Neba man

Neba man ከሀገር ውስጥ እንዲሁም ከውጪ ወቅታዊና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎችን ፡ልዩ ክስተቶችን እና መረጃዎችን ማድረስ።

በቅርቡ ይለቀቃል !!
09/11/2023

በቅርቡ ይለቀቃል !!

06/11/2023
አንዳንድ ሀብታም ከመንግስትም በላይ ነው--------------------------------------መንግስት ኢንተርኔት ዘጋብህ ? ችግር የለም ።ወራሪዋ እስራኤል ፡ ጋዛን ወደ ፍርስራሽ ስት...
28/10/2023

አንዳንድ ሀብታም ከመንግስትም በላይ ነው
--------------------------------------
መንግስት ኢንተርኔት ዘጋብህ ? ችግር የለም ።

ወራሪዋ እስራኤል ፡ ጋዛን ወደ ፍርስራሽ ስትቀይር መሰረተ ልማቶች ወድመዋል ።በዚህ ኢሰብአዊ በሆነ የቦንብ ድብደባ. . መብራትና ውሀ ብቻ ሳይሆን ምንም
አይነት የኢንተርኔት አገልግሎት እንዳይሰራ በመደረጉ መኖሪያቸው ፈርሶና ፡በግዳጅ እንዲፈናቀሉ የተደረጉ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያን የእርዳታ
ያለህ እያሉ ነው ።

ሆኖም ምንም አይነት የኢንተርኔት ግንኙነት ስለሌለ የተባበሩት መንግስታትን ጨምሮ ብዙ የሰብአዊ እርዳታ ተቋማት ለነዚህ የጋዛ ነዋሪዎች እርዳታ ማድረስ
አልቻሉም ።

እና ይህ ችግር የሆነባቸው ተቋማትና ፡ ተፅእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች የ Space x ን ባለቤት ኤሎን መስክን ፡ አግዘን ሲሉ ጠየቁት ።

ለተቸገሩ ሰወች ለመድረስ የመገናኛ መሳሪያዎች ወሳኝ ናቸውና የእስራኤል መንግስት የከለከለንን የኢንተርኔት አገልግሎት ፡ አንተ ስጠን አሉት ።

በነገራችን ላይ ኤለን መስክ ወደ ጠፈር ባመጠቃቸው ብዛት ያላቸው ሳተላይቶች አማካኝነት የሚሰራው የStarlink የኢንተርኔት አገልግሎት ፡ የትኛውም መንግስት ማፈን እና ማቋረጥ አይችልም ።

እናም ይህ የሰብአዊነት ጥያቄ የቀረበለት ኤለን መስክ ፡ ከጥቂት ሰአታት በፊት ፡በጋዛ ለሚሰሩ የሰብአዊ እርዳታ ድርጅቶችና ፡ ለራሱ ለተባበሩት መንግስታት
ጭምር ፡ የኢንተርኔት አገልግሎት ለመስጠት ፈቃደኛ መሆኑን አስታውቋል ።....

tesfaye

ፍልስጤማውያን ዛሬ በአልናስር ሆስፒታል ለጁምዓ ሰላት ተሰባስበዋል።__________________________ፍልስጤማውያን እስራኤል ጋዛን በአየር መደብደብ ከጀመረች በ21 ኛው ቀን  ጋዛ ዉስ...
27/10/2023

ፍልስጤማውያን ዛሬ በአልናስር ሆስፒታል ለጁምዓ ሰላት ተሰባስበዋል።
__________________________
ፍልስጤማውያን እስራኤል ጋዛን በአየር መደብደብ ከጀመረች በ21 ኛው ቀን ጋዛ ዉስጥ በሚገኘው አልናስር ሆስፒታል ጁምአ ሰላት ለመስገድ ተሰባስበዋል።

በእስራኤል ጦር የተከበቡና ያለምንም ማቋረጥ ለሶስት ተከታታይ ሳምንታት የቦምብ ድብደባ ናዳ ሲወርድባቸው የቆዩት ሰፈሮች ሙሉ በሙሉ ወድመዋል።

በዚህ ድብደባ ከ 7000 በላይ ፍልስጤማውያን ተገድለዋል እንዲሁም ከፍተኛ የሆነ ሰብዓዊ ቀውስ ተከስቷል።

በሁለት እጁ የሁለት ልጆቹን ጀናዛ ይዞ የሚሄድ ጠንካራ አባት ያለባት ሀገር ፍልስጤም ብቻ ናት የአላህ ድል አድራጊ አድርጋቸው
26/10/2023

በሁለት እጁ የሁለት ልጆቹን ጀናዛ ይዞ የሚሄድ ጠንካራ አባት ያለባት ሀገር ፍልስጤም ብቻ ናት የአላህ ድል አድራጊ አድርጋቸው

ካሪም ቤንዜማ ለፍልስጤሞች አጋርነቱን አሳይቷል
20/10/2023

ካሪም ቤንዜማ ለፍልስጤሞች አጋርነቱን አሳይቷል

መሀመድ ሳላህ ለጋዛ በኢንስታግራም ድጋፉን በንግግር ገልጿልበግማሽ ሰዓት ውስጥ 4 ሚሊዮን እይታዎች ፣ እረጅም እድሜ ይኑሩ" ሰበአዊነት ሊከበር ይገባል " ሳላህግብፃዊው የሊቨርፑል የፊት መስ...
18/10/2023

መሀመድ ሳላህ ለጋዛ በኢንስታግራም ድጋፉን በንግግር ገልጿል
በግማሽ ሰዓት ውስጥ 4 ሚሊዮን እይታዎች ፣ እረጅም እድሜ ይኑሩ
" ሰበአዊነት ሊከበር ይገባል " ሳላህ
ግብፃዊው የሊቨርፑል የፊት መስመር ተጨዋች ሞሀመድ ሳላህ በቅርቡ
በእስራኤል እና ፍልስጤም መካከል በተፈጠረው ግጭት ዙሪያ በማህበራዊ
ትስስር ገፁ መልዕክት አጋርቷል።
እንደዚህ አይነት ልብ ሰባሪ ሁነቶች ባሉበት ጉዳይ አስተያየት መስጠት ቀላል
እንዳልሆነ የገለፀው መሀመድ ሳላህ " ጋዛ ያለው ነገር በጣም አስፈሪ ነው።"ሲል
ገልጿል።
" ጋዛ በፍጥነት ምግብ ፣ ውሀ እና የህክምና ቁሳቁስ ያስፈልጋታል " የሚለው
ሳላህ " የአለም መሪዎች ተጨማሪ እልቂት እንዳይመጣ እንዲመክሩ ጥሪዬን
አቀርባለሁ።"ብሏል።
ሞሀመድ ሳላህ ቀጥሎም " እዛ ያሉ ሁሉም የሰው ልጆች ጥበቃ ሊደረግላቸው
ይገባል ሰበአዊነት መከበር አለበት " ያለ ሲሆን ትላንት በጋዛ ሆስፒታል
የተፈጠረው ነገር በጣም አሰቃቂ ነበር ሲል አክሏል።

Free palestine
18/10/2023

Free palestine

አላህ ነብስህን በጀነት ያኑራት ስለ ፍልስጤም ባለህ ጠንካራ አቋም በአይሁዶችና በነ አልሲሲ ሴራ ከስልጣንህ አወረዱህ ለእስርም ዳረጉህ ነገር ግን አንተ ሸሂድ ሆንክ እንጂ አልሞትክም።
18/10/2023

አላህ ነብስህን በጀነት ያኑራት ስለ ፍልስጤም ባለህ ጠንካራ አቋም በአይሁዶችና በነ አልሲሲ ሴራ ከስልጣንህ አወረዱህ ለእስርም ዳረጉህ ነገር ግን አንተ ሸሂድ ሆንክ እንጂ አልሞትክም።

ጃፓን ድምጽ ለፍልስጤም
13/10/2023

ጃፓን ድምጽ ለፍልስጤም

በሀሰተኛ ትምህርት ማስረጃ ተቀጥረው ተማሪዎችን ሲያስተምሩና ደመወዝ ሲበሉ የቆዩ ግለሰቦች ተፈረደባቸው።**************************************ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ...
13/10/2023

በሀሰተኛ ትምህርት ማስረጃ ተቀጥረው ተማሪዎችን ሲያስተምሩና ደመወዝ ሲበሉ የቆዩ ግለሰቦች ተፈረደባቸው።
**************************************

ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ በማሰራት በአንድ ትምህርት ቤት ውስጥ ተቀጥረው ሲሰሩ የነበሩ 3 ግለሰቦች ያለ ብቃታቸው እና ያለ ሙያቸው ሲያስተምሩ በመገኘታቸው ክስ ተመስርቶባቸው ውሳኔ ተላለፈባቸው።

1ኛ ተከሳሽ እዮብ ዲኖ፣
2ኛ ተከሳሽ ደስታ ዳርጫ፣
3ኛ ተከሳሽ በላቸው በየነ የተባሉት ግለሰቦች በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን ውስጥ " አንዝሬ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት " በሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ተቀጥረው ያለ ሙያቸው እና ያለ ብቃታቸው ተማሪዎችን ሲያስተምሩ ተይዘው የወልቂጤ አካባቢ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ዓቃቤ ህግ ክስ መስርቶባቸዋል።

1ኛ ተከሳሽ እዮብ ዲኖ ፦ ከአርባ ምንጭ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ #በባዮሎጂ መምህርነት በዲፕሎማ እንደተመረቀ በማስመሰል ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ አዘጋጅቶ ከቀን 10/04 /2011 ዓ/ም ጀምሮ በአንዝሬ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በተለያየ የደመወዝ መጠን #በሂሳብ መምህርነት ተቀጥሮ ሲያስተምር ቆይቶ በድምሩ 215 ሺህ 739 ብር ተከፍሎታል።

2ኛ ተከሳሽ ደስታ ዳርጫ ፦ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ኮሌጅ #በእንግሊዘኛ መምህርነት በዲፕሎማ እንደተመረቀ በማስመሰል ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ አዘጋጅቶ ከ04/07/2012 ዓ/ም ጀምሮ በአንዝሬ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት #በሂሳብ መምህርነት ተቀጥሮ ሲያስተምር ቆይቶ በድምሩ 119 ሺህ 800 ብር ተከፍሎታል።

3ኛ ተከሳሽ በላቸው በየነ ፦ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ኮሌጅ በሂሳብ ትምህርት በዲፕሎማ እንደተመረቀ በማስመሰል ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ አዘጋጅቶ ከቀን 04/07/2012 ዓ/ም ጀምሮ በአንዝሬ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህርነት ተቀጥሮ ሲያስተምር ቆይቶ በድምሩ 119 ሺህ 008 ብር ደመወዝ ተከፍሎታል።

ሶስቱም ተከሳሾች ያለሙያቸውና ብቃታቸው ሲያስተምሩ በቆዩባቸው ጊዜያት በተማሪዎች ላይ በገንዘብ የማይተመን እጅግ ከፍተኛ ጉዳት እና በመንግሥት ላይ ባልተገባ መልኩ በተቀበሉት ደመወዝ 455, 755 የሚገመት ብር ጉዳት አድርሰዋል።

ዓቃቤ ህግ በፈፀሙት ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ በማዘጋጀት እና በመገልገል በመንግሥት ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ የሙስና ወንጀል ክስ መስርቷል።

የበሉትን ደመወዝም እንዲመልሱ በክሱ ላይ ቀርቧል።

የወልቂጤ አካባቢ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዓቃቤ ህግ ያቀረባቸው ማስረጃዎች ከበቂ በላይ ናቸው በማለት ሶስቱም ተከሾች ጥፋተኛ ብሏቸዋል።

እያንዳንዳቸው በ5 ዓመት ፅኑ እስራት እና በ2 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ እንዲሁም ያለአግባብ የበሉትን አጠቃላይ 455,755 ብር ለመንግሥት እንዲመልሱ ውሳኔ አሳልፏል።

"የእስራኤል የጋዛ ከበባ በአለም አቀፍ ህግ የተከለከለ ነው" የተባበሩት መንግስታት ድርጅትየእስራኤል በጋዛ ሰርጥ የሚኖሩ ሰላሚዊ ዜጎች ለህልውና አስፈላጊ የሆኑ ማንኛውንም አገልግሎቶች እንዳ...
10/10/2023

"የእስራኤል የጋዛ ከበባ በአለም አቀፍ ህግ የተከለከለ ነው" የተባበሩት መንግስታት ድርጅት

የእስራኤል በጋዛ ሰርጥ የሚኖሩ ሰላሚዊ ዜጎች ለህልውና አስፈላጊ የሆኑ ማንኛውንም አገልግሎቶች እንዳያገኙ ማገዷ በአለም አቀፍ ህግ የተከለከለ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ሃላፊ ዘግቧል ።

እንደ ዘገባው ከሆነ የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ቮልከር “ይህን አስቸጋሪ ሆኔታ ለማርገብ ለሁሉም ወገኖች ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን ከሁሉም በፊት ግን የሰዎች ክብር እና ህልውና መከበር አለበት ብለዋል።

በተጨማሪም ኮሚሽነሩ “በፍልስጤም የታጠቁ ቡድኖች አባላት የሚፈጸመውን ዘግናኝ የጅምላ ግድያ” አውግዞ ታጣቂዎቹ ታጋቾችን ማፈን በአለም አቀፍ ህግም የተከለከለ ነው ብለዋል።

ቮልከር እስራኤል እያደረገች ያለው “የሰላማዊ ሰዎችን ህይወት አደጋ ላይ የሚጥል ከበባ በአለም አቀፍ የሰብአዊነት ህግ የተከለከለ ነው” ብለዋል።

"ይህ ቀደም ሲል በጋዛ ውስጥ ያለውን አስከፊ የሰብአዊ መብት እና የሰብአዊነት ሁኔታን በተለይም የሕክምና ተቋማትን የመስራት አቅምን ጨምሮ በተለይም የተጎዱትን ቁጥር በመጨመር ላይ ያለውን አደጋ በእጅጉ ሊያባብሰው ይችላል" ብለዋል

ዘገባው የአል-ሞኒተር ነው

 በኢትዮጵያ 🇪🇹 ደረጃ የ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበችው የክሩዝ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪ ናት።ተማሪ ሀናን ናጂ አህመድ በተፈጥሮ ሳይንስ 649 ው...
10/10/2023



በኢትዮጵያ 🇪🇹 ደረጃ የ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበችው የክሩዝ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪ ናት።

ተማሪ ሀናን ናጂ አህመድ በተፈጥሮ ሳይንስ 649 ውጤት በማስመዝገብ ከዘንድሮ ተፈታኞች በቀዳሚነት ተቀምጣለች፡፡

ተማሪ ሀናን ናጂ ባስመዘገበችው ውጤት በጣም ደስተኛ መሆኗን ገልጻለች።

በቀጣይም ለበለጠ ውጤት እንደመትተጋ ተናግራለች፡፡

የክሩዝ ሁተኛ ደረጃ ት/ቤት በአዲስ አበባ ከተማ ልደታ ክፍለ ከተማ የሚገኝ የግል ትምህርት ቤት ነው፡፡

Credit - AMN

10/10/2023

አረቦች እንዲህ ይላሉ ...
"ሰነፍ መምህር እንጂ ሰነፍ ተማሪ የለም"
ተማሪን ጎበዝም ሰነፍም የሚያደርገው መምህሩ ነው በሚለው እኔም እስማማለሁ።

10/10/2023

96 likes, 4 comments. “ይህች ጀግና ፍልስጤማዊት ህጻን ያለችው እውነት ሆነ አጃዒብ ነው።”

ቱርኪ እስራኤል በፍልስጤም መሬቶች ላይ የምታደርገውን የቦምብ ጥቃት እንድታቆም ጠይቃለች ፍልስጤማውያንም በእስራኤል ውስጥ በሲቪል ሰፈሮች ላይ የሚያደርሱትን ትንኮሳ እንዲያቆሙ አሳስቧል ፕሬዝ...
10/10/2023

ቱርኪ እስራኤል በፍልስጤም መሬቶች ላይ የምታደርገውን የቦምብ ጥቃት እንድታቆም ጠይቃለች ፍልስጤማውያንም በእስራኤል ውስጥ በሲቪል ሰፈሮች ላይ የሚያደርሱትን ትንኮሳ እንዲያቆሙ አሳስቧል ፕሬዝዳንቱ አክለውም ..

"በጋዛ ላይ በአየር እና በምድር ጥቃት መውደሟ፣ በመስጊዶች ላይ የቦምብ ጥቃት እና የንፁሀን ህጻናት፣ ሴቶች፣ አዛውንቶች እና ሰላማዊ ዜጎች ሞት ፈጽሞ ተቀባይነት የላቸውም" ሲሉ ኤርዶጋን አፅንኦት ሰጥተዋል።

ኤርዶጋን በድጋሚ ሲናገሩ "በ1967 ድንበሮች ውስጥ የፍልስጤም ነጻ የሆነች፣ ሉዓላዊ የሆነች የፍልስጤም ግዛት እስካልተመሰረተች ድረስ በቀጠናው ሰላም አይኖርም ብለን እናምናለን።

የአሜሪካ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ከኢየሱስ ጋር ቻት ማድረጊያ አፕ ሰርቻለሁ አለ።--------------------------------------------------------------ዋና መቀመጫውን ...
25/09/2023

የአሜሪካ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ከኢየሱስ ጋር ቻት ማድረጊያ አፕ ሰርቻለሁ አለ።
--------------------------------------------------------------
ዋና መቀመጫውን አሜሪካ ሎስ አንጀለስ ያደረገው catloaf software ኩባንያ ሰዎች ከኢየሱስ ጋር በጽሁፍ መልዕክት ማውራት የሚያስችል መተግበሪያ መስራቱን አስታውቋል፡፡

ቻትጅቢቲ የተሰኘው የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የተሰራው ይህ አፕ ወይም መተግበሪያ ሰዎች ኢየሱስ ክርስቶስን ጨምሮ በመጽሃፍ ቅዱስ ውስጥ ስማቸው ከተጠቀሱ አካላት ጋርም ማውራት ያስችላል ተብሏል፡፡

መተግበሪያው ሰዎች ከኢየሱስ በተጨማሪ ከአስቁሮቱ ይሁዳ፣ አብርሃም እና ሌሎች የቤተ ክርስቲያን አባቶች እና ጻድቃን ጋር እንዲያወሩ ተደርጎ የበለፀገ ሲሆን ከሰይጣን ጋር እንዲነጋገሩ የሆነበት ክፍል ደግሞ ብዙዎችን አጨቃጭቋል።
ይህ የድርጅቱ ድርጊት ብዙ ክርስትያኖችን ያናደደ ሲሆን በተለይ ስለተመሳሳይ ፆታ ጋብቻ አፕሊኬሽኑ እንዲመልስ የተደረገበት ክፍል ብዙዎችን ለከፍተኛ ቁጣ አነሳስቷል።

08/09/2023

849 Followers, 900 Following, 5733 Likes - Watch awesome short videos created by Nebat

07/09/2023

tiktok.com/

01/09/2023
የምበሪማ ፈርኒቸር ለአዲሱ አመት በታላቅ ቅናሽ የቤት ዉስጥ ፈርኒቸሮችን አቅርበናል ይላችኋል።0966515051/0966515052 ደውለው ያናግሩን ይዘዙን
30/08/2023

የምበሪማ ፈርኒቸር ለአዲሱ አመት በታላቅ ቅናሽ የቤት ዉስጥ ፈርኒቸሮችን አቅርበናል ይላችኋል።

0966515051/0966515052 ደውለው ያናግሩን ይዘዙን

24/12/2022

Missing Qatar already ❤️🇶🇦 I had so much fun ... 😁

13/09/2022
13/09/2022

𝐌𝐄𝐄𝐓 𝐓𝐇𝐄 𝐑𝐈𝐂𝐇𝐄𝐒𝐓 𝐌.𝐀𝐍 𝐖𝐇𝐎 𝐄𝐕𝐄𝐑 𝐋𝐈𝐕𝐄𝐃

Mansa Musa (Musa I of Mali)🇲🇱 was the king of the ancient empire of Mali in West Africa.

Mansa Musa (Musa I of Mali) was the ruler of the kingdom of Mali from 1312 C.E. to 1337 C.E. During his reign, Mali was one of the richest kingdoms of Africa, and Mansa Musa was among the richest individuals in the world. The ancient kingdom of Mali spread across parts of modern-day Mali, Senegal, the Gambia, Guinea, Niger, Nigeria, Chad, Mauritania, and Burkina Faso. Mansa Musa developed cities like Timbuktu and Gao into important cultural centers. He also brought architects from the Middle East and across Africa to design new buildings for his cities. Mansa Musa turned the kingdom of Mali into a sophisticated center of learning in the Islamic world.

Mansa Musa came to power in 1312 C.E., after the previous king, Abu Bakr II, disappeared at sea. Mansa Abu Bakr II had departed on a large fleet of ships to explore the Atlantic Ocean, and never returned. Mansa Musa inherited a kingdom that was already wealthy, but his work in expanding trade made Mali the wealthiest kingdom in Africa. His riches came from mining significant salt and gold deposits in the Mali kingdom. Elephant ivory was another major source of wealth.

When Mansa Musa went on a pilgrimage (hajj) to Mecca in 1324 C.E., his journey through Egypt caused quite a stir. The kingdom of Mali was relatively unknown outside of West Africa until this event. Arab writers from the time said that he travelled with an entourage of tens of thousands of people and dozens of camels, each carrying 136 kilograms (300 pounds) of gold. While in Cairo, Mansa Musa met with the Sultan of Egypt, and his caravan spent and gave away so much gold that the overall value of gold decreased in Egypt for the next 12 years. Stories of his fabulous wealth even reached Europe. The Catalan Atlas, created in 1375 C.E. by Spanish cartographers, shows West Africa dominated by a depiction of Mansa Musa sitting on a throne, holding a nugget of gold in one hand and a golden staff in the other. After the publication of this atlas, Mansa Musa became cemented in the global imagination as a figure of stupendous wealth.

After his return from Mecca, Mansa Musa began to revitalize cities in his kingdom. He built mosques and large public buildings in cities like Gao and, most famously, Timbuktu. Timbuktu became a major Islamic university center during the 14th century due to Mansa Musa’s developments. Mansa Musa brought architects and scholars from across the Islamic world into his kingdom, and the reputation of the Mali kingdom grew. The kingdom of Mali reached its greatest extent around the same time, a bustling, wealthy kingdom thanks to Mansa Musa’s expansion and administration.

Mansa Musa died in 1337 and was succeeded by his sons. His skillful administration left his empire well-off at the time of his death, but eventually, the empire fell apart. Well after his death, Mansa Musa remained engrained in the imagination of the world as a symbol of fabulous wealth. However, his riches are only one part of his legacy, and he is also remembered for his Islamic faith, promotion of scholarship, and patronage of culture in Mali.

Guys let's get our YouTube channel (YT: Historical Africa) to 40k subscribers. Kindly click on the link to subscribe. 🙏 https://youtube.com/c/HistoricalAfricaa/

ፑቲን የዩክሬን ጦር ስልጣን እንዲይዝ ጠየቁ==============================የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አርብ ዕለት  ፕሬዚደንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪን ከስልጣን በማውረድ...
26/02/2022

ፑቲን የዩክሬን ጦር ስልጣን እንዲይዝ ጠየቁ
==============================

የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አርብ ዕለት ፕሬዚደንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪን ከስልጣን በማውረድ
የዩክሬን ጦር በኪዬቭ "ስልጣን እንዲረከብ" ጠይቀዋል።

ፑቲን የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት እና አጃቢዎቻቸውን "የሱሰኞች እና የኒዮ-ናዚዎች ቡድን" ናቸው ብለዋል ።

ቀጥሎም ለዩክሬን ጦር በሩሲያ ቴሌቪዥን ባቀረበው ንግግር "ስልጣን ያዙ በእኔና በእናንተ መካከል መደራደር ቀላል መስሎ ይታየኛል" ሲል ተናግሯል።

ፑቲን እየተዋጋ ያለው የዩክሬን የጦር ክፍል ሳይሆን እንደ “አሸባሪ” የሚንቀሳቀሱ እና ንጹሃንን እንደ " ጋሻ” ከሚጠቀሙ ብሔርተኞች ነው።

ፑቲን እንደተናገሩት ወረራዉ የመጣው ዩክሬን በዶንባስ ሪፐብሊካኖች ላይ የምትከተለውን ፖሊሲ ለማረም ሞስኮ የሰጠቻቸውን በርካታ እድሎች ካስመለጠች በኋላ ነው።

"ከአውሮፓ እና አሜሪካ ጋር ለመነጋገር ፈልገን ነበር, ነገር ግን ለዚያ የሰጡት ምላሽ እኛን ችላ ማለት ብቻ ነው" ብለዋል.

በመቀጠልም "በእነዚህ ሁሉ አመታት ምዕራባውያን የዩክሬንን አገዛዝ በመደገፍ ከሩሲያ ጋር እንዲዋጉ ሲገፉ ነበር እኛ ጎረቤቶቻችንን እንዳንዋጋ ጠየቅን, ምክንያቱም እነዚህ መሳሪያዎች በዶንባስ ውስጥ በንጹሃን ላይ ጥቅም ላይ ይውላሉ."።

"የዩክሬን ህዝብ ለሩሲያውያን ወንድማማች ህዝቦች ናቸው, ነገር ግን አመራራቸው እና ዩናይትድ ስቴትስ ወደ ገደል እየመሯቸው ለሩሲያ ጥላቻ እንዲያድርባቸው እያደረጉ ነው።

አል-አረቢያ

22/02/2022

In 875 CE, at the age of 65, 'Abbās ibn Firnās tried to fly. Using a hang-glider made of feathers and wood that he built after hours of observing birds in flight, he leapt off the roof of the Rusāfa palace in Cordoba. By all accounts, he flew for several minutes, gliding on the air currents like a raptor!

He is known as "the first man to ever fly", but other than that, he also designed a water clock. He devised means of manufacturing glass, and he developed a chain of rings that could be used to display the motions of the planets and stars. He also devoloped a process for cutting rock crystal. Thereafter, Spain no longer needed to export quarts to Egypt, but could finish it at home.

Ibn Firnās was an Andalusi polymath, an inventor, astronomer, physician, chemist, engineer and an Arabic-language poet.

But the question is: Have you ever heard of this man before? If not, you now probably know the reason why. He was a Muslim with a beard and turban.

የዩክሬን ወረራ እየተቃረበ ነው...የሩሲያ እና የአሜሪካ ዲፕሎማቶች ኪየቭን ለቀው ወጡ።==================================ምንም እንኳን ሞስኮ ድርጊቱን ውድቅ ብታደርግም እ...
13/02/2022

የዩክሬን ወረራ እየተቃረበ ነው...የሩሲያ እና የአሜሪካ ዲፕሎማቶች ኪየቭን ለቀው ወጡ።
==================================

ምንም እንኳን ሞስኮ ድርጊቱን ውድቅ ብታደርግም እና ይህን በሚያመለክቱት ዘገባዎች ሁሉ እየተሳለቀች ቢሆንም በቅርቡ የዩክሬንን ወረራ እውነታነት የሚያሳዩ በርካታ ምልክቶች ታይተዋል።

የሩሲያ የመገናኛ ብዙሃን ምንጮች የሩሲያ ዲፕሎማቶች እና የቆንስላ ሰራተኞች ዩክሬን መልቀቅ መጀመራቸውን ያረጋገጡ ሲሆን ዋሽንግተን በኪዬቭ የሚገኘውን ኤምባሲዋን ለመልቀቅ መዘጋጀቷን አስታውቃለች።

አርብ ዕለት የዩኤስ የመከላከያ ሚኒስትር ሎይድ ኦስቲን በፖላንድ፣ ጀርመን፣ ካናዳ፣ ፈረንሳይ፣ ሮማኒያ እና ጣሊያን ላሉት አቻዎቻቸው እንደተናገሩት የሩሲያ ወረራ በማንኛውም ጊዜ ሊጀመር ይችላል ብለዋል።

"ኦስቲን የኔቶ አጋሮችን ለማረጋጋት የአሜሪካ እርምጃዎችን ከሚኒስትሮቹ ጋር በመሆን ገምግሟል፣ እና ለጋራ መከላከያ ያለንን የማያወላውል ቁርጠኝነት አረጋግጧል" ሲል ፔንታጎን ተናግሯል።

የኦስቲን አስተያየት የዩናይትድ ስቴትስ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ጃክ ሱሊቫን ከሰጡት መግለጫ በኋላ “በዚህ ወር በ20ኛው ቀን የሚጠናቀቀው በቻይና የሚካሄደው የኦሊምፒክ ጨዋታ ከማብቃቱ በፊት ሩሲያ ዩክሬንን ልትወር የምትችልበት እድል ሰፊ ነው” ብለዋል።

አክለውም "የሩሲያ ጥቃት በዩክሬን ላይ ከየትኛውም ቀን በኋላ ሊከሰት ይችላል, እና ምናልባትም በአየር ጥቃት ሊጀምር ይችላል, እናም የሩሲያ ወረራ ዋና ከተማዋን ኪየቭን ጨምሮ በዩክሬን ውስጥ ያሉ ዋና ዋና ከተሞችን ሊያካትት ስለሚችልበት ትልቅ እድል ተናግሯል. ."

ዲፕሎማቶች እየወጡ ነው!!!

ወታደራዊ ቀውሱ መባባሱን የሚያሳዩ ምልክቶች እየታዩ ነው በሌላ በኩል፣ የዩኤስ ባለስልጣናት ቅዳሜ ዕለት እንዳስታወቁት፣ ሩሲያ በዩክሬን ልትወረር ትችላለች በሚል ስጋት ዩናይትድ ስቴትስ በዩክሬን ዋና ከተማ ኪየቭ የሚገኘውን ኤምባሲዋን ለቃ ለመውጣት እየተዘጋጀች መሆኑን፣ ቅዳሜ ዕለት አስታውቀዋል። ሲል አሶሺየትድ ፕሬስ ዘግቧል።

(ስማቸው ያልተገለፀ) የዩኤስ ኤጀንሲ ባለስልጣናትን ጠቅሶ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ በኪዬቭ የሚገኙ ሁሉም አሜሪካዊያን ሰራተኞች የሩሲያ ወረራ ከመከሰቱ በፊት ለቀው እንዲወጡ ማቀዱን አስታውቋል።

ባለስልጣናት እንዳሉት ጥቂት የማይባሉ የአሜሪካ ባለስልጣናት በኪዬቭ ሊቆዩ ይችላሉ፣ ነገር ግን በኤምባሲው ውስጥ ከሚገኙት 200 የሚጠጉ አሜሪካውያን አብዛኛዎቹ ዩናይትድ ስቴትስ የዲፕሎማሲያዊ ስራዋን እስክታሻሽል ድረስ ወደ ዩክሬን ምእራብ በፖላንድ ድንበር አቅራቢያ ይወሰዳሉ ወይም ይዛወራሉ።

በሌላ በኩል የሩስያ "ስፑትኒክ" የዜና ወኪል የሩሲያ ዲፕሎማቶች እና የቆንስላ ሰራተኞች ዩክሬንን መልቀቅ መጀመራቸውን ምንጭ ጠቅሶ ዘግቧል።

የአውሮፓ ህብረት በበኩሉ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው በስተቀር የዲፕሎማቲክ ሰራተኞቻቸው ዩክሬንን ለቀው እንዲወጡ ጠይቋል።

የአውሮፓ ኮሚሽኑ ቃል አቀባይ ፒተር ስታኖ በመግለጫው እንዳስታወቁት ከፍተኛ ትኩረት ያልተሰጣቸው ሰራተኞች ዩክሬንን ለቀው እንዲወጡ ተፈቅዶላቸዋል ብሏል።

የሩስያ ባለስልጣናት ሞስኮ ወደ ዩክሬን ምንም አይነት ወታደራዊ እርምጃ ለመውሰድ እንደማትፈልግ በድጋሚ ተናግረዋል.

በተባበሩት መንግስታት የሩስያ ቋሚ ተወካይ ዲሚትሪ ፖሊያንስኪ "ዩክሬንን ልትወር የምትችለው ዩናይትድ ስቴትስ ናት" ብለዋል.

ቦያንስኪ በትዊተር ገፃቸው ላይ ዩናይትድ ስቴትስ ተከሰተ በተባለው የሩስያ ወረራ ዙሪያ “የሽብር ዘመቻ” ስትመራ ኖራለች ብለዋል።

justice for our brothers.
10/02/2022

justice for our brothers.

"ወጣት ልጅ ሳለው አንድ ቀን ትልቅ ተጫዋች ሆኜ ለትልቅ ክለብ እንደምጫወት ለሁሉም ሰው እናገር ነበር ይህን ስላቸው ይስቁብኝ ነበር ይህን መቀበል ያቃታቸው ችሎታ የለውም ብለው ስለሚያስቡ አ...
08/02/2022

"ወጣት ልጅ ሳለው አንድ ቀን ትልቅ ተጫዋች ሆኜ ለትልቅ ክለብ እንደምጫወት ለሁሉም ሰው እናገር ነበር ይህን ስላቸው ይስቁብኝ ነበር ይህን መቀበል ያቃታቸው ችሎታ የለውም ብለው ስለሚያስቡ አልነበረም ከሴኒጋል ተነስቶ እዛ ከፍታ ላይ መድረስ የማይቻል መስሎ ስለታያቸው ነበር እኔ ግን ይህን የማድረግ አቅም ውስጤ እንዳለ አውቅ ነበር።"
ሳዲዮ ማኔ

አልሐምዱሊላህ ረያን በሰላም ከጉድጓዱ ወጣቷል።
05/02/2022

አልሐምዱሊላህ ረያን በሰላም ከጉድጓዱ ወጣቷል።

አውሮፓውያን ሀገራት የኢኮኖሚ ፖሊሲዎቻቸውን የቀረጹበት አፍሪካዊው የምጣኔ ሀብት ሊቅ ኢብን ኻልዱን።_________________________________________"ኮሌጅ እያለሁ በወጣትነቴ...
01/02/2022

አውሮፓውያን ሀገራት የኢኮኖሚ ፖሊሲዎቻቸውን የቀረጹበት አፍሪካዊው የምጣኔ ሀብት ሊቅ ኢብን ኻልዱን።
_________________________________________
"ኮሌጅ እያለሁ በወጣትነቴ ኢኮኖሚክስ አጥንቻለሁ እዚያ ሳለሁ ከ 1200 ዓመት በፊት ግብጽ ውስጥ ስለሚኖር ኢብን ኻልዱን ስለሚባል ሰው ተምርያለሁ።

በግዛተ አጼው (መንግስት) መጀመሪያ ላይ የግብር መጠን ዝቅተኛ ሲሆን የገቢ መጠን ግን ከፍተኛ ነው በግዛተ አጼው መጨረሻ (መንግስት ሊወድቅ ሲል) ላይ ግዛተ አጼው ሲዳከም የግብር መጠን ይጨምራል ገቢ ግን ይቀንሳል ብሏል።"

ከላይ ያነበባችሁት ጽሁፍ የቀድሞው የአሜሪካ ፕ/ት ሮናልድ ሬገን ከ45 ዓመታት በፊት መስከረም 21 ቀን 1974 በዋይት ኃውስ ከሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የተቀነጨበ ነው።

በዚህ መግለጫቸው ፕ/ት ሮናልድ ሬገን ቀዳሚ የአቅርቦት ተኮር ምጣኔ ሀብት ንድፈ ሃሳብ አመንጪ የሆነውን የ14 ኛው ክፍለ ዘመን ሊቅ ኢብን ኻልዱንን ገልጸዋል።

የሬገን አስተዳደር አብዛኛውን የምጣኔ ሃብት ፖሊሲውን የመሰረተው ኢብን ኻልዱን በቀዳሚነት በቀመረው ኃላም በሌሎች የምዕራቡ ዓለም ሊቃውንት በዳበረው የምጣኔ ሃብት ንድፈ ሃሳብ ነው።

የስነ ምጣኔ የእውቀት ሃሳብ ሲነሳ በአብዛኛዎቹ የመስኩ ሊቃውንት በቀዳሚነት ስሙ የሚጠቀሰው የዘመናዊ ምጣኔ ሃብት በመባል የሚታወቀውና በ1723 በስኮትላንድ የተወለደው አዳም ስሚዝ ነው።

ነገር ግን አዳም ስሚዝ በ18 መቶ ክፍለ ዘመን የምጣኔ ሃብት ንድፈ ሃሳቡን ከማመንጨቱ 400 ዓመታት በፊት ብዙዎቹን ሃሳቦች የቱኒስ ተወላጁ አፍሪካዊ የምጣኔ ሃብት ሊቅ ኢብን ኻልዱን አንስቷቸው ነበር።

እንደ ስሚዝ ሁሉ ኻልዱን የሃብት ምንጭ ወርቅ ወይም ብር ሳይሆን የሰው ጉልበት መሆኑን ቀድሞ ተናግሯል።

የስራ ክፍፍል ፋይዳም ቢሆን ከስሚዝ በፊት በኻልዱን የተወሳ ሃሳብ ነው። ሁለቱ ሊቃውንት ሌሎች ብዙ ስነ-ምጣኔ ሃብታዊያ ንድፈ ሃሳቦችንም ይጋራሉ።

የኻልዱን ስራዎች እስከ 17 ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ግድም ወደ አውሮፓ አልደረሱም ነበር ይባላል።
በ1697 ወደ አውሮፓ የተሻገረው የመጀመሪያው የኻልዱን ስራ በፈረንሳያዊው የምስራቅ ባህሎች አጥኚ ወደ ፈረንሳይኛ የተተረጎመ የኻልዱን የህይወት ታሪክ ነበር።

በ1723 የተወለደው አዳም ስሚዝ በቀጥታም እንኳን ባይሆን በተዘዋዋሪ በኦቶማን ግዛተ አጼ አማካኝነት የኻልዱን ስራዎች ሳይደርሱት እንዳልቀረ ይታመናል

በሶሺዮሎጂ የሳይንስ ዘርፍ ስማቸው ከሚጠቀሱት እንደ ማርክስ ፣ ዱርኸይም እና ዌበር መካከል ልዩ የሆነ አንድ ስም አለ ፡፡

የሶሺዮሎጂ አባት የሆኑት እና በጂኦግራፊም ሆነ በታሪክ ውስጥ ትልቅ ተጽዕኖ ያሳደሩት፣ ባለ ብሩህ አዕምሮው ኢብኑ ካልዱን በማግሪብ በተለይም በአንዳሉሺያ እና በቱኒዚያ በሰፊው ይከበራሉ፡፡ ሐውልቶቹ ከተሞቹን ያስጌጡ ሲሆን ስሙም በገንዘብ ፣ በጎዳናዎች እና በሙዚየሞች ላይ ሰፍሮ ይገኛል ፡፡

የእሱ ሥራዎች ወደ አውሮፓ ከገቡ በኋላ በብዙ ቋንቋዎች የተተረጎሙ ሲሆን በመላው አውሮፓ በጣም ተወዳጅነትን እና አድናቆትን አትርፈዋል፡፡

እንግሊዛዊው የታሪክ ምሁር አርኖልድ ቶይንቢ የኢብኑ ካልዱን ሥራ በፍልስፍና እና በታሪክ ዘርፍ ውስጥ እጅግ አስፈላጊ እንደሆነ አውጀዋል ፡፡

መረጃውን ከወደዱት ለሌሎችም ያጋሩት።

ሚሊየነሮች የሚያፈሱባቸው 5 ተስፋ ሰጭ ቴክኖሎጂዎች... እወቃቸው==================================techygeeks ሚሊየነሮች ኢንቨስት በሚያደርጉባቸው አምስት ተስፋ ሰጭ...
22/01/2022

ሚሊየነሮች የሚያፈሱባቸው 5 ተስፋ ሰጭ ቴክኖሎጂዎች... እወቃቸው
==================================
techygeeks ሚሊየነሮች ኢንቨስት በሚያደርጉባቸው አምስት ተስፋ ሰጭ ቴክኖሎጂዎች ላይ መረጃ አሳትሟል እናም እነዚህ ቴክኖሎጂዎች በቅርብ ጊዜ ውስጥ በሰፊው ይስፋፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በ አረቢ21 የተተረጎመው ዘገባ፣ ወደፊት የሚደረጉ ኢንቨስትመንቶች በሰዎች ህይወትና አኗኗር ላይ ቀጥታ ተጽዕኖ በሚያሳድሩ ቴክኖሎጂዎች ላይ እንደሚያተኩሩ ገልጿል።

1) ዘላቂ ኃይል

ከእነዚህ ተስፋ ሰጭ ቴክኖሎጂዎች መካከል ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ የሆነ ታዳሽ ኃይል ከጊዜ ወደ ጊዜ ባለሀብቶችን እየሳበ ያለ የኢንቬስትመንት ዘርፍ ነው።

ለምሳሌ ቢል ጌትስ፣ ጄፍ ቤዞስ፣ ጃክ ማ፣ ማይክል ብሉምበርግ እና ሪቻርድ ብራንሰንን ጨምሮ በርካታ የቢሊየነሮች ቡድን በዚህ ዘርፍ ለመስራት ልዩ ፈንድ አቋቁመዋል፣ ዓላማውም ለፕላኔቷ ነዋሪዎች የተሻለ የኑሮ ደረጃን ማረጋገጥ ሲሆን ጥሩ የኤሌክትሪክ ኃይል, ጤናማ ምግብ, ምቹ መኖሪያ እና መጓጓዣን ጨምሮ, ከአየር ንብረት ለውጥ መባባስ ጋር በተያያዘ ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎችን መከላከል ነው።

ፈንዱ በየአመቱ ቢያንስ የአለም ሙቀት አማቂ ጋዝ ልቀትን በ 0.5 ጊጋ ቶን መቀነስ የሚችሉ ኩባንያዎችን ይመርጣል።

ይህ ማለት ፈንዱ አሁንም ባልለሙ የአረንጓዴ ኢነርጂ መስኮች ላይ ኢንቨስት ሊያደርግ የሚችል ሲሆን ከ 14 ኩባንያዎች ጋር የኢነርጂ ማከማቻ ስርዓቶችን፣ የጂኦተርማል ኢነርጂ ማመንጫዎችን እና ውህድ ኢነርጂዎችን ለመስራት ውል ገብቷል።

2) የጠፈር ጉዞ

ስራ ፈጣሪዎች በህዋ ቴክኖሎጂ ልማት ላይ ኢንቨስት በማድረግ ላይ ሲሆኑ በዚህ ኢንዱስትሪ ልማት ዘርፍ ውስጥ የሚሰሩ የግል ኩባንያዎች አሏቸው።

ለምሳሌ ስፔስኤክስ ማስክ እና ቨርጂን ጋላክቲክ ብራንሰን ከፕላኔታችን ውጭ ያለውን የሰው ልጅ ሰፈራ ህልምን እውን ለማድረግ ይፈልጋሉ።

የአለማችን ባለጸጋ ተብሎ የሚታሰበው የአማዞን ዋና ስራ አስፈፃሚ ጄፍ ቤዞስ በ 2019 "blue origin" የተሰኘውን የጠፈር አየር መንገድ መሰረተ።

ቤዞስ በጨረቃ ላይ ለማረፍ ምሳሌ የሆነ የጠፈር መንኮራኩር ለማምረት እና ለማሳደግ በናሳ ከተመረጡት ሰዎች ዝርዝር ውስጥ ተካቷል ።

ቀሪዎቹን ሶስቱን በቀጣይ ክፍል ይጠብቁ

አዲሷ የቻይና ሳተላይት ለአሜሪካ ጦር አዲስ ራስ ምታት? ===============================ቻይና በትንሿ ሳተላይቷ ' የአሜሪካ ከተሞች ምስሎችን ማንሳት እንደምትችል ተናገረች።...
30/12/2021

አዲሷ የቻይና ሳተላይት ለአሜሪካ ጦር አዲስ ራስ ምታት?
===============================
ቻይና በትንሿ ሳተላይቷ ' የአሜሪካ ከተሞች ምስሎችን ማንሳት እንደምትችል ተናገረች።

ቻይናውያን ወደ ህዋ ሳይንስ በሰፊው የገቡበት ሁኔታ በአሜሪካ እና በቀድሞዋ የሶቪየት ኅብረት መካከል የነበረውን የቀዝቃዛ ጦርነት አይነት ውድድር ይመስላል።

ቻይና ወደ ጨረቃ ወይም ማርስ ተልእኮዎችን ከመላክ ባለፈ በወሰደችው እርምጃ አሁንም የዜና ዘገባዎችን ማዘጋጀቷን ቀጥላለች።

ቻይና ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን የአሜሪካ ከተሞች ፎቶግራፎች ከህዋ ላይ የሚያነሳ ሳተላይት አምጥቅያለሁ ስትል የገለጸች ሲሆን ይህም የተሸከርካሪውን ታርጋ እንኳን የሚያሳይ ነው ተብሏል።

ባለሙያዎች እንደሚሉት, ይህ የቻይና ሳተላይት በ 42 ሴኮንድ ውስጥ ብቻ አንድን የአሜሪካ ሰፊ ከተማ ዙሪያ ክልል ፎቶግራፍ ማንሳት ይችላል ፎቶግራፎቹ, በመንገድ ላይ ያለን አንድ ወታደራዊ ተሽከርካሪ መለየት እንዲሁም የተሸከው መሣሪያ ምን ዓይነት ሊሆን እንደሚችል ለመንገር በቂ ጥራት ያላቸው ናቸው።

በሌላ በኩል በቻይና በሰኔ ወር የተላከውና አንድ ቶን የሚመዝነው "ቤጂንግ-3" አነስተኛ የንግድ ሳተላይት 3,800 ስኩዌር ኪሎ ሜትር በሚሸፍነው በሳን ፍራንሲስኮ የባህር ወሽመጥ ዋና አካባቢ ላይ ሲያደርግ የነበረውን ጥልቅ ጥናት ማጠናቀቁን በፕሮጀክቱ ላይ የተሳተፉ ሳይንቲስቶች ገልጸዋል።

ቻይና ለተለያዩ ዓላማዎች በርካታ የመሬት ምልከታ ሳተላይቶችን ወደ ህዋ አምጥቃለች። ከዚህ ቀደም በታህሳስ 26 ቻይና አምስት ሜትር ርዝመት ያላቸውን የመሬት ፎቶግራፎች ማንሳት የሚችል ካሜራ ያለው አዲስ ሳተላይት ማምጠቋን የቻይና ብሄራዊ የጠፈር አስተዳደር (ሲኤንኤ) እንደገለጸ ዘ ታይምስ ኦፍ ኢንዲያ ዘግቧል ።

“ዚዩአን-1 02ኢ” ወይም “አምስት ሜትር ኦፕቲካል ሳተላይት 02” በመባል የምትታወቀው ሳተላይት በቻይና ሻንዚ ግዛት ከሚገኘው የታይዋን ሳተላይት ማስጀመሪያ ማእከል በሎንግ ማርች-4ሲ ሮኬት አመጠቀች።

የቤጂንግ-3 የፕሮጀክት መሪ ያንግ ፋንግ እና ባልደረቦቿ በአገር ውስጥ በአቻ በተገመገመው ስፔስክራፍት ኢንጂነሪንግ በተሰኘው ጆርናል በዚህ ወር ባሳተሙት ጽሁፍ “ቻይና በአንፃራዊነት ዘግይቶ በቀላል የሳተላይት ቴክኖሎጂ የጀመረች ቢሆንም በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ እድገት አሳይታለች ብሏል።

ኦሳማ ቢን ሊድን ስለ አሜሪካ እና ሲ አይ ኤ ያጋለጠው ሚስጢር።(በትዕግስት ሙሉውን ያንብቡት)=================================በሰኔ 2006 የኤፌ.ቢ.አይ የምርመራ ውጤቶች...
27/12/2021

ኦሳማ ቢን ሊድን ስለ አሜሪካ እና ሲ አይ ኤ ያጋለጠው ሚስጢር።

(በትዕግስት ሙሉውን ያንብቡት)
=================================

በሰኔ 2006 የኤፌ.ቢ.አይ የምርመራ ውጤቶች ህትመት ሃላፊ የሆነው ሬክስ ቶምብ (FBI Chief of Investigative Publicity Rex Tomb) እንደገለፀው፡ ኦሳማ ቢን ላድን በጥብቅ የሚፈለግ የሚለው ገፁ ላይ 9/11 ያልተጠቀሰበት ምክንያት
ኤፌ.ቢ.አይ. ቢን ሊድንን ከ9/11 ጋር የሚያገናኝበት ጠንካራ ማስረጃ ስላሌለው ነው፡፡‛ ብሎ ነበር፡፡

እንዲያውም ቢን ሊድን እራሱ ኡመት ከተባለ የፓኪስታን ጋዜጣ ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ በ9/11 ጥቃት እጁ እንደሌለበት ገልጿል፡፡

ቢን ሊድን እንደሚከተለው ብሏል፡-

ከዚህ ቀደምም ተናግሬያለው ዩናይትዴ ስቴትስ ላይ በደረሰው የመስከረም 11 ጥቃት የለሁበትም፡፡ እንደ ሙስሊምነቴ ከውሸት ለመራቅ እሞክራለው፡፡
…ንፁሃን ሰዎችን፣ ሴቶችንና፣ ህፃናት ልጆን መግደልን እንደሚደነቅ ተግባር አልቆጥረውም፡፡ ኢስላም
በጥብቅ ይከለላቸዋል…፡፡

እንዲህ አይነት ድርጊት በጦርነት ግዜ እን`ኳ የተከለከለ ነው፡፡ ዩናይትድ ስቴትስ ነች ለሌሎች እምነት
ተከታዮች፣ለሴቶች፣ ህፃናትና ተራ ሰዎች ጉስቁልና ተጠያቂዋ፡፡

የመስከረም 11 ጥቃትን ያደረሱት የአሜሪካ ህዝቦች ወዳጆች አይደሉም፡፡ ከዚህ ቀድሞም ተናግሬያለው የአሜሪካን ስርአት ተጻራሪ ነን እንጂ ህዝቡን አንፃረርም፣ በነዚህ ጥቃቶች ግን ተራው የአሜሪካ ህዝብ ነው የተጎዳው፡፡

ዩናይትድ ስቴትስ የነዚህ ጥቃቶች ተጠያቂዎችን ከውስጧ ነው መፈለግ ያለባት፣ የአሜሪካ
ስርአት አካል የሆኑና ስርዓቱን ተጻረው የተነሱትን፡፡

ወይም ለሌላ ዓይነት ስርዓት እየሰሩ ያለ፤ ይህኛውን ክ/ዘመን የእስልምናና ክርስቲያን ግጭት ዘመን ማድረግ የሚፈልጉ፣ እናም የራሳቸው ስሌጣኔ፣ ህዝብ፣ ሃገር፣ ወይም ርእዮተ አለም እንዲሰፍን የሚሹ ሰዎች፡፡

በተጨማሪም ደሞ በዩ.ኤስ የደህንነት ተቋማት አሉ፣ በየአመቱ ከኮንግረስና ከመንግስት በቢሊዮን ዶላሮች የሚቆጠር ፈንድ የሚፈልጉ፡፡

ይህ [የፈንድ ጉዳይ] የቀድሞ ሶቭየት ዩኒየን እስካለች ድረስ አስቸጋሪ ጉዳይ አልነበረም ከዛ በኋላ ግን የነዚህ
ተቋማት በጀት አደጋ ውስጥ ገብቷል፡፡ ጠላት አስፈለጋቸው፡፡ ከዚህም አንፃር የኦሳማና ታሊባን ፕሮፖጋንዳ ጀመሩ፣ ቀጥሎ ይህ [ጥቃቱ] ተከሰተ፡፡

አየህ የቡሽ አስተዳደር የ40 ቢሊዮን ዶላር በጀት አፀደቀላቸው፡፡ …አሁን ይህን ገንዘብ አላማቸውን ለማስፋፋትና ጥንካሬአቸውን ለመጨመር ይጠቀሙበታል፡፡

ምሳሌ እሰጥሃለው፡፡ በመላው ዓለም የሚገኙ እፅ አዘዋዋሪዎች ከዩ.ኤስ የሚስጥር ተቋማት ጋር ግንኑነት አላቸው፡፡

እነዚህ ተቋሞች አደንዛዥ እፅ ማብቀልንና ማዘዋወርን መቆጣጠር አይሹም፣ያለበለዝያ አስፈላጊነታቸው ይቀንሳል፡፡

ጀነራሌ ኖሬጋ በሲ.አይ.ኤ ነው የአደንዛዥ እፅ ጌታ የተደረገው፣ አስፈላጊነቱ ሲያበቃ ደሞ ለሌሊ ጉዳይ ማመኻኛ ተደርጓል፡፡

‚… ይህ ምን ማለት ነው? ይህ ታድያ በዩናይትድ ስቴትስ በመንግስት ውስጥ ሌላ መንግስት እንዳለ አያሳይም? ይህ የሚስጥር መንግስት ጥቃቶቹን ማን እንደፈፀማቸው መጠየቅ አለበት፡፡

‛ (mmat, Karachi, September 28, 2001)

ይህን ስናነብ ቢን ሊድን ጥቃቱን ያመነበት ቪድዮስ ልንል እንችላለን፡፡ ቪድዮው ግን የሃሰት (fake) ነው፡፡ ለዚህም በቂ ማስረጃ አለ፡፡

ታህሳስ 14፣ 2001 ላይ በህዳር 9፣ 2001 ተቀረፀ የተለው ቪድዮ ብቅ አለ፡፡ በዚህም ቢን ሊድን
ሃሊፊነቱን እንደሚወስድ ተረጋገጠ ተባለ፡፡ ሆኖም ግን ሙያተኞች ቪድዮውን የሃሰት ቅንብር መሆኑን አጋልጠውታል፤ ካገኙበት እንከን ውስጥ፡-

1. ቢን ሊድን ወፍሯል፡፡
2. አፍንጫው አነስ ብሏል፡፡
3. በቀኝ እጁ ተጠቅሞ ሲፅፍ ይታያል፤ በኤፌ.ቢ.አይ መረጃ መሰረት ግን ቢን ላድን ግራኝ ነው፡፡
4. ለመጀመርያ ግዜ የወርቅ ቀለበት አድርጓል፡፡ (በእምነቱ ሃራም ነው፡፡)
5. የቪድዮው ጥራት እጅግ ደካማ ነው፡፡
6. የቪድዮው አብዛኛው ክፍል የተጓደለ (ባዶ) ነው፡፡
7. የቪድዮው ድምፅ ደግሞ የባሰውኑ ደካማ ነው፣ ጫጫታ የበዛበት ሲሆን የሚለውን ባግባቡ መስማት አይቻልም፡፡
8. ብዙ ጋዜጦች የንግግሩ ፍቺ ልክ እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡ ወዘተ

ካነበቡ በኋላ ሼር ማድረግ እንዳይረሱ

Address

Butajira

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00
Sunday 09:00 - 17:00

Telephone

+251966515051

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Neba man posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share