Mujib Amino

Mujib Amino ስለፍትህ እንጮሀለን፣ ሠላምን እንሰብካለን፣ አንድነትንና መከባበርን እንሻለን!
(31)

አቢሲንያ ባንክ Bank of Abyssinia የተሰጠዉን ጊዜ በመጠቀም ይቅርታ ጠይቋልከአቢ ሲንያ ባንክ የስራ ኃላፊዎች ጋር በተደረገ ንግግ ር መሰረት የባንክ ሰራተኛዉ ላይ የዲሲፒሊን እርምጃ...
06/02/2024

አቢሲንያ ባንክ Bank of Abyssinia የተሰጠዉን ጊዜ በመጠቀም ይቅርታ ጠይቋል

ከአቢ ሲንያ ባንክ የስራ ኃላፊዎች ጋር በተደረገ ንግግ ር መሰረት የባንክ ሰራተኛዉ ላይ የዲሲፒሊን እርምጃ ተወስዷል።
••••••••••••••••••••••••••••••
Mujib Amino

የአቢ ሲንያ ባንክ አለምገና ቅርንጫፍ አከባቢ የተፈጸመዉ ኀይማኖታዊ ትንኮሳና ንቀት የተሞላበት ድርጊት ከባንኩ አሰራርና አላማ እንዲሁም ምንም አይነት መብትና ግዴታ ባልኖረበት ተጨባጭ ሁናቴ የተከናወነ የነዉር ድርጊትና ጥላቻ ሕዝባችንን ያስቆጠ በመሆኑ የአቢ ሲንያ ባንክ የስራ ኃላፊዎች ይቅርታ እንዲጠይቁና ድርጊቱን የፈጸመዉ ሰራተኛም እምርጃ እንዲወሰድ መጠየቃችን ይታወሳል።

ባለፉት ቀናት ከባንኩ የስራ ኃላፊዎችና ከሚምለከታቸዉ አካላት ጋር ንግግር ካደረግን ቡኃላ በዛሬው እለት የአቢሲንያ ባንክ ሕዝበ ሙስሊሙን ከፍ ያለ ይቅርታ ጠይቋል።

በድርጊቱ የተሳተፈዉን የባንኩ ስራተኛ ላይም የዲሲፒሊን እርምጃ መዉሰዱን በኦፊሲዬላዊ ገጹ ላይ ገልጿል።

የአቢ ሲንያ ባንክ የስራ ኃላፊዎች ጉዳዩን እልባት ለመስጠትና ከሕዝበ ሙስሊሙ ጋር ግንኙንታቸዉን ለማጠናከር የሄዱብትን መንገድ እያደነቀ፣ በሌሎች ጊዜያት መሰል ድርጊቶች እንዳይፈጸሙ ጥንቃቄ እንዲያደርግ እናሳስባለን። እናመሰግናለን።

 😭 "                               የወራቤ ዩኒቨርሲቲው መምህር                    ወላጅ አባት መ/ር አብዱልፈታ አሊከታች የምትመለከቱት ህፃን ፋሂም አብዱልፈታ...
05/02/2024

😭 "
የወራቤ ዩኒቨርሲቲው መምህር
ወላጅ አባት መ/ር አብዱልፈታ አሊ

ከታች የምትመለከቱት ህፃን ፋሂም አብዱልፈታ ይባላል ። ይህ ህፃን ልጅ በወራቤ ዩኒቨርሲቲ በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በህ/ሰብ ጤና ት/ክፍል ስር Epidemiology and biostat ኮርሶችን የሚያስተምር የወንድማችን መምህር አብዱልፈታ አሊ ልጅ ነው።

አብዱልፈታ ልጁ ታሞበት ከ1 ዓመት በላይ አዲስ አበባ ጥቁር አንበሳ እና ጳውሎስ ሆስፒታል በየሁለት ሳምንት እየተመላለሰ ለልጁ ደም እየተሰጠው የቆየ ቢሆንም አሁን ከአቅማቸው በላይ ስለሆነ ህንድ ሀገር ሄዶ እንዲታከም ሃኪሞቹ ወስነዋል 😪

ፋሂም አብዱልፈታ የአጥንት መቅኔው ካልተቀየረ ሁሌ እየደማ ደም እየሰጡት መኖር የማይቻልበት ደረጃ ደርሷል😪

አባት አብዱልፈታ በአቅሙ የሰው እጅ ሳይመለከት ብዙ ለፍቷል ደክሟል ። ነገር ግን ደከመ ገንዘብም አጠረው ! የእናንተን የደጋጎቹን ድጋፍ ጠይቋል

ህፃኑን ለማሳከም 48ሺ ዶላር ተጠይቋል።

እባካችሁ እንተጋገዝ 🤲

ህፃኑ በዚህ እድሜው ቀርቶ ትልቅ ሰው የማይችለው በሽታ ነው ። ነገር ግን ታክሞ መዳን ይችላል ።

#እኛም ፣ ልጆቻችንም ነገ ምን እንደሚገጥመን አናውቅምና እንረዳዳ!

መርዳት የምትፈልጉ ፦

ንግድ ባንክ
1000097649948 አብዱልፈታህ አሊ ዩሱፍ

ለበለጠ መረጃ +251920814604 ( ወላጅ አባት አብዱልፈታ)

🙏ሁላችሁም በያላችሁበት ዱዓ አድርጉለት🙏

#ሼር በማድረግ ለብዙ ደጋጎች መረጃው እናድርስ🙏

ለአቢሲንያ ባንክ Bank of Abyssinia የ 24 ሰዓታት ጊዜ ብቻ ሰጥተናል••••••••••••••••••••••••••••••የባንኩ የስራ አመራር የአቢሲንያ ባንክ አለምገና አከባቢ የቅርን...
05/02/2024

ለአቢሲንያ ባንክ Bank of Abyssinia የ 24 ሰዓታት ጊዜ ብቻ ሰጥተናል
••••••••••••••••••••••••••••••

የባንኩ የስራ አመራር የአቢሲንያ ባንክ አለምገና አከባቢ የቅርንጫፍ ኃላፊ የሆነው ግለሰብ ከባንኩ አሰራርና ከተሰጠዉ ኃላፊነት ውጪ በእምነት ላይ ያለዉን ጥላቻ ማሳየቱ ተገልጾ አስተዳደራዊ እርምጃ እንድትወስዱ አሳስበናል።

በሚቀጥሉት ተጨማሪ 24 ሰዐታት በግለሰቡ ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ የማትወስዱ ከሆነ ሙስሊም የባንክ ተጠቃሚዎች፣ ነጋዴዎች፣ ባለሀብቶች የባንክ ደብተራቸዉን ሰርዘዉ ገንዘቦቻቸዉን ወደሌሎች ባንኮች እንዲያዘዋዉሩ እንደምናደርግ በድጋሚ እናሳዉቃለን።

Mujib Amino

ለአቢሲንያ ባንክ Bank of Abyssiniaየስራ አመራሮች በሙሉ ሙስሊም የባንኩ ተጠቃሚዎች በተለይም ባለሀብቶችና ነጋዴዎች የባንክ ደብተራቸዉን እንዲቀዱ ትፈልጋላችሁ?••••••••••••••...
04/02/2024

ለአቢሲንያ ባንክ Bank of Abyssiniaየስራ አመራሮች በሙሉ

ሙስሊም የባንኩ ተጠቃሚዎች በተለይም ባለሀብቶችና ነጋዴዎች የባንክ ደብተራቸዉን እንዲቀዱ ትፈልጋላችሁ?
••••••••••••••••••••••••••••••
Mujib Amino

በማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ በተለቀቀዉ ተንቀሳቃሽ ምስል እንደተመለከትነዉ አንድ የእስልምና እምነት ተከታይ መምህር(ኡስታዝ ሙሐመድ ከድር) በሕገ መንግስቱ በተቀመጠዉ የእምነት ነጻነት መሰረት የመንገድ ላይ ሰባካ(ዳዕዋ) በማድረግ ላይ እንዳለ የአቢሲንያ ባንክ የአለምገና ቅርንጫፍ ኀላፊ ከባንኩ ይዞታና በርቀት ወደሚገኘዉ ስብከት ወደሚካሄድበት ቦታ ሆዶ ትንኮሳ ሲፈጽም ታይቷል።

በአካባቢዉ በተለያየ ጊዜያት የተለያዩ እምነት ተከታይ መምህራን በነፃነት ስብከት ሲያካሄዱ ምንም አይነት ተቃዉም ለማሰማት ያልደፈረዉ ይህ የአቢሲንያ ባንክ አለምገና ቅርንጫፍ ኀላፊ በጥላቻ በመታወሩ የተነሳ ከእስልምና እምነት ተከታይ መምህር ጋር ከፍተኛ ፀብ ዉስጥ ለመግባት ትንኮሳ ሲፈጽም በግልጽ የታየ በመሆኑ ሕዝባችንን አስቆጥቶታል።

ሙስሊም የባንኩ ተጠቃሚዎች በተለይም ባለሀብቶችና ነጋዴዎች የባንክ ደብተራቸዉን እንዲቀዱና ተቀማጭ ገንዘባቸዉን እዲያወጡ እንድናደርግ ትፈልጋላችሁ?

አይ ከሆነ መልሳችሁ በአፋጣኝ አለምገና አካባቢ የሚገኘው የአቢሲንያ ባንክ የቅርንጫፍ ኃላፊ የሆነውን ግለሰብ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወስድ እናሳስባለን::

03/02/2024

15 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ የንብረት ውድመት የደረሰበትን ወንድማችንን እንደግፈዉ
••••••••••••••••••••••••••••••

በባዩሽ መስጅድ የዲን ትምህርትን ጨምሮ ቁርኣንን በመሀፈዝ ፣ በኡስታዝነትና በኢማምነት እያገለገለ የሚገኘው ኡስታዝ ኸሊፋ በርታ በኮልፌ የገበያ ማዕከል በደረሰው የእሳት አደጋ በመጋዘናቸው ውስጥ የነበረ ግምቱ 15 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ንብረት ውድመት ደርሶበታል።

ወንድማችን የቤተሰብ አስተዳዳሪ ከመሆኑም በተጨማሪ አብዛኛው ንብረት በዕዳ የገባ በመሆኑ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ወንድማችንን ከጭንቀት ለመፈረጅ የበኩላችንን ድጋፍ እናደርግ ዘንድ እንጠይቃለን።

“ከሙዕሚን ወንድሙ የዱንያን ጭንቀት የገላገለ ሰው አላህ (ሱ.ወ) ከቂያማ ቀን ጭንቀት እርሱን ይገላግለዋል” ነብዩ መሀመድ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)

የአካውንት ስም:- ከሊፋ በርታ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ:-1000230579548
አዋሽ ባንክ:- 01425224548200
ዳሽን ባንክ:- 2920310294311
አቢሲኒያ ባንክ:-47469767
ኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ:- 1000068036805

ዳሩል ኩብራ ኦንላይን የቁርዐን ማዕከል ቁርኣንን ከነመልዕክቱ መሀፈዝ የሚቻልበትን እድል አመቻችቶ እየጠበቃችሁ ይገኛል።••••••••••••••••••••••••••••••ቁርአንን መሃፈዝና መልእ...
03/02/2024

ዳሩል ኩብራ ኦንላይን የቁርዐን ማዕከል ቁርኣንን ከነመልዕክቱ መሀፈዝ የሚቻልበትን እድል አመቻችቶ እየጠበቃችሁ ይገኛል።
••••••••••••••••••••••••••••••

ቁርአንን መሃፈዝና መልእክቱን መረዳት የሁላችንም ፍላጎት ነው። እርስዎ ከስራ ገበታዎ ሳይስተጓጎሉ አልያም በቤትዎ ሆነው ቁርአንን ከነትርጉሙ መሃፈዝ ይፈልጋሉ?
ዳሩል ኩብራ ኦንላይን የቁርዐን ማዕከል

በ4 ወር ጊዜ አራት ጁዝ የቁርዐን ክፍል ከነመልዕክቱ ይሀፍዙ ይልዎታል።

በሚንበር ቲቪ የመOል ቁርዐን ፕሮግራም አዘጋጅ እና አቅራቢ በሆነው ቃሪዕ አብዱረህማን የሚመራው የዳሩል ኩብራ ኦንላይን የቁርዐን ማዕከል ከረዥም ጥናት እና ዝግጅት በኋላ ቀላል እና ምቹ በሆነ መንገድ ቁርኣንን ከነ መልክቱ መሀፈዝ የሚቻልበትን እድል አመቻችቶ እየጠበቃቹህ ይገኛል።

በዘርፋ ብቁ በሆኑ ኡስታዞች ቁርኣንን በቤትዎ በኦንላይን በሳምንት ለ6 ቀን በቀን ለ30 ደቂቃ አንድ ዑስታዝ ለ አንድ ተማሪ ብቻ በመማር በ 4 ወር አራት ጁዝ ቁርኣንን ከነመልዕክቱ ይሀፍዙ።

ለበለጠ መረጃ
ስልክ ቁጥር
📲+251 95 328 8234
📲+251 98 257 0254
ዳሩል ኩብራ ኦንላይን የቁርዐን ማዕከል

የመመዝገቢያ ሊንክ
https://wa.me/message/IWZCUSKUAEMTN1

እናፋልጋቸዉወንድማችን ሀሰን ከማል ይባላል:: ይኖር የነበረዉ በአዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ ሞላማሩ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ነው::ከአራት አመታት በፊት  ወደ አፋር ክልልለስራ ጉዳይ እሄዳለው...
03/02/2024

እናፋልጋቸዉ

ወንድማችን ሀሰን ከማል ይባላል:: ይኖር የነበረዉ በአዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ ሞላማሩ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ነው::

ከአራት አመታት በፊት ወደ አፋር ክልልለስራ ጉዳይ እሄዳለው ብሎ እንደወጣ የት እንደገባ አናውቅም :: ድምፁንም ስምተን አናውቅም፣ ስልኩም ቢደወል አይሳራም:: እባካችሁ አፋልጉን ይላሉ ቤተሰቦቹ

ወንድማችንን ያየ ወይም ያለበትን የሚያውቅ ከታች በተቀመጠዉ ስልክ እንዲያሳውቃቸዉ ይጠይቃሉ:-

📲 251911606842 ፈላጊ ሀሰን ወርቁ

Loading📸Bright Production
02/02/2024

Loading

📸Bright Production

ወጣቱ ትውልድThe new Generation Ustaz Yassin Nuru / ياسين نورو🍃🍃🍃🍃🍃…….Loading
02/02/2024

ወጣቱ ትውልድ
The new Generation Ustaz Yassin Nuru / ياسين نورو
🍃🍃🍃🍃🍃
…….Loading

ቅንጅቱ ትርፋማ ነዉ••••••••••••••••••••••••••••••የሠላም ስብስብና የልማት ቅንጅት ለመጅሊስም ሆነ ለመንግስት አቅም መጎልበት የለም አፈር፣ የእርሻና የዘርን ያህል ቅንጅቱ ት...
02/02/2024

ቅንጅቱ ትርፋማ ነዉ
••••••••••••••••••••••••••••••
የሠላም ስብስብና የልማት ቅንጅት ለመጅሊስም ሆነ ለመንግስት አቅም መጎልበት የለም አፈር፣ የእርሻና የዘርን ያህል ቅንጅቱ ትርፋማ ነዉ።

ወጣቶች ሆይ! በሀገራችን ጉዳይ፣ በእምነታችን ጉዳይ፣ ... እንመካከር፣ እንደማመጥ፣ እንተዛዘን፣ እንደጋገፍ። ያኔ አንዳችንም ከመደናቀፍ ውጪ ሳንወድቅ በጋራ ስኬትን እናስመዘግባለን።

ኢንሻ አሏህ።

Mujib Amino

ከቀናት ሁሉ በላጯ ቀን  #ጁምዐ   🥰መልካም ቀን🤎ደግ ደጉን ያሰማን 🤎ሀገራችንን 🇪🇹ሠላም አድርግልን🤎
02/02/2024

ከቀናት ሁሉ በላጯ ቀን #ጁምዐ
🥰
መልካም ቀን🤎
ደግ ደጉን ያሰማን 🤎
ሀገራችንን 🇪🇹ሠላም አድርግልን🤎

ስለሰላም ስብስባችን ስጋት አይግባችሁ••••••••••••••••••••••••••••••በመደራጀታችን ራዕይና እሳቤ ዙሪያ በሺዎች የሚቆጠሩ ፤ ገንቢና አበረታች መልዕክቶች ደርሰዉናል። ዋነኛ አላ...
01/02/2024

ስለሰላም ስብስባችን ስጋት አይግባችሁ
••••••••••••••••••••••••••••••

በመደራጀታችን ራዕይና እሳቤ ዙሪያ በሺዎች የሚቆጠሩ ፤ ገንቢና አበረታች መልዕክቶች ደርሰዉናል። ዋነኛ አላማችን መሪ ድርጅትን መነቅነቅ ሳይሆን እንዳይነቀነቅ ማድረግ፣ ሕዝባዊ ፍላጎትን በይበልጥ መመለስ፣ ብልሹ አሰራሮችን መጠገን፣ ተቋማዊ አሰራሮችን ማጎልበት፣ ከግለሰቦችን ጥገኝነት ማላቀቅ... በመሆኑ ለማንም አጋር እንጂ ስጋት ሊሆን አይችልም።

ጥቂት የማይባሉ ግለሰቦች የመጅሊሱን መዋቅር ከግምት ዉስጥ በማስገባት ስጋታችሁን ያጋራችሁን ቢሆንም ይህ ትጉ ወጣት ኀይል በመጅሊስ መዋቅር ብቻ ፈጽሞ ሊገደብ እንደማይቻል፣ ኀይሉ ከመጅሊስም በላይ እንደሆነ፣ የወጣቱ ጥያቄና ፍላጎት ከመጅሊስ አጥር ላዕላይ መሆኑ፣ መጅሊስ ከኀይማኖታዊ ውጪ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ፍላጎቱን መጠርነፍ ስለማይችል... በቀረቡላችሁ በወዘተረፈ ዝርዝር ምክንያቶች ተማምነን በጋራ ለመሰለፍ ከፍላጎት ባለፈ ቃል መስጠትና ለተግባር የእንቀሳቀስ ሞራላችሁ አክብሮታችንን በላቀ መልኩ እንድንገልጽ ያስገድደናል። እናመሰግናለን።

የሰላም ስብስብና የልማት ቅንጅት ለመጅሊስም ሆነ ለመንግስት አቅም መጎልበት የለም አፈር፣ የእርሻና የዘርን ያህል ቅንጅቱ ትርፋማ ነዉ።

ወጣቶች ሆይ! በሀገራችን ጉዳይ፣ በእምነታችን ጉዳይ፣ ...እንመካከር፣ እንደማመጥ፣ እንተዛዘን፣ እንደጋገፍ። ያኔ አንዳችንም ከመደናቀፍ ውጪ ሳንወድቅ በጋራ ስኬትን እናስመዘግባለን። ኢንሻ አሏህ።
Mujib Amino

01/02/2024

🫵🏽💪🏻👳🏽‍♂️👨🏼‍🔬👨🏿‍🔧👨‍👧‍👧🫂👨‍💻🙋🏽‍♂️
ዝግጁ?
🙋🏽‍♂️🧑🏽‍💻🫂👨‍👧‍👧👨🏿‍🔧👨🏼‍🔬👳🏽‍♂️💪🏻🫵🏽

ታላቅ የምክክር እና የውይይት ፕሮግራም በደቡብ አፍሪካ በጆሃንስበርግ  ሱልጣን ባሆ አዳራሽ••••••••••••••••••••••••••••••ልጆቻችንን እንዴት እናሳድግ ?ህዝባዊ ውይይት የልጆች...
01/02/2024

ታላቅ የምክክር እና የውይይት ፕሮግራም በደቡብ አፍሪካ በጆሃንስበርግ ሱልጣን ባሆ አዳራሽ
••••••••••••••••••••••••••••••

ልጆቻችንን እንዴት እናሳድግ ?
ህዝባዊ ውይይት

የልጆች አስተዳደግ (በኢስላም)
በኡስታዝ ማህሙድ ሀሰን

የህፃናት ልዩ ብቃትና ተስጥኦ የሚቀርበበት መድረክ።

በልጆቹ ላይ ሀላፊነት የሚሰማው ሁሉ የማይቀርበት ታላቅ ጥሪ

አዘጋጅ :- ኢማሙ አህመድ (ሰንደይ ሊግ)

04/02/24 ( መጭው እሁድ )
4:30pm ከአስር ቡሃላ

ትኩረት ለልጆቻችን
ኢማሙ አህመድ( አዘጋጅ )

31/01/2024

🧍‍♂️📢አንድም ለማገዝና ለማጠናከር፤በሌላም በኩል ለማረምና ህፀፆችን ነቅሶ ለማዉጣት
✨✨✨✨✨✨✨✨✨



በሁሉም ክ/ከተሞች ወጣቶችን ስለማደራጀት••••••••••••••••••••••••••••••ከመጅሊስ መዋቅር ውጪ በ 11ዱ ክፍለ ከተሞች  ሙስሊም ወጣቶችን ብናደራጅ ምን ይመስላችኃል?በቀጣይም ሀ...
31/01/2024

በሁሉም ክ/ከተሞች ወጣቶችን ስለማደራጀት
••••••••••••••••••••••••••••••

ከመጅሊስ መዋቅር ውጪ በ 11ዱ ክፍለ ከተሞች ሙስሊም ወጣቶችን ብናደራጅ ምን ይመስላችኃል?
በቀጣይም ሀገር አቀፍ በሆነ መልኩ ብናስፋፋዉስ?

ይህን ምስል ስታዩ ፣ አዕምሯችሁ ላይ ምን ይመጣል? ምን ይሰማችኃል?
31/01/2024

ይህን ምስል ስታዩ ፣ አዕምሯችሁ ላይ ምን ይመጣል? ምን ይሰማችኃል?

አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁጉዳዩ፡-በልብ በሽታ እየተሰቃየ ለሚገኘው ለተማሪ አብዱልመጂድ ጀማል የነፍስ አድን እርዳታ ጥሪን ይመለከታል ።   ተማሪ አብዱልመጂድ ጀማል ይባላል።የ2...
31/01/2024

አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ

ጉዳዩ፡-በልብ በሽታ እየተሰቃየ ለሚገኘው ለተማሪ አብዱልመጂድ ጀማል የነፍስ አድን እርዳታ ጥሪን ይመለከታል ።

ተማሪ አብዱልመጂድ ጀማል ይባላል።የ20 ዓመት ወጣት ነው። ነዋሪነቱ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ አገታ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ሲሆን በአገታ ኤጀሬ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ውስጥ የ11ኛ ክፍል ተማሪ ነው። የተማሪ አብዱልመጂድ ጀማል ወላጆቹ አርሶ አደሮች እና በገጠር ደረጃም ከእጅ ወደ አፍ ኑሮን የሚገፉ ናቸው።የጤናው ሁኔታ ከህፃንነቱም ጀምሮ የማፈን፣የትንፋሽ መቆራረጥ እና ድካም ድካም የማለት ስሜት የነበረው ስለነበረ ከጓደኞቹ እኩል በለጋ እድሜው የመቦረቅ እና የመጫወት አጋጣሚዎች አልነበሩትም። ባሳለፍነው 2015 ዓመት ላይ ከፍተኛ ህመም አጋጥሞት ወደ አቅራቢያ ወደሚገኘው አልቾ ውሪሮ ወረዳ ቃወቆቶ ጤና ጣቢያ በፈረስ ተደግፎ ተወሰደ። የመጀመሪያ የህክምና እርዳታ በቃወቆቶ ጤና ጣቢያ ተደርጎለት የጤናው ሁኔታ አስጊ ስለነበር ኦክስጂን ተደርጎለት ከጤና ጣቢያው የህክምና ባለሙያ ጋር በአምቡላንስ ወደ ወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሪፈር ተደርጎ እንዲወሰድ ተደረገ።
በወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልም ኤም አር አይ፣አልትራሳውንድ፣ ኢኮሆ ዶፕላር፣ ኤክስ ሬይ እና መሰል ምርመራዎች እየተደረጉለት ለ1ወር ያህል በፅኑ ህክምና በኦክስጂን ከቆየ በኋላ የጤናው ሁኔታ መጠነኛ ላውጥ እያሳየ ሲመጣ በተመላላሽ ህክምና እየተደረገለት የቆየ ሲሆን የተደረጉለት ምርመራዎች ውጤቱ አስደንገጭ ሆነ ። ይህም ከፍተኛ የልብ ክፍተት እንዳለበት እና ልቡ ውስጥ ጠባሳ እንዳለበት ተነገረው። ለዚህም የተቻለው ህክምና ሁሉ በወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በየወሩ ክትትል ሲደረግለት እና ተከታታይ የማይቋረጡ መድሃኒቶችን እየወሰደ እስከ አንድ አመት የዘለቀ ቢሆንም በወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የልብ ህክምና ክፍል ውስጥ ሲከታተሉት የነበሩት ሀኪሞች ኬዙ ከባድ እና አስቸኳይ ቀዶ ጥገና ህክምና ካልተደረገለት እየተባባሰ ከመሄዱም ባሻገር መዳን እንደማይችል ተነገረው። ወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የልብ ቀዶ ጥገና ስለሌለ የተሻለ የቀዶ ህክምና ለማግኘት ሀገር ውስጥ ታዝማ ልዩ የልብ ቀዶ ህክምና ሆስፒታል አልያም ከተቻለ ከሀገር ውጭ ሊሆን እንደሚችል በማስረዳት ለጊዜው አቅማችንን ለመፈተሽ ወደ ታዝማ የልብ ህክምና ማዕከል ሪፈር እንዲፃፍለት ተደረገ።

ታዝማ ልዩ የልብ ቀዶ ህክምና ሆስፒታልም ከወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተፃፈውን ሪፈር መሰረት በማድረግ ከላይ የተገለፁትን የምርመራ አይነቶች በአዲስ መልክ ያደረጉለት ሲሆን ውጤቱም ተመሳሳይ እና የልቡ ሁኔታ አስጊ ደረጃ ላይ እንዳለ ተነገረን ። በምርመራ ውጤቱ መሰረት የልብ ክፍተቱ የተከሰተው በተፈጥሮ እና አብሮት ያደገ እንደዚሁም ልቡ ላይ ክፍተት እና ጠባሳ የተከሰተበት ቦታ ልባችን የሚመታበት (የሚርገበገብበት ክፍል) ላይ ባለው የደም ቱቦ(የልቡ ኤሌክትሪክ ሲስተም) ላይ ሲሆን ከቀኝ እና ከግራ የልቡ ክፍል የሚመጣውን የተጣራ ደም እና ያልተጣራ ቆሻሻ ደም አብሮ ቀላቅሎ የሚረጭ ስለሆነ የደም እርጭቱ ሲጨናነቅ ደሙን ወደ ሳንባው እየለቀቀው በመሆኑ ሳንባውም ላይ ጉዳት ማድረሱን ሌላ አሳሳቢ ሁኔታ አሳወቁን።
ይህንን ለማስተካከል ብቸኛው መፍትሔ አማራጭ አስቸኳይ የቀዶ ህክምና ማድረጉ የግድ እና ምንም አማራጭ የሌለው መሆኑን አሳውቀውን ቀዶ ህክምናውም በሀገር ውስጥ እዚያው ታዝማ የልብ ህክምና ማዕከል እንደሚሰሩት ነገሩን። ነገር ግን ቀዶ ህክምናው እጅግ ውስብስብ መሆኑን እና ቀዶ ጥገና የሚደረግበት ቦታ የልቡ ኤሌክትሪክ ሲስተም ላይ ስለሆነ የልቡ ኤሌክትሪክ ሲስተም በተለዋጭ አርተፊሻል ዲናሞ እንዲንቀሳቀስ እንደሚገጠምለት ነው የተነገረን ።
ለዚህም የአልጋ፣የመድሃኒት እና ሌሎች ተያያዥ የህክምና ወጪዎችን ሳያካትት ለቀዶ ህክምናው የእጃቸው ብቻ ብር 545,000 (አምስት መቶ አርባ አምስት ሺህ ብር) ወጭ የተጠየቅን ሲሆን ለጠቅላላ ህክምናው ከ650,000-700,000 ብር እንደሚያስፈልግ ነው የተነገረን።

እስካሁን በነበረውም የህክምና ሂደት ውስጥ እና በተከታታይ ያለማቋረጥ ለሚወስዳቸው መድሃኒቶች በቻልነው ያህል ከፍተኛ ወጭዎችን በብድርም ጭምር እያወጣን ህክምናውን እየተከታተለ የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ ግን የተጠየቅነው ገንዘብ በአርሶ አደር ወላጆቹ አቅም መሸፈን እጅጉን ፈታኝ እና ተስፋ አስቆራጭ ስለሆነብን ለናንተ ለወገን ደራሽ ወገኖቻችን ጭንቀታችንን አቃላችሁ አብዱልመጂድም ጤናውን አግኝቶ ትምህርቱን እንዲከታተል የዘወትር የትብብር አጋርነታችሁን በማሳየት ትተባበሩን ዘንድ የእርዳታ እጃችሁን እንድትዘረጉልን እና ከአላህ በታች ለመዳኑ ሰበብ ትሆኑን ዘንድ በአላህ ስም እንጠይቃለን።

ከሰላምታ ጋር
አስታማሚ ቤተሰቦቹ

አካውንት ቁጥሮች

1:የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000600862937
ናስር ላሌ እና አብዱልመጂድ ጀማል

2:ዘምዘም ባንክ
0036692920101
ናስር ላሌ እና አብዱልመጂድ ጀማል

3:አዋሽ ባንክ
014251281909400
ናስር ላሌ እና አብዱልመጂድ ጀማል

4:አቢሲኒያ ባንክ
171375967
ናስር ላሌ እና አብዱልመጂድ ጀማል

ለበለጠ መረጃ
ስልክ ቁጥር
0921810196
0940106005

ሼር ሼር ሼር6መቶ ሺዉን እንሙላላቸዉ••••••••••••••••••••••••••••••ለህክምናው የሚፈለገው ገንዘብ አንድ ሚሊየን ሲሆን እስካሁን ስድስት መቶ ሺህ ብር ተሰብስቧል:: በአሏህ ተ...
31/01/2024

ሼር ሼር ሼር
6መቶ ሺዉን እንሙላላቸዉ
••••••••••••••••••••••••••••••

ለህክምናው የሚፈለገው ገንዘብ አንድ ሚሊየን ሲሆን እስካሁን ስድስት መቶ ሺህ ብር ተሰብስቧል:: በአሏህ ተወኩል ህክምናውን ለመጀመር ሆስፒታል ገብተዋል።

የወንድማችንን እናት ሙሉ ህክምናቸዉን ተከታትለዉ እንዲጨርሱና አፊያቸዉ ይመለስ ዘንድ ቀሪዉን 6መቶ ሺ ብር ለመሙላት የሁላችንንም ርብርብ ይፈልጋል::
ዱዐ እናድርግላቸዉ : እንተባበር : እንተጋገዝ

ከአቅሜ በላይ ሆነብኝ የሶስት ዓመቷን ልጄን አድኑልኝ ❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️የሶስት ዓመቷን ህፃን ኢክላስ ሰይፉ ያሲን ትባላለች ። እንደ እኩዮቿ መጫወትን ያልታደ...
31/01/2024

ከአቅሜ በላይ ሆነብኝ የሶስት ዓመቷን ልጄን አድኑልኝ
❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️

የሶስት ዓመቷን ህፃን ኢክላስ ሰይፉ ያሲን ትባላለች ። እንደ እኩዮቿ መጫወትን ያልታደለች ፣ የሁለት ዓመት ህፃን ሳለች የጀመራት ምስሎቹ ላይ እንደምትመለከቱት ከፍተኛ የሆነ የአጥንት ህምም ይገጥማታል፣ ወላጆቿም ያላቸውን ንብረት እና አቅም አሟጠው ልጃቸውን ለማትረፍ የሚችሉትን ሁሉ አድርገዋል።

ህክምና እንድታገኝ ህክምና ቦታዎችም ድጋፍና ክትትል በማድረግ ተከታታይ ሰርጀሪዎችን በመስራት እንደምትድን ህመሟም የአጥንት ቲቢ እንደሆነ እና አጥንቷ ሙሉ ለሙሉ የተደካመ በመሆኑ ተጨማሪ አጥንቶችን ለመቀጠልና አንደኛው ሲድን ሌላኛው ይታከማል በሚል የተለያዩ ሰርጀሪዎችን አከናውናለች።

የመጨረሻ የተባለውን ሰርጀሪ ለማድረግ ቀነ ቀጠሮዋ ያሳለፍነው ሀሙስ የነበረ ቢሆንም የሰው ፊት ላለማየት ብዙ አማራጮችን ብጠቀምም ሊሳካልኝ አልቻለም።

እግሯ ላይ የተሳረው ጀሶ ተፈቶ ለቀዶ ጥገና የተዘጋጀ ቢሆንም የተጠየኩትን 500 ሺህ ብር ካላሟላው ልጄን ማትረፍ አልችልምና የልጄ ኢክላስ መዳን እናንተ ወንድሞቼ እህቶቼ አባቶቼና እንዲሁም ወገኖቼ ሰበብ ሁኑኝ ከጎኔ ቁሙልኝ አላህ አይፈትናችሁ ይላሉ አባቷ ሰይፉ ያሲን።

ሁላችንም ይህችን ህፃን ለማሳከም ምክንያት በመሆን የምንችለውን በመሰደቅ ለመዳኗ ሰበብ እንሁን።

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

የአካውንት ስም:- ሰይፉ ያሲን (አባት)
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ:- 1000328289508
ኦሮሚያ ሕብረት ስራ ባንክ:-1000036553573

መረጃውን ሼር በማድረግ የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ

አላህ ሆይ በልጆቻችን የማንሸከመውን ፈተና አትፈትነን እዘንልን

ጅማ እንገናኝበክቡ ዶር ሸይኽ ሀጅ ኢብራሂም ቱፋ የሚመራዉ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የበላይ ጠባቂነት በጅማ ከተማ  ታላቅ የሰላም፣ የአብሮነትና የምስጋና ኮንፈረንስ ስና...
29/01/2024

ጅማ እንገናኝ

በክቡ ዶር ሸይኽ ሀጅ ኢብራሂም ቱፋ የሚመራዉ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የበላይ ጠባቂነት በጅማ ከተማ ታላቅ የሰላም፣ የአብሮነትና የምስጋና ኮንፈረንስ ስናዘጋጅ ሕዝባችንን በማክበር፣ ተቋሙን በጠንካራ መሰረት ላይ ለማኖር፣ ስለሰላም ልንሰብክ፣ አብሮነትን ልናጠነክር በመሆኑ ደስታችን ወደር የለዉም።

Jimmatti wal haa agarru!!
**************************
" የተከፈለውን መስዋዕትነት ለተቋማዊ ለውጥ " የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የሰላምና የምስጋና ኮንፈረንስ
በሚል መሪ ቃል በጅማ ከተማ የካቲት 03 ቀን 2016 በድምቀት ይከናወናል ።

Koonfaransii Nageenyaafi Galateeffannaa Muslimoota Itoophiyaa. Dhaadannoo "Aarsaa Kaffalame Jijjiirama Dhaabbataatiif" jedhuun Magaalaa Jimmaatti gaafa 3/06/2016 wal haa agarru.

ወንድማችን አቡበከር ኸይረዲንን ተጋግዘን እናድነዉ!••••••••••••••••••••••••••••••አንዳንዴ አጋዥ መሆን ቀርቶ የሰውን እጅ የሚያስፈልገን ቀን ይመጣል .....ትንሹ አቡኪ በዚ...
29/01/2024

ወንድማችን አቡበከር ኸይረዲንን ተጋግዘን እናድነዉ!
••••••••••••••••••••••••••••••

አንዳንዴ አጋዥ መሆን ቀርቶ የሰውን እጅ የሚያስፈልገን ቀን ይመጣል .....

ትንሹ አቡኪ በዚህ ትንሽ እድሜው ለሰዎች ለመድረስ በበርካታ የበጎ አድራጎት ማህበራት ሲሳተፍና ቆይቷል::

ዛሬ ቀን ጥሎት በተራው እሱ የእኛን እርዳታ ፈላጊ ሆኗል:: በገጠመው የሽንት ትቦ ህመም እና የነርቭ ችግር በጳውሎስ ሆስፒታል ህክምናው እየተከታተለ ቢቆይም ከእነሱ አቅም በላይ ሆኖ ወደ ውጪ ሄዶ እንዲታከም ወስነዋል::

ነገር ግን ለህክምናው የሚያስፈልገው ገንዘብ እንኳን በቤተሰቡ በሰፈራችን እንኳን የማይሸፈን ሆኖብናል ከአሏህ(ሱ.ወ) በታች እንድታግዙት በአላህ ስም ልጠይቃችሁ🤲

የኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000481402585 አቡበከር ኸይረዲን
151196578 አቢሲኒያ ባንክ

አሰላሙአለይኩም   ወራህመቱላሂ  ወበረካትሁ   "ወንድሜን አፋልጉኝ" ከላይ በፎቶው ላይ የምትመለከቱት ተፈላጊ ወንድማችን  አብዶ ድልቢ ይባላል። የትውልድ ቦታው ጅማ መንቾ ወረዳ ድዲቦ ባሮዶ...
28/01/2024

አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ

"ወንድሜን አፋልጉኝ"

ከላይ በፎቶው ላይ የምትመለከቱት ተፈላጊ ወንድማችን አብዶ ድልቢ ይባላል። የትውልድ ቦታው ጅማ መንቾ ወረዳ ድዲቦ ባሮዶ ሲሆን ከጠፋ 1ወር አስቆጥሯል።

አብዶ በሥደት ከነበረባት ሳውዲ አረቢያ ስመለስ ታይዞ በየመን እስር ቤት ውስጥ አይቼዋለሁ እሚል ሰው መጣ ፎቶውንም አይቶ ያየው ሰው እሱ መሆኑን አረጋግጦልናል።

አሁንም በድጋሚ የመጀመሪያው ሰው አየሁ ብሎ ከመጣ ከጥቂት ቀናትች በሗላ ሌላ ሰው አዲስ አበባ ውስጥ እንዳገኘው እና ከሱዳናዊ ( ስወች)መገናኛ 24 አከባቢ ይኖር እንደ ነበር አህቴናል የምሉ ስወች ነግሮናል።

ይህን የሰማች እናት ከዛሬ ነገ ልጄ ይመጣልኛል ብላ መተኪያ የሌለውን ልጇን በተስፍ ትጠብቃለች።የእናትን ነገር የሚያውቅ ያውቀዋል።የኛም የእህት እና ወንድሞች ጉዳይ ብዙም ከዚህ የተለየ አይደለም።

ስለዚህ ወንድማችንን በመፈለግ ላይ ስለሆንን ፎቶውን ሼር በማድረግ ወንድማችንን ሊያውቁ የሚችሉ ሰዎች ያዩት ዘንድ በሶሻል ሚዲያ በተለይም ብዙ ተከታዮች ያሏችሁ ወንድምና እህቶች በማፈላለግ ትብብር እንድታደርጉልን እንጠይቃለን።

መረጃው ያላችሁ ሰዎች በነዚህ ስልክ ቁጥሮች በመደወል አሳውቁት ።አላህ መልካምን ይመንዳችሁ ወቶ ከመቅረት አላህ ይጠብቃችሁ ።
ዙላሊዲልቢ:-
📲0955059663
📲0911957734

ሙባረክ ሙሀመድ
📲0917546866

የወንድማችንን እናት በጋራ እናሳክም••••••••••••••••••••••••••••••እናታችን ስማቸዉ ወሮ ነፊሳ ጀማል ይባላሉ:: በህሙም ላይ ይጉኛሉ:: ለህክምናው የሚፈለገው ገንዘብ አንድ ሚ...
28/01/2024

የወንድማችንን እናት በጋራ እናሳክም
••••••••••••••••••••••••••••••

እናታችን ስማቸዉ ወሮ ነፊሳ ጀማል ይባላሉ:: በህሙም ላይ ይጉኛሉ:: ለህክምናው የሚፈለገው ገንዘብ አንድ ሚሊየን ሲሆን እስካሁን ስድስት መቶ ሺህ ብር ተሰብስቧል:: በአሏህ ተወኩል ህክምናውን ለመጀመር ሆስፒታል ገብተዋል።

በቀጣይም ሙሉ ህክምናቸዉን ተከታትለዉ እንዲጨርሱና አፊያቸዉ ይመለስ ዘንድ የሁላችንንም ርብርብ ይፈልጋል::

የበኩላችንን ሰደቃ በማዉጣት ለእኛም በረካ : ለታማሚ እናታችንም ጤና መጎልበት አስተዋፅዎ እናበርክት:-

የኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000042690663
ነፊሳ ጀማል
ለበለጠ መረጃ:-📲0925745852

እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን!ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትችን በተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት፣ የፋኦ አግሪኮላ ሜዳልያ ተሸልመዋል። ይህ  ሽልማታቸዉ በስንዴ ምርት ላይ ...
28/01/2024

እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን!

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትችን በተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት፣ የፋኦ አግሪኮላ ሜዳልያ ተሸልመዋል። ይህ ሽልማታቸዉ በስንዴ ምርት ላይ ላመጡት ለውጥ የተሰጠ እውቅና ነው።

Baga Gammanne! Baga Gammaddan!

Muummeen ministeeraa keenya kabajamoon Dr. Abiyyi Ahimad biyya keenyatti jijjiirama oomisha Qamadiin agarsiisaniin Dhaabbata Nyaataa fi Qonnaa Dhaabbata Mootummoota Gamtoomaniitti Meedaaliyaa badhaafamuu isaanitti baay'ee gammadeera.

Oomishni Qamadii kabajaa fi birmadummaa biyya keenyaaf shoora olaanaa qaba. Gama kanaan milkaa'ina agarsiifnee addunyaa irratti badhaafamoo ta'uun ammoo injifannoo dachaadha.

28/01/2024

በዱዓ እናግዛቸዉ

በዲን ጉዳይ በርካታ ዉጣዉረዶችን ያሳለፈ የወንድማችን አባት በጠና ታመዉ ሆስፒታል ይገኛሉና አባታችንን አሏህ(ሱ.ወ) አፊያ እንዲያደርጋቸዉ : እንዲበረቱ ዱዓ እንድታደርጉላቸው በአሏህ ስም እጠይቃለዉ::
🤲🏻🤲🏻🤲🏻

27/01/2024

ወንድማችንን ለማዳን እንረባረብ!
••••••••••••••••••••••••••••••

"ሽንት ከሸናሁ አራት ዓመት አለፈኝ "(የኩላሊት ታማሚው ሰለሀዲን ሻፊ)

ሰለሀዲን ሻፊ ይባላል አብዛኛው የህይወት ክፍሉን ያሳለፈው ቁርኣን በመቅራት ነው ከዛም አዲስ አበባ በመምጣት ኢልም ፈላጊ ሰዎችን ማስተማር ጀመረ…

ሰልሀዲን ሰዎችን በማስተማር ላይ እያለ ህመም አጋጠመው ህመሙም ቀላል መስሎት ወደሀኪም ቤት በሚሄድበት ሰዓት ሁለቱም ኩላሊቶቹ ፌል እንዳደረጉ እንዲሁም ሽንት መሽናት እንደማይችል ተነገረው ከዛም ክንዱ ላይ መሳሪያ ተገጥሞለት በሳምንት ሶስት ቀን ዳያሌስስ እያረገ ይገኛል።

የዳያሌሲስ ህክምና ወጪም ከባድ ስለሆነ ባስቸኮይ ውጭ ሀገር ኤዶ መታከም እንዳለበት ወህክምናም ከ4 ሚሊየን ብር በላይ ስለሚያስፈልግ ገንዘቡ በሱ አቅም ሚቻል ስላልሆነ መላው ኢትዮጲያውያን የእርዳታ እጃችሁን እንድተዘረጉለት በአላህ ስም ጥሪ አቅርቧል።

በሚከቱሉት አካውንቶች ሰለሀዲን ሻፊን መደገፍ ትችላላችሁ!
:ሰለሃዲን ሻፊ ሀሰን
፡ንግድ ባንክ 1000430058375
ኦሮሚያ ህብረተ ስራ ባንክ 1012500020816
https://youtu.be/-EoOYMuG_WM

26/01/2024

ታላቅ የሰላም፣የአብሮነትና የምስጋና ኮንፈረንስ በዉቢቷ ጅማ ከተማ
••••••••••••••••••••••••••••••
Mujib Amino

በክቡ ዶር ሸይኽ ሀጅ ኢብራሂም ቱፋ የሚመራዉ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የበላይ ጠባቂነት በጅማ ከተማ ታላቅ የሰላም፣ የአብሮነትና የምስጋና ኮንፈረንስ ስናዘጋጅ ሕዝባችንን በማክበር፣ ተቋሙን በጠንካራ መሰረት ላይ ለማኖር፣ ስለሰላም ልንሰብክ፣ አብሮነትን ልናጠነክር በመሆኑ ደስታችን ወደር የለዉም።

ዝግጅቱም በዉቢቷ ጅማ ከተማ እሁድ የካቲት 3/2016 በጅማ ስታዲየም የሚካሄድ ሲሆን ስለሰላም በህብረት ለማስተጋባት፣ ስለአንድነታችን ለመመካከር፣ ስለተከፈለዉ መስዕዋትነት ለመዘከር ድንቅ አጋጣሚ በመሆኑ ሁላችሁም ተጋብዛችኅል።

Gumii dhimma islaamaa Federaalaatin kan qindaawe,konfaransiin guddaan guyyaa Gurraandhala 3/2016 geggeeffama.

Konfaransiin kun kan geggeeffamu,Istaadiyamii Magaalaa Jimmaatti yoo tahu,Hundi keessan yaamamtanii jirtu.

Address

Addis Ababa

Telephone

+251912776721

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mujib Amino posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share