የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit

  • Home
  • Ethiopia
  • Butajira
  • የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit

የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit public and government service

በእንሴኖ ከተማ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሄደ!!!=============እንሴኖ፤ሰኔ/21/2016 ዓ.ምዜጎችን ከተረጂነት አስተሳሰብ ለማለቀቅ፣የምግብ ዋስትናን ለ...
28/06/2024

በእንሴኖ ከተማ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሄደ!!!
=============
እንሴኖ፤ሰኔ/21/2016 ዓ.ም

ዜጎችን ከተረጂነት አስተሳሰብ ለማለቀቅ፣የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የመንግስት የትኩረት መስክ በመሆን በባለፉት አመታት እየተተገበረ ይገኛል።

በተለይ በባለፉት ጊዜያት ሀገራችን ኢትዮጵያ በውጭ ወራሪ ሃይሎች እንዳትገዛ ህዝቧ እጅጉን ታግሎ ነፃነቷን አስረክቧል።

ይሁንና ድህነትን በማስወገድ ረገድ ክፍተቶች በመኖራቸው ዜጎች የምግብ ዋስትናቸውን አስተማማኝ ማድረግ አልቻሉም።

ይህን መሰረት በማድረግ ከለውጡ ማግስት የበጋና የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን መርህ አድርጎ በመያዝ ብዙ አቅመ ደካማ ወገኖችን እንዲረዱ ሆነዋል ።

በእንሴኖ ከተማ አስተዳደርም የበጋ በጎ ፈቃድ አገልግሎትን በመዝጋት የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀምሯል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዘይኑ ቃሲም የተገኙ ሲሆን መልዕክትም አስተላልፈዋል።

በዚህም መንግስት የህዝቡን ዘርፈ ብዙ ችግሮችን ለመፍታት ዕቅድ ይዞ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

በተለይ አቅመ ደካማ ግለሰቦችን ካሉበት የድህነት ህይወት ለማለቀቅ በምግብ እራሳቸውን እንዲችሉ እያደረገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ይህን መሰረት በማድረግ ቤት የሌላቸው ወገኖችን ቤት የመገንባት፣ያረጁ ቤቶችን የማደስ እና የተለያዩ የቁሳቁስ ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል በያዝነው የክረምት ወራት የበጎ አድራጎት ተግባራትን እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

የከተማው የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና ሪዮተ አለም ዘርፍ ሃላፊ አቶ ሸምሱ አደም በበኩላቸው፡-የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች ሰውነትን የምንላበስበት የእርስ በእርስ መደጋገፋችንን፣መተባበራችንን እና አንድነታችንን የምናጠናክርበት ነው ብለዋል።

ለዚህ ደግሞ ጊዜው ክረምት በመሆኑ አቅመ ደካማ ወገኖች በብዙ የሚቸገሩበት በመሆኑ ተረባርበን በአረጋውያን ቤት እድሳት፣የምግብ ቁሳቁስ ድጋፍና ሌሎች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች ላይ በመሳተፍ የበኩላችንን አስተዋጽኦ እናድርግ ብለዋል።

የእንሴኖ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ዩኒት ኃላፊ አቶ ያሲን ሸምሱ እንደተናገሩት፡-አዲስና ያረጁ የአረጋዊያንና አቅመ ደካሞች ቤት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለመስራት የቅድመ ዝግጅት ስራ መሰራቱን የገለፁ ሲሆን

ወጣቶችን መሰረት ያደረገ እንዲሁም ህዝብን በተለይ ጣሪና አቅመ ደካማ ወገኖችን የማገልገል ተግባር በትኩረት እየተሰራበት እንዲመገኝ አመላክተዋል።

የበጎ አድራጎት ስራው በብዙ ዘርፈ እንደሚተገበር በመግለጽ በበጋ ወቅትና በክረምት መርሃ ግብር እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

በያዝነው የክረምት ወቅት የአረጋውያን ቤት እድሳትና አዲስ ግንባታ ለማከናወን ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል።

በመጨረሻም የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዘይኑ ቃሲም የአንዲት አቅመ ደካማ እናት ቤት ግንባታን አስጀምረዋል።

የክረምት ወራት የአረንጓዴ አሻራ የማስጀመሪያ መልሃ ግብር ተካሄደ!!!===============እንሴኖ፤ሰኔ/21/2016 ዓ.ምበእንሴኖ ከተማ የክረምት ወራት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የማስ...
28/06/2024

የክረምት ወራት የአረንጓዴ አሻራ የማስጀመሪያ መልሃ ግብር ተካሄደ!!!
===============
እንሴኖ፤ሰኔ/21/2016 ዓ.ም
በእንሴኖ ከተማ የክረምት ወራት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።

ፕሮግራሙን ላይ የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዘይኑ ቃሲም በመገኘት አስጀምረውታል።

በዚህም መንግስት ከለውጡ ወዲህ የተለያዩ የዕድገትና ብልፅግና ምሶሶ ያላቸውን ፕሮግራሞችን ነድፎ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

በዋናነት የአረንጓዴ ልማትን ለተከታታይ አመታት በመላው የሀገሪቱ ክፍል እዲተገበር ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ የተናገሩ ሲሆን

ይህን መሰረት በማድረግ በከተማችን እንሴኖ የአረንጓዴ ልማት በማስፋት የለመለመች፣ፅዱ፣ንፁህ የአየር ንብረት የተላበሰች ከተማን ለመስራት ክረምቱን በመጠቀም የተለያዩ ችግኞችን በመትከል የድርሻችንን መወጣት ያስፈልጋል ብለዋል።

የከተማው የግብርና ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ኸይሩ ሙዜ በበኩላቸው፡-ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የቅድመ-ዝግጅት ስራዎች እንደተሰሩ የገለፁ ሲሆን

በአረንጓዴ የልማት ስራዎች ላይ በመሳተፍ የአየር ብክለትን ከመከላከል ባለፈ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የከተማው ነዋሪ ይህንን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በመጨረሻም በእንሴኖ ሃይስኩል ግቢ ውስጥ ለሰርቶ ማሳየነት እንዲሆን የከተማው ከንቲባ አቶ ዘይኑ ቃሲም፣የብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ምክትል የመንግስት ተጠሪና የፖለቲካና ርዮተ አለም ዘርፍ ሃላፊ አቶ ሸምሱ አደም፣የከተማው አመራሮች፣ወጣቶች፣ነዋሪዎች፣ተማሪዎች በተገኙበት 1500 የሮዝመሪ ችግኞችን በመትከል የአረንጓዴ አሻራ አኑረዋል።

የማንችስተር ዩናይትድ የቀድሞ ኮከብ ተጫዋች ሉዊስ ናኒ ወደ ኢትዮጵያ ሊመጣ ነው!!!============እንሴኖ፣ ሰኔ 20፣ 2016  የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድንና የማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋች ...
27/06/2024

የማንችስተር ዩናይትድ የቀድሞ ኮከብ ተጫዋች ሉዊስ ናኒ ወደ ኢትዮጵያ ሊመጣ ነው!!!
============

እንሴኖ፣ ሰኔ 20፣ 2016
የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድንና የማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋች የነበረው ሉዊስ ናኒ የመቻል ስፖርት ክለብ 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ላይ በክብር እንግድነት እንደሚታደም የክለቡ ቦርድ ገለጸ።

ናኒ ያቋቋመው የስፖርት አካዳሚ ከመቻል ጋር የትብብር ሥምምነት እንደሚፈራረምም ተገልጿል።

የመቻል ስፖርት ክለብ ቦርድ የቡድኑን 80ኛ ምስረታ በዓል ዝግጅትን አስመልክቶ ዛሬ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥቷል።

በዚህም ሉዊስ ናኒ የመቻል ስፖርት ክለብ 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ላይ በክብር እንግድነት እንደሚታደም ተገልጿል፡፡

የቦርዱ ሰብሳቢ ሰይፉ ጌታሁን (ዶ/ር)÷የመቻል ስፖርት ክለብን 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች ማክበር የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጠናቀቁን ገልጸዋል።

የመርሐ ግብሩ አካል የሆነ የ10 ኪሎ ሜትር ሩጫ ውድድር ሰኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ እንደሚካሄድና በሺህዎች የሚቆጠሩ ዜጎች እንደሚሳተፉ ጠቁመዋል።

ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ.ም ደግሞ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ባለኃብቶች የሚሳተፉበት የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር እንደሚካሄድ ጠቅሰዋል፡፡

የ37 ዓመቱ የፖርቹጋል ብሄራዊ ቡድንና የማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋች የነበረው ሉዊስ ናኒ ሐምሌ 6 ቀን 2016 ዓ.ም በክለቡ የምስረታ በዓል ለመገኘት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጣም ነው ሰብሳቢው የገለጹት።

ሐምሌ 7 ቀን 2016 ዓ.ም መቻል ከዩጋንዳው ኪታራ ስፖርት ክለብ ጋር የወዳጅነት ጨዋታ እንደሚያካሄድ መጠቆማቸውን የመከላከያ ሰራዊት መረጃ ያመላክታል፡፡

የ37 ዓመቱ ፖርቹጋላዊ የክንፍ መስመር ተጫዋች ናኒ ማንችስተር ዩናይትድ፣ ቫሌንሺያ፣ ላዚዮ፣ ስፖርቲንግ ሊዝበንና ፊነርባቼ ከተጫወተባቸው ክለቦች መካከል ይጠቀሳሉ።

የመቻል ስፖርት ክለብ በ1936 ዓ.ም የተመሰረተ ሲሆን÷ እግር ኳስና አትሌቲክስን ጨምሮ በልዩ ልዩ የስፖርት አይነቶች ሥመ-ጥር ስፖርተኞችን ያፈራ የስፖርት ክለብ መሆኑ ይታወቃል።

ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የፌስቡክ ገፅ የተወሰደ

በመስቃንና ማረቆ ምርጫ ክልል 2 በድጋሚ የተካሄደው ምርጫ ነጻና ሰላማዊ በሆነ መልኩ መካሄዱ በጠንካራ ጎን ተገመገመ!!!================ሰኔ 20/2016 ዓ/ም እንሴኖየምስራቅ ጉራጌ...
27/06/2024

በመስቃንና ማረቆ ምርጫ ክልል 2 በድጋሚ የተካሄደው ምርጫ ነጻና ሰላማዊ በሆነ መልኩ መካሄዱ በጠንካራ ጎን ተገመገመ!!!
================
ሰኔ 20/2016 ዓ/ም እንሴኖ

የምስራቅ ጉራጌ ብልፅግና ፖርቲ ፅ/ቤት በመስቃንና ማረቆ ምርጫ ክልል 2 በድጋሚ በተካሄደው 6ኛው ዙር ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫን አስመልክቶ በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫው ዕለት እና በድህረ-ምርጫ ተግባር አፈፃፀም ላይ ምርጫው በተካሄደባቸው አካባቢ ያሉ የብልፅግና ፖርቲ አመራሮች በተገኙበት ግምገማ አካሂዷል።

በዋናነት ምርጫው ሠላማዊ ዴሞክራሲያዊና ታዐማኝነት ያለው ምርጫ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ግብ ተጥሎ ወደ ተግባር ተገብቶ የነበረ ሲሆን ከዚህ አኳያ የተሳካ ውጤት መገኘቱን የምስራቅ ጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና ዋና የመንግሥት ተጠሪ አቶ መሰለ ጫካ ገልፀዋል።

በቀጠናው ከዚህ ቀደም ከነበረው የደህንነትና የፀጥታ ችግር አኳያ የምርጫውን ሰላማዊና ፍትሀዊ ሂደት ሊያስተጓጉል የሚችል የፀጥታ ችግር እንዳይከሰት ከተለያዩ አጎራባች ወረዳዎች ጭምር የፖሊስና ፀጥታ አስከባሪ ሀይሎች በየምርጫ ጣቢያው እንዲገቡና የደህንነትና የፀጥታ ችግር እንዳይኖር በመሰራቱ ምርጫው ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ ሠላማዊ በሆነ መልኩ ያለምንም የፀጥታ ችግር ማጠናቀቅ መቻሉን በግምገማ መድረኩ በጠንካራ ጎን አስተያየት ተሰጥቶበታል።

ምርጫው ከታዐማኒነት አንፃርም ሲቪክ ማህበራትቶች እና ምርጫ ቦርድ በሀላፊነት ስሜት ገብተው የተከታተሉት እንደነበርና የተለያዩ ሚዲያዎችም በቦታው ተገኝተው እየዘገቡ እንደነበርም ተጠቅሷል።

ከምርጫው ተሳትፎ መጠን አኳያም ከተያዘው ግብ አንፃር በዕለቱ በማህበራዊ ችግሮች ምክንያት እና ከቀዬአቸው ተፈናቅለው ወደ ተለያዩ አካባቢ የተንቀሳቀሱ አካላት ድምፅ አለመስጠታቸው የተነሳ የታየ ውስን ጉድለት ካልሆነ በቀር የጎላ ክፍተት እንዳልነበር ተገምግሟል።

በመጨረሻም የምስራቅ ጉራጌ ዞን የብልፅግና ፖርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ መሰለ ጫካ ምርጫው የተጠናቀቀ እንደመሆኑ አሁን አመራሩ፣ መላው አባላችን፣ ህዝቡ እንዲሁም ባለሙያው ፊቱን ወደ መኸር ተግባር በማዞር ህዝባችንን ተጠቃሚ መሆን የሚያስችል ስራ ላይ ርብርብ ማድረግ ይገባል የሚል የስራ መመሪያ ሰጥተዋል። አቶ መሰለ ጫካ አክለውም እንደገለፁት ፖርቲያችን ብልፅግና ፓርቲ ምርጫው ሰላማዊ፣ ነፃ፣ ፍትሀዊና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን የጣለው ግብ እንዲሳካ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ሁሉ እንዲሁም ፖርቲያችን በምርጫው ለተጎናፀፈው ድል መራጩንና ለምርጫው ስኬት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አመራሮች፣ አባላት፣ የፀጥታ መዋቅሮችና አባሎቻቸው እንዲሁም ለአካባቢው ሰላም ወዳድ ህዝብ ከፍተኛምስጋና አቅርበዋል።

ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው

በብልጽግና ፓርቲ መሪነት በሁሉም የስራ መስክች እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ውጤታማ  መሆናቸውና የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው!!!=====================  እንሴ...
27/06/2024

በብልጽግና ፓርቲ መሪነት በሁሉም የስራ መስክች እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውና የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው!!!
=====================
እንሴኖ:-ሰኔ=20/2016 ዓ/ም

በእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት የህዋስና የመሰረታዊ ድርጅት አደረጃጀቶች በማጠናከር ግንባር ቀደም ሆነው የተጣለባቸውን ኃላፊነት መወጣት እና የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንዳለባቸው።

በከተማ ደረጃ የሚገኙ የብልጽግና ፓርቲ የመሠረታዊ ድርጅት የ2016 በጀት አመት የእቅድ አፈጻጸም ተገምግሟል።

የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ሙህዲን ደድገባ እንደገለፁት በከተማው በብልጽግና ፓርቲ መሪነት በሁሉም የስራ መስክች የተሰሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውና የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እየተረጋገጠ ይገኛል ብለዋል።

በኢኮኖሚ፣በማህበራዊ ልማቶች በተለይም በትምህርት፣ በመንገድ ልማት፣ በጤና፣ በግብርና በሌሎችም የስራ መስኮች ፓርቲው ከፍተኛ የህዝብ ንቅናቄ በመፍጠር ለሌላው አካባቢ ተሞክሮ ሊሆን የሚችሉ ውጤቶች ተመዝግበዋል።

የህዋሰና የመሰረታዊ ድርጅት አደረጃጀቶች እንዲጠናከሩና ግንባር ቀደም ሆነው የተጣለባቸው ኃላፊነት በመወጣት የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በይበልጥ ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል።

አክለውም በአመራሩና በአባላት ላይ የጋራ አስተሳሰብና የተግባር አንድነት በመፍጠር የተመዘገቡ ተሞክሮዎችን ለማስፋት እንዲሁም ገዢ ትርክቶችን ለማስረጽ የሚዲያ አጠቃቀም ማሻሻል ይገባልም ብለዋል።

የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ሹራላ ሳኒ በበኩላቸው የብልጽግና ፓርቲ ህዋስና መሰረታዊ ድርጅት አደረጃቶች ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ፣ ውይይቶችና ኮንፈረሶች የፓርቲው ሆነ የመንግስት ስራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ አስችለዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የሚመራው መንግስት የከተማውን ህዝብ የልማቱ ተሳታፊና ተጠቃሚ ለማድረግ በተሰሩ ሁሉ አቀፍ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧል

ለዚህም መላው አመራሩና አባላት ከመቼውም ጊዜ በተለየ ለሰላሙ ዘብ በመቆም የበኩሉን እገዛ ሊያደርግ እንደሚገባ በመግለጽ።

የመድረኩ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት በፓርቲው መሪነትና በመንግስት እና መላው ህብረተሰብ በማሳተፍ የተሰሩ ስራዎች አበረታች በመሆናቸው ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልጸው በቀጣይ በሰላምና የህዝቡ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በሆኑ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ ሊሰራ ይገባል ብለዋል።

በህዋስና በመሰረታዊ ድርጅት ደረጃ የተገመገሙ ክፍተቶችን ለማረምና በቀጣይ በጀት አመት የእቅድ አካል ተደርገው ለመስራት መዘጋጀታቸው ተናግረዋል።

ጠንካራ አንድነት ለዘላቂ ልማት
==============================

26/06/2024

ሰኔ /19/2016 ዓ.ም
ዋልታ ቴሌቪዥን "ሰላም ኢትዮጵያ"የማለዳ ፕሮግራም የእንሴኖ ከተማ የማለዳ ድባብ ምን እንደሚመስል በአካል በመገኘት ቅኝት አድርጓል።

ሙሉ ዝግጅቱን ቪድዮን መመልከት ትችላላችሁ

እንሴኖን በጋራ እናልማ

26/06/2024

ሰኔ /19/2016 ዓ.ም
ዋልታ ቴሌቪዥን "ሰላም ኢትዮጵያ"የማለዳ ፕሮግራም የእንሴኖ ከተማ የማለዳ ድባብ ምን እንደሚመስል በአካል በመገኘት ቅኝት አድርጓል።

ሙሉ ዝግጅቱን ቪድዮን መመልከት ትችላላችሁ

እንሴኖ በጋራ እናልማ

ለእንሴኖ ከተማ ፅዳትና ውበት የአረንጓዴ ልማት              #32ኛ ሳምንት የፅዳት ዘመቻ #      እንሴኖ፣ሰኔ/19/2016 ዓ.ምበእንሴኖ ከተማ የፅዱ ከተሞች ንቅናቄ በሳምንት ዕለ...
26/06/2024

ለእንሴኖ ከተማ ፅዳትና ውበት የአረንጓዴ ልማት
#32ኛ ሳምንት የፅዳት ዘመቻ #
እንሴኖ፣ሰኔ/19/2016 ዓ.ም
በእንሴኖ ከተማ የፅዱ ከተሞች ንቅናቄ በሳምንት ዕለተ ረቡዕ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት በስፋት እየተተገበረ ይገኛል።

በዚህም የፅዳትና ውበት ስራ ባህል እንዲሆን ከተማ አስተዳደሩ ሳይታክት ይሰራል።

በዋናነት ለኑሮ ምቹ፣የአየር ንብረቷ በተሻለ ደረጃ ላይ እንዲገኝ፣ማራኪና ሳቢ ለማድረግ ችግኞችን በሁሉም የከተማዋ አቅጣጫ እንዲተከሉ ይደረጋል።

ለዚህ ደግሞ ከተማዋ አረንጓዴ ልምላሜዋን ይዛ እንድትለማ የአረንጓዴ አሻራን ለማስተግበር የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል።

በዛሬው ዕለትም 32ኛ ሳምንት የፅዳት ዘመቻን መሰረት በማድረግ በቀጣይ አርብ በእንሴኖ ሃይስኩል ግቢ ለሚካሄደው የችግኝ ተከላ ፕሮግራም የቅደመ ዝግጅት ስራዎች ተሰርተዋል።

በተለይ ቦታውን የማመቻቸት፣የጉድጓድ ቁፋሮና እንዲሁም ቀደም ሲል የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ኮሽሞችን የመመንጠር ስራዎች ተሰርተዋል።

የመስቃንና ማረቆ  ምርጫ ክልል ቁጥር 2  በ6ኛው ዙር ሀገራዊና ክልላዊ የድጋሚ  ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረጉ አካላት የምስጋና መልዕክት ተላለፈ!!!======================...
25/06/2024

የመስቃንና ማረቆ ምርጫ ክልል ቁጥር 2 በ6ኛው ዙር ሀገራዊና ክልላዊ የድጋሚ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረጉ አካላት የምስጋና መልዕክት ተላለፈ!!!
==========================
ሰኔ/18/2016 ዓ.ም እንሴኖ
የመስቃንና ማረቆ ምርጫ ክልል ቁጥር 2 በ6ኛው ዙር ሀገራዊና ክልላዊ የድጋሚ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረጉ አካላት የምስጋና መልዕክት ተላልፏል።

ከትናንት በስቲያ ስድስተኛ ዙር የማሟያ ሃገራዊ ምርጫ በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎች ተካሂዷል።

ከእነዚህ መካከል የመስቃንና ማረቆ ቁጥር ሁለት የምርጫ ክልል አንዱ ሲሆን
የምርጫ ሂደቱ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ በስኬት ተጠናቋል።
ይህን መሰረት በማድረግ የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዘይኑ ቃሲም እንዲሁም የከተማው የብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ እና ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ደርብ ታደሰ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ክቡር ከንቲባ አቶ ዘይኑ ቃሲም በመልዕክታቸው ምርጫው ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ በስኬት እንዲጠናቀቅ የእንሴኖ ከተማ መላው ነዋሪ ማ፣የከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ የፖሊስ አባላት፣ የክልሉ አድማ ብተና፣ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት የየአካባቢው የሚሊሻ አካላት እንዲሁም በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡኢ፣ የደ/ሶዶ፣ የቡታጅራ መዋቅሮች እና ከአጎራባች ዞኖች የስልጤ፣ የሃላባና የጉራጌ ዞኖች ለመጡት የፖሊስ አባላት፣ በምርጫው ለተሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ተወዳዳሪዎች ለምርጫ አስፈፃሚዎች በሙሉ

ምርጫው ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ በስኬት እንዲጠናቀቅና በህዝቡ ዘንድ ታዓማኒነት እንዲኖረው ላበረከታችሁት ታላቅ አስተዋጽዖ በራሴና በከተማው አስተዳደሩ ስም የከበረ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ያሉ ሲሆን

ህዝቡ በምርጫው ላሳየው ተሳትፎ በቀጣይም በልማትና በመልካም አስተዳደር ስራዎች እንዲደግመው በዚሁ አጋጣሚ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ ብለዋል።

የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ደርብ ታደሰ በበኩላቸው

ከዞን እስከ ከተማ ተግባሩን ለመሩ አመራሮቻችን እና የፀጥታ ሀይሎች እና ለእንሴኖ ከተማ መራጭ ህዝብ በሙሉ ዳግም እንድናገለግላችሁ ፓርቲያችንን ስለመረጣችሁ እጅግ በራሴና በእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ስም አመስግናለሁ ሲሉ ተናግረዋል።

በዚህም ከህዝቡ የሚነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለሰ እና ከየትኛውም ጊዜ በበለጠ ሁኔታ ለማገልገል ዳግም ቃል እንገባለን ሲሉ ጠቁመዋል።

#ጠንካራ አንድነት ለዘላቂ ልማት #31ኛ
ምንጭ የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ነው

ጠንካራ ኢንስፔክሸን ፣ለጠንካራ ፓርቲ ግንባታ ሥራ ወሳኝ ነዉ!! በምስራቅ ጉራጌ ዞን  በዛሬው ዕለት የክልሉ ብልጸግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን የተወጣጣ ልዑክ ቡድን ቡታጅራ...
25/06/2024

ጠንካራ ኢንስፔክሸን ፣ለጠንካራ ፓርቲ ግንባታ ሥራ ወሳኝ ነዉ!!

በምስራቅ ጉራጌ ዞን በዛሬው ዕለት የክልሉ ብልጸግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን የተወጣጣ ልዑክ ቡድን ቡታጅራ ገቡ።

ሰኔ 18/2016 ዓ.ም እንሴኖ

የኢንስፔክሽን ቡድኑ ከዞን እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ ድገፍና ክትትል የሚያደርግ ይሆናል ።

የኢንስፔክሽን ቲሙ በተለይም የፓርቲ አደረጃጀቶች ፤የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብና መመሪያዎች፤ቃላ ጉቀዔዎች፣ሪፖርቶች ተከትለው የፓርቲ ሥራዎችን በመመልከትና በማረጋገጥ ድጋፍ ለመስጠት ጠንካራ ፓርቲ ለመገንባት መሆኑ ተገልፃል ።

ከምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን መምሪያ የፌስቡክ ገፅ የተወሰደ

ሰኔ 17/2016 ዓ.ም ቡታጅራ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመስቃንና ማረቆ  ምርጫ ክልል ቁጥር 2  በ6ኛው ዙር ሀገራዊና ክልላዊ የድጋሚና  ምርጫ በስኬት በመጠናቀቁ የምስጋና መልዕክት ተላ...
24/06/2024

ሰኔ 17/2016 ዓ.ም ቡታጅራ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመስቃንና ማረቆ ምርጫ ክልል ቁጥር 2 በ6ኛው ዙር ሀገራዊና ክልላዊ የድጋሚና ምርጫ በስኬት በመጠናቀቁ የምስጋና መልዕክት ተላለፈ!!!
=========
ሰኔ 17/2016 ዓ.ም እንሴኖ

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን የመስቃንና ማረቆ ምርጫ ክልል ቁጥር 2 የተደረገው ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረጉ የምስራቅ መስቃን ወረዳ፣ መስቃን ወረዳ እና የእንሴኖ ከተማ መላው ነዋሪ ማህበረሰብ፣

የዞን፣ የወረዳና ከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ የፖሊስ አባላት፣ የክልሉ አድማ ብተና፣ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት የየአካባቢው የሚሊሻ አካላት እንዲሁም በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡኢ፣ የደ/ሶዶ፣ የቡታጅራ መዋቅሮች እና ከአጎራባች ዞኖች የስልጤ፣ የሃላባና የጉራጌ ዞኖች ለመጡት የፖሊስ አባላት፣ በምርጫው ለተሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ተወዳዳሪዎች ለምርጫ አስፈፃሚዎች በሙሉ

ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና በህዝቡ ዘንድ ታዓማኒነት እንዲኖረው ላበረከታችሁት ታላቅ አስተዋጽዖ በራሴና በዞኑ አስተዳደር ስም የከበረ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ሲሉ ትናግረዋል።

አቶ ሙስጠፋ ሀሰን አክለውም ለሁሉም አካላት በምርጫው ላሳየው ተሳትፎ በቀጣይም በልማትና በመልካም አስተዳደር ስራዎች እንድትደግሙት በዚህ አጋጣሚ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ ብለዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ መሰለ ጫካ እንዲሁ የመስቃንና ማረቆ ምርጫ ክልል 2 የተደረገው ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረጉ አካላት የምስጋና መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

አቶ መሰለ ጫካ በመልዕክታቸው እንዳሉት ለክልላችን፣ ለዞናችን፣ ለምስራቅ መስቃን ወረዳና ለእንሴኖ ከተማ መራጩ ህዝብ በሙሉ ዳግም እንድናገለግላችሁ ፓርቲያችን ስለመረጣችሁ እጅግ አድርጌ በራሴና በምስራቅ ጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ስም አመስግናለሁ ሲሉ ተናግረዋል።

በተጨማሪም አቶ መሰለ ጫካ እንዳሉት ከህዝቡ የሚነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለሰ ከየትኛው ጊዜ በበለጠ ዳግም ቃል እንገባለን ሲሉ ጠቁመዋል።

ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።

በመስቃንና ማረቆ ቁጥር ሁለተኛ የምርጫ ክልል  ዙር ቀሪ  የድጋሚ ምርጫ ጊዜያዊ ውጤቶች ይፋ እየተደረጉ ነው!!!           እንሴኖ፤ሰኔ 17/2016 በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተካሄደ...
24/06/2024

በመስቃንና ማረቆ ቁጥር ሁለተኛ የምርጫ ክልል ዙር ቀሪ የድጋሚ ምርጫ ጊዜያዊ ውጤቶች ይፋ እየተደረጉ ነው!!!

እንሴኖ፤ሰኔ 17/2016
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተካሄደው ቀሪ እና የድጋሚ ምርጫ ድምጽ የተሰጠባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ ውጤቶችን ይፋ እያደረጉ ይገኛል።

በክልሉ በመስቃን እና ማረቆ ምርጫ ክልል 2 ጣቢያዎች የምርጫ ውጤቶች ይፋ ተደርገዋል።

6ኛው ዙር ቀሪ እና የድጋሚ ምርጫ የተካሄደባቸው 169 የመስቃን ማረቆ የምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ ቆጠራው ውጤቶች በየምርጫ ጣቢያዎቹ ተለጥፈዋል።

2 የተፎካካሪ ፓርቲዎች እና 9 የግል እጩዎች የቀረቡበት የምርጫ ሂደቱ በትላንትናው እለት ከንጋት 12 ሰአት እስከ ምሽት 12 ሰአት ተካሂዶ በሰላም መጠናቀቁ ይታወሳል።

ለክልል ምክር ቤት እና ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚወክላቸውን የመረጡ የህብረተሰብ ክፍሎችም በየምርጫ ጣቢያዎቻቸው ውጤቶችን እየተመለከቱ ይገኛል።

እንሴኖ፤ሰኔ/16/2016 ዓ.ም         የሳምንቱ ዋና ዋና አርዕስተ ዜናዎች➡ 1445ኛው የኢድ አል አድሃ አረፋ በአል በተለያዩ ሃይማኖታዊ ክዋኔዎች በድምቀት ተከብሮ ውሏል።➡ የበረካ በ...
23/06/2024

እንሴኖ፤ሰኔ/16/2016 ዓ.ም

የሳምንቱ ዋና ዋና አርዕስተ ዜናዎች

➡ 1445ኛው የኢድ አል አድሃ አረፋ በአል በተለያዩ ሃይማኖታዊ ክዋኔዎች በድምቀት ተከብሮ ውሏል።
➡ የበረካ በጎ አድራጎት ማህበር በእንሴኖ ከተማ ለሚገኙ ለ25 ለሚሆኑ አቅመ ደካሞች ቤት ለቤት በመዞር የቅርጫ ስጋ አከፋፈለ።

➡ ፅዱ እንሴኖ ከተማን ለመገንባት ሳምንታዊው የዕለተ ረቡዕ የፅዳት ዘመቻ በተጠናከረ መልኩ እየተሰራበት ይገኛል።

ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ፅዱና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ እንሴኖን ለመፍጠር የከተማዋ ወጣቾች ሚና የጎላ እንደሆነ ተገለፀ!

➡ በመስቃን እና ማረቆ ምርጫ ክልል ሁለት ስድስተኛ ዙር ሃገራዊ የማሟያ ምርጫ በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ አሰጣጥ መርሃ ግብር ሲካሄድ ቆይቶ በሰላም ተጠናቀቀ!!!

ዘገባው የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት ነው

በመስቃን እና ማረቆ ምርጫ ክልል ሁለት በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ አሰጣጥ መርሃ ግብር ተጠናቀቀ!!!=============  በመስቃን እና ማረቆ ምርጫ ክልል ሁለት በዛሬው ዕለት በሁሉም ...
23/06/2024

በመስቃን እና ማረቆ ምርጫ ክልል ሁለት በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ አሰጣጥ መርሃ ግብር ተጠናቀቀ!!!
=============
በመስቃን እና ማረቆ ምርጫ ክልል ሁለት በዛሬው ዕለት በሁሉም የምርጫጣቢያዎች የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ በሰላም ተጠናቋል።

በእንሴኖ ከተማ በ9 የምርጫ ጣቢያዎች ከንጋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የምርጫ ሂደት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት መላው የከተማዋ ነዋሪዎች ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ድምፅ ሰጥተዋል።

ዜጎች ያለምንም ስጋት የፈለጉትን የፖለቲካ ፓርቲና የግል እጩዎችን መርጠዋል።

የምርጫ ስርዓቱ ፍፁም ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ተከናውኗል።

በዚህም የድምፅ አሰጣጥ መርሃ ግብሩ በመጠናቀቁ በእያንዳንዱ የምርጫ ጣቢያ ታዛቢዎች በተገኙበት ድምፅ የመቁጠር ስራ እየተካሄደ ይገኛል።

በምርጫ ጣቢያዎች የተሰበሰቡ ድምፆች ወደ ማዕከል የሚላክ ሲሆን

በቀጣይ ጊዜያት ምርጫ ቦርዱ በሚያወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ውጤቶች ይፋ እንደሚደረግ ተገልጿል።

ዘገባው የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት ነው

በመስቃንና ማረቆ ቁጥር ሁለት ምርጫ ክልል ከጠዋቱ 12 ጀምሮ መራጮች ድምፅ በመስጠት ላይ ይገኛሉ።============እንሴኖ፤ሰኔ/16/2016 ዓ.ምበመስቃናና ማረቆ ቁጥር ሁለት የምርጫ ክልል...
23/06/2024

በመስቃንና ማረቆ ቁጥር ሁለት ምርጫ ክልል ከጠዋቱ 12 ጀምሮ መራጮች ድምፅ በመስጠት ላይ ይገኛሉ።
============
እንሴኖ፤ሰኔ/16/2016 ዓ.ም

በመስቃናና ማረቆ ቁጥር ሁለት የምርጫ ክልል በእንሴኖ ከተማ በሚገኙ በአስሩም የምርጫ ጣቢያዎች የከተማዋ ነዋሪዎች ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ድምፅ በመስጠት ላይ ይገኛል።

በከተማው ውስጥ በሚገኙ በእያንዳንዱ የምርጫ ጣቢያዎች 5 አስፈፃሚዎች የተዘጋጁ ሲሆን በአማካይ በአንድ የምርጫ ጣቢያ እስከ 750 መራጮች ድምፅ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በምርጫ ጣቢያዎቹ 3 የተፎካካሪ ፓርቲዎች እና 6 የግል እጩዎች የቀረቡ ሲሆን የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በምርጫ ሂደቱ በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

ዘገባው የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት ነው

አስቸኳይ ማሳሰቢያ!👉 ነገ ከቡታጅራ -ኢንሴኖ እና ከቡታጅራ-ቆሼ በተመላሽም በተመሣሣይ እንዲሁም አልፈው የሚሄዱ ተሽከርካሪዎች ምርጫ በሚከናወንባቸው ቦታዎች መቆምም (መጫንም ሆነ ማውረድ) የ...
22/06/2024

አስቸኳይ ማሳሰቢያ!
👉 ነገ ከቡታጅራ -ኢንሴኖ እና ከቡታጅራ-ቆሼ በተመላሽም በተመሣሣይ እንዲሁም አልፈው የሚሄዱ ተሽከርካሪዎች ምርጫ በሚከናወንባቸው ቦታዎች መቆምም (መጫንም ሆነ ማውረድ) የተከለከለ ነው።
# # # # # # # # # # # # # # # # # # # # # # #
በነገዉ እለት ሰኔ 16 ፣ 2016 ዓ,ም በማዕከላዊ ኢትዮጺያ ክልል በመስቃንና ማረቆ ምርጫ ጣቢያ ሁለት በድጋሚ የሚካሄደዉን 6ኛዉ ዙር ሃገራዊና ክልላዊ ምርጫ ምክንያት በማድረግ ነገ በተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ገደብ ተጥሏል ከመለስተኛ እስከ አነስተኛ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ፣ባለሶስት እግር ባጃጅና የሞተር ብስክሌት ከቡታጅራ -ኢንሴኖ እና ከቡታጅራ-ቆሼ በተመላሽም በተመሣሣይ እንዲሁም አልፈው የሚሄዱ ተሽከርካሪዎች መቆምም (መጫንም ሆነ ማውረድ) አይፈቀድላቸውም።

የፀጥታ ሃይሉ ለሚያደርገዉ ህግ የማስከበር ስራ የትራንስፖርት ክፍል ተባባሪ እንዲሆኑ ጠይቀዋል።

ስድስተኛ ዙር ለሚካሄደው ማሟያ ምርጫ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቁ ተገለፀ!!!===========እንሴኖ፤ሰኔ/15/2016 ዓ.ምበነገው ዕለት በመስቃንና ማረቆ ቁጥር ሁለት የምርጫ ክልል የ...
22/06/2024

ስድስተኛ ዙር ለሚካሄደው ማሟያ ምርጫ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቁ ተገለፀ!!!
===========
እንሴኖ፤ሰኔ/15/2016 ዓ.ም

በነገው ዕለት በመስቃንና ማረቆ ቁጥር ሁለት የምርጫ ክልል የሚካሄደውን ስድስተኛው ዙር የማሟያ ምርጫ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቁ ተገልጿል።

የምርጫ ሂደቱ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በሁሉም መስክ ሰፊ ስራዎች መሰራታቸው ታውቋል።

በተለይ ምርጫው ያለምንም የፀጥታ ችግርና ስጋት እንዲካሄድ በከተማው የሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች በተጠናከረ መልኩ እየተከናወኑ መሆኑ ተጠቁሟል።

በዚህም ምርጫው ፍትሃዊና ተዓማኒ እንዲሆን ነፃና ገለልተኛ ታዛቢዎችን በልዩ ሁኔታ ስልጠና እንዲወስዱ መደረጉም ተመላክቷል።

ስለሆነም ማህበረሰቡ ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ በምርጫው ተሳታፊ እንዲሆን ያስፈልጋል።

ሁለንተናዊ የዜጎች ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የህዝብ የነቃ ተሳትፎ እጅግ ወሳኝ ነው።

የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ የብሪክስ ፕላስ የከተሞች ህብረት የመስራችነት ፊርማ አኖሩ!!!=========እንሴኖ፤ሰኔ 14/2016 ዓ.ምአለም አቀፉ የብሪክስ ፕላስ አ...
21/06/2024

የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ የብሪክስ ፕላስ የከተሞች ህብረት የመስራችነት ፊርማ አኖሩ!!!
=========
እንሴኖ፤ሰኔ 14/2016 ዓ.ም

አለም አቀፉ የብሪክስ ፕላስ አባል ሀገራት የከተሞች ህብረት ጉባኤ ላይ የመስራችነት ፊርማ መፈራረማቸውን እና ትልቅ ተሞክሮ የሚለዋወጡበት እንደሚሆን ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

አለም አቀፍ የብሪክስ ፕላስ አባል ሀገራት የከተሞች ህብረት መስራች ጉባኤ በሩሲያ ካዛን ከተማ የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ የከበሩ አቶ አብዱ አህመድ እየተሳተፉ ይገኛል።

አቶ አብዱ አህመድ በፌስ ቡክ ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት አለም አቀፉ የብሪክስ ፕላስ አባል ሀገራት የከተሞች ህብረት መስራች ጉባኤ ትልቅ ልምድ ሼር የምናደርግበት ይሆናል ብለዋል።

በመድረኩም ውቢት ቡታጅራን ጨምሮ አራት (4) የኢትዮጲያ ከተሞች እና የኢትዮጲያ ከተሞች ህብረት ዋና ዳይሬክተር መስራች ጉባኤውን እየተሳተፉ እንደሆነ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ጉባኤውም በተለያዩ ሁነቶች ለተወሰኑ ቀናት የሚቀጥል እንደሚሆን ከስፍራው ሆነው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ሲል የዘገበው የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ነው

አለም አቀፍ የብሪክስ ፕላስ አባል ሀገራት የከተሞች ህብረት መስራች ጉባኤ መካሄድ ጀመረ!!!========== እንሴኖ፤ ሰኔ/14/2016በምስረታ ጉባኤው  የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አ...
21/06/2024

አለም አቀፍ የብሪክስ ፕላስ አባል ሀገራት የከተሞች ህብረት መስራች ጉባኤ መካሄድ ጀመረ!!!
==========
እንሴኖ፤ ሰኔ/14/2016
በምስረታ ጉባኤው የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ ሩስያ ካዛን ከተማ ላይ እየተካሄደ በሚገኘው ታሪካዊው የመስራች ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ ይገኛሉ።

በምስረታ ጉባኤው ላይ ከኢትዮጵያ ቡታጅራ ከተማን ጨምሮ 4 ከተሞች ጥሪ በተደረገላቸው መሰረት እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ልህቀትና ብልፅግና ለሀገራችን ኢትዮጵያ!!

ዘገባው የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ነው

በእንሴኖ ከተማ ልማትና መልካም አስተዳደር ጉዳይ ላይ ከወጣቶች ጋር የምክክር መድረክ ተካሄደ!!!=============እንሴኖ፤ሰኔ 12/2016 ዓ.ምለአንድ ሀገር የዕድገት ጉዞ መሰረታዊው ጉዳ...
19/06/2024

በእንሴኖ ከተማ ልማትና መልካም አስተዳደር ጉዳይ ላይ ከወጣቶች ጋር የምክክር መድረክ ተካሄደ!!!
=============
እንሴኖ፤ሰኔ 12/2016 ዓ.ም
ለአንድ ሀገር የዕድገት ጉዞ መሰረታዊው ጉዳይ የወጣቱ ክፍል ጠንክሮ መስራትና አምራች ሃይል መሆን ቀዳሚው ተግባር እንደሆነ ይታመናል።

ለዚህም የተለያዩ ሃገራት በኢኮኖሚ የፈረጠሙ፣የበለፀጉና ለዜጎቻቸው ምቹ ለመሆን የወጣቱን ሃይል አጋዥ በማድረግ በተጠናከረ መልኩ ይሰሩበታል።

ለዚህም ሀገራችን ኢትዮጵያ ወጣቱን በማሳተፍ ከጫፍ እስከ ጫፍ ዘርፈ ብዙ ችግሮችን ለመፍታት ርብርብ እየተደረገ ነው።

በዛሬው ዕለት እንሴኖ ከተማ አስተዳደር ከተማዋን መለወጥና ልማቷን ማፋጠንና ፅዱ እንድትሆን ለማድረግ እንዲያስችል ከወጣቶች ጋር የምክክር መድረክ ተካሄዷል።

በበጎ አድራጎት፣በልማትና በሰላም ጉዳይ ከተማ አስተዳደሩን ሲያግዙ የነበሩ ወጣቶችን በማመስገን እውቅና ሰጥቷል።

ወጣቶቹ ከተማው በሚያከናውናቸው የልማት ስራዎች አቅም በመሆን ድጋፍ ሲያደርጉ እንደነበር የተገለፀ ሲሆን

ይህን መሰረት በማድረግ ማመስገን እውቅናና መስጠቱ ተገቢ መሆኑ ተነግሯል።

በቀጣይ ጊዜያት እንሴኖን በሁሉም መስክ እንድትለማና እንድትበለፅግ የወጣቱ ተሳትፎ እጅግ ወሳኝ ስለመሆኑ ተመላክቷል።

በተለይ በከተማው በሚሰሩ ስራዎች የመጀመሪያው ተቆርቋሪ ሊሆን ይገባልም ተብሏል።

በዋናነት በሳምንት ዕለተ ረቡዕ በሚካሄዱ የፅዳት ፕሮግራም ላይ በመሳተፍ ማህበረሰቡ ባህል አድርጎ እንዲይዝ ምሳሌ መሆን እንዳለበትም ተመላክቷል።

በመጪው የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ በመሰማራት አቅመ ደካማ ግለሰቦችን መርዳትና ማገዝ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።

በመድረኩ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሃሰን፣የዞኑ የብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት የፖለቲካና ሪዮተ አለም ዘርፍ ሃላፊ አቶ መሰረት ሺፋና የአደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ሃሰን ከድር፣የእንሴኖ ከተማ ከንቲባ አቶ ዘይኑ ቃሲም፣የምስራቅ ጉራጌ ዞን የሴቶችና ህፃናት መምሪያ ኃላፊ ወ/ሪት ሲቲ ሙስጠፋ እንዲሁም የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር የብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ምክትል ኃላፊ እና የፖለቲካና ሪዮተ አለም ዘርፍ ሃላፊ አቶ ሸምሱ አደም ተገኝተዋል።

 #31ኛ ሳምንት የፅዳት ዘመቻ #እንሴኖ፣ሰኔ 12/2016 ዓ.ምዕለተ ረቡዕ የእንሴኖ ከተማ የፅዳት ቀን ለ31ኛ ጊዜ ቀጥሎ በዛሬው ዕለትም የከተማው ወጣቶች የተሳተፉበት ፅዳት ተከናውኗል።ፅዱ...
19/06/2024

#31ኛ ሳምንት የፅዳት ዘመቻ #
እንሴኖ፣ሰኔ 12/2016 ዓ.ም
ዕለተ ረቡዕ የእንሴኖ ከተማ የፅዳት ቀን ለ31ኛ ጊዜ ቀጥሎ በዛሬው ዕለትም የከተማው ወጣቶች የተሳተፉበት ፅዳት ተከናውኗል።

ፅዱ እንሴኖ ለመፍጠር፣
ለኑሮ ምቹ እንሴኖን ለመስራት
ለንግድና ኢንቨስትመንት ተመራጭ እንሴኖን ለመገንባት
የሁሉም ርብርብ፣ጥረት፣እገዛና ድጋፍ እጅጉን ይፈለጋል።

# እንሴኖን እናልማ #

የመሰረተ ልማት ስራዎችን ጀምሮ ማጠናቀቅ ለህዝብ ግልጋሎት እንዲውሉ ማድረግ የብልፅግና መርህ መሆኑ ተገለጸ!!!============እንሴኖ ሰኔ 12/2016 ዓ.ምየምስራቅ መስቃን ወረዳ ከተመሰ...
19/06/2024

የመሰረተ ልማት ስራዎችን ጀምሮ ማጠናቀቅ ለህዝብ ግልጋሎት እንዲውሉ ማድረግ የብልፅግና መርህ መሆኑ ተገለጸ!!!
============
እንሴኖ ሰኔ 12/2016 ዓ.ም

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ከተመሰረተ ወዲህ ለማህበረሰቡ የአገልግሎት አሰጣጥን ተደራሽ ለማድረግ ብዙ ችግሮችን በመጋፈጥ እየሰራ ይገኛል።

በተለይ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ህዝብ በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴዎቹ የሚጎበኛቸው እንደሆኑ ይታመናል።

በዚህም ከለውጡ ማግስት ትኩረት ከተደረገባቸው ዋነኛ ጉዳዮች ተቋማትን ከስር ጀምሮ በሁሉም ዘርፍ በማነፅ በአገልግሎት አስምጣጣቸው ምቹ እንዲሆኑ በተጠናከረ መልኩ እየተሰራበት ይገኛል።

ይህን መሰረት በማድረግ የምስራቅ መስቃን ወረዳ ከተመሰረተ ቅርብ አመታት ቢሆንም የሚስተዋሉ ችግሮችን በመጋፈጥ በዛሬው ዕለት እጅግ ባማረና በደመቀ ሁኔታ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ስራዎችን አስመርቋል።

የመንገድና የውሃ ፕሮጀክት፣የመሰብሰቢያ አዳራሽ ግንባታ፣የወረዳው የፍትህ ተቋምን በመገንባት ለምረቃ እንዲበቁ አድርጓል።

ለህዝብ ጠቃሚ የሆኑ ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ አጠናቅቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ የብልፅግና ፓርቲ መርህና ዓላማ አድርጎ የሚያከናውናቸው ቀዳሚ ተግባራት እንደሆኑ ማሳያ ነው።

ለዚህም የተጀመሩ ልማቶችን ለማስቀጠልና ተጠቃሚነታችንን ለማረጋገጥ ከመንግስትና ፓርቲ ጎን በመሰለፍ የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ዕድገት ማፋጠን እንደሚገባ ተጠቁሟል።

ስለሆነም የህዝብ ለህዝብ ትስስር፣አብሮነትና አንድነት እንዲቀጥል ለማድረግ እንዲሁም የበለፀገች ሀገር ለትውልድ ለማስረከብ ምርጫ መሰረታዊ ጉዳይ ነውና በመጪው ሰኔ 16 በሚካሄደው ምርጫ በመሳተፍ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ያስፈልጋልም ተብሏል።

የተመረቁ የካፒታል ፕሮጀክቶችን ተጀምረው ለህዝብ ግልጋሎት ጥቅም እንዲውሉ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

ለዚህም መንግስት የተጣለበትን የህዝብ አደራ ለመወጣት መሰል ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ የህዝቡን እንግልት ለመቅረፍ ወደ ስራ እያስገባ ይገኛል ያሉ ሲሆን በቀጣይ ጊዜያት የህዝቡ ከፓርቲው ጎን በመቆም መንግስት ሀገርን ለማሻገር የወጠናቸውን በጎ አላማዎችን ለማሳካት አጋዥ መሆን እንዳለበት ተመላክቷል።


በመጨረሻም በዝግጅቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ስዎች የተሳተፉበት ፕሮግራም እንዲሰካ ወጣቶች፣እናቶች፣አባቶች፣የሀገር ሽማግሌዎች፣የፀጥታ አካላት እንዲሁም የከተማው አጠቃላይ ነዋሪ ከእንግዳ አቀባበል ጀምሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ ላበረከቱት አስተዋጽኦ የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር የምስጋና መልዕክቱን ይገልፃል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ በካፒታል ፕሮጀክት የተገነቡ የመሰረተ ልማት ስራዎችን እያስመረቀ ይገኛል!!!============እንሴኔ፡ሰኔ 11/2016 ዓ.ምየምስራቅ መስቃን ወረዳ ከተመሰረተ ቅርብ ...
18/06/2024

የምስራቅ መስቃን ወረዳ በካፒታል ፕሮጀክት የተገነቡ የመሰረተ ልማት ስራዎችን እያስመረቀ ይገኛል!!!
============
እንሴኔ፡ሰኔ 11/2016 ዓ.ም

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ከተመሰረተ ቅርብ አመታት ቢሆንም ወረዳው የነበረቡበትን ዘርፈ ብዙ ችግሮችን ተቋቁሞ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ስራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል።

በተለይ የሃሙስ ገበያ ከተማ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ፣የዉሃ ፕሮጀክት መንገድ፣መብራት፣ዲቾችና የፍትህ ተቋምን በመገንባት በዛሬው ዕለት እያስመረቀ ይገኛል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ እና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ዲላሞ ኦቶሬ፣የክልሉ ረዳት የመንግስት ተጠሪዎች አቶ ይሁን አሰፋና ይግለጡ አብዛ፣የምስራቅ ጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ደሱ አበጋዝ ፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ እንዳልካቸው ጌታቸው፣የምስራቅ መስቃን ወረዳ አስተዳዳሪ ጀማል አወል፣የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዘይኑ ቃሲም፣የምስራቅ ስልጢ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሳሎ ፋኔ የስልጢ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ከድር ደድገባ፣የቅበት ከተማ አስተዳደር የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ከድር ሁሴን፣የክልሉ፣የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር አመራሮችና የስራ ኃላፊዎች ሌሎች እንግዶችና ጥሪ የተደረገላቸዉ አካላት በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።

የምረቃ ዝግጅቱን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አወል አስተዳደር የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር በማድረግ ያስጀመሩ ሲሆን

ወረዳው ላይ የሚስተዋሉ የልማት ችግሮችን ለመቅረፍ በሰፊው ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

በዋናነት የዛሬዎቹ የልማት ስራዎች መገንባት በመንግስትና በህዝብ ተሳትፎ የተሰሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

በአሁን ሰዓት የዞን ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣በዞኑ ውስጥ የሚገኙ መዋቅር አስተባባሪዎች በመገኘት የተሰሩ የልማት ስራዎችን በአካል በመገኘት እየተመለከቱ ይገኛል።

ዝርዝር መረጃውን የምናደርሳችሁ ይሆናል።

በረካ የበጎ አድራጎት ማህበር ለአቅመ ደካሞች የአረፋ በዓልን ምክንያት በማድረግ ድጋፍ አድርገ!!!===========እንሴኖ፤ሰኔ/,10/2016 ዓ.ምበረካ የበጎ አድራጎት ማህበር ለ25 ለአቅመ...
17/06/2024

በረካ የበጎ አድራጎት ማህበር ለአቅመ ደካሞች የአረፋ በዓልን ምክንያት በማድረግ ድጋፍ አድርገ!!!
===========
እንሴኖ፤ሰኔ/,10/2016 ዓ.ም

በረካ የበጎ አድራጎት ማህበር ለ25 ለአቅመ ደካሞች ዘንድሮ 1445ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘውን የአረፋ በዓልን ምክንያት በማድረግ የቅርጫ ስጋ ድጋፍ አድርጓል።

ማህበሩ በተለያየ ጊዜ ከሃገር ውስጥ እና ውጪ በሚያገኘው ድጋፍ ችግረኛ እና ጣሪ ለሌላቸው አቅመ ደካማ ወገኖችን የቁሳቁስ ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል።

ዘንድሮም የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓልን ምክንያት በማድረግ በእንሴኖ ከተማ ለሚገኙ አቅመ ደካማ ወገኖች ቤት ለቤት በመዞር ደጋፍ አድርጓል።

የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ኤልያስ ከድር እንደገለፁት፡-በዚህ የኢድ አል አድሃ አረፋ በአል ህዝበ ሙስሊሙ በደስታ በሚያሳልፍበት ወቅት ምንም የሚላስ የሚቀመስ የሌላቸው ወገኖችን መርዳትና መደገፍ ግዴታ አድርገን መያዝ አለብን ያሉ ሲሆን

የአንዳችን ለሌላኛው ማዘን፣መደገፍና መርዳት ያስፈልጋልና በጎ ተግባር ላይ ትኩረት ሰጥተን ልንሰራ ይገባል ብለዋል።

የማህበሩ ዋና ሰብሳቢ አቶ ፈቱ መሃመድ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ሁሉም ካለው በመቀነስ መጠጊያ የሌላቸው፣መጠለያ ያጡ፣በረሃብ የሚሰቀዩ ወገኖቻችንን አለንላችሁ ልንላቸው ይገባል ሲሉ ገልፀዋል።

በምስራቅ መስቃን ወረዳ በነገዉ እለት ለሚካሄደዉ አጠቃላይ የልማት ፕሮጄክቶች  የምረቃ ፕሮግራም የቅድመ ዝግጁት ስራዎች እየተከናወነ ይገኛል!!!============እንሴኖ/ሰኔ 10/2016 ዓ...
17/06/2024

በምስራቅ መስቃን ወረዳ በነገዉ እለት ለሚካሄደዉ አጠቃላይ የልማት ፕሮጄክቶች የምረቃ ፕሮግራም የቅድመ ዝግጁት ስራዎች እየተከናወነ ይገኛል!!!
============
እንሴኖ/ሰኔ 10/2016 ዓ,ም በምስራቅ መስቃን ወረዳ በነገዉ እለት ለሚካሄደዉ አጠቃላይ የልማት ፕሮጄክቶች የምረቃ ፕሮግራም የቅድመ ዝግጁት ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።

የምረቃ ፕሮግራሙን አስመልክቶ የበቼ ቀበሌና የእንሴኖ ከተማ ወጣቶች አዲስ በተገነባዉ የወረዳዉ የፍርድ ቤትና አቃቤ ህግ ህንፃ ግቢ በመገኘት የፅዳትና ለፕሮግራሙ የሚሆን የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን እያከናወኑ ይገኛሉ።

በምረቃ ፕሮግራሙ ላይ የዞን፣ የወረዳና ሌሎች የአጎራባች መዋቅር እንግዶችና ጥሪ የተደረገላቸዉ አካላት ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ዘገባው የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ነው

1445ኛ የኢድ አል አድሃ አረፋ በአል በእንሴኖ ከተማ በደማቅ ተከበረ!!!=============እንሴኖ፡ሰኔ/9/2016 ዓ.ም1445ኛ የኢድ አል አድሃ አረፋ በአል በእንሴኖ ከተማ ትልቁ መስጂ...
16/06/2024

1445ኛ የኢድ አል አድሃ አረፋ በአል በእንሴኖ ከተማ በደማቅ ተከበረ!!!
=============
እንሴኖ፡ሰኔ/9/2016 ዓ.ም

1445ኛ የኢድ አል አድሃ አረፋ በአል በእንሴኖ ከተማ ትልቁ መስጂድ በደማቅ ተከብሯል።

ኢድ አል አድሃ አረፋ በዓል የመስዋዕትነት ቀን፣በኢስላማዊ አስተምህሮቱ አቅሙ በፈቀደው ኡዱህያን በማድረግ የግዴታውን እንዲያደርስ ለሚስኪኖችም እንዲያጋራ በጥብቅ የታዘዘ ስለመሆኑ ተገልጿል።

ዛሬ የምናከብረው 1445ኛው የዒድ አል አድሃ አረፋ በዓል ለህዝባችን የሰላም፣የአብሮነት፣የአንድነት እና የመተሳሰብ በዓል እንዲሆን ተጠቁሟል።

ስለሆነም የአላህ እዝነት፣የፍጡሩ በእርሱ ትዕዛዝ ስር መሆኑን ተረድቶ የኢስማኤል መስዋዕትነትን በበግ መቀየሩ የእዝነቱ ጥግ የታየበት ነውና

ህዝበ ሙስሊሙ እርስ በእርሱ በመተዛዘን ካለው ላይ ለአቅመ ደካማው በማጋራት በዓሉን በእኩል ማሳለፍ እንዳለበት ተነግሯል።

በዚህም የቀደመው ማህበራዊ መስተጋብራችን በማስቀጠል ብዝሃነታችንን የማክበርና የማስተናገድ የአብሮነት መንገድ ከመሆኑ ባሻገር፣ የወንድም/እህትማማችነትን እሴትን ለማጠናከር አጋዥ በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንዲሚገባ ተመላክቷል።

"የአረፋ ገባተውታን የፍቸ ቅረረውታን ኸማ ድመቆ" እንኳን ለሴቶች አረፋ በዓል በሰላም አደረሳቹ!!!===========እንሴኖ፤ሰኔ/8/2016 ዓ.ም እንደ አረፋ ምሽት እንደ ኢድ ጠዋቱን እመሩ...
15/06/2024

"የአረፋ ገባተውታን የፍቸ ቅረረውታን ኸማ ድመቆ" እንኳን ለሴቶች አረፋ በዓል በሰላም አደረሳቹ!!!
===========
እንሴኖ፤ሰኔ/8/2016 ዓ.ም

እንደ አረፋ ምሽት እንደ ኢድ ጠዋቱን እመሩ በዚህ ምርቃት የሚታወቀው የሴቶች አረፋ ዛሬ በመስቃን ወረዳ በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ድምቀት ይከበራል።

በዙልሂጃ በ9ኛዉ ቀን (አረፋ) ሁሉም ሁጃጆች በሙሉ አርዱል አረፋ ላይ ዉቁፍ ለማድረግ ሲሄዱ ሀጅ የማያደርጉ የመካ ወንዶችም ለመኻደም ይሄዳሉ።

በዛን ጊዜ ሀረሙ በጠቅላላ ባዶ ሲሆን ቀኑን ሙሉ ሀረሙ የሴቶች ብቻ እስኪመስል ድረስ በሴቶች ይጥለቀለቅ ነበር፣ የማፍጠሪያ ምግብም አዘጋጅተዉ የመካ ሴቶች ናቸዉ ቀኑን እስከ ምሽት ድረስ ሀረሙን ሞልተዉ ካዕባዉን ከበዉ በኢባዳ ስለሚያሳልፉ የሴቶች የመካ አረፋ የሚል ስያሜ ተሠጠዉ።

ያን (ባህል) በየሀገሩ እየመጣ በተለያየ አከባበር የሴቶች አረፋ በሚል ስያሜ ይከበራል።

ህዚህም ወረዳችን ላይ የእናቶች ዝግጅት ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል።

እናቶች ቆጮ ከመፋቅ እስከ መጋገር፣ ቅቤ በማዘጋጀት፣ሚጥሚጣ በመውቀጥና ጎመን በመቀቀል ትኩረት ሰጥተው ሲሰሩ ሴት ልጃ ገረዶች ደግሞ የመኖሪያ ቤቶችን በማስዋብ፣ የመመገቢያ ቁሶችን በማፅዳት፣ የቤተሰቡን አልባሳት ሁሉ በማጠብና ሌሎች ለበዓሉ የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችን በሚያሟሉ ስራዎች ላይ ይጠመዳሉ፡፡

የሴቶች አረፋ ከዋናው አረፋ በዓል በዋዜማው የሚከበር በዓል ሲሆን በዚህ ዕለት ሴቶች የበዓሉ ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን የሚያረጋግጡበት ቀን ነው፡፡

በዚሁ እለት ሴቶች የጎመን ክትፎ እና ዝሟሙጃት በማዘጋጀት እንዲሁም የቅቤ ቡና በማፍላት ቤተ-ዘመድና ጎረቤት ጠርተው በፍቅር የሚገባበዙበት፣የሚደሰቱበትና ''የአረፋ ገባተውታን የፍቸ ቅረረውታን ኸማ ድመቆ''ብለው እየተመራረቁ የሚያሳልፍት ደማቅ በዓል ነው፡፡
አቤም አሰላነ

ዘገባው የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ነው

ለ1445ኛ ጊዜ የሚከበረው የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓልን ምክንያት በማድረግ የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ዘይኑ ቃሲም  የእንኳን አደረሳችሁ  መልዕክት አስተላለፉ!!!====...
15/06/2024

ለ1445ኛ ጊዜ የሚከበረው የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓልን ምክንያት በማድረግ የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ዘይኑ ቃሲም የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ!!!
===================
እንሴኖ፣ሰኔ 8/2016 ዓ.ም

የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ዘይኑ ቃሲም ለ1445ኛ ጊዜ የሚከበረውን የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለመላው የእስልምና ዕምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓል "የመስዋዕትነት በዓል′′
የመላው ዓለም ሙስሊሞች በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ስፍራ ተሰጥቶት የሚከበር እንደሆነ ገልፀዋል።

አረፋ የሐጅ ስነስርአት ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ ምዕመኑ ለፈጣሪው ፀሎትን የሚያደርስበትም ነው ብለዋል።

በዛሬዋ ዕለት አላህ ከፀጋዎቼ በላይ ብሎ ያለውን ለሙስሊሙ እምነት ተከታይ ፀጋን የቸረበት ሲሆን

ዲኑን(ሃይማኖታችሁን) ምሉእ(ሞላሁላችሁ) ፀጋዬንም በናንተ ላይ ፈፀምኩ ብሎ ያወጀበት በዚህ ቀን እንደሆነም ተናግረዋል።

ነብዩላህ ኢብራሂም በእርጅና ዘመናቸው የወለዱትን አንድ ልጃቸው እንዲያርዱ ከፈጣሪያቸው በታዘዙ ጊዜ ትዕዛዙን ያከበሩበት

ልጅ ኢስማኤልም አንድም ሳያመነታ ከአላህ ዘንድ ታዘህ ከሆነ አድርግ የተባልከውን ፈፅም በማለት ለመታረድ ዝግጁ የሆኑ ሲሆን

አላህ ታዛዥ መሆናቸው አስተውሎ እስማኤልን በበግ እንደቀየረላቸው አውስተዋል።

ስለሆነም የእርስ በእርሳችን መከባበር፤መተዛዘን፤መደጋገፍና መተባበር እጅጉን አስፈላጊ መሆኑንም አመላክተዋል።

በተለይ ዕለቱ አቅመ ደካሞችን የምናስጠጋበት፣ካለን ላይ የምናካፍልበትና ኢድ አል አድሃ አረፋ በአል ሁሉም አማኝ ተደስቶ ቀኑን እንዲያሳልፍ ነውና ኡድህያ እርድ ስንፈፅም ምንም መጠጊያ የሌላቸው ቤተሰቦችን ለእነሱም በማጋራት አብሮነታችንን እናጎልብት ብለዋል።

በዚህም የተለመደመዋደዳችንአንድነታችን፣ሰላማዊ የመቻቻል ዕሴታችንን በማስጠበቅ በዓሉን እንድናከብር መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

በድጋሚ እንኳን ለ1445ኛ ኢድ አልአድሃ አረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ
ኢድ ሙባረክ

በእንሴኖ ከተማ የኢድ-አል አድሃ ዓረፋ በዓል የቅዳሜ ገበያ                     እንሴኖ ሰኔ/ 8/2016በእንሴኖ ከተማ የ1445ኛውን የኢድ-አል አደሃ አረፋ በዓል የቅዳሜ ገበያ ...
15/06/2024

በእንሴኖ ከተማ የኢድ-አል አድሃ ዓረፋ በዓል የቅዳሜ ገበያ
እንሴኖ ሰኔ/ 8/2016
በእንሴኖ ከተማ የ1445ኛውን የኢድ-አል አደሃ አረፋ በዓል የቅዳሜ ገበያ ድባብ ሰላማዊ ሆኖ እየተካሄደ ይገኛል።

ዕለተ ቅዳሜ ሰፊ የግብይትና ሽያጭ የሚከናወንበት ሲሆን
ከተለያዩ የአጎራባች አካባቢ ህዝቦች ተመራጭና
ሁሉም አይነት ግብይይት የሚከናወንበትም ነው።

በዚህም የዘንድሮ የአረፋ በዓልን ምክንያት በማድረግ ህዝቡ ሞቅ ደመቅ ባለ መልኩ እየተገበያየ ይገኛል።

እንኳን ለኢድ-አል አደሃ የአረፋ በዓል
በሰላም አደረሳችሁ።
#ኢድ ሙባረክ #

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን የአቅመ ደካማ ቤት በማደስ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አስጀመሩ!!!===============እንሴኖ፤ሰኔ  07/2016 ዓ.ም ዋና አ...
14/06/2024

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን የአቅመ ደካማ ቤት በማደስ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አስጀመሩ!!!
===============
እንሴኖ፤ሰኔ 07/2016 ዓ.ም

ዋና አስተዳዳሪው አቶ ሙስጠፋ ሀሰን የ2016/17 ዞናዊ የክረምት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ዛሬ በቡታጅራ ከተማ አስጀምረዋል።

በዕለቱ የ2016 ዓ.ም የበጋ ወራት የወጣቶች የበጎ ፍቃድ አገልግሎት መዝጊያና የክረምት ወራት የመክፈቻ ፕሮግራም በቡታጅራ ከተማ ተካሄዷል ።

በዞኑ በክረምት ወራት የወጣቶች የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በ13 የትኩረት መስኮች በተጠናከረ መልኩ እንደሚሰራ ተገልጿል።

በዋናነት በትምህርት ፣ጤና ፣የአካባቢ ጥበቃ ፣ማህበራዊ ድጋፍና እንክብካቤና በሌሎች ተግባራት ለማከናወንና መታቀዱን የመምሪያው ምክትል ኃላፊና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሀመድ አወል ዕቅዱን ባቀረቡበት ወቅት ገልፀዋል።

በክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፍቃድ አገልግሎት ለአዳዲስ ቤቶችን ለመስራትና ለመጠገን መታቀዱ ተገጠቁሟል።

ከ11.9 ችግኝ በላይ በመትከል በአካባቢው ጥበቃ ስራዎች ከ5 መቶ 70 ዩኒት ደም በላይ ለመሰብሰብ ይሰራል ብለዋል።

በዚህም 91 ሺ በላይ ወጣቶች የሚሳተፉና 284 ሺ በላይ የማህበረሰብ ክፍሎች ተጠቃሚነት የሚሆኑበት ስራ ለመስራት መታቀዱ ተገልጿል።

በሚሰሩት የበጎ ፍቃድ አገልግሎቶች ከ71 ሚሊየነን ብር በላይ ከመንግስትና ከማህበረሰቡ ካዝና ይወጣ የሚችል ገንዘቡ ለማዳን ዕቅድ መታቀዱን ተገልጿል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን የበጎ ፍቃድ ተግባራት በሁሉም መዋቅሮችን በየደረጃ አጠናክሮ መስራት እንደሚጠበቅ ገልፀዋል።

ማህበረሰባችን ካስተባበር በርካታ ስራዎችን መስራት እንችላለን በመሆኑም አቅመ ደካሞች የመረዳት ተግባር በተገቢው መምራት እንደሚገባ ጠይቀዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ረዳት የመንግስት ተጠሪና የፓለቲካ ሪዮዐተዓለም ዘርፍ ኃላፊና የበጎ ፍቃድ አብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ መሰረት ሽፊ በበኩላቸው የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራዎች ማህበረሰብ በማስተባበል በክረምት ወራት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በተሻለ መልኩ ለመፈፀም ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ወጣቶ ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አህመድ ኑሪ በከረምት ወራት በጎ ፋቃድ አገልግሎት በ13 የትኩረት መስኮች ወጣቶችን በማስተባር ማህበረሰቡን አገልግሎት በመስጠት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ይሰራል ብለዋል።

ለዚህም ወጣቶች በክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ላይ በስፋት እንዲሳተፉ በማድረግ የታቀደው እቅድ ማሳካት እንደሚቻል ገልፀዋል።

በመድረኩ በበጋ ወራት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት አፈፃፀምና በቀጣይ የክረምት ወራት ዕቅድ ላይ ከተሰብሳቢዎቹ ሃሳብ አስተያየት በመስጠት የንቅናቄ መድረኩ ተጠናቋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን ፣የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ እንዳልካቸው ጌታቸው፣የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ መሰለ ጫካ ፣የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ ደሱ አበጋዝ፣ የረዳት የመንግስት ተጠሪና የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሀሰን ከድር ፣ረዳት የመንግስት ተጠሪና የበጎ ፍቃድ አብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ መሰረት ሽፈ፣የምስራቅ ጉራጌ ዞን ወጣቶ ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አህመድ ኑሪን ጨምሮ የዞን ፣የወረዳና የከተማ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የዘገበው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።

Address

Butajira

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዩኒት Enseno City Government Communication Unit:

Videos

Share