01/04/2024
ክብረ ቢሱ EBC
"…ጋዜጠኛ ታ ፋዬ ወልደ ሥላሴ EBC የብልፅግና መንግሥቱን ገመና ለመሸፈን ከመጣደፉ በፊት ዜናውን ሙያው በሚፈቅደው ሥነ ምግባር ሠርቶ በፌስቡክ ገፁ ለጥፎት ነበር።
• ሥራ ለምን ለቀቅሽ?
~ አሞኝ ነው ታምሜ ነበር ያለችው። በቃ ሴትየዋ መንግሥትን አልከሰሰችም። ዩኒቨርስቲውን አልከሰሰችም። አልወቀሰችም። አሞኝ ተቸገርኩ፣ ራበኝ፣ እርዱኝ ነው ያለችው። ይሄ ምን ያሰድባል? ምንስ ያስወቅሳል?
"…ዜናው ከተሠራ ከ5 ሰዓት በኋላ የመጣው EBC ወሎ ዩኒቨስቲ ደውሎ የሠራውን ዘገባ ተመልከቱትማ። ወደ ወሎ ዩኒቨርስቲ ደውዬ እውነታውን አጣርቻለው በማለት እጅግ በጣም አሳዛኝና አሳፋሪ ዘገባ ነው የሠራው።
"…ይህች እህት "ወሎ ዩኒቨርስቲ 12 አመት ልምድ አለኝ" አለች እንጂ ዩኒቨርስቲው አባረረኝ ወይም ከሥራ ገበታ አፈናቀለኝ አላለችም። በተቋሙ ላይ ምንም ክስ ይሁን አሉባልታ አላነሳችም። የዩኒቨርስቲው ተወካይ ነኝ ያለውም ሰው እንደምትሰሙት የዚህችን ሴት ችግር ያስረዳበት ቋንቋ ከትልቅ ተቋም የማይጠበቅ ከመሆኑም በላይ በምስጥር ሊጠበቅ የሚገባ የግል ጉዳይ ሁሉ "የአዕምሮ ታማሚ ነች" ከዚያም "የማህፀን ህመም አለብኝ ምናምን ትል ነበር" የሚሉ ቃላት በመጠቀም የግለሰቧን የግል ምስጢሮች በአደባባይ አዝረክርኳል - ዝርክርክ ተቋም - ዝርክርክ ሚዲያ።ነውረኛ እና በጣም አሳፋሪ ሚዲያ - EBC
"…እጠይቃለሁ በአሁን ሰዓት ከሌባ፣ ከዘራፊ በቀር ጋዜጠኛ፣ ፕሮፌሰሮች፣ የህክማና ባለሙያ ዶክተሮች፣ የመንግሥት ሠራተኞች ኑሮ ነው እየኖሩ ያሉት? የቤት ኪራዩ ከደሞዙ ያልበለጠበት አለ? ባልና ሚስቶች በኑሮ ውድነቱ ምክንያት እየተፋቱ አይደለምን? የሚገርመው በቅርቡ የዩኒቨርስቲው አስተማሪም ሆነ የ EBC ጋዜጠኛው ለህክምና ብለው የልመና አቁፋዳቸውን ይዘረጋሉ።
• ቲሽ ጨቅላ ሁላ…!