በዛሬው ዕለት ሃምሌ 23/2015 ዓ/ም በይፋ ተመሰረተ።

ይህንን ምስረታ አስመልክቶ ከዚህ ቀደም በርካታ ስራ ሲሰራ የቆየው ቴውድሮስ ብርጌድ ዛሬ አፄ ፋሲለደስን ሻለቃ ሲያቆም ሻለቃ መሪ አድርጎ የሾመው

ፋኖ ተስፍሽ መንጌና
ምክትል ሻለቃ
ፋኖ ናሁሰናይ አንዳርጌን አድርጎ ሰይሟል።

የአማራ ፋኖ በጎንደር ቴውድሮስ ብርጌድ አመራርና አባላቶች በምስረታው ተገኝተው ይህን መሰል ለአማራ የጀርባ አጥንት የሚሆኑ ወጣቶችን መልምሎ ወደዚህ ሻለቃ ስያካትት ከኮብልስቶን እሰከ ነፍጥ የታጠቀውን ነባር ታጋይ ተካታችና መሪ ያደረገ መሆኑ ይበል የሚያስብልና ትግሉን ለማሻገር የስራ ድርሻ ቅብብሎሽ ማሳየቱ ዘመናዊ እና ስልታዊ ትግል መሆኑን በማሳወቅ በአንድነት እንደሚሰሩ የጋር ወሳኔ አሳርፈዋል።

  የአማራ_ሕዝባዊ_ኃይል_ፋኖ_ ጥምረት ፈጥሯል።በዛሬው ዕለት 23/11/15 ዓ.ም በደጋ ዳሞት መናገሻ ከተማ  #ፈረስቤት የአማራ ሕዝባዊ ኃይል ፋኖ በጎጃም ጥምረት ፈጥሯል። ጥምረቱን የፈጠሩ...
30/07/2023

የአማራ_ሕዝባዊ_ኃይል_ፋኖ_ ጥምረት ፈጥሯል።

በዛሬው ዕለት 23/11/15 ዓ.ም በደጋ ዳሞት መናገሻ ከተማ #ፈረስቤት የአማራ ሕዝባዊ ኃይል ፋኖ በጎጃም ጥምረት ፈጥሯል።

ጥምረቱን የፈጠሩት፦
1. የአማራ ሕዝባዊ ኃይል(ፋኖ) በደጋ ዳሞት!
2. የአማራ ሕዝባዊ ኃይል(ፋኖ) በደምበጫ!
3. የአማራ ሕዝባዊ ኃይል(ፋኖ) በማቻከል
4. የአማራ ሕዝባዊ ኃይል(ፋኖ) በጅጋ
5. የአማራ ሕዝባዊ ኃይል(ፋኖ) በፍ/ሠላም
6. የአማራ ሕዝባዊ ኃይል(ፋኖ) በባ/ዳር ሲሆኑ እያንዳንዳቸው ከ20 ፋኖ በላይ ተወካይ በመላክ ጥምረቱ ተፈጥሯል።

ከዚህ በተጨማሪ ባለፈው የአማራን ፋኖ የተቀላቀሉት የደጋ ዳሞት ፖሊሶች "እንኳን ወደ ፋኖ ተቀላቀላችሁ" የሚል አቀባበልም ተደርጓል።

መሰባሰቡ ይቀጥላል!

 #ሌላድልፋኖ አስከተማ  ተቆጣጥሯል!!በዛሬው ዕለት አስከተማ እና መቄትን እና ጋሸናል ሙሉ በሙሉ በአማራ ፋኖ በላስታ አውራጃ አሳምነው ብርጌድ ተቆጣጥሯል።ብአዴን እስከዘላለሙ ይቀበራል።ድል ...
29/07/2023

#ሌላድል
ፋኖ አስከተማ ተቆጣጥሯል!!

በዛሬው ዕለት አስከተማ እና መቄትን እና ጋሸናል ሙሉ በሙሉ በአማራ ፋኖ በላስታ አውራጃ አሳምነው ብርጌድ ተቆጣጥሯል።

ብአዴን እስከዘላለሙ ይቀበራል።

ድል ለታላቁ አማራ ሕዝብ‼️

የአብይና የብርሀኑ ወታደር የአማራ ህዝብ ጠላት መሆኑ ታውቆ ከክልሉ ሙሉ በሙሉ እንዲወጣ መደረገ አለበት። የመጫወቻ ሜዳውን መቀየር ያስፈልጋል። መከላከያ ህዝባችን የካደ ጠላት ነው!
29/07/2023

የአብይና የብርሀኑ ወታደር የአማራ ህዝብ ጠላት መሆኑ ታውቆ ከክልሉ ሙሉ በሙሉ እንዲወጣ መደረገ አለበት። የመጫወቻ ሜዳውን መቀየር ያስፈልጋል። መከላከያ ህዝባችን የካደ ጠላት ነው!

የምስራቅ አማራ ፋኖ መቄትን ተቆጣጠረ!!
28/07/2023

የምስራቅ አማራ ፋኖ መቄትን ተቆጣጠረ!!

ብአዴን እየተመናመነ ነው!የወልድያ ከተማ ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ዋና ኃላፊ ኮማንደር አሻግሬ ተስፋው በራሳቸው ፈቃድ የሥራ የመልቀቂያ ደብዳቤ አስገብተው ከስራ ለቀዋል፡፡ኮማንደሩ በብዙ የኃላፊ...
28/07/2023

ብአዴን እየተመናመነ ነው!

የወልድያ ከተማ ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ዋና ኃላፊ ኮማንደር አሻግሬ ተስፋው በራሳቸው ፈቃድ የሥራ የመልቀቂያ ደብዳቤ አስገብተው ከስራ ለቀዋል፡፡

ኮማንደሩ በብዙ የኃላፊነት ቦታወች ከህዝብ ጎን ሆነው የሠሩ እና በህወሀት ወረራ ጊዜም ግንባር ድረስ በመግባት እስከ መቁሠል ድረስ ዋጋ የከፈሉ ጀግና ናቸው፡፡ የከተማዋ ዲክታተር ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ "በፋኖ ላይ ዝመቱ፤ ከፋኖ ጎን ናችሁ፤ እንዲሁም የፋኖ አሸናፊ አለሙ ቤተሠብ ነህ" እያለ ሲያቀረሽ ከዋለ በኋላ ቆራጡ ሰው ወደፋኖ አልዘምትም ከቻልኩ እደግፋለሁ ብለው በኩራት ጥለውት ወጥተዋል፡፡

አደራው አንሙት ይባላል የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ የብልፅግና ሀላፊ ሲሆን፤ የደምበጫ ፋኖ ጎጃም ላይ ያለዉን ፋኖ እየዞሩ የቀሰቀሱት ነዉ በፍጥነት መክሰም አለባቸዉ ብሎ ከኦነግ/አብይ ቡድን ጋር ...
28/07/2023

አደራው አንሙት ይባላል የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ የብልፅግና ሀላፊ ሲሆን፤ የደምበጫ ፋኖ ጎጃም ላይ ያለዉን ፋኖ እየዞሩ የቀሰቀሱት ነዉ በፍጥነት መክሰም አለባቸዉ ብሎ ከኦነግ/አብይ ቡድን ጋር እየሰራ ያለ ባንዳ ነው ሲሉ የመረጃ ቲቪ ምንጮች ገልጸዋል።

አያይዘውም ይህ ግለሰብ በህዝባችን ላይ እያደረገ ያለውን የክህደት ተግባር ባስቸኳይ እንዲያቆም የምታውቁት የቅርብ ዘመዶቹ እና ጓደኞቹ እንድትመክሩት እናሳስባለን ብለዋል።

©mereja tv

የአማራ ብልፅግና  ፈረሰ!!ከጎጃም ከደጋ ዳሞት ወረዳ 18 የፖሊስ አባላት ከነሙለ ትጥቃቸው ከዱየሠራዊቱ አባላት ከፈረስ ቤት ከተማ ሙሉ ትጥቃቸው እንደያዙ ነው ስራቸውን በመልቀቅ አብዛኛው ከ...
27/07/2023

የአማራ ብልፅግና ፈረሰ!!

ከጎጃም ከደጋ ዳሞት ወረዳ 18 የፖሊስ አባላት ከነሙለ ትጥቃቸው ከዱ

የሠራዊቱ አባላት ከፈረስ ቤት ከተማ ሙሉ ትጥቃቸው እንደያዙ ነው ስራቸውን በመልቀቅ አብዛኛው ከህዝባዊ ግንባሩ እና ከህዛባዊ ኃይሉ ጋር በዛሬው ዕለት የተቀላቀሉት።

ከደጋ ዳሞት የፋኖ መሪዎች በደረሰን መረጃ መሰረት የፖሊስ አባላቱ ከድተው ጫካ የገቡት ከፋኖ ጋር ተቀላቅለው የአማራ ጠላት የሆነውን የብልጽግና መንግስት ለማስወገድ እንደሆነ ታውቋል።

የፖሊስ አባላቱ በአማራ ክልል የሚገኝ ሀሉም የመንግስት ታጣቂ እየከዳ ከፋኖ ጋር እንዲቀላቀልና ለአማራ ህዝብ እንዲታገል ጥሪ አስተላልፈዋል።

ረ ሳጅን ደሳለኝ
ረ ሳጅን ወርቅነህ
ረ ሳጅን ጊዜው
ም ስጅን ፈለቀ
ም ሳጅን መልካሙ
ዛሬ ቀን 20/11/2015 ዓም ጀምሮ
"ለኦነጉ አብይ ህገ መገንግስት
አገዛዝ አንገዛም፤ አናገለግልም፣በህዝባችን ላይ አንተኩስም፣አንሞታለን እንጂ" በሚል ከነሙሉ ትጥቃቸው ከድተው ጫካ ከገቡት መካከል ናቸው።

27/07/2023

የአማራ ህዝባዊ ግንባር!!💪💪💪

እንኳን ተወለድክባቸው!
27/07/2023

እንኳን ተወለድክባቸው!

" ከዛሬዋ ቀን ጋር.."
ተገናኘን።
በአማራ ምድር የምትገኝዋ በምስራቅ ጐጃም ዞን ያለችዋ ትርፍ አምራቿ የቅኔዋ ምድር የአባታችን አቡነ ቲዎፍሎስ

የእነ ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ ክቡር ዶ/ር አዲስ አለማየሁ ሀገር የትውልድ ቀዬ ጥንታዊቷ ገዳም ደብረ ኤልያስ በዛሬዋ ቀን ተወለድኩኝ። በአፄ ዳዊት ከተማ የዘብርያዕቆብ የሸዋ እምብር መናገሻ በሆነችው (በረራ ) አዲስ አበባ አደኩኝ። ከደብረኤልያስ ወደ ደብረ አዲስአበባ ማለት ነው።
ከቤት ወደቤት ከእናቴ ጋር በመምጣት ኖርኩኝ።

በሕይወት በኖርኩባቸው አራት አስርታት የእድሜ ዘመን ውስጥ ለጭቁን ሕዝብ ነፃነት ሃያ አምስቱን አመት ለገስን ይኸው እዚህ ደርሰናል። ወጉ አይቅር በማለት እንጅ ልደት የምናስታውስበት ጊዜና ሰዓት አይደለም። ቢሆንም የዛሬዋ ልደቴን በርካታ ጊዜዎች በውጭ ሆኜ ማክበር አልቻልኩም እና አስታወስኩት በታላቅ ኩራትና በስፋት በምኒልክ ቤተመንግስት ከመጪዉ ንጉሥ ጋር ከነፃነት በኃላ እናከብረዋለን። አሁን ሙሉ ስራችን ከመጣብን እና ከተጋረጠብን የህልውና ፈተና የጦር ነጋሪት በትግላችን ነፃነታችንን ማረጋገጥ ብቻ ነው። የሰማይ አባት መልካም ፍቃዱ ተጨምሮበት እመነኝ ይሳካል።

የነገዉን ቀን እና እድሜ ባንተ ቸርነት ጌታዬ ትባርከው ዘንድ ለመንኩኽ አሜን!

"ድል ለሰፊዉ ጀግና የአማራ ህዝብ!
እናሸንፋለን።

ለዛሬ መታሰቢያ
ተጻፈ ሀምሌ 20/2015 ዓ,ም

24/07/2023
ጋዜጠኞቹ ተሰደዱ!የኢትዮ 251 ሚዲያ ባለቤት ጋዜጠኛ ሙሉጌታ  አንበርብር እና የዘ-አማራ ሚዲያ ባለቤት ጋዜጠኛ አዲሱ ደርብ ሀገር ጥለው መሰደዳቸው ታውቋል። ጋዜጠኞቹ በሚደርስባቸው መንግስታ...
24/07/2023

ጋዜጠኞቹ ተሰደዱ!

የኢትዮ 251 ሚዲያ ባለቤት ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር እና የዘ-አማራ ሚዲያ ባለቤት ጋዜጠኛ አዲሱ ደርብ ሀገር ጥለው መሰደዳቸው ታውቋል።

ጋዜጠኞቹ በሚደርስባቸው መንግስታዊ እስር እና መሳደድ ምክንያት በሀገር ውስጥ መኖር ባለመቻላቸው ኢትዮጲያን ጥለው ዛሬ ለመሰደድ ተገደዋል።

" እኛ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚሰጠውን ውሳኔ እየጠበቅን ነው " - ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱየአማራ እና የትግራይ ክልሎች የሚዋሰኑባቸውን የወልቃይት፣ የጠለምትና የራያ አካባቢዎችን " ይገባኛል ...
23/07/2023

" እኛ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚሰጠውን ውሳኔ እየጠበቅን ነው " - ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ

የአማራ እና የትግራይ ክልሎች የሚዋሰኑባቸውን የወልቃይት፣ የጠለምትና የራያ አካባቢዎችን " ይገባኛል " ጥያቄን በተመለከተ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚሰጠውን ውሳኔ እየተጠበቁ መሆናቸውን ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል አሳውቀዋል።

ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በአሁን ሰዓት የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ምክትል አስተዳዳሪ እና የሰላምና የፀጥታ መምርያ ኃላፊ በመሆን እያገለገሉ ሲሆን በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በፓርላማ በቀረቡበት ወቅት " ሁለቱ ክልሎች የሚዋሰኑባቸውን አካባቢዎች በሕዝብ ውሳኔና በሕጋዊ መንገድ መፍታት አለባቸው " በሚል ስለሰጡት አስተያየት ተጠይቀው መልሰዋል።

ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ምን አሉ ?

" በወልቃይት ጉዳይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ውሳኔ እናደርጋለን ሲሉ በግልጽ አልሰማንም፡፡

ነገር ግን በሕጋዊ መንገድ ቢፈታ ይሻላል የሚለውን ምክር አዘል ነገር ለፓርላማው ሲናገሩ ሰምተናል፡፡

ግን በዚህኛው ቀጣና በዚህኛው ዞን ብለው ሲያነሱ እኔም በግል አልሰማሁም፣ እኛም የምናውቀው ነገርም የለም። ነገር ግን የወልቃይት ጉዳይ በየትኛው መንገድ ነው ሊፈታ የሚገባው የሚለውን ቀደም ሲል በተደጋጋሚ ተናግረናል፡፡

ሊፈታ በሚገባው መንገድ እንዲፈታ ለመንግሥት አመልክተናል።

ራያም፣ ጠለምትም፣ ወልቃይትም ስላሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለየትኛው እንደተናገሩ ግልጽ አልሆነልኝም። በግምት መልስ ለመስጠት ያስቸግራል።

ብዙ ሰው መላምት ሊኖረው ይችላል፡፡ ነገር ግን የወልቃይት ጉዳይ ሊፈታ የሚገባበትን መንገድ ጠቅሰን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ስላቀረብን ውሳኔውን እየጠበቅን ነው።

በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ወቅትም ሆነ አሁን ከማኅበረሰቡ ጋር ነኝ ፤ የአገር መከላከያ ሠራዊት የወልቃይት አካባቢን እየተከላከለና እየጠበቀ እንዳለ ነው የምናውቀው።

በአካባቢው ከመከላከያ ጋር ምንም ዓይነት ጦርነት የለም፣ ተባብረን ነው እየሠራን ያለነው፡፡ አካባቢው ሰላማዊ በመሆኑ ፋኖ በሚል ምክንያት ምንም ዓይነት ግጭትም ሆነ ጦርነት የለም። "

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳዳር በበኩሉ የክልሉ አስተዳደራዊ ወሰን ከጦርነቱ በፊት ወደ ነበረበት እንዲመለስ፣ በጦርነቱ ምክንያት ከምዕራብ ትግራይና ከሌሎች የአማራ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች የተፈናቀሉ የክልሉ ነዋሪዎቸ በአፋጣኝ ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱ በተደጋጋሚ ጥያቄ እያቀረበ ነው፡፡

#ሪፖርተር

የብልፅግና ፓርቲ አባላት መልቀቂያ አስገቡ !!በፍኖተሰላም የመንግስት ስራ ላይ የሚገኙ የብልፅግና ፓርቲ አባላት፣ ከአባልነት መልቀቃቸው ደብዳቤ አሳውቀዋል።  በከተማው በከፍተኛ ሁኔታ መነጋገ...
20/07/2023

የብልፅግና ፓርቲ አባላት መልቀቂያ አስገቡ !!

በፍኖተሰላም የመንግስት ስራ ላይ የሚገኙ የብልፅግና ፓርቲ አባላት፣ ከአባልነት መልቀቃቸው ደብዳቤ አሳውቀዋል። በከተማው በከፍተኛ ሁኔታ መነጋገሪየ የሆነ ጉዳይ ሆኗል፣በብልፅግናዎች መነድ መፍረክረክ ተከስቷል።

Mereja TV

“በብልፅግና ሰዎች ዘመቻ ተከፍቶብኛል!” የምክር ቤት አባሉዶር ካሳ ተሻገር የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል እና የከተማው የኮሚንኬሽን ቢሮ ሀላፊ ናቸው። በምክርቤቱ ስብሰባ ላይ “የአማራ ተወ...
20/07/2023

“በብልፅግና ሰዎች ዘመቻ ተከፍቶብኛል!” የምክር ቤት አባሉ

ዶር ካሳ ተሻገር የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል እና የከተማው የኮሚንኬሽን ቢሮ ሀላፊ ናቸው። በምክርቤቱ ስብሰባ ላይ “የአማራ ተወላጆች በብሄራቸው ምክንያት እየተጠቁ ነው” ማለታቸውን ተከትሎ ዘመቻ እንደተከፈተባቸው በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አሳታወቁ።

ዶ/ር ካሳ እንዲህ ብለዋል።

“በማህበራዊ ሚዲያ (በፌስቡክ፣ በቴሌግራም፣ በዋትስአፕ፣ ወዘተ) ዘመቻ ተከፍቶብኛል። እኔ ለህሌናዬ የማድር ሰው በመሆኔ የሚመጣውን ሁሉ ለመቀበል ዝግጅ ነኝ። ለፍትህ፣ ለእኩልነትና ለነጻነት እታገላለሁ። ብልጽግናን ስለወከልኩ ህጋዊ ያልሆነና አግባብነት የሌለው ነገር ሳይ ዝም አልልም። ህሊናዬም አይፈቅድም። የህዝብ ድምጽ ላሰማ ነው ም/ቤት የገባሁት። ለታሰሩት ድምጽ መሆን፣ ሰብአዊ መብታቸው እንዲከበር መጠየቅ ወንጀልን ማበረታታት አይደለም። ካድሬዎች ወደቀልባችሁ ተመለሱና የሚገባውን አድርጉ!! ይኸው ነው!”

ቢኒ ወንድሜ እንኳን እግዜር አስፈታህ!!
20/07/2023

ቢኒ ወንድሜ እንኳን እግዜር አስፈታህ!!

ተሰዷል!ጋዜጠኛ እና የፖለቲካ ተንታኙ ቴዎድሮስ አስፋው በዛሬው ዕለት ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ምክንያት ከሀገር ውጪ መሰደዱ ታውቋል።ልጆችሽ የሚሰደዱብሽ፤ የሚሰቃዩብሽ፤ የሚፈናቀሉብሽ እና ...
20/07/2023

ተሰዷል!

ጋዜጠኛ እና የፖለቲካ ተንታኙ ቴዎድሮስ አስፋው በዛሬው ዕለት ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ምክንያት ከሀገር ውጪ መሰደዱ ታውቋል።

ልጆችሽ የሚሰደዱብሽ፤ የሚሰቃዩብሽ፤ የሚፈናቀሉብሽ እና የሚገደሉብሽ ኢትዮጵያ የዚህ ሁሉ ሰቆቃሽ የሚያበቃበት ጊዜ መቼ ይሆን?!

Wondmeneh fikadu ወንድሜነህ ፍቃዱ

አሸባሪው የብልፅግና መንግስት የአማራ ህዝብ መግደል አልበቃው ብሎ መዝረፍ ጀምሯል።በደሴ ከተማ የብልጽግና መንግስት ከእያንዳንዱ ነጋዴ ላይ አንድ አንድ ሺህ ብር በነፍስወከፍ ማህተም በሌለው ...
19/07/2023

አሸባሪው የብልፅግና መንግስት የአማራ ህዝብ መግደል አልበቃው ብሎ መዝረፍ ጀምሯል።

በደሴ ከተማ የብልጽግና መንግስት ከእያንዳንዱ ነጋዴ ላይ አንድ አንድ ሺህ ብር በነፍስወከፍ ማህተም በሌለው ፎርጅድ ደረሰኝ ለመከላከያ እየሰበሰቡ መሆኑን የውስጥ አዋቂ ምንጮች ለቻናላችን ገለፁ።

ምንጮቻችን እንደገለፁት ገንዘቡን እየሰበሰበ ያሉት “ለከተማ ልማት ማስመረቂያ” ነው ቢሉም አላማው ግን ለመከላከያ ድጋፍ እንደሆነ የውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን ገልፀውልናል። ለከተማ ልማት በሚል መሰብሰብ ያስፈለገበት ምክንያት ለመከላከያ ብንል እሺ ብሎ የሚከፍል ነጋዴ አይኖርም በሚል ነው።

የሚገርመው የሚሰበስቡበት ደረሰኝ ምንም አይነት ማህተም የሌለውና ህጋዊነት የሌለው ደረሰኝ መሆኑን ጨምረው ገልፀውልናል።

Address

Six Killo
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wondmeneh Fikadu posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Wondmeneh Fikadu:

Videos

Share