Kundi Press

Kundi Press Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Kundi Press, Magazine, Debre Birhan.

የዛይራይድ ተጠቃሚዎች ክፍያን በዲጂታል መንገድ በVISA ካርድ መፈፀም ይችላሉ ተባለ!ዛይ ራይድ ከአለም አቀፉ የፋይናንስ ድርጅት VISA ጋር እና አቢሲኒያ ባንክ ጋር በመተባበር ወደ ኢትዮጵ...
19/05/2023

የዛይራይድ ተጠቃሚዎች ክፍያን በዲጂታል መንገድ በVISA ካርድ መፈፀም ይችላሉ ተባለ!

ዛይ ራይድ ከአለም አቀፉ የፋይናንስ ድርጅት VISA ጋር እና አቢሲኒያ ባንክ ጋር በመተባበር ወደ ኢትዮጵያ ለሚመጡ ቱሪስቶች ጥሬ ገንዘቦችን በማስቀረት በኤሌክትሮኒክ ክፍያ መፈፀም የሚያስችል ቪዛ ካርድ ይፋ አደረገ።

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከፍተኛውን የዲፕሎማቲክ ፍስት የምታስተናግድ ቢሆንም ብዙዎቹ ግብይቶች በጥሬ ገንዘብ ተወስነው የቆዩ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየታዩ ያሉ ለውጦች አበረታች ናቸው ያሉት የዛይ ራይድ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ታደሰ ዛይ ራይድም የአግልግሎት ድርሻውን ለማድግ፣ አግልግሎቱን ለማሻሻል እንዲሁም አለም በቴክኖሎጂ እየተራመደ ያለበትን የኤሌክትሮኒክ የክፍያ ስርዓትን በሀገራችን ለማስፋፋት የተለያዩ ጥረቶችን ሲያድርግ ቆይቷል ብለዋል።

በአለም አቀፍ ደረጃ እጅግ የተለመደውን በካርድ የአግልግሎት ክፍያን የመፈጸም ዘዴ ከአቢሲንያ ባንክ እና በአለም አቀፍ ደረጃ የካርድ ክፍያ አግልግሎት ቴክኖሎጂ አቅራቢ ከሆነው ቪዛ ጋር በመተባበር ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ የቪዛ ተጠቃሚዎች የትራንስፖርት አግልግሎቱን ዋጋ በካርዳቸው መክፈል የሚያስችልበትን አግልግሎቱን ለማግኘት ዘመናዊ፣ ቀላል፣ ቀልጣፋ እና ፍፁም አስተማማኝ መንገድ መዘርጋቱን ነው ዛይ ራይድ ዛሬ ያስተዋወቀው።

ደንበኞች የዛይ ራይድን በአዲስ መልክ የተሻሻለውን አፕልኬሽን ከፕሌይ ስቶር ወይም ከአፕ ስቶር በማወረድ እና የሚያስፈልግውን የደንበኛ መረጃ በማስገባት መጠቀም የሚችሉ መሆኑ ተገልጿል።

የሰ/ሸዋ ሀገረ ስብከት ዘመናዊ መንፈሳዊ ኮሌጅ ሊገነባ ነው!ቋንቋን ከነሙሉ ፊደሉ ፣ ሥነ ጽሑፍን ከነአገባቡ ፣ ኪነ ሕንጻን ከነጥበቡ ፣ ዘመን አቆጣጠርን ከነቀመሩ ፣ ነጻነትን ከነሙሉ ክብሩ...
18/05/2023

የሰ/ሸዋ ሀገረ ስብከት ዘመናዊ መንፈሳዊ ኮሌጅ ሊገነባ ነው!

ቋንቋን ከነሙሉ ፊደሉ ፣ ሥነ ጽሑፍን ከነአገባቡ ፣ ኪነ ሕንጻን ከነጥበቡ ፣ ዘመን አቆጣጠርን ከነቀመሩ ፣ ነጻነትን ከነሙሉ ክብሩ ፣ ታሪክን ከነሙሉ ባሕሉ ፣ ቅርስን ከነሙሉ ሥርዓቱ ለሀገር ያበረከተች በራሷ ሀገር የሆነች ሐዋርያዊት ፣ ቀኖናዊት ፣ ኲላዊት፣ ዓለም አቀፋዊት ፣ ታሪካዊት እና ጥንታዊት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችንን እንደ ጥንቱ በቀደመ ክብሯ እና ማዕረጓ ለማስቀጠል የድንቁርና ጨለማን እየገፈፉ ለጨለማው ዓለም ብርሃን የሚሰጡ ለአልጫው ዓለም የሕይወት ማጣፈጫ ቅመም የሚሆኑ የጥበብ ፣ የእውቀት ፣ የሊቃውንት እና የምሁራን መፍለቂያ እና መገኛ መካነ አእምሮ የሆኑ አብነት ትምህርት ቤቶቿን ማጠናከር ፣ የካህናት ማሠልጠኛ እና መንፈሳውያን ኮሌጆቿን ማስፋፋት እና መክፈት ለጥያቄ የማይቀርብ መተኪያ የለሽ ቀዳሚው ጉዳይ ነው ።

በመሆኑም ከ730 በላይ የሚሆኑ ታላላቅ የአብነት ትምህርት ጉባኤ ቤቶችን እና ሊቃውንት መምህራንን ፣ ከ25000 ሺህ በላይ የአብነት ትምህርት ቤት ደቀመዛሙርትን አንድ ካህናት ማሠልጠኛን እና አንድ አዳሪ ትምህርት ቤትን አቋቁሞ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን መጠበቅ የድንርሻውን እየተወጣ የሚገኘው ታላቁ ፣ አንጋፋው እና መጠነ ግዙፉ በብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሚመራው የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የብዙ ዘመናት የማኅበረ ሰባችን እና የማኅበረ ካህናቱ ጥያቄ የሆነውን የመንፈሳዊ ኮሌጅ ጥያቄ በከፍተኛ ምሁራን የተዘጋጀ ዘመኑን የሚዋጅ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን አይነተኛ ችግር ሊፈታ የሚችል ፕሮጀክት ለቅዱስ ሲኖዶስ አቅርቦ ቅዱስ ሲኖዶስም አስፈላጊነቱን አይቶ መርምሮ በጠቅላይ ቤተ ክህነት በኩል በበጀት ተይዞ ለጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ እንዲቀርብ በመፍቀዱ ደስታችን ወደር የለውም ።

ኆኅተ ጥበብ ቅዱስ ባስልዮስ መንፈሳዊ ኮሌጃችን የቅዱስ ሲኖዶስ መልካም ፈቃድ ሆኖ ወደ ሥራ ሲገባ በነገረ ሃይማኖት፣ በቅርስ ፣ ቱሪዝም እና የሕግ አገልግሎት በቂ እና ብቁ የተማረ የሰው ኃይል በማፍራት ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ተጨማሪ ምሁራንን እና ሊቃውንትን በመውለድ ረገድ የበኩሉን በጎ አበርክቶ ያበረክታል ብለን ተስፋ እናደርጋለን ።

በቅዱስ ሲኖዶስ መልካም ፈቃድ ሊከፈት ስለታሰበው ኆኅተ ጥበብ ቅዱስ ባስልዮስ መንፈሳዊ ኮሌጅም የቦታ ጥያቄ ለከተማ አስተዳደራችን አቅርበን በከተማ አስተዳደራችንም በኩል በጎ ምልሽ አግኝተን ቦታውን ለመረከብ ጫፍ ላይ የምንገኝ ሲሆን ለመንፈሳዊ ኮሌጁ ሊገነባ የተዘጋጀው አስደናቂ ዲዛይን እና ሙሉ ዞኒንግ ሳይት ብላኑ ይህንን ይመስላል ።

ስለዚህ የተወደዳችሁ እና የተከበራችሁ በመላው ዓለም የምትገኙ ውሉደ ቤተ ክርስቲያን ይኽ በሂደት ላይ የሚገኘው የመንፈሳዊ ኮሌጅ መከፈት በቅዱስ ሲኖዶስ መልካም ፈቃድ እውን ይሆን ዘንድ በጸሎት ፣ በሀሳብ ፣ በእውቀት እና በገንዘብ ከጎናችን በመሆን ታግዙን ዘንድ በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ስም በአክብሮት ለማሳሰብ እንወዳለን ።

ገባሬ ኲሉ ወፈጻሜ ኩሉ ወጣኔ ኲሉ ወአኀዜ ኲሉ ቅዱስ እግዚአብሔር የተጀመረው በጎ ነገር ለፍጻሜ በቅቶ በዓይናችን አይተን ለመደሰት ያበቃን ዘንድ መልካም ፈቃዱ ይሁንልን !!!
ግንቦት ፱ ቀን ፱ ወር ፳፻ ፲፭ ዓም

መረጃው:- የሀገረ ስብከቱ ስራ አስኪያጅ መጋቤ ሀዲስ ነቅዐ ጥበብ አባቡ ነው።

ፋኖ ምሬ ወዳጆ ከሀገር ሽማግሌዎች ጋር በመግባባት ወደ ሰላማዊ ህይወት እንደሚመለሱ ገለፀ !
13/04/2023

ፋኖ ምሬ ወዳጆ ከሀገር ሽማግሌዎች ጋር በመግባባት ወደ ሰላማዊ ህይወት እንደሚመለሱ ገለፀ !

Address

Debre Birhan

Telephone

+251920088008

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kundi Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Kundi Press:

Share

Category