26/04/2024
We have the power, the energy and the perfect reasons to win life!!
SDL- Strives to provide you truthfull information.
We have the power, the energy and the perfect reasons to win life!!
ጥምቀት 2016 ዓ.ም
መልካም በዓል!!
የህፃናት መራመጃ ጋሪ (ጂሬሎ) ለልጆች ጠቃሚ ነው ወይስ ጎጂ?
ብዙ ወላጆች ላይ ከሚፈጠሩ ጥያቄዎች መካከል አንዱ የህፃናት መራመጃ ጋሪ (ጂሬሎ) ለልጆች ጠቃሚ ነው ወይስ ጎጂ የሚለው ነው። ታዲያ ለዚሁ ጥያቄ መልስ ምን እንደሆነ አብረን እናያለን።
በተለያዩ ሆስፒታሎች የህፃናት መራመጃ ጋሪ በሚጠቀሙ እና በማይጠቀሙ ህፃናት ላይ የተደረገው ጥናት ይህንን ውጤት አስቀምጧል
የህፃናት መራመጃ ጋሪ ጥቅሞቹ
1. ህፃናት መቆምና መራመድ እንዴት እንደሆነ ያውቃሉ
2. ያለማንም እርዳታ እንደልባቸው በመዟዟር ይጫወታሉ
3. ከጎናቸው ወላጆች በነፃነት ሌላ ስራን ማከናወን ይችላሉ
4. ጋሪው የተለያዩ ማጫወቻዎች ስላሉት ልጆችን ያዝናናል
የህፃናት መራመጃ ጋሪ ጉዳቶቹ
1. አብዛኛውን ጊዜ ከሚጠበቅባቸው ፍጥነት በላይ ስለሚሄዱ ለተለያዩ አደጋዎች ይጋለጣሉ። ለምሳሌ
- ከተጋጩ ጭንቅላታቸው ላይ እቃ ሊወድቅባቸው እና ጉዳት ሊደርስባቸው ይችላል
- የምግብ ማብሰያ እሳት ጋር ሊደርሱና የቃጠሎ አደጋ ወይም ትኩስ የሆነ ነገር ሊደፋባቸው ይችላል
- በቀላሉ ባእድ የሆኑ ነገሮችን ስለሚያገኙ እና በመብላት ለትንታ ወይም ለመታነቅ አደጋ ሊጋለጡ ይችላሉ
- ከደረጃ ላይ በመገልበጥ ወይም በራሳቸው ሲጫወቱ በመገልበጥ የጭንቅላት እና የአንገት እስከሞት ሊያደርስ የሚችል ጉዳት ሊደርስባቸው ይችላል።
2. በራሳቸው ጊዜ እና ጥረት ለመገላበጥ ለመቀመጥ ለመዳህ ለመቆም እንዲሁም ለመራመድ የሚጠቅሟቸውን ጡንቻዎች እንዲዳከሙ በማድረግ የእንቅስቃሴ እድገታቸውን ያዘገየዋል
3. ጋሪ ውስጥ ሆነው ሲራመዱ እግራቸውን ማየት ስለማይችሉ የአይን እይታ እና እርምጃ ጥምረትን ያዛባል
4. የወገብ እና ጉልበት መገጣጠሚያዎችን የሰውነት ክብደት የመሸከም ብቃትን ይቀንሳል
5. ራሳቸውን ችለው ሚዛናቸውን ጠብቀው እንዳይቆሙ እና እንዳይራመዱ ያሰንፋቸዋል
6. የጀርባ አከርካሪ አጥነታቸው ላይ ሚዛኑን ያልጠበቀ ጫና ስለሚፈጥር ካደጉ በኋላ ለወገብ ለህመም ሊያጋልጣቸው ይችላል
ስለዚህ በአጠቃላይ በተደረገው ጥናት መሰረት ውጤቱ የሚያሳየው የህፃናት መራመጃ ጋሪ (ጂሬሎ) ጥቅሞቹ እንዳሉ ሆነው ጉዳቶቹ ግን ያመዝናሉ ማለት ነው።
ዶ/ር ዮናታን ከተማ: በቅዱስ ፓውሎስ ሆስፒታል የህፃናት ቀዶ ህክምና ሬዚደንት ሀኪም።
በፓኔሲያ ሆስፒታል ከአንድ የ40 አመት እድሜ ካላቸው 2094 የሃሞት ጠጠር በቀዶ ህክምና ሊወገድ ችሏል። ይህንን ያክል ቁጥር ያለው ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሃሞት ጠጠር በህክምና እንደ ሃገር ተወግዶ አያውቅም።
በቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ሃኪም ዶ/ር Tsegaye Chebo እና የቀዶ ህክምና ቡድን ግን ይህ ተችሏል።
ADEEROO, RABBI JANNATAAN HAA QANANIISU😭
የክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ (አዴሮ) 1ኛ ዓመት የሙት መታሰቢያ ቀን በድሬደዋ ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች በመከበር ላይ ይገኛል።
Sirni yaadannoo Doctora kabajaa Artist Alii Birraa magaalaa Dirree dhawaa Parkii Alii Birraatti gaggeefamaa jira.
Abbaa keenyaaf rabbiin jannataan haa qananiisu.🤲
To think too much is a disease.
~Fyodor Dostoyevsky
(Book: Notes from Underground https://amzn.to/454ouxg)
(Art: 'The Weight Of Thought' sculpture by Thomas Lerooy)
የልጇ አባት ነፍሰ ጡር እያለች ጥሏት የጠፋባት እናት ልጄን አልፈልግም እያለች ነው!!😭😭😭😭
በምስሉ ላይ የምትመለከቷት እህታችን ስታረግዝ ፤ ያስረገዛት ወንድ ጥሏት ጠፍቷል
እህታችንም በሰርጀሪ ልጇን በፖውሎስ ሆስፒታል በሰላም ተገላግላለች። ነገርን ግን አንድ ወር ሀኪም ቤት ከቆየች በኃላ ልጇን መንገድ ላይ ለመጣል ስትል ሰዎች ደርሰው ይዘዋታል። በአቅራቢያዋ ወደሚገኝ የሴቶች ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ፅ/ቤትም ወስደዋታል።
እናት በስነ ልቦና በጣም የተጎዳች ሲሆን ልጄን ጡት ማጥባትም ሆነ መያዝ አልፈልግም ብላለች።
የህፃኑን የርሃብ ሲቃ ቸተመለከተች በሴቶች ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ፅ/ቤት የምትስራ አንዲት እናት ህፃኑን ጡት አጥብታ ለጊዜውም ቢሆን ከርሃብ ሲቃ ታድጋዋለች።
ቀጣይ የህፃኑ እጣ ፈንታ ምን ሊሆን ይችላል? ማን ምን ማድረግ አለበት?? ህፃኑን ለጨከነበት የእናት አንጀት መልሶ መስጠት ተገቢ ሊሆን ይችል ይሆን??
ሃሳባችሁን አጋሩ!!
የእነዚህ 3 ህፃናት ልጆችች ቤተሰቦች ልጆቻቸውን ማግኘት ይችሉ ዘንድ share ኘድርጉላቸው!!
* እናታቸው ወይንም
* አባታቸው ነኝ አልያም አውቃቸዋለሁ የሚል ወገን እንዲያገኛቸው አድርጉ!!
ከትላንትና ወዲያ በአዲስ አበባ በአውቶብስ ተራ አካባቢ አንዲት ሴት እነዚህ ሶሶት ልጆች ይዛ ስትሄድ ፖሊስ ጠርጥሮ የያዛት ሲሆን እሷም ልጆቹን ከቡታጅራ ከተማ ነው ያመጣዋቸው ብላለች። እንዲሁም አሳዳጊ ነኝ ብላለች!!
ነገር ግን ፖሊስ ሴትየዋን በመጠራጠሩ ፖሊስ ጣቢያ አስገብቷታል።
የእነዚህ 3 ልጆች ቤተሰብነኝ የሚል አካል ካለ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ማመልከት እንደሚችል እና ስለ ህፃናቱ ተጨማሪ መረጃ ያለው ማንኛውም ግለሰብ ለመምሪያው መረጃ በመስጠት እንዲተባበር የአዲስ አበባ ፖሊስ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡
8.2 ኪ.ሜ ርዝመት እና ከ10 እስከ 40 ሜትር የጎን ስፋት ያለውን የኮዬ ፈጬ ኮንዶሚኒየም ቤቶች የውስጥ ለውስጥ የመንገድ ግንባታ አጠናቅቀን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል።
ህዳር 2013 ዓ.ም የመንገዱን ግንባታ ባስጀመርንበት ወቅት የአካባቢው መህበረሰብ እና የጋራ መኖርያ ቤት ባለዕድለኞች “ቶሎ ገንቡልን” ሲል ጋቢ አልብሰው አደራ ሰጥተውን ነበር።
እኛም መንገዱ በአካባቢው ያለውን የመንገድ መሰረተ ልማት እጥረት የሚቀርፍ እና የጋራ መኖርያ ቤት ባለዕድለኞች ወደ ቤታቸው ሲገቡ የሚሰጣቸውን ፋይዳ በመገንዘብ ግንባታውን ባስጀመርንበት ወቅት በገባነው ቃል መሰረት በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቅቀን ዛሬ ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል።
በዚህ በጀት አመት የያዝናቸው ትልልቅ ተሻጋሪ ድልድዮች እና የመንገድ ፕሮጀክቶችም እየተጠናቀቁ ነው።
Mayor Adanech Abiebie.
በፊፋ የደረጃ ስንጠረዥ ምርጥ 10 የአፍሪካ ብሄራዊ ቡድኖች የትኞቹ ናቸው?
ፊፋ የሰኔ ወር የሀገራት የደረጃ ሰንጠረዥን ይፋ ያደረገ ሲሆን፤ አርጀንቲነ ከዓለም ቀዳሚ ናት። በሰኔ ወር የደረጃ ሰንጠረዥ ሞሮኮ ከአፍሪካ 1ኛ ከዓለም 13ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
ኢትዮጵያ በፊፋ የሰኔ ወር የደረጃ ሰንጠረዥ ከዓለም 143ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠች ሲሆን፤ ከአፍሪካ ደግሞ 42ኛ ደረጃን ይዛለችይዛለች።
Gargaarsa lamummaa
Artist rakkoo fayyaa cimaaf saaxilamee Hospitaala jogla magaala harar ciisaa jira birmannaa ummataa barbaada .
Abrahiim adam yeroo ammaa haala ulfaataa keessa jiraachuu fi Wal'aansa fooyya'aa yoo argate garuu dhibee isa mudate kana dandamachuu ni danda'a .
"Artist Abrahiim adam guyyaa tokkollee ofiif jiraatee hin beeku. Amma isa dhukkubsatee haala kana keessa jira.arts abrahiim adam bara jireenyasaa artii Oromoof jiraate malee qabeenya dhuunfaasaa horachuu irratti hin xiyyeeffanne .
Abrahiinm Adam Artistii jabaa yeroo dheeraaf ogummaa isaatiin ummatasaaf sagalee ta'aa turedha.
Artist Abrahiim adam haa gargaaru akkasuma du'aa'ii haa goonuf.
ዛሬ የኢቢሲ አዲሱ ኮምፕሌክስ ምረቃ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ መልኩ ታይተዋል
የቀድሞዋ አፈጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም መረጃ በማጥፋታቸው የራያ አላማጣ የማንነት ጥያቄ እንዲጓተት ምክንያት ሆኗል ተባለ
የራያ አላማጣ ማህበረሰብ የማንነት ጥያቄ እልባት እንዲሰጠው በሚል ለፌዴሬሽን ምክር ቤት የላከው ደብዳቤ በቀድሞ የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም አማካኝነት እንዲጠፋ ተደርጓል ተብሏል።
የአላማጣ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ሞገስ እያሱ፤ የራያ አላማጣ የማንነት እና የበጀት ጥያቄ ከ2011 ጀምሮ ለፌደሬሽን ምክርቤት ሲቀርብ እንደነበር ገልጸው፤ “የወቅቱ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ኬሪያ ኢብራሂም የማንነት ጥያቄውን ለማዳፈን በማሰብ ለምክር ቤቱ የገባው መረጃ እንዲጠፋ አድርገዋል፡፡” ሲሉ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።
በዚህም ለምክር ቤቱ የገባው መረጃ እንዲጠፋ መደረጉ፤ የራያ አላማጣ ማህበረሰብ የማንነት ጥያቄ መፍትሄ ሳያገኝ ለአራት ዓመታት እንዲጓተት ምክንያት ሆኗል ነው ያሉት።
“አፈጉባኤዋ ስልጣን ከለቀቁ በኋላ በገባው ደብዳቤ መሰረት የማንነት ጥያቄው መልስ እንዲያገኝ የፌዴሬሽን ምክር ቤቱን ስንጠይቅ፤ መረጃው መጥፋቱ ስለተነገረን ቅጂውን በድጋሜ ለማስገባት ተገደናል፡፡” ሲሉ ጠቁመዋል።
ባሳለፍነው ሰኞ ሰኔ 12/2015 የራያ አላማጣ እና ባላ አካባቢዎች በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ ከ150 ሺሕ በላይ የሕዝብ ፊርማ ተሰብስቦ ለፌደሬሽን ምክር ቤት መግባቱን የጠቀሱት ኃላፊው፤ “ዋና ዓላማውም የማንነት ጥያቄያችን ተፈቶ ወደ አማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን እንድንካተትና በጀቱ በትግራይ ክልል ሳይሆን በአማራ ክልል በኩል እንዲለቀቅልን ነው፡፡” ብለዋል።
አክለውም፤ በተለይ የፌደራል ተቋማት በአካባቢው የተሟላ አገልግሎት እየሰጡ ባለመሆኑ፣ ከባንክ፣ ከኤሌክትሪክና ከኢንተርኔት ጋር ያለው አገልግሎት በቶሎ ምላሽ ሊስጠው እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ለዚህም አራት ዓመታትን ያስቆጠረው የራያ አላማጣ የማንነት እና የበጀት ጥያቄ መልስ እንዲያገኝ ኮሚቴ ተቋቁሞ፤ ሰኞ ሰኔ 12/2015 ለፌድሬሽን ምክር ቤት መግባቱ ነው የተገለጸው።
ሕወሓት ለራያ እና አላማጣ አካባቢዎች አመራር መድቧል በሚል የሚነሳውን ጉዳይ በተመለከተም መድቧል ከተባለበት ጊዜ ጀምሮ አምስት አመራሮችን የቀያየረ መሆኑን ጠቁመው፤ “ወደ ራያ እና አላማጣ ግን ሊመጡ አይችሉም፡፡” ሲሉ ተናግረዋል።
ራያ አላማጣ ለኹለት ዓመታት ያለ በጀት መቆየቱን የገለጹት ኃላፊው፤ የማንነት ጥያቄው እና ለኹለት ዓመት የተቋረጠው በጀት በአስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጠው ህዝቡ በተደጋጋሚ በመጠየቅ ላይ መሆኑን ጠቁመዋል።
አዲስ ማለዳ በጉዳዩ ላይ ከፌደሬሽን ምክር ቤት ፅሕፈት ቤት ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት ጥረት ብታደርግም ሳይሳካ ቀርቷል።
በተያያዘም፤ በዛሬው ዕለት የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች ''መንግሥት የማንነት ጥያቄቸውን ሕጋዊ እንዲያደርግላቸው'' በሰላማዊ ሰልፍ የጠየቁ ሲሆን፤ ነዋሪዎቹ በሰላማዊ ሰልፉ “አማራ ነን እንጂ አማራ እንሁን አላልንም”፣ “የፌደራል መንግሥት ተቋማት ዲስትሪክት ወደ ሰሜን ወሎ ዞን ይዛወሩልን”ና ሌሎች የተለያዩ መፈክሮችን ማሰማታቸውን የሰሜን ወሎ ዞን ኮሙኒኬሽን አስታውቋል።
🇺🇸
ዛሬ በኒውዮርክ
ድምፃዊ ጎሳዬ እና ቴዎድሮስ ታደሰ
ይሄ ነገር ዓለምን እያነነጋገረ ነው
በዓለም ላይ ያሉ ዜና አውታሮች እየዘገቡት ነው
ለሀበሻ ስትነግረው ግን:-
* ከኛ ህይወት ጋር ምን ያገናኘዋል😎
* ኑሮ መሮናል😎
* ኑሮ ተወዶብናል😎
* ቲክ ቶክ ታብ ታብ አድርጉልኝ😎
ይልሀል::
እነዚህ 5 በዓለም ላይ የናጠጡ ሀብታሞች ናቸው እነዚህ ሀብታም ሰዎች ከብዙ ዓመት በፊት በፈረንጆቹ አቆጣጠር April 15, 1912 ገደማ 2,240 ሰዎች ይዛ ስትጏዝ የነበረውን በአትላንቲስ ባህር የሰመጠችውን የታይታንክ መርከብ ፍርሽራሽ ለማየት ነበር በአትላንቲስ ውቂያኖስ ባህር ለእያንዳንደቸው 250 ሺህ ዶላር ወደ ብር ሲመነዘር በባንክ ወደ 13 ሚሊዮን 739 ሺህ ከ34 ሳንቲም ሲሆን ይህን ሁሉ ሚሊዮን ብር ከፈለው ነበር የታይታኒክ መርከብ ለማየት በአስጏብኚ ሰርጎ ገብ መርከብ ወደ ባህር ውስጥ የገቡት። ነገር ግን ከገቡ በኃላ ድምፃቸው ጠፍቷል አሁን እነዚህ ሰዎች የገቡበት ለመፈለገ ከተለያዩ የዓለም ሃገራት የጥልቅዘፋቂዎች እየመጡ እየፍለጏቸው ሲሆን እነሆ ድምፃቸው ከጠፋ ብዙ ስአታትን ወስዷል የሚተነፍሱበትን የኦክስጅን መጠን እንዳያልቅ ተፈርቷል::
እነዚህ ሰዎች በህይወት ይኖሩ ይሆን ወይንስ እነሱም ልክ እንደ ታይታኒክ መርከብ ሰምጠው ይቀሩ ይሆን ተብሎ ዓለም እየትነጋገረበት ይገኛል::
13 ሚሊዮን 739 ሺህ ከ34 ሳንቲም ከፍለው ራሳቸው ላይ ችግር መፍጠራቸውም አነጋጋሪ ሆኗል::
በረከት ገበሬዋ ለአባቶች ቀን ያስተልለፈችውን ግጥም ብዙ ሰው እያነጋገረ ነው
ቪዲዮውን እነሆ
እሷ ቪዲዮውን ከቲክ ቶክ ላይ አጥፍታዋለች
*****"መልዓከ ነህ ሉሲፈር" **
ሰው ብቻ አይደለህም ከአፈር ወጥተህ ለአፈር
"መልዓከ ነህ ሉሲፈር" ክብር ማንነትህ በዓመጽ የሚታፈር
የማትንበረከክ የማትርመጠመጥ
ከባለጌ ዙፋን በርጩማን የምትመርጥ
ለባህር ሰርጓጅ ያለ ሙሴ በትር
በትዕግስት ብቻ ባህር የምትመትር
ካዘልከኝ ጀምሮ እንኮኮ ጫንቃህ ላይ
ከፍታን እንጂ ዝቅታን አላይ
እንደ ንስር በረርኩ እንደ እንቁ አበራሁ
የገዛ ክንፎቼን እንደ ዳንቴል ሰራሁ
በእርግጥ ደሃ ነበርኩ የነጣ የጠራ
ከጦር ሜዳ ይልቅ ገበያ የሚያስፈራ
ቤዛ ባታወርሰኝ አወረስከኝ ትዕግስት
ለወደፊት ህልም እንድኖር በጽናት
አባ ብርሃኔ ነህ አባ የምስራቅ በር
ገበና ሸሻጊ እንደ ካባ ገበር
አባቴ ባትሆን ይጸጽተኝ ነበር
ወደ አውሮፓ ሃገራት እልካለሁ በሚል ግለሰቦችን ሲያጭበረብር የነበረው ሰው መሰወሩ ተነገረ።
ሲሳይ አበበ ማስረሻ ይባላል በአዲስ አበባ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወደ አውሮፖ እልካለው በማለት ከ150 የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች እስከ 150 ሺህ የኢትዮጵያ ብር በመውስድ ተሰውሯል።
በ15 ቀን ውስጥ አውሮፖ (ሩማንያ ) እወስዳችዋለው ብሎ በህጋዊ መንገድ ቢሮ ከፍቶ ብዙ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ቢሮ ሲሄዱ ግን ቢሮውን ዘግቶ መጥፋቱ ተሰምቷል። ገንዘብ የተበሉት ወጣቶቹ ወደ 150 የሚሆኑ ሲሆኑ ነገር ግን 60 የሚሆኑ ወጣቶች ወደ ፖሊስ በመሄድ ክስ መስርተዋል።
የህንድ መንግስት በምሰጠዉ Indian Council for Cultural Relations (ICCR) Scholarship ትምህርታችን እየተከታተልን ያለን የሶስተኛ ዲግሪ (PhD) ተማሪዎች እና ቤተሰቦቻችን ችግር ላይ ወድቀናል።
እንደምታወቀው በህንድ ሀገር በICCR scholarship ትምህርታቸውን ለሚከታተሉ ለዩኒቨርሲቲ መምህራን ፥በህንድ መንግስት የሚከፈለው ክፍያ በቂ ካለመሆኑ የተነሳ በአዋጅ ቁጥር 1152/2011 እና በተሻሻለው የከፍተኛ ትምህርት የስኮላርሺፕ ማስፈፀሚያ መመርያ ቁጥር 916/2014 በእትዮጵያ ትምህርት ሚኒስቴር በኩል በድጎማ መልክ በየወሩ $218 ዶላሪ ለረጅም አመት ሲከፈል እንደነበረ ይታወቃል። እኛ ለትምህርት ወደ ህንድ ሀገር ሲንመጣ ፥ ይህንን ታሳቢ በማድረግ ፥ ከሚናገኘው 218 ዶላር ለቤተሰቦቻችን እንደምንዶጉማቸዉ አስበን ነበር።
ነገር ግን ለረጅም ዓመት ሲከፈል የቆየዉን ክፍያ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ July 2022/23 ጀምሮ ከላይ የተጠቀሰው መመሪያ ሥራ ላይ እያለ jully ክፍያዉን እንዲቋረጥ ተደርጓል። በመሆኑም የተወሰነዉ ዉሳኔ ወቅቱን ያላገናዘበ በመሆኑ በተደጋጋሚ ለትምህርት ሚንስቴር ከነማስረጃ አቅርበን ለማሳመን ብንሞክርም የሚሰማን አጥተናል።
አንድ የዩኒቨርሲቲ ማስተርስ ያለው መምህር ዉጭ ሀገር ለሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት ሲሄድ ከሚያገኘው 9,300ብር ወራዊ ደሞዝ ግማሽ ማለትም 4,550 ብር አከባቢ ይከፈለዋል። የኑሮው ሁኔታ በተወደደበት በዚህ ዘመን እንኳንስ ግማሽ ደሞሚዝ ሙሉዉንም እያያገኙ መኖር አልተቻለም።
ወደ ህንድ ሀገር ከመሄዳችን በፊት በህንድ መንግስት የሚከፈለው በቂ ስላልሆነ በእትዮጵያ ትምህርት ሚንስቴር በኩል በድጎማ መልክ የሚከፌለዉን ገንዘብ ታሳቢ በማድረግ ከሚከፈለን $218 ዶላር ቤተሰቦቻችን ለመዶገም እና አብቃቅተን ለመማር አስበን ቢንመጣም እንኳንስ ለቤተሰቦቻችን ለራሳችን መሆን አቅቶን ችግር ላይ ወድቀናል።
ስለሆነም የእትዮጵያ ትምህርት ሚንስቴር እንድያዉቅልን የሚንፈልገው ከሚከፈለው ግማሽ ወራዊ ደሞዎዝ ማለትም 4550 ብር ፥ የቤት ክራይ ከፍለን ፥ ለልጆች ትምህርት ቤት ወጪ ከፍለን ፥ እንዲሁም የተለያዩ ወጪዎችን ሸፍነን ቤተሰቦቻችን ማኖር አቅቶናል። ስለዚህ እኛም በሰዉ አገር ከሚከፈለን ትንሽ ብር ቆንጥሬን እየላክን ወይ ከትምርታችን ወይ ከቤተሰብ ሳንሆን መሀል ላይ ትምህርታችን ለማቋረጥ እየተገደድን ነዉ።
ስለሆነም የሚመለከተው አካል አፋጣኝ መልስ እንዲሰጠን በታላቅ ትህትና እንጠይቃለን።
ከሰላምታ ጋር
በህንድ ሀገር በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የምንገኝ ተማሪዎች!
5/10/2015
Arsenal had been top of the Premier League for 94% of the season 🤯
የዓለም የጤና ድርጅት ከ3 ዓመት በኃላ ኮቪድ-19 ዓለም አቀፍ አጣዳፊ የጤና ስጋት መሆን ማብቃቱን ይፋ አደረገ።
የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ከዚህ ቀደም አውጀውት የነበረው የኮቪድ-19 የምድራችን አጣዳፊ የጤና ስጋት አሁን ላይ ማብቃቱን አሳውቀዋል።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው ትላንት ለዚሁ ጉዳይ የተቋቋመው ኮሚቴ ለ15ኛ ጊዜ በመገናኘት ባደረገው ስብሰባ ወቅት ባቀረበው ምክረ ሃሳብ መሆኑን ዶ/ር ቴድሮስ ገልጸው በዚህም መሰረት የኮሚቴውን ምክረ ሃሳብ በመቀበል የኮቪድ-19 ዓለም አቀፍ አጣዳፊ የጤና ስጋትነት ማብቃቱን አውጀዋል።
ይህ ማለት ግን የኮቪድ-19 አብቅቷል ማለት እንዳልሆነ አስገንዝበዋል።
የዓለም ጤና ድርጅት እኤአ ጥር 20/2020 ላይ ነበር ኮቪድ-19 የዓለም አቀፍ የጤና ስጋት ብሎ ያወጀው።
ይኸው ወረርሽኝ በትንሹ 20 ሚሊዮን ሰዎችን ገድሏል (እንደ WHO መረጃ)፣ በርካቶችን ቤተሰብ አሳጥቷል ፤ የዓለምን ኢኮኖሚ እንዳልነበር አድርጓል።
ኢትዮጵያ ለውጭ ባለሀብቶች አምስት የባንክ ፈቃድ ልትሰጥ መሆኑ ተገለጸ!
ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በባንክ ዘርፍ ለመሰማራት ፍላጎት ላላቸው የውጭ ባለሀብቶች አምስት የሚደርሱ የባንክ ፈቃድ ለመስጠት ማቀዷ ተገለጸ፡፡
የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ሰለሞን ደስታ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ከሦስት እስከ አምስት ለሚደርሱ በኢትዮጵያ በባንክ ዘርፉ መሰማራት ለሚፈልጉ የውጭ ባለሀብቶች የባንክ ፈቃድ እንደሚሰጥ መናገራቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ ይህም የአገሪቱን የፋይናንስ ዘርፍ አገልግሎት ለውጭ ተፎካካሪዎች ክፍት ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል፡፡
እስካሁን የባንኩ ዘርፍ ለውጭ አገራት መዋዕለ ነዋይ አፍሳሾች ዝግ ሆኖ የቆየ ሲሆን፤ በቀጣይ አምስት ዓመታት ውስጥ ግን ለውጭ አገራት ተፎካካሪዎች ክፍት እንደሚደረግ ነው የተገለጸው፡፡
በተጨማሪም የውጭ ባለሀብቶች በኢንዱስትሪ ዘርፉም ከአገር ውስጥ ባለሀብቶች ጋር በጋራ የሚሰሩበት አማራጭ ሊኖር እንደሚችል በምክትል ገዥው በኩል ተጠቅሷል፡፡የውጭ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በተለይም በባንክ፣ በቴሌኮም፣ በትራንስፖርት እና አቬሽን ዘርፎች ለመሰማራት ፍላጎት ካሳዩ ቆይተዋል ተብሏል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ለውጭ ኢንቨስተሮች ዝግ ተደርገው የቆዩ ዘርፎች ክፍ እንደሚደረጉ ቃል የገቡ ሲሆን፤ የመጀመሪያው የውጭ ቴሌኮም ፈቃድ ማግኘቱም ይታወቃል፡፡በተጨማሪም የመንግሥት የልማት ድርጅት እና ብቸኛ የቴሌኮም ድርጅት ሆኖ የቆየውን የኢትዮ ቴሌኮም 45 በመቶ ድርሻ ለውጭ ባለሀብት በመሸጥ ሦስተኛ የውጭ ቴሌኮም ፈቃድ ለመስጠት ጨረታ መጀመሩ ተገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአህጉር አቀፍ ደረጃ እያስመዘገበ ያለው ስኬት ለሌሎች ተቋማትም ትምህርት የሚሰጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአህጉር አቀፍ ደረጃ እያስመዘገበ ያለው ስኬት ለሌሎች ተቋማትም ትምህርት የሚሰጥ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ ያስገነባውን ምዕራፍ ሁለት ስካይ ላይት ሆቴል መርቀው ከፍተዋል፡፡
መረሃ-ግብሩ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ን ጨምሮ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ ሚኒስትሮች፣ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ዲፕሎማቶች ታድመዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ አየር መንገዱ ደንበኞችን ከማጓጓዝ ባሻገር ምቹ ማረፊያ ጭምር እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል።
አየር መንገዱ በትውልድ ቅብብሎሽ አሁን በደረሰበት እድገት ከሀገር አልፎ ለአፍሪካ ኩራት ሆኗል ነው ያሉት ፡፡
ሌሎች ተቋማትም ከአየር መንገዱ ስኬት ልምድ በመውሰድ ከአገር ባሻገር በአፍሪካም ተወዳዳሪ ለመሆን መስራት አንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው፣ የምዕራፍ ሁለት ስካይ ላይት ሆቴል በአፍሪካ ከሚገኙ ሆቴሎች መካከል የሚጠቀስ ነው ብለዋል።
አየር መንገዱ በአቪዬሽን መስክ አሁን የደረሰበትን እድገት ከማስቀጠል ባሻገር አዲስ አበባን የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ ጭምር ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ ነው ብለዋል።
አየር መንገዱ ከምዕራፍ አንድ የስካይ ላይት ሆቴል በተጨማሪ ዛሬ ያስመረቀው ምዕራፍ ሁለት የስካይ ላይት ሆቴል አዲስ አበባን የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የሚከናወኑ ተግባራት አካል መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
አዲስ የተገነባው ምዕራፍ ሁለት ስካይ ላይት ሆቴል በ11 ሺህ 500 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ ሲሆን 651 የመኝታ ክፍሎች እንዳሉትም አብራርተዋል።
በተጨማሪም ዘመናዊ የስብሰባ አዳራሾች፣ የጤና ማዕከል፣ ምግብ ቤቶችና የመዝናኛ ስፍራዎችን አካቷል፡፡
የሆቴሉ ግንባታ የተከናወነው "አቪክ" በተሰኘ የቻይና ህንጻ ተቋራጭ መሆኑም ተመላክቷል፡፡
ባይ ባይ
አስታራቂ
በእውነት መንገድ
አለቀ
AB ትለያለህ!!
ታዋቂው የክላርኔት የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዋች፤ ዳዊት ፍሬው አረፈ
በቅርቡ ለሥራ ወደ ጣሊያን ሀገር የተጓዘው ክላርኔት ተጫዋች ሙዚቀኛ ዳዊት ፍሬው በተኛበት ክፍል ሞቶ ተገኘ።
Addaggeen maaf akkatti safuu dhabanii?
akkamitri addaa irraatti olchuu dadhabnaa!??
የዒድ አልፈጥር በዓል መቼ ነው ?
የፌዴራል ጠቅላይ ሼሪዓ ፍርድ ቤት ፥ የዒድ አልፈጥር በዓል ጨረቃ ዛሬ ሀሙስ ማታ ከታየች ነገ አርብ ፣ ካልታየች ደግሞ ቅዳሜ ይከበራል ሲል አሳውቋል።
ይህን ያሳወቀው ዛሬ በሰጠው መግለጫ ነው።
1 ሺህ 444ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል ፤ ለኢትዮጵያና ለመላው ዓለም ህብረተሰብ የሰላም፣ የደስታና የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞቱን የገለፀው ሼሪዓ ፍርድ ቤቱ ሙስሊሙ ህብረተሰብ በዓሉን ሲያከብር ያጡና የተቸገሩ ወገኖችን በማሰብና በመርዳት እንዲሆን ጥሪ አቅርቧል።
Haile Gebresilassie
Addis Ababa
Be the first to know and let us send you an email when SDL posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.
በረከት ገበሬዋ ለአባቶች ቀን ያስተልለፈችውን ግጥም ብዙ ሰው እያነጋገረ ነው ቪዲዮውን እነሆ እሷ ቪዲዮውን ከቲክ ቶክ ላይ አጥፍታዋለች *****"መልዓከ ነህ ሉሲፈር" ** ሰው ብቻ አይደለህም ከአፈር ወጥተህ ለአፈር "መልዓከ ነህ ሉሲፈር" ክብር ማንነትህ በዓመጽ የሚታፈር የማትንበረከክ የማትርመጠመጥ ከባለጌ ዙፋን በርጩማን የምትመርጥ ለባህር ሰርጓጅ ያለ ሙሴ በትር በትዕግስት ብቻ ባህር የምትመትር ካዘልከኝ ጀምሮ እንኮኮ ጫንቃህ ላይ ከፍታን እንጂ ዝቅታን አላይ እንደ ንስር በረርኩ እንደ እንቁ አበራሁ የገዛ ክንፎቼን እንደ ዳንቴል ሰራሁ በእርግጥ ደሃ ነበርኩ የነጣ የጠራ ከጦር ሜዳ ይልቅ ገበያ የሚያስፈራ ቤዛ ባታወርሰኝ አወረስከኝ ትዕግስት ለወደፊት ህልም እንድኖር በጽናት አባ ብርሃኔ ነህ አባ የምስራቅ በር ገበና ሸሻጊ እንደ ካባ ገበር አባቴ ባትሆን ይጸጽተኝ ነበር
በአሸባሪው የወያኔ ቡድን ወረራ ለበርካታ ወራት ግፍ ሲፈጸምባት የቆየችው የኮረም ከተማ ወደ ቀደመው ሰላማዊ እንቅስቃሴ እየተመለሰች መኾኑን ነዋሪዎች ለአሚኮ ተናግረዋል። የከተማው ነዋሪዎች እንደተናገሩት ባለፉት ዓመታት አሸባሪው የወያኔ ቡድን ጦርነት በመክፈቱ ምክንያት በኑሮ ውድነት ሲሰቃዩ መቆየታቸውንና በሰላም ወጥቶ መግባት የማይችሉበት ደረጃ ደርሰው እንደነበር ገልጸዋል። አሁን ላይ ኮረምና አካባቢው ላይ ሰላም በመስፈኑ በሰላም ወጥተው እየገቡ መኾናቸውን ነው የተናገሩት። ባለፉት ወራት ግብይት ተቋርጦ እንደነበር የገለጹት ነዋሪዎቹ አሁን ላይ ሰላማዊ በኾነ መንገድ ገበያ መጀመሩን ተናግረዋል። ለወገን ጦር ደጀን በመኾን ከአካባቢው የመንግሥት የፀጥታ መዋቅር ጋር ተቀናጅተው ለሰላም ዘብ እንደሚቆሙም ነዋሪዎቹ አረጋግጠዋል።
መሪዎቹ በለንደን...🚌 በንግስት ኤልዛቤት ዳግማዊት ስርዓተ ቀብር ወቅት የተለያዩ ሀገራት መሪዎች እና የሀገራት ተወካዮች #በአውቶብስ እንዲጓጓዙ ሲደረግ የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን በራሳቸው ጥይት መከላከያ ባላት " ዘ ቢስት " የተሰኘችው ሊሞዚን እንዲጓዙ መደረጉ መነጋገሪያ ሆኗል።
ጉቴሬዝ በኢትዮጵያ የተኩስ አቁም በአስቸኳይ ወደነበረበት እንዲመለስ አሳሰቡ የተመድ ዋና ፀሃፊ በኢትዮጵያ ዳግም ግጭት ዜና መደንገጣቸውን አስታውቀዋል በኢትዮጵያ ሁኔታ “የደነገጡት” የተመድ ዋና ጸሃፊ ጉቴሬዝ በኢትዮጵያ ተደርሶ የነበረው ተኩስ አቁም “በአስቸኳይ” ወደ ነበረበት እንዲመለስ አሳሰቡ፡፡
የኢትዮጵያን መዳከም የሚፈልጉ ታሪካዊ ጠላቶች ንብረት እንደሆነ የሚታመን አውሮፕላን ለአሸባሪው ህወሃት ድጋፍ ለማድረግ የኢትዮጵያን የአየር ክልል ጥሶ በመግባቱ በጀግናው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ተመትቶ ወድቋል።
ወጣቶች የኢትዮጵያን መጻኢ ተስፋ ለማበላሸት የሚሰሩ ሃይሎችን ሴራ በመታገልና አብሮነትን በማጽናት በአገር ግንባታ ሂደት ላይ ንቁ ተሳትፎ ሊያደርጉ ይገባል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጥሪ አቀረቡ።
የ22 አመቱ ኢትዮጵያዊው አጥቂ አቡበከር ናስር በዲኤስቲቪ ፕሪሚየርሺፕ ተጠባቂ ጨዋታ ማሜሎዲ ሰንዳውንስ ካይዘር ቺፍን 4-0 ባሸነፈበት ጨዋታ ላይ ተቀይሮ በመግባት የመጀመሪያ የሰንዳውንስ ጎሉን አስቆጥሯል።
ሰበር!! ቻይና PCL 191 የተሰኘ የባለስቲክ ሚሳኤል ጥቃት ወደ ታይዋን ሰነዘረች፡፡ በጥቃቱ ስለደረሰው ጉዳት እስካሁን ከታይዋን በኩል የተባለ ነገር የለም፡፡ አሮጊቷ ናንሲ ፔሎሲ ጭራው የሄደችው እሳት ታይዋንን መለብለብ ጀምሯል፡፡
#DrAbiyAhmed ዛሬ ከሰዓት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ አባላት ስብሰባ የተካሄደ ሲሆን በአጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ መክሯል። እንዲሁም የአረንጓዴ ዐሻራ ክንውን ያለበትን ደረጃ አንስቷል። በተጨማሪም የ2015 የበጀት ዓመት ዕቅድ የትኩረት አቅጣጫን መቃኘቱን የጠ/ሚ ፅ/ቤት አሳውቋል። ዶ/ር ዐቢይ ስብሰባውን በተመለከተ ፤" ባለፈው ዓመት የሚያበረታታ የወጪ ንግድ አፈጻጸም፣ ቀጥተኛ የውጭ ሙዓለ ነዋይ ፍሰት መጨመር ታይቷል። ባለፉት ሁለት ወራት የዋጋ ግሽበት መቀነስ፣ ከፍተኛ የአረንጓዴ ዐሻራ ክንውን፣ የበጎ ፈቃደኝነት ተግባራት፣ የሬሚታንስ ጭማሪ እና በቴክኖሎጂ የታገዘ የሥራ ክንውን የተመዘገቡበት እንደ ሆነ አረጋግጠናል። በዚህ ዓመት የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ መቀጠል በእጅጉ አስፈላጊ ነው። " ብለዋል።
የአዲስ አበባ መገናኛ ብዙሃን አዲስ ቴሌቭዥን ለተሻለ ጥራት በመስራት ላይ ይገኛል በመሆኑም በEutlesat 8 WB @west Frequency 12688 Polarization V Symbol rate 27500 ላይ በጥራት መከታተል ትችላላችሁ