Daily News

Daily News Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Daily News, Debre Berhan, Debre Birhan.

በኢንቨስትመንት ዘርፉ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት እየሠራ መኾኑን የደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር ገለጸ። አዲስ አበባ: ጥር 17/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር ...
25/01/2025

በኢንቨስትመንት ዘርፉ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት እየሠራ መኾኑን የደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር ገለጸ።

አዲስ አበባ: ጥር 17/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር አዲስ አበባ ከሚኖሩ የደብረ ብርሃን ከተማ ተወላጅ ባለሀብቶች ጋር በሰላም እና በልማት ዙሪያ መክሯል።

የባለሀብቱ የገቢ ምንጭ መዳከም፣ የፋይናስ ተቋማት የብድር አቅርቦት ችግር መኖር በከተማዋ በሚፈለገው ልክ ኢንቨስት ለማድረግ ፈታኝ መኾኑን ባለሀብቶቹ አንስተዋል።

በተለይም ደግሞ በአገልግሎት ሰጭ ተቋማት ቀልጣፋ እና ፍትሐዊ አገልግሎት አለመኖር፣ ከተማውን እና ወረዳውን የሚያስተሳስር የመንገድ መሠረተ ልማት አለመሟላት ለልማት እንቅፋት መኾናቸውን ነው የጠቆሙት።

እነዚህ ችግሮች በመንግሥት በኩል እንዲፈቱ እና አስፈላጊው ትብብር እንዲደረግላቸውም ተሳታፊዎቹ ጠይቀዋል።

የደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ በድሉ ውብሸት በከተማ አሥተዳደሩ የአምራች ኢንድስትሪውን የልማት እንቅስቃሴ የሚያስቆም ምንም አይነት የጸጥታ ሥጋት እንደሌለ አንስተዋል።

በከተማው ያለውን አንጻራዊ ሰላም ወደ ዘላቂ ሰላም ለማሸጋገር ኅብረተሰቡ እና መሪዎች በቁርጠኝነት እየሠሩ መኾኑንም ጠቁመዋል።

ከተማዋን ለማልማት የባለሀብቶች ሚና ከፍተኛ መኾኑን የጠቀሱት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ባለሀብቶች በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ኢንቨስት እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል።

ባለሀብቶች ኢንቨስት ማድረግ የሚችሉበት አስቻይ ኹኔታዎች በከተማ አሥተዳደሩ በኩል ማዘጋጀታቸውን ነው የተናገሩት። በከተማዋ የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶች በታለመላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ እና መሬት ወስደው ወደ ልማት ያልገቡ ባለሀብቶች እንዲያለሙም አሳስበዋል።

ለኢንዱስትሪ ዘርፉ አጋዥ የኾኑ እንደ መንገድ፣ የንጹህ መጠጥ ውኃ እና ሌሎች የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎች እየተገነቡ ነው ብለዋል።

ከአሁን በፊት በከተማው የነበረው ትልቁ ችግር የደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃ ነበር ያሉት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው አሁን ላይ ችግሩን የሚፈታ ሥርዓት ተዘርግቶ እየተሠራ ነው ብለዋል።

አልሚ ባለሀብቶች ከመሬት ጋር የሚያነሱትን የመልካም አሥተዳደር ጥያቄዎች ለመፍታትም ከተማ አሥተዳደሩ ከምንጊዜውም በበለጠ በቁርጠኝነት እየሠራ መኾኑንም ተናግረዋል። የብድር አቅርቦት ችግሩ እንዲፈታ ከፋይናንስ ተቋማት ጋር ምቹ ሁኔታ ለመፍጠርም በጋራ እንሠራለን ነው ያሉት።

የከተማውን ዕድገት የሚመጥን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን በሁሉም አገልግሎት ሰጭ ተቋማት የዲጅታላይዜሽን አገልግሎት ተግባራዊ እየተደረገ ስለመኾኑም አብራርተዋል።

ዘጋቢ:- ቴዎድሮስ ደሴ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

25/01/2025

ማህበራችን ከከተማ አስተዳደራችን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር አስቀድሞ ከውድድር ሜዳ ዝግጅት ጋር በተያያዘ ብዙ ወጪዎችን አውጥቶ በመሸፈን ከ..13../04/2017 ዓ.ም ጀምሮ በከተማችን በዓይነቱ ከፍ ያለ የክለቦች የዋንጫ ሽሚያ ውድድርን ማካሄድ በመጀመር ..4ኛ... ሳምንት ውድድርን አካሂዶ በማጠናቀቅ የ..5ኛ.. ሳምንት ውድድርን እየደመቀና እየጠነከረ ባለ የውድድር ሁኔታ ለማካሄድ 17 እና 18/05/2017 ዓ.ም የቅዳሜና የእሁድ መደበኛ የውድድር ቀናትን እየተጠባበቅን ባለንበት ሁኔታ በጥምቀት ማግስት ለጊዜው በውል ባልታወቁ አካላት ጎሉ (ፖሉ) ከፍተኛ ጉልበትና ወጪ ወጥቶበት እያለ ያለማንም እውቅናና ትዕዛዝ ተነቅሎ ተነስቷል። ስለሆነም የተፈጠረውን ችግር ለማስተካከል ሲባል የፊታችን ቅዳሜና እሁድ በ17 እና 18/05/2017 ዓ.ም ሊካሄዱ በመርሃ ግብር ተይዘው የነበሩ ውድድሮች በቀጣይ አስቀድመን ለተወዳዳሪ ቡድኖች ወደምናሳውቀው የውድድር ጊዜያት በይደር የተላለፈ ስለሆነ፤ ከአቅማችን በላይ ሆኖ ለተፈጠረው ችግር አስቀድመን ተወዳዳሪ ቡድኖችንና ተወዳዳሪዎችን በአወዳዳሪው አካል ስም ይቅርታን እንጠይቃለን።
ተስፋ ብርሃን የስፖርት ባለሙያዎች ማህበር !!!

25/01/2025
በትራፊክ አደጋ ልጆቿን ወደ ትምህርት ቤት ስትሸኝ የነበረች እናትን ጨምሮ የ3 ሰዎች ሕይዎት አለፈ ከአዲስ አበባ ወደ ደብረ ብርሃን ሲጓዝ የነበረ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪ ጠባሴ አካባቢ ሲደ...
21/01/2025

በትራፊክ አደጋ ልጆቿን ወደ ትምህርት ቤት ስትሸኝ የነበረች እናትን ጨምሮ የ3 ሰዎች ሕይዎት አለፈ

ከአዲስ አበባ ወደ ደብረ ብርሃን ሲጓዝ የነበረ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪ ጠባሴ አካባቢ ሲደርስ መንገድ ስቶ በመውጣቱ የሦስት እግረኞችን ሕይዎት ቀጠፈ፡፡

ዛሬ ጠዋት 1 ሠዓት ከ30 ላይ በደረሰው የትራፊክ አደጋ÷ ልጆቿን ወደ ትምህርት ቤት ስትሸኝ የነበረች እናትን ጨምሮ የሦስት ሰዎች ሕይዎት ማለፉን የደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።

ከሟቾች በተጨማሪም በአደጋው የ1 ዓመት ከ7 ወር ሕጻንን ጨምሮ በ9 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት መድረሱን የመምሪያው የትራፊክ መረጃ ክፍል ኃላፊ ኮማንደር ኪዳኔ በቀለ አስታውቀዋል፡፡

የአደጋው መንስኤ ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር መሆኑንም ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል፡፡

አደጋውን ያደረሰው አሽከርካሪ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

ኤፍ ኤም ሲ

 የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በደብረ ብርሃን ከተማ በድምቀት እየተከበረ ነው::ደብረ ብርሃን ፡ጥር 11/2017ዓ.ም፡(ደብኮመ):  በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳ...
19/01/2025



የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በደብረ ብርሃን ከተማ በድምቀት እየተከበረ ነው::

ደብረ ብርሃን ፡ጥር 11/2017ዓ.ም፡(ደብኮመ): በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል ሃይማኖታዊ መሰረቱና ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

የደብረ ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በበአሉ ላይ ተገኝተው እንዳነሱት የጥምቀት በአል ኢትዮጵያውያንን አንድነት ፣ መተሳሰብ የበለጠ የሚያስተሳስር ነው ብለዋል።

የህዝብ ክርስቲያኑን የጥምቀት ማክበሪያ ቦታ ምቹ እንዲሆን ከተማ አስተዳደሩ መስራቱንም ጠቁመዋል።

የጥምቀት በአል በደብረ ብርሃን ሲከበር የከተማውን ደረጃ በጠበቀ እንዲከበር ይሰራልም ነው ያሉት

በመጨረሻም እንኳን ለጥምቀት በዓል አደረሳችሁ ብለዋል።

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በደብረ ብርሃን ከተማ በድምቀት እየተከበረ ነው::ደብረ ብርሃን ፡ጥር 11/2017ዓ.ም፡(ደብኮመ):  በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደ...
19/01/2025

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በደብረ ብርሃን ከተማ በድምቀት እየተከበረ ነው::

ደብረ ብርሃን ፡ጥር 11/2017ዓ.ም፡(ደብኮመ): በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል ሃይማኖታዊ መሰረቱና ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

የደብረ ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በበአሉ ላይ ተገኝተው እንዳነሱት የጥምቀት በአል ኢትዮጵያውያንን አንድነት ፣ መተሳሰብ የበለጠ የሚያስተሳስር ነው ብለዋል።

የህዝብ ክርስቲያኑን የጥምቀት ማክበሪያ ቦታ ምቹ እንዲሆን ከተማ አስተዳደሩ መስራቱንም ጠቁመዋል።

የጥምቀት በአል በደብረ ብርሃን ሲከበር የከተማውን ደረጃ በጠበቀ እንዲከበር ይሰራልም ነው ያሉት

በመጨረሻም እንኳን ለጥምቀት በዓል አደረሳችሁ ብለዋል።

መልካም በአል!

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በደብረ ብርሃን ከተማ እየተከበረ ነው::ደብረ ብርሃን ፡ጥር 11/2017ዓ.ም፡(ደብኮመ):  በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የጌታች...
19/01/2025

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በደብረ ብርሃን ከተማ እየተከበረ ነው::

ደብረ ብርሃን ፡ጥር 11/2017ዓ.ም፡(ደብኮመ): በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል ሃይማኖታዊ መሰረቱና ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ፣ የደብረ ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት ፣ የደብረ ብርሃን ከተማ የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኀላፊ አቶ ሰለሞን ጌታቸው፣ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር መጋቤ ሐዲስ ነቅዓጥበብ አባቡ፣ የከተማ ከፍተኛ አመራሮች፣ የየአድባራቱ አስተዳዳሪዎች፣ በርካታ የእምነቱ ተከታዮች በጥምቀተ ቦታ ተገኝተዋል።

መልካም በአል

በባሕር ዳር የአባይ ማዶ አባይ ዳር ጥምቀት በድምቀት እየተከበረ ነው።ባሕር ዳር: ጥር 11/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በባሕር ዳር ከተማ የ2017 ዓ.ም የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል ከሚከ...
19/01/2025

በባሕር ዳር የአባይ ማዶ አባይ ዳር ጥምቀት በድምቀት እየተከበረ ነው።

ባሕር ዳር: ጥር 11/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በባሕር ዳር ከተማ የ2017 ዓ.ም የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል ከሚከበርባቸው ቦታዎች መካከል አንዱ ማኅደረ ስብሐት ቀድስት በዓታ በሚገኘው ባሕረ ጥምቀት ነው።

ቀሳውስት ከሌሊቱ ጀምረው ሥርዓተ ቅዳሴ ሲያከናውኑ አድረዋል። ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ጸሎተ ኪዳን ተደርጓል።

ባሕረ ጥምቀቱም በባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሰላም ኤፍሬም ሙሉዓለም ተባርኮ ምዕመናኑ ጸበል ተረጭተዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በሰቲት ሁመራ ከተማ በተከዜ ወንዝ ዳርቻ የጥምቀት ስነስርዓት።
19/01/2025

በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በሰቲት ሁመራ ከተማ በተከዜ ወንዝ ዳርቻ የጥምቀት ስነስርዓት።

19/01/2025
የጥምቀት በዓል  በቅዱስ ላሊበላ በድምቀት እየተከበረ ነው። ባሕርዳር፡ ጥር 11/2017 ዓ.ም { አሚኮ}  የጥምቀት በዓል በቅዱስ ላሊበላ በድምቀት እየተከበረ ነው። በበዓሉ ሊቃውንት፣ የሰን...
19/01/2025

የጥምቀት በዓል በቅዱስ ላሊበላ በድምቀት እየተከበረ ነው።

ባሕርዳር፡ ጥር 11/2017 ዓ.ም { አሚኮ} የጥምቀት በዓል በቅዱስ ላሊበላ በድምቀት እየተከበረ ነው። በበዓሉ ሊቃውንት፣ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን፣ ምዕመናን እና የውጭ ሀገር ጎብኝዎች ተገኝተዋል።

ላሊበላ የጥምቀት በዓል በድምቀት ከሚከበርባቸው ከተሞች መካከል አንደኛዋ ናት። በበዓሉ በርካታ የውጭ ሀገር ጎብኝዎች የሚገኙበት እና የቱሪዝም እንቅስቃሴ የሚጎላበት ነው።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

#አሚኮ

ሥርዓተ ጥምቀት በደብረ ብርሃን ከተማ በምስል
19/01/2025

ሥርዓተ ጥምቀት በደብረ ብርሃን ከተማ በምስል

19/01/2025
የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በደብረ ብርሃን ከተማ እየተከበረ ነው::በበዓሉ ላይ የሀይማኖት አባቶች ለምዕመናን ትምህርተ ወንጌል እየሰጡ  ይገኛሉ።የእምነቱ ተካታ...
19/01/2025

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በደብረ ብርሃን ከተማ እየተከበረ ነው::

በበዓሉ ላይ የሀይማኖት አባቶች ለምዕመናን ትምህርተ ወንጌል እየሰጡ ይገኛሉ።

የእምነቱ ተካታዮችም በአውደ ምህረቱ መዳረሻቸውን እያደረጉ ናቸው።

 "የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን ታቦት ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ፥ ከሰፈራችሁ ተነስታችሁ ተከተሉት" ኢያ.፫÷፫++++++++++++++++
18/01/2025



"የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን ታቦት ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ፥ ከሰፈራችሁ ተነስታችሁ ተከተሉት" ኢያ.፫÷፫
++++++++++++++++

የ2017 ዓ/ም በዓለ ጥምቀትን በሰሜን ሸዋ ሀገረስብከት ደብረ ብርሃን ከተማ በድምቀት ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸየ2017 ዓ/ም በዓለ ጥምቀትን በሰሜን ሸዋ ...
17/01/2025

የ2017 ዓ/ም በዓለ ጥምቀትን በሰሜን ሸዋ ሀገረስብከት ደብረ ብርሃን ከተማ በድምቀት ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸ

የ2017 ዓ/ም በዓለ ጥምቀትን በሰሜን ሸዋ ሀገረስብከት ደብረ ብርሃን ከተማ ከከተማ አስተዳደሩ አዲስ በተረከበው የጥምቀት በዓል ማክበሪያ ቦታ ላይ በድምቀት ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የጥምቀተ ባሕር ዐቢይ ኮሚቴ ገልጿል።

በዓሉ ለበርካታ ዘመናት የሀገረ ስብከቱ ይዞታ በሆነው በንጉሠ ነገሥት አፄ ዘርዐ ያዕቆብ አደባባይ በድምቀት ሲከበር የቆየ ሲሆን መጋቢት ፳፬ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም ሀገረስብከቱ አዲስ የተረከበው 100,000 ካሬ ቦታ በብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረስብከት ሊቀ ጳጳስ ለጥምቀተ ባሕር አገልግሎት እንዲውል ቦታው ተባርኮ የመሠረት ድንጋይ እንደተቀመጠ ይታወቃል።

መረጃው አቡቀለምሲስ ሚዲያ

  ቤተመንግስት ዕድሳትየፋሲለደስ ዕድሳት እጅግ ውብ፣ የከተማዋን ታሪካዊነት በሚያጎላና የቱሪስት መዳረሻነቷን በሚያሳድግ ሁኔታ በመሰራት ላይ  ይገኛል። የፋሲለደስ የዕድሳት ስራ አሁናዊ ገፅታ
15/01/2025

ቤተመንግስት ዕድሳት

የፋሲለደስ ዕድሳት እጅግ ውብ፣ የከተማዋን ታሪካዊነት በሚያጎላና የቱሪስት መዳረሻነቷን በሚያሳድግ ሁኔታ በመሰራት ላይ ይገኛል።
የፋሲለደስ የዕድሳት ስራ አሁናዊ ገፅታ

Address

Debre Berhan
Debre Birhan

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Daily News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Daily News:

Videos

Share