ሸዋ/Shoa/

ሸዋ/Shoa/ Reflects on this Page personal Opinions and suggestion
(1)

23/07/2024

የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ አለም አቀፍና ቀጣናዊ ትስስር ሃላፊ ፋኖ ዳዊት ቀፀላ መልዕክት

**********************************

ጋሽ አሰግድ ዛሬ ላይ በጠላት እጅ ቢወድቅም ሺሺሺሺዎች አሰግድ አለንና ልባችሁ አይታወክ ሁላችንም በያለንበት ጸንተን እንቁም!!
የትግሉ ባለቤት አማራ የተባለ ህዝብ ነው የምናደርገው የነፃነት ጉዞ ውጣ ውረድ ያለበት ብርሃንና ጨለማም የሚፈራረቅበት ብዙ ሥቃይና መንገላታት የማይታጠበት ነው እንደሁኔታው የራስ ጥላም ሳይቀር ይሸሻል በየትኛውም አጋጣሚ ቢሆን ሞገድ በማይሰብረው ጽኑ ዓላማ ከጫፍ መድረስን ግብ ያደረገ እልፍ ሰራዊት አለን እናም ልባችሁ አይታወክ። መጣ ሄደ በሚል ጉዳይ ላይ የሚባክን ጊዜ የለንም አንበሳው መሬት ላይ ታሪክ መስራቱን እንደቀጠለ ነው ይልቅስ በደራሽ አጀንዳ አትራኮቱ እያለፋችሁ ሂዱ ድላችንን አጣጥሙ ትግላችንን በልኩ ደግፉ በዚህ ግርግር ውስጥም የቆመ ስራ የለም በርካታ ድሎች ተመዝግበዋል።

ይህ ጉዞ መራራ ነው ነብስ የሚገበርበት ነው እንጂ የቅንጦት አይደለም በውስጥ ባንዳ አሳልፎ መስጠትም መማረክም የትግል አጋጣሚዎች ናቸው። ይህ ነውረኛ የሆነ የአገዛዝ ስርዐት ከእስከዛሬው ትግላችን በላይ ዛሬ አንድ ነገር አብራርቶልናል። በተለያዩ የዜና አውታሮቹና በዲጅታል ሰራዊቱ በኩል ካለበት የድል ናፍቆት የተነሳ በሰበር ያራገበው እጅ የመስጠት ዘገባ ለረጅም ጊዜ ያጣውን ደስታ እየካሰበት ቢሆንም ለእኛ ግን ክንዳችን በርግጥም ኃያል እንደሆነ አቅማችንም ጠንካራ ጉልበታችንም የተፈራ ስማችንም የሚያስጨንቅ እንደሆነ የተረዳንበት በጎ አጋጣሚ ነው።

የአማራ ትግል ከዚህም ከፍ ሲል ብዙ ጀግኖችን የሰዋ ነው ይሄው የአማራ ትግል በጀግኖች የደም መስዋዕትነት እልፎች እየተወለዱ ዛሬ መላው የአማራ ምድር በጀግኖች ተሞልቷል እናም አትሸበሩ አይዟችሁ እጅ በአፍ የሚያስጭን ተጋድሎ ውስጥ ያለው ብዙ ነው። ከፊት ካለው ኃያል ስም በላይ እጆቻቸው ኢላማ የማይስቱ ጽኑ ተፋላሚዎች አሉ መሬት ላይ ባሉት ተአምር አድራጊዎች ትገረማላችሁ የሰነፎች ወሬ አይጥለፋችሁ ዝም ብላችሁ እለፉ። ተስፋ የሚያስቆርጥ የትግል ጉዞ የለንም መራራ ዋጋ የሚጠይቅ የድል ጉዞ ላይ ነን ፍፃሜያችን የሚሆነው የፍትህ አደባባይ ላይ ነው። የመላእክት ዓለም በሁከት ተሞልቶ ነበር ነገር ግን በያለንበት ፀንተን እንቁም የሚል የሚያረጋጋ ድምጽ ነበር እኛም እንላለን ሁላችን በያለንበት ፀንተን እንቁም።

25/05/2024

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ በ2016 ዓ.ም አብረውት በአጋርነት በመስራት የላቀ የደረቅ ጭነት አገልግሎት የሰጡ ኩባንያዎችን ዕውቅና በሰጠበት በከልቻ ትራንስፖርት አ.ማ ....

አረጋሽ እጅሽን ይዞ ሲያሽኮረምምሽ ለምን ትስቂለታለሽ ሰውዬው ብዙ አግብቶ የፈታ ነው  እንዳያታልልሽ ©Fikre selam
21/05/2024

አረጋሽ እጅሽን ይዞ ሲያሽኮረምምሽ ለምን ትስቂለታለሽ
ሰውዬው ብዙ አግብቶ የፈታ ነው እንዳያታልልሽ
©Fikre selam

18/05/2024

ስሙልኝ ይህን ገመድ አፍ

"ሀገራችን ኦሮሚያ ናት ሀይማኖታችን ተዋህዶ ናት።ፓትርያካችን አንድ ነው ቀጣዩ 7ኛ ፓትርያክ ደሞ ኦሮሞ ነው።ኦሮሞ ፓትርያክ መሆን አለበት።ከባርነት መላቀቅ አለብን። ትግል ማለት ይሄ ነው እንጅ እንጅ ጫካ መግባት አይደለም።መተህ ከኔ ጋር ድምፅ ሆነህ ጩህ 4ኪሎ ኦሮሞ ፓትርያክ ይግባ እያልክ ታገል።የቁልቢ ገብርኤል ብዙ ገንዘብ እና በንግድ ባንክ ያለው ወርቅ ትተን ተገንጥለን አንቀመጥም።በባንክ ያለውን ገንዘብ ጥለን ደሃውን አናስቸግርም እንካፈላለን እን።ከዚህ አምስት ሳንቲም አንለምንም ከ4ኪሎ እና 5ኪሎ እንወስዳለን።ኦሮሞነት ማለት ለዚህ መታገል ነው ፕሮፖጋንዳም ሳይሆን በስራ ነው የምናሳየው"
Hanna R Waktolaa

17/05/2024

ኑ የልጃችሁን አስክሬን ውሰዱ!
አስክሬን በቆሻሻ መጣያ ወድቆላችኋል!
አስክሬን በር ላይ ተጥሎላችኋል!
ማንነቱ ያልተለዬ አስክሬን መንገድ ዳር ወድቋል!
ከእስር ቤት በሌሊት እንደተወሰዱ ተከታታይ የጥይት ድምፅ ተሰምቷል፤ ከዚያ በኋላ አልተገኙም!

ይሄ በዚያኛው ዘመን በኮሎኔል መንግሥቱ ቀይ ሽብር የሰማነው ታሪክ አይደለም!

በአሁኑ በኮሎኔል ዐቢይ በብልጽግና ዘመን የእናቶች የሲቃ ድምፅ ነው!
==========================
ኢሳያስ በላይ የሞተው በድብደባ ብዛት ነው!

ኢሳያስ የአማራ ባንክ የማኔጅመንት ባልደረባ በመሆኑ በሞያው የሚታወቅ ሰው ስለሆነ፣ በብልጽግና አገዛዝ ታፍኖ ሲወሰድ ሰዎች ያዩ በመሆኑ ከታፈነ በኋላ በደረሰበት ድብደባ መሞቱን ተከትሎ ሬሳውን ለመመለስ ተገደዋል፡፡

ነገር ግን በስም የማይታወቁ፣ ሲታፈኑ ሰው ያላየላቸው፣… ከየአካባቢያቸው የታፈኑ የአማራ ልጆች በድብደባ ብዛት ሕይወታቸው ሲያልፍ፣ በለሊት ከታሰሩበት እስር ቤት እየተጎተቱ ወጥተው የተረሸኑ ወንድም እህቶቻችን አስከሬን ግን እንደቆሻሻ በየቦታው ተጥሏል።

ፖሊስ የኢሳያስን አስከሬን የሰጠው በሁኔታዎች አስገዳጅነት እንጅ እንደብዙሃኑ አጥፍቶት ይቀር ነበር።

በዚህ መንገድ ተገድለው ድምፃቸው የጠፋውን ቤቱ ይቁጠራቸው፡፡

በር በሩን የሚያዩት በእምባ የጎደጎዱ የእናቶች ዓይኖች በቀጭን ክር የታሰሩ የእናቶች አንጀት አምላክ በቃ ይበላቸው!

ግንቦት 8/2016 ዓ.ም

11/05/2024

እንኳን ድልድይ ፀሀይና ጨረቃን በግራና በቀኝ እጆችህ ይዘህ ብትመጣ ~ The father of all evils ~ ነትህን ከተረዳነው ቆየንና ~ We will never allow ourselves to be hypotonized and disoriented by the gesture of a very pretentious and deceitful phony man and con artist.
©Mohammed hassen

11/05/2024

#በወለጋው ሰልፍ
ዐብይ አህመድ
የኦሮሞ ሕዝብ ብዙ ሆኖ ሳለ አማራ እና ትግራዋይ
መቶ አመት ገዝተውናል ።

#ተመስገን ጥሩነህና ፣አገኘሁ ተሻገር አዎ ጌታችን ሽ አመት ይንገሱ ሥጋት አይግባዎት እርስዎም መቶ ዓመት ይነግሳሉ ይገዛሉ .....ይህን ብሽቅ ንግግር አማራ ሆኖ ቁጭ ብሎ መስማት ይገርማል.....

#ዐብይ አህመድ
ስልጣኑ ከእጃችን ወጥቶ የኦሮሞን ሕዝብ እንዳናዋርደው
ስልጣን ላይም ጫካም ያለነው እንስማማ አንድ እንሁን ።

ሰልፍ መንግስትን ለመደገፍ በማንኛውም ሰዓት ይፈቀዳል መንግሥትን ለመቃወም ግን ምንም እድል የለም።

10/05/2024

EBC ለመራዊ ጭፍጨፋ ወደፊት ተጠያቂ የሚሆኑ ሰዎችን በምስል በማስረጃ በማቅረቡ ሊመሰገን ይገባል ።
የፋኖንም ሥራ ያቀላል

✏የበቀል እርምጃው ቀጥሏል ፦👉ብፁዕ አቡነ አብርሃም ከሀገር እንዳይወጡ ፓስፖርታቸውን ተያዘ  ፣ 👉ስማቸውም በዛሬው  የደቡብ አፍሪካ ጉዞ  ከቅዱስ ፓትርያርኩ ጋር ለመጓዝ  ዝርዝር ውስጥ ቢገ...
10/05/2024

✏የበቀል እርምጃው ቀጥሏል ፦

👉ብፁዕ አቡነ አብርሃም ከሀገር እንዳይወጡ ፓስፖርታቸውን ተያዘ ፣

👉ስማቸውም በዛሬው የደቡብ አፍሪካ ጉዞ ከቅዱስ ፓትርያርኩ ጋር ለመጓዝ ዝርዝር ውስጥ ቢገባም ፓስፖርታቸው ተይዞ ወደ ደቡብ አፍሪካ እንዳይጓዙ ተደርጓል የቤተክህነቱ የመረጃ ምንጮጫችን አድርሰውናል
Ethio Beteseb Media

09/05/2024

የወለጋው የአብይ ኑዛዜ በጥቅሉ ስልጣኔን የሚገዳደረኝ ሃይል እየመጣ ነው :: የኔ መውደቅ የናናንተም ነው:: ይህ በደማችን ያገኘነው የገዥነት ስልጣን ጥቅምና መብት ከእጃችን እንዳይወጣ ለመንግስታችሁ ኑና ተሰው:: ይህ ካልሆነ ታላቅ የሚቆጨን ታሪካዊ ስህተት ይፈጠራል:: ይህ የስልጣን ጥመኛ ሚሊየኖች ለሱ ወንበር ማስጠበቂያ ህይወታቸውን እንዲሰው ይፈልጋል:: ኢትዯጲያን ወደለየለት የእርስ በርስ ጧርነትና እልቂት የመጨመር ፍላጏቱ በጉልህ ታይቷል:: ለአብይ የማትሆን ኢትዯጲያ ገደል የምትገባበትን ሴራ እያጠነጠነ ነው:: የዚህ አገር አጥፊ ህልውና ከኢትዯጲያ ህልውና አይበልጥም :: ይህ ሰው ላይ በጊዜ እርምጃ በመውሰድ ከስልጣን ማስወገድ የዜገኝነት ግዳጅ ነው:: ይህ ግዳጅ የተቋሚዎቹ ብቻ ሳይሆን የወዳጇቹም ጭምር ሊሆን ይገባል::

ላሜ ቧራ([email protected])

09/05/2024

ለምንም ለማንም የማይጨናነው መከላከያ ፣ለማን ለምን እንደሚታገል ፣ከማን እንደሚታገ የማያውቀው ኃይል ከወራኢሉ ወደግሼ ወረዳ መንደሮች ( ሕዝብ ላይ ) ከባድ መሳሪያ አሻግሮ እየተኮሰ ነው።

ፋኖን እየደበደብኩ ነው የሚል መግለጫ ይቀጥላል. ..

ኢትዮጵያ በሚዲያ ነጻነት ከ180 አገራት 141ኛ ደረጃን ይዛለች‼️👉🏿 ካለፈው ዓመት 11 ደረጃዎችን አሽቆልቁላለች።ኢትዮጵያ የብዙኀን መገናኛ/ ፕሬስ ነጻነት ከተከበረባቸው አገራት 141ኛ ደ...
07/05/2024

ኢትዮጵያ በሚዲያ ነጻነት ከ180 አገራት 141ኛ ደረጃን ይዛለች‼️
👉🏿 ካለፈው ዓመት 11 ደረጃዎችን አሽቆልቁላለች።
ኢትዮጵያ የብዙኀን መገናኛ/ ፕሬስ ነጻነት ከተከበረባቸው አገራት 141ኛ ደረጃን ይዛለች።
ድንበር የለሽ ጋዜጠኞች (reporters without borders) ዓለም አቀፍ ተቋም ባወጣው የ2024 ይርፕሬስ ነጻነት ሪፖርት ባለፈው ዓመት 130ኛ ደረጃ ላይ የነበረችው ኢትዮጵያ፤ በዚህ ዓመት 141ኛ ደረጃን ከ180 አገራት ይዛ መገኘቷን አዩዘሀበሻ ከሪፖርቱ ተመልክቷል።
ከስድስት ዓመታት በፊት የታየው የሚዲያ ነጻነት አውድ የማንነት ግጭቶች እና የእርስ በእርስ ግጭቶች ሳቢያ ተቀልብሶ አሳሳቢ ሁኔታ መፈጠሩን ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች ተቋም አስታውቋል።
በወቅታዊነት ደግሞ በአማራ ክልል የቀጠለው በትጥቅ የታገዘ ግጭት የጋዜጠኞችን ስራ ጫና ውስጥ እያስገባ እንደሆነ በሪፖርቱ ተካቷል።
ባለፉት አምስት ወራት ብቻ 15 ጋዜጠኞች እስካሁን መታሰራቸውንም ተቋሙ ገልጿል። በዓመታዊ ሪፖርቱ ኤርትራ በፕሬስ ነጻነት የመጨረሻውን ደረጃ ስትይዝ ኖርዌይ የጋዜጠኞች ነጻነት የተከበረባት አገር ሆናለች።
አዩዘሀበሻ

05/05/2024

እንኳን ለ83ኛው የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች የድል ቀን አደረሳችሁ።

ይህ የድል በዓል እናት ኢትዮጵያን በፋሽዝም ቀንበር ሥር እንዳትወድቅ ጀግኖች አባቶችና እናቶች በዱር በገደል ለክብር እና ለሰብዓዊነት ያደረጉት ተጋድሎ ነው።

ሰው ተከፍሎበታል ከደምና ከአጥንት!

መልካም የድል በዓል!

የማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም እና የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ መ/ር ዋሲሁን በላይ በትናንትናው ዕለት ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም በመንግሥት የጸጥታ አካላት ከ...
03/05/2024

የማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም እና የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ መ/ር ዋሲሁን በላይ በትናንትናው ዕለት ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም በመንግሥት የጸጥታ አካላት ከመኖሪያ ቤታቸው ተወስደው ሜክሲኮ በሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ እንደሚገኙ አሳውቀን ነበር።

በዛሬው ዕለት ሚያዚያ 25 ቀን 2016 ዓ.ም ወደ ቤታቸው መመለሳቸውን እየገለጽን፣ በሂደቱ ጉዳዩን በመረዳት አፋጣኝ ምላሽ የሰጡንን የመንግሥት የጸጥታ አካላት እናመሰግናለን።

በተጨማሪም በትዕግሥት ስትከታተሉና በጸሎት ስታስቡ ለነበራችሁ አባቶች፣ ምእመናን እና የማኅበረ ቅዱሳን አባላት እያመሰገንን፣ በዓሉ የሰላምና የበረከት እንዲሆንላችሁ እንመኛለን።

ማኅበረ ቅዱሳን!

03/05/2024

እንኳን አደረሳችሁ!

የክርስትና እምነት ተከታይ ለሆናችሁ የንጋት ኮርፖሬት እና የኩባንያ ባልደረቦቻችን እና መላው ኢትዮጵያውያን እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል በጤና አደረሳችሁ።

በዓሉን በኢትዮጵያዊ ነባር ዕሳቤ መሠረት በመተሳሰብ፣ በመደጋገፍና በፍቅር ታሳልፉ ዘንድ ልባዊ ምኞታችንን እንገልጻለን።

መልካም በዓል!

ንጋት ኮርፖሬት
ዘላቂ የልማት መሠረት

www.nigat.et

 የማኅበራት ሕብረት ሰብሳቢ የሆነችው   #ወ/ት ፌበን_ዘሪሁን እና የሕብረቱ ሥራ አመራር የሆነው  እንዳልክ  #በፖሊስ ተይዘው ተወስደዋልወንጄለኛ እንኳን ለበዓል ይፈታ ነበር ፣ምንም ወንጄል...
03/05/2024


የማኅበራት ሕብረት ሰብሳቢ የሆነችው
#ወ/ት ፌበን_ዘሪሁን እና የሕብረቱ ሥራ አመራር የሆነው እንዳልክ
#በፖሊስ ተይዘው ተወስደዋል
ወንጄለኛ እንኳን ለበዓል ይፈታ ነበር ፣ምንም ወንጄል የሌለባቸው የሚታፈኑበት ዘመን .....ይሁና

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ ዛሬ ሚያዚያ 2...
02/05/2024

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ ዛሬ ሚያዚያ 24/2016 ዓ.ም ከመኖሪያ ቤታቸው በጸጥታ አካላት መወሰዳቸው ታውቋል።

የሁለቱ አገልጋዮች መኖሪያ ቤት መፈተሹም ተገልጿል።

በአሁኑ ሰዓት ሜክሲኮ ፌዴራል ፓሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ የሚገኙ ሲሆን የተያዙበት ምክንያት አልታወቀም።

ዝርዝር እንደደረሰን እናቀርባለን።

ማኅበረ ቅዱሳን

መርጌታ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ዛሬ ጠዋት 12 ሰዓት ከመኖሪያ ቤታቸው በፖሊሶች ተይዘው ሜክሲኮ ወደ ሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ተወስደዋል።በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕ...
02/05/2024

መርጌታ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ዛሬ ጠዋት 12 ሰዓት ከመኖሪያ ቤታቸው በፖሊሶች ተይዘው ሜክሲኮ ወደ ሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ተወስደዋል።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት በጸሐፊነት ያገለግሉ የነበሩት መርጌታ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ የደቡብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ በመሆን መሾማቸው ከቀናት በፊት ተገልጿል።

ፊደራል ፖሊስ ገለልተኛ ሚዛናዊ ነኝ አለ ነው ያላችሁኝ ድንቄም ሚዛናዊ
24/04/2024

ፊደራል ፖሊስ ገለልተኛ ሚዛናዊ ነኝ አለ ነው ያላችሁኝ
ድንቄም ሚዛናዊ

17/04/2024

የቁም ተዝካር ያብላ፡ ዋይ ትበል እናቱ
ሸዋ ገብቶ ጠላት፡ መቃብር ነው ቤቱ።

ግዙፍ አድባር ሸዋ!💪💪

አማራነት ወኔነት፣ አልደፈር ባይነት ፣ጄግንነት ፣ባርነት መጥላት ነው።ምድረ ግም ግትልትል ሸኔ  ሴትና ኅጻናት አራጅ ዳግም ሰልጥኖና ታጥቆ ሊያርድ አሁን  ማረኩ እና ተማረኩ እያለ የፎቶ ፖለ...
13/04/2024

አማራነት ወኔነት፣ አልደፈር ባይነት ፣ጄግንነት ፣ባርነት መጥላት ነው።

ምድረ ግም ግትልትል ሸኔ ሴትና ኅጻናት አራጅ ዳግም ሰልጥኖና ታጥቆ ሊያርድ አሁን ማረኩ እና ተማረኩ እያለ የፎቶ ፖለቲካ ሲነሳ ይውላል።

# አማራ ጋር ይህ አይሰራም እኛ ያባቶቻችን ልጆች ነን ስንወጣ በምክንያት ነው፣ማንንም የማንበድል ከበደሉን ከገፋን ፣ከገደሉን ካሳደዱን ለማንም የማናጎበድድ ሞት የማንፈራ ለጥላት እጅ የማንሰጥ የአባቶቻችን ልጆች ነን።

#ናሁ ሠናይ (አሁን ጥሩ ነው) አሁን ትግሉን አንድ እርምጃ አድርሰኸዋል ። እየታገልን ጥላትን እየረፈረፍን እንጂ በተኛንበት እየሞትን የዘር ማጥፋት ወንጄል እየተፈጸበብን እንዳንቀጥል እንዲሁም ጥላት እደጃችን ድረስ ሲመጣ ሳይሆን እደጁ ድረስ በመሄድ የሞትን መራራነት እንዲቀምስ ማድረግን እንደሚገባ ያንተ ጄግንነት ማሳያ ነው ።
መሰዋዕትነትህን ታሪክ ይዘክረዋል ትግሉም ይቀጥላል::

የአማራ ብርቅዬ አበባዎች ከጎንደርና ከሸዋ በቅለው አዲስ አበባን ባርከዋታል። በረራ በቅርቡ የዘመቻ ኢላማ ትሆናለች። የጀግኖቻችንን ደም በክንዳችን መልሰን ለጀግኖቹ በትውልድ የማይረሳ የዘለዓ...
13/04/2024

የአማራ ብርቅዬ አበባዎች ከጎንደርና ከሸዋ በቅለው አዲስ አበባን ባርከዋታል። በረራ በቅርቡ የዘመቻ ኢላማ ትሆናለች። የጀግኖቻችንን ደም በክንዳችን መልሰን ለጀግኖቹ በትውልድ የማይረሳ የዘለዓለም ስም እንሰጣለን!

አሳዛኝ ነውይህ ሰው በጋምቤላ ዩኒቨርስቲ ውስጥ ጥበቃ ሁኖ የሚስራ ነበር በ29/7/2016 ዓ.ም የመንግስት የድጋፍ ሰልፍ ተብሎ ሰዎችን ንግድ ቤታችሁን ዝጉና ወደ ስልፉ ውጡ እየተባለ በግዳጅ...
11/04/2024

አሳዛኝ ነው

ይህ ሰው በጋምቤላ ዩኒቨርስቲ ውስጥ ጥበቃ ሁኖ የሚስራ ነበር በ29/7/2016 ዓ.ም የመንግስት የድጋፍ ሰልፍ ተብሎ ሰዎችን ንግድ ቤታችሁን ዝጉና ወደ ስልፉ ውጡ እየተባለ በግዳጅ ሰውን እያስወጡ ነበር፣ አንሄድም እሚለውን እየደበደቡ ነበር።
በዚህ ወቅት የዚህ እራሱን አንቆ የገደለው አባት ልጁ ፀጉር ቤት ነበር የሚሰራው በወቅቱ ዝጋና ወደ ስልፉ ውጣ ሲባል አልወጣም በማለቱ ተደብድቦ ከባድ የሆነ ጉዳት ደርሶበት ነበር ነገር ግን በህይወት ሊተርፍ ባለመቻሉ በቀን 30/7/2016 ህይወቱ ሲያልፍ አባትየውም ሞቱን እንደሰማ በምስል በምታዩት መልኩ ራሱን አንቆ ህይወቱን አጥፍቷል

Via አዩዘሀበሻ

10/04/2024

ተስፍሽ ሊያሳስረው የሚችል ምን ይሆን????ማንንስ ነካ በምታዩት መልኩ ቃለ እግዚአብሔርን ጽፎ ከማስነበብ ውጪ ከማንም ጋር ንግግር የሌለው ሰው ነውበሕዝብ አደባባይ ሕዝብ በሚበዛባቸው  እንደ...
08/04/2024

ተስፍሽ ሊያሳስረው የሚችል ምን ይሆን????
ማንንስ ነካ በምታዩት መልኩ ቃለ እግዚአብሔርን ጽፎ ከማስነበብ ውጪ ከማንም ጋር ንግግር የሌለው ሰው ነው

በሕዝብ አደባባይ ሕዝብ በሚበዛባቸው እንደ መገናኛ በመሳሰሉት ቦታዎች ሞንታርቦ ተክለው እየተወራጩ የሚያደነቁሩን አላሳልፍ የሚሉንን ለምን አያስርም

Address

Debre Birhan

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሸዋ/Shoa/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share

Nearby media companies


Other News & Media Websites in Debre Birhan

Show All