ወይ አዲስ አበባ በሸገር ኤፍኤም 102.1 Wey Addis Ababa on Sheger FM 102.1

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • ወይ አዲስ አበባ በሸገር ኤፍኤም 102.1 Wey Addis Ababa on Sheger FM 102.1

ወይ አዲስ አበባ በሸገር ኤፍኤም 102.1 Wey Addis Ababa on Sheger FM 102.1 Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ወይ አዲስ አበባ በሸገር ኤፍኤም 102.1 Wey Addis Ababa on Sheger FM 102.1, Radio Station, General Abebe Damtew Street, Addis Ababa.
(6)

• About ‘Wey Addis Ababa’ radio program and its ‘content segments’:
The overall goal of Wey Addis Ababa radio program is to contribute to the development of a modern, civilized, progressive and healthy community in Addis Ababa and Ethiopia as we

ዛሬ ሐሙስ ሚያዝያ 3/2016 ዓ.ም.  …  “ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ  … ከ8:00 እስከ 10:00 ሰዓት ድረስ  መሰናዶዎቹን ያቀርባል።☞  በዛሬው የ"...
18/04/2024

ዛሬ ሐሙስ ሚያዝያ 3/2016 ዓ.ም. … “ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ … ከ8:00 እስከ 10:00 ሰዓት ድረስ መሰናዶዎቹን ያቀርባል።

☞ በዛሬው የ"ሰፈራችን" መሰናዶ እህል በረንዳና አካባቢውን የሚያስቃኘው ቅንብራችን 3ኛው ክፍል ይቀርብላችኋል።

☞ ተጓዡ ጋዜጠኛ ሔኖክ ስዩም፤ .. "ጉዞ ሔኖክ" በተሰኘ ቅንብሩ የዓለም ቅርስ ቀንን አስመልክቶ ወደ ሾንኬ መንደር ይወስደናል። "ተደብቆ ስለኖረው ቅርሳችን" ብዙ የሚለን አለው። ተጋብዛችኋል!

☞ ከወዲያና ወዲህ ያሰባሰብናቸው የከተማ ወሬዎችም አሉን።

ለአስተያየቶቻችሁ በ011 -1- 27 5454 ደውሉልን።

አጫጭር መልዕክቶቻችሁንም :- በ8101 እና በ0939-939393 አኑሩልን!

ሰኞ ሚያዚያ 7/2016 ዓ.ም.  …  የ“ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ  … ከ10:00 እስከ 12:00 ሰዓት ድረስ  መሰናዶዎቹን ያቀርባል።☞  ተቀዳሚውና ድሮ...
15/04/2024

ሰኞ ሚያዚያ 7/2016 ዓ.ም. … የ“ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ … ከ10:00 እስከ 12:00 ሰዓት ድረስ መሰናዶዎቹን ያቀርባል።

☞ ተቀዳሚውና ድሮን ከዘንድሮ የምናነጻጽርበት ቅንብር ይኖረናል። በ"ሐሜት" ዙሪያ የሚለው አለው። አዘጋጇ ጽዮን አምሳሉ ናት።

☞ የኦምኒ ሚዲያ የሙዚቃ መረጃዎችንም ታገኛላችሁ።

☞ በ“ዘፈን እና ዘመን” ደግሞ … "ስለሙሉቀን ያልተነገሩ ታሪኮች"ን ይዳስሳል።

☞ ከየአቅጣጫው ያሰባሰብናቸው የከተማ ወሬዎችም ይኖሩናል።

ለአስተያየቶቻችሁ በ011 -1- 27 5454 ደውሉልን።

አጫጭር መልዕክቶቻችሁንም :- በ8101 እና በ0939-939393 አኑሩልን!

ዛሬ ሐሙስ ሚያዝያ 3/2016 ዓ.ም.  …  “ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ  … ከ8:00 እስከ 10:00 ሰዓት ድረስ  መሰናዶዎቹን ያቀርባል።☞  በዛሬው የ"...
11/04/2024

ዛሬ ሐሙስ ሚያዝያ 3/2016 ዓ.ም. … “ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ … ከ8:00 እስከ 10:00 ሰዓት ድረስ መሰናዶዎቹን ያቀርባል።

☞ በዛሬው የ"ሰፈራችን" መሰናዶ እህል በረንዳና አካባቢውን የሚያስቃኘው ቅንብራችን 2ኛው ክፍል ይቀርብላችኋል።

☞ ተጓዡ ጋዜጠኛ ሔኖክ ስዩም "ጉዞ ሔኖክ" በተሰኘ ቅንብሩ "ወደ ከፋ ማንኪራ" ይወስደናል። ታደምጡት ዘንድ ተጋብዛችኋል!

☞ ከወዲያና ወዲህ ያሰባሰብናቸው የከተማ ወሬዎችም አሉን።

ለአስተያየቶቻችሁ በ011 -1- 27 5454 ደውሉልን።

አጫጭር መልዕክቶቻችሁንም :- በ8101 እና በ0939-939393 አኑሩልን!

የኢትዮ ጃዝ ቀን መመዝገቢያ ቅጽ
08/04/2024

የኢትዮ ጃዝ ቀን መመዝገቢያ ቅጽ

On the Festival of and The Renowned Ethiopian Jazz Musician and Composer Samuel Yirga’s Concert (And Other Music groups are performing) Location: In the Ethiopian Academy of Sciences Headquarters (Behind St. Paul’s Hospital) https://maps.app.goo.gl/Qk4HxkxTfD2P...

ሰኞ መጋቢት 29/2016 ዓ.ም.  …  የ“ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ  … ከ10:00 እስከ 12:00 ሰዓት ድረስ  መሰናዶዎቹን ያቀርባል።☞  የ"10 ከ 1...
08/04/2024

ሰኞ መጋቢት 29/2016 ዓ.ም. … የ“ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ … ከ10:00 እስከ 12:00 ሰዓት ድረስ መሰናዶዎቹን ያቀርባል።

☞ የ"10 ከ 10" ቅንብራችን ለአትሌት መሠረት ደፋር አክብሮታችን የተገለጸበት ነው። የዚህ ሳምንት የ"10/10 ባለክብራችን"ም አድርገናታል!!!

☞ የኦምኒ ሚዲያ የሙዚቃ መረጃዎችንም ታገኛላችሁ።

☞ በ“ዘፈን እና ዘመን” ደግሞ … "መንዙማና ዓለማዊ ሙዚቃ" በተሰኘ ርዕስ ላይ ያተኩራል።

☞ ከየአቅጣጫው ያሰባሰብናቸው የከተማ ወሬዎችም ይኖሩናል።

ለአስተያየቶቻችሁ በ011 -1- 27 5454 ደውሉልን።

አጫጭር መልዕክቶቻችሁንም :- በ8101 እና በ0939-939393 አኑሩልን!

ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 26/2016 ዓ.ም.  …  “ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ  … ከ8:00 እስከ 10:00 ሰዓት ድረስ  መሰናዶዎቹን ያቀርባል።☞  በዛሬው የ...
04/04/2024

ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 26/2016 ዓ.ም. … “ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ … ከ8:00 እስከ 10:00 ሰዓት ድረስ መሰናዶዎቹን ያቀርባል።

☞ በዛሬው የ"ሰፈራችን" መሰናዶ ወደ መሳለሚያ አካባቢ አምርተን "እህል በረንዳንና አካባቢው"ን የሚያስቃኘው ቅንብራችን የመጀመሪያው ክፍል ይቀርብላችኋል።

☞ ተጓዡ ጋዜጠኛ ሔኖክ ስዩም "ጉዞ ሔኖክ" በተሰኘ ቅንብሩ "ሞህር ኢየሱስ ገዳም"ን ያስቃኘናል። ... ታደምጡት ዘንድ ተጋብዛችኋል!

☞ ከወዲያና ወዲህ የቃረምናቸው የከተማ ወሬዎችም አሉን።

ለአስተያየቶቻችሁ በ011 -1- 27 5454 ደውሉልን።

አጫጭር መልዕክቶቻችሁንም :- በ8101 እና በ0939-939393 አኑሩልን!

"ወይ አዲስ አበባ" ፡-  ብዙዎቹ ጓደኞችህ የሥነ-ጽሑፍ ሰዎች ናቸው፤ ይህ የሆነው በምርጫህ ነው ወይስ በአጋጣሚ?! ጥበበ ተርፋ፡- ይኼ ቤት በጣም ሞቅ ያለ ነበር፤ እንዲህ ነው ብዬ ልነግር...
03/04/2024

"ወይ አዲስ አበባ" ፡- ብዙዎቹ ጓደኞችህ የሥነ-ጽሑፍ ሰዎች ናቸው፤ ይህ የሆነው በምርጫህ ነው ወይስ በአጋጣሚ?!



ጥበበ ተርፋ፡- ይኼ ቤት በጣም ሞቅ ያለ ነበር፤ እንዲህ ነው ብዬ ልነግርህ አልችልም፡፡ ጸጋዬ ገብረ መድኅን ይመጣል እዚህጋ ይቀመጣል፤ ተስፋዬ ገሰሰ ይመጣና ደግሞ እዚያ ጥግ ይቀመጣል (ቦታዎችን እያመላከተ) በቃ ሲተራረቡ ታገኛቸዋለህ፡፡ አበበ ባልቻ፣ ደምሴ ጽጌ፣ ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር፣ ነቢይ መኮንን እና ሌሎችም ይመጣሉ፤ ጨዋታው ይደራል፡፡ ብዙ ጊዜ በየጨዋታዎቻችንም ሆነ በየመድረኮቻችን ብዙም የማናስታውሳቸውና የምንዘነጋቸው የሐረር ሰው የሆኑት ሰይፉ መታፈሪያ ፍሬውም ይመጡ ነበር፤ ከእኔ ጋር መጫወት ደስ ይላቸው ነበር፤ ያደንቁኝም፣ ስጦታዎችም ይሰጡኝ ነበር፡፡

("ወይ አዲስ አበባ" መጽሔት፣ ቅጽ 1፣ ቁጥር 14፣ 2014)

"ወይ አዲስ አበባ :-  እስቲ የንባብ ተመክሮህን አጋራን፤ ምን ዓይነት መጻሕፍትን ማንበብ ትመርጣለህ? ከደራሲያንስ ማንን ታደንቃለህ? ጥበበ ተርፋ:-  ያገኘሁትን ነው የማነበው፤ አልመርጥም...
03/04/2024

"ወይ አዲስ አበባ :- እስቲ የንባብ ተመክሮህን አጋራን፤ ምን ዓይነት መጻሕፍትን ማንበብ ትመርጣለህ? ከደራሲያንስ ማንን ታደንቃለህ?

ጥበበ ተርፋ:- ያገኘሁትን ነው የማነበው፤ አልመርጥም። ከድሮዎቹ እነቶልስቶይ እና ሄሚንግወይ አሉ። (በነገራችን ላይ መስፍን ዓለማየሁ ተርጉሞት ለንባብ ለበቃው “ሽማግሌውና ባህሩ” መጽሐፍ ከድርሰቶቹ ጋር ውስጥ የተካተቱትንና የሽፋን ሥዕሉን እኔ ነኝ የሠራሁት።) የዋልት ዊትማን ሥራዎችም ያስደስቱኛል። የአሜሪካንን ክፍለ-አሕጉር ሀብታምነት (Richness)፣ ውበት የገለጸበት መንገድ መሳጭ ነው። ሳሙኤል ቤኬትም ከምወዳቸው አንዱ ነው። “End game” የተሰኘውን ሥራውን እወድለታለሁ። መጽሐፏን መስፍን ዓለማየሁ እኔ ዘንድ አግኝቷት እዚሁ እየቃመ ተርጉሟት በተስፋዬ ገሰሰ አማካይነት አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ባህል ማዕከል ታይታለች። አጭር ናት፤ አንድ ግርዶ ሳይዘጋ የምታበቃ። የጀምስ ጆይስ “Ulysses” የተሰኘው መጽሐፍም ድንቅ ነው። በተለየ መንገድ የተጻፈና የተለየ ሐሳብ የሚንጸባረቅበት Imaginative (ምናባዊ) ነው። ጥልቀት ያለው በመሆኑም ቶሎ ለመረዳት ይከብዳል። ብዙዎቹ የሩሲያ ድርሰቶች ደስ ይሉኛል፤ በተለይ ደግሞ ማክሲም ጎርኪይ። የዩቫል ኖሕ ሐራሪ “Sapiens” እና “Homo Deus”ም በቅርቡ አንብቤ እጅግ የተደመምኩባቸው ናቸው።

("ወይ አዲስ አበባ" መጽሔት፣ ቅጽ 1፣ ቁጥር 14፣ 2014)

የሸገር ጋዜጠኛ የኔነህ ሲሳይ መኪና ተሰርቃለች!   | የሸገር 102.1 ኤፍ ኤም ጋዜጠኛ የየኔነህ ሲሳይ ኮድ 2 አ/አ 81589 መኪና ከሰባተኛ አካባቢ ከማደሪያዋ ተሰርቃለች።ለማንኛውም ጥቆ...
02/04/2024

የሸገር ጋዜጠኛ የኔነህ ሲሳይ መኪና ተሰርቃለች!

| የሸገር 102.1 ኤፍ ኤም ጋዜጠኛ የየኔነህ ሲሳይ ኮድ 2 አ/አ 81589 መኪና ከሰባተኛ አካባቢ ከማደሪያዋ ተሰርቃለች።

ለማንኛውም ጥቆማ
+251911684561
የጋዜጠኛ የኔነህ ሲሳይ ስልክ ቁጥር ነው።

ወዳጆች ይህን መረጃ ሼር በማድረግ በማፈላለግ አስተዋጽኦ እንድታደርጉ ትብብር እንጠይቃለን።


Sisay

ሰኞ መጋቢት 23/2016 ዓ.ም.  …  የ“ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ  … ከ10:00 እስከ 12:00 ሰዓት ድረስ  መሰናዶዎቹን ያቀርባል።☞  የ"10 ከ 1...
01/04/2024

ሰኞ መጋቢት 23/2016 ዓ.ም. … የ“ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ … ከ10:00 እስከ 12:00 ሰዓት ድረስ መሰናዶዎቹን ያቀርባል።

☞ የ"10 ከ 10" ቅንብራችን ለፕሮፌሰር ዓለምፀሐይ መኮንን አክብሮታችን የተገለጸበት ነው። የዚህ ሳምንት የ"10/10 ባለክብራችን"ም አድርገናየዋል!!!

☞ የኦምኒ ሚዲያ የሙዚቃ መረጃዎችንም ታገኛላችሁ።

☞ በ“ዘፈን እና ዘመን” ደግሞ … በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎችና ባህሎች "የሴት ልጅ ውበት፣ ጀግንነት እና አበርክቶ 'ኤትኖግራፈፊክ ይዘት' ባላቸው ሙዚቃዎቻችን” እንዴት እንደተገለጹ ዛሬም በ4ኛ ክፍል መሰናዶአችን ይዳስሳሉ።

☞ ከየአቅጣጫው ያሰባሰብናቸው የከተማ ወሬዎችም ይኖሩናል።

ለአስተያየቶቻችሁ በ011 -1- 27 5454 ደውሉልን።

አጫጭር መልዕክቶቻችሁንም :- በ8101 እና በ0939-939393 አኑሩልን!

“ዘፈን እና ዘመን”ን የመሰለ ውብ ፎቶ!
31/03/2024

“ዘፈን እና ዘመን”ን የመሰለ ውብ ፎቶ!

ዛሬ ሐሙስ ኅዳር 13/2016 ዓ.ም.  …  “ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ  … ከ8:00 እስከ 10:00 ሰዓት ድረስ  መሰናዶዎቹን ያቀርባል።☞  በዛሬው የ"...
28/03/2024

ዛሬ ሐሙስ ኅዳር 13/2016 ዓ.ም. … “ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ … ከ8:00 እስከ 10:00 ሰዓት ድረስ መሰናዶዎቹን ያቀርባል።

☞ በዛሬው የ"ሰፈራችን" መሰናዶ ፈረንሳይ ለጋሲዮንን የሚያስቃኘው ቅንብራችን 3ኛውና የመጨረሻው ክፍል ይቀርብላችኋል።

☞ ተጓዡ ጋዜጠኛ ሔኖክ ስዩም "ጉዞ ሔኖክ" በተሰኘ ቅንብሩ "የቃጥባሬ ከዋክብቶችን" ያወሳቸዋል ... እነሼኽ ኢሳ ሃምዛን። ረመዳንም አይደል?! ታደምጡት ዘንድ ተጋብዛችኋል!

☞ ከወዲያና ወዲህ የቃረምናቸው የከተማ ወሬዎችም አሉን።

ለአስተያየቶቻችሁ በ011 -1- 27 5454 ደውሉልን።

አጫጭር መልዕክቶቻችሁንም :- በ8101 እና በ0939-939393 አኑሩልን!

ሰኞ መጋቢት 16/2016 ዓ.ም.  …  የ“ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ  … ከ10:00 እስከ 12:00 ሰዓት ድረስ  መሰናዶዎቹን ያቀርባል።☞  የ"10 ከ 1...
25/03/2024

ሰኞ መጋቢት 16/2016 ዓ.ም. … የ“ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ … ከ10:00 እስከ 12:00 ሰዓት ድረስ መሰናዶዎቹን ያቀርባል።

☞ የ"10 ከ 10" ቅንብራችን ለድንቋ አትሌታችን ጥሩነሽ ዲባባ አክብሮታችን የተገለጸበት ነው። የዚህ ሳምንት የ"10/10 ባለክብራችን"ም ናት!!!

☞ የኦምኒ ሚዲያ የሙዚቃ መረጃዎችንም ታገኛላችሁ።

☞ በ“ዘፈን እና ዘመን” ደግሞ … “የሴት ልጅን ውበት፣ ጀግንነት እና አበርክቶ በክብር ያወደሱ ሙዚቃዎቻችን” ዛሬም በ3ኛ ክፍል መሰናዶአችን ይዳሰሳሉ።

☞ ከየአቅጣጫው ያሰባሰብናቸው የከተማ ወሬዎችም ይኖሩናል።

ለአስተያየቶቻችሁ በ011 -1- 27 5454 ደውሉልን።

አጫጭር መልዕክቶቻችሁንም :- በ8101 እና በ0939-939393 አኑሩልን!

ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 05/2016 ዓ.ም.  …  “ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ  … ከ8:00 እስከ 10:00 ሰዓት ድረስ  መሰናዶዎቹን ያቀርባል።☞  በዛሬው የ...
14/03/2024

ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 05/2016 ዓ.ም. … “ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ … ከ8:00 እስከ 10:00 ሰዓት ድረስ መሰናዶዎቹን ያቀርባል።

☞ በዛሬው የ"ሰፈራችን" ክፍል ቅንብር "ፈረንሳይ ለጋሲዮን" ላይ እንቆያለን!

☞ ተጓዡ ጋዜጠኛ ሔኖክ ስዩም "ጉዞ ሔኖክ" በተሰኘ ቅንብሩ ከዕለቱ ጋር አያይዞ ስለዝቋላ አቦ ገዳም የሚለን አለው።

☞ የተለያዩ ከተማ-ነክ ወሬዎችም አሉን።

ለአስተያየቶቻችሁ በ011 -1- 27 5454 ደውሉልን።

አጫጭር መልዕክቶቻችሁንም :- በ8101 እና በ0939-939393 አኑሩልን!

የሰንሻይን ኮንስትራክሽን 35ኛ ዓመት የምሥረታ ክብረ-በዓልና በኩባንያው ውስጥ በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ላገለገሉ 20 ሠራተኞች መኖሪያ ቤቶች የመሸለም ፕሮግራም ባሳለፍነው ቅዳሜ የካቲት 30/...
11/03/2024

የሰንሻይን ኮንስትራክሽን 35ኛ ዓመት የምሥረታ ክብረ-በዓልና በኩባንያው ውስጥ በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ላገለገሉ 20 ሠራተኞች መኖሪያ ቤቶች የመሸለም ፕሮግራም ባሳለፍነው ቅዳሜ የካቲት 30/2016 ዓ.ም. ተካሂዷል።

በክብረ - በዓሉ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አረጋ በክብር እንግድነት የተገኙ ሲሆን የአቢሲኒያ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ በቃሉ ዘለቀ፣ የሕብረት ኢንሹራንስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ መሠረት በዛብህ እና የጌት-አስ ኩባንያ ባለቤት አቶ ጌቱ ገለቴ በክብረ-በዓሉ ላይ ከተገኙት መካከል ናቸው።

በምሥረታ በዓሉ መክፈቻ ላይ የሰንሻይን ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የክብር ዶ/ር ሳሙኤል ታፈሰ ባደረጉት ንግግር ኩባንያው በ35 ዓመታት ጉዞው ያስመዘገባቸውን ስኬቶች ዘርዝረዋል።

በሪል እስቴት ዘርፍ ከአሁን ቀደም 3500 ቤቶች ገንብቶ ያስረከበው ሰንሻይን ኩባንያ ሌሎች ተጨማሪ 5000 ቤቶችንም በክብረ በዓሉ ላይ አስረክቧል፡፡

የኩባንያው ዋና ሥራ አስፈጻሚ በንግግራቸው ላይ "ሰንሻይን በመንገድ ዘርፍ ከአሁን በፊት 1270 ኪ.ሜ መንገድ ጨርሶ ያስረከበ መሆኑን ጠቅሰው በቅርቡም የደብረብርሃን-አንኮበር መንገድን ሙሉ በመሉ ሠርቶ መጨረሱንም ተናግረዋል፡፡

ከግንባታው ዘርፍ በተጨማሪም ሰንሻይን ኢንቨስትመንት ግሩፕ፤ .. ሰንሻይን ቢዝነስ፣ ማርዮት ሆቴልና ሰንሻይን ሃይራይዝ ኮሜርሻል ሕንፃዎችን የሚያስተዳድር ዘርፍ፤ .. ሰንሲስተርስ ትሬዲንግ ኢንዱስትሪያል ላውንደሪና የውበት ሳሎን አገልግሎት ኩባንያ እንደመሠረተም አውስተዋል፡፡

ማህበራዊ ኃላፊነቶችን በመወጣት ረገድም ሰንሻይን ፊላንትሮፊ ፋውንዴሽንን አቋቁሞ በገነባቸው ትምህርት ቤቶች ውስጥ ነፃ የትምህርት ዕድል መስጠት፣ አረጋውያን መርጃ ማዕከልን መሥርቶ መንከባከብ፣ አብያተ-ክርስትያናትን ማገዝ እያካሄዳቸው ካሉት ተግባራት መካከል መሆኑን ገልጸዋል።

በኩባንያው ምሥረታ ክብረ-በዓልና በሲ.ኤም.ሲ አካባቢ ያስገነባቸውን ባለ 4 ፎቅ 114 የጋራ መኖሪያ ሕንፃዎችን ሲያስመርቅ በክብር እንግድነት የተገኙት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው ባደረጉት ንግግር በቤት አቅርቦት ረገድ የፍላጎትና የአቅርቦት ክፍተቱን ለመድፈን ሰንሻይን ኮንስትራክሽን እና መሰል በሪል ስቴት ግንባታ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች ሚና ቀላል አለመሆኑን መስክረዋል፡፡

"ባለፉት 5 ዓመታት 30 ሺህ ቤቶችን ለቤት ፈላጊዎች አቅርበናል" ያሉት ከንቲባዋ፣ ቤቶቹን ገንብቶ በማቅረብ በኩል ማኅበራዊ ኃላፊነታቸውን ከተወጡት መሐል ሰንሻይን ኮንስትራክሽን አንዱ መሆኑንም አመልክተዋል፡፡

በ35ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ላይ ካምፓኒው ለበጎ አድራጎት ሥራ ካቋቋማቸው አራት ትምህርት ቤቶች መሐል በነቀምት፣ አክሱምና አገና ተምረው ለቁም ነገር የበቁ የ3 ተማሪዎች ምስክርነት ተደምጧል፡፡

በዕለቱ በሰንሻይን ካምፓኒ የተለያዩ የሥራ ክፍሎችና ኃላፊነቶች በተለያየ ደረጃ ላገለገሉ 20 ሠራተኞች የመኖሪያ ቤት ሽልማት ተበርክቷል፡፡ ከእነዚህ ተሸላሚዎች መሐል የዶ/ር ሳሙኤል ታፈሰ እና የወ/ሮ ፈትለወርቅ ኢላላ መኖሪያ ቤት ሠራተኛ የሆነችው ወ/ት አበባ ምስጋናው አንዷ ነበረች፡፡ ለተሸላሚዎች ሽልማት የሰጡትም የሰንሻይን መሥራችና ምክትል ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ፈትለወርቅ ኢላላ ናቸው።

(ነቢዩ ግርማ)

ሰኞ መጋቢት 2/2016 ዓ.ም.  …  የ“ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ  … ከ10:00 እስከ 12:00 ሰዓት ድረስ  መሰናዶዎቹን ያቀርባል።☞  በ"10 ከ 10...
11/03/2024

ሰኞ መጋቢት 2/2016 ዓ.ም. … የ“ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ … ከ10:00 እስከ 12:00 ሰዓት ድረስ መሰናዶዎቹን ያቀርባል።

☞ በ"10 ከ 10" ቅንብራችን በቴአትር አምራችነቱ የሚታወቀው የሁለ-ገቡ ባለሙያ ውድነህ ክፍሌ ሙያዊ አስተዋጽኦ ይነገራል። የዚህ ሳምንት የ"10/10 ባለክብራችን"ም አድርገነዋል!!!

☞ የኦምኒ ሚዲያ የሙዚቃ መረጃዎችንም ታገኛላችሁ።

☞ የ“ዘፈን እና ዘመን” መሰናዶአችን … “የሴት ልጅን ውበት፣ ጀግንነት እና አበርክቶ በክብር ያወደሱ ሙዚቃዎቻችን”ን ይዳስሳል።

☞ ከየአቅጣጫው ያሰባሰብናቸው የከተማ ወሬዎችም ይኖሩናል።

ለአስተያየቶቻችሁ በ011 -1- 27 5454 ደውሉልን።

አጫጭር መልዕክቶቻችሁንም :- በ8101 እና በ0939-939393 አኑሩልን!

ዛሬ ሐሙስ የካቲት 28/2016 ዓ.ም.  …  “ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ  … ከ8:00 እስከ 10:00 ሰዓት ድረስ  መሰናዶዎቹን ያቀርባል።☞  ዛሬም "ሰ...
07/03/2024

ዛሬ ሐሙስ የካቲት 28/2016 ዓ.ም. … “ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ … ከ8:00 እስከ 10:00 ሰዓት ድረስ መሰናዶዎቹን ያቀርባል።

☞ ዛሬም "ሰፈራችን" በተሰኘው መሰናዶአችን የ"አብነት" ላይ ቆይታችን ክፍል 2 ይቀርባል።

☞ ተጓዡ ጋዜጠኛ ሔኖክ ስዩም "በሴቶች ቀን ስለ’ኛ ሴቶች" ያወጋናል። በተለይ ደግሞ ጌዴኦዎች ስለሴቶች የነበራቸውንና አሁንም ያላቸውን ውብ ባህል ይዳስሳል።

☞ የተለያዩ ከተማ-ነክ ወሬዎችም አሉን።

ለአስተያየቶቻችሁ በ011 -1- 27 5454 ደውሉልን።

አጫጭር መልዕክቶቻችሁንም :- በ8101 እና በ0939-939393 አኑሩልን!

ሰኞ የካቲት 25/2016 ዓ.ም.  …  የ“ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ  … ከ10:00 እስከ 12:00 ሰዓት ድረስ  መሰናዶዎቹን ያቀርባል።☞  በ"10 ከ 1...
04/03/2024

ሰኞ የካቲት 25/2016 ዓ.ም. … የ“ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ … ከ10:00 እስከ 12:00 ሰዓት ድረስ መሰናዶዎቹን ያቀርባል።

☞ በ"10 ከ 10" ቅንብራችን በዘመነ-አጤ ኃይለሥላሴ እና በደርጉ ዘመን በተለያዩ መንግስታዊ ኃላፊነቶችና በዲፕሎማሲው መስክ፤... እንዲሁም የተለያዩ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን በመመሥረትና በመምራት ቅን አገልግሎት በመስጠታቸው የሚታወቁትን አቶ ሽመልስ አዱኛን ያመሰግናል። የዚህ ሳምንት የ"10/10 ባለክብራችን"ም አድርገናቸዋል!!!

☞ የኦምኒ ሚዲያ የሙዚቃ መረጃዎችንም ታገኛላችሁ።

☞ የ“ዘፈን እና ዘመን” መሰናዶአችን ደግሞ "ከአዳዲሶቹ አልበሞች ቡፌ ምን አዲስ ቀለም እና ይዘት አገኘን? …" በሚል ርዕስ ዳሰሳ ያካሂዳል።

☞ ከየአቅጣጫው ያሰባሰብናቸው የከተማ ወሬዎችም ይኖሩናል።

ለአስተያየቶቻችሁ በ011 -1- 27 5454 ደውሉልን።

አጫጭር መልዕክቶቻችሁንም :- በ8101 እና በ0939-939393 አኑሩልን!

ዛሬ ሐሙስ የካቲት 21/2016 ዓ.ም.  …  “ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ  … ከ8:00 እስከ 10:00 ሰዓት ድረስ  መሰናዶዎቹን ያቀርባል።☞  ዛሬም "ሰ...
29/02/2024

ዛሬ ሐሙስ የካቲት 21/2016 ዓ.ም. … “ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ … ከ8:00 እስከ 10:00 ሰዓት ድረስ መሰናዶዎቹን ያቀርባል።

☞ ዛሬም "ሰፈራችን" በተሰኘው መሰናዶአችን "አብነት" ላይ እንቆያለን!

☞ ተጓዡ ጋዜጠኛ ሔኖክ ስዩም "ጉዞ ሔኖክ" በተሰኘ ቅንብሩ ስለዐድዋ ድል ከፍታ፣ ስለአበው ጀግኖች እውነታ ያወጋናል። ስለታላቁ ድልና አበው ጀግኖች ሲያወጋ በኩራት፣ ስለአንዳንዶቻችን ሲናገር በቁጭት ነው።

☞ የተለያዩ ከተማ-ነክ ወሬዎችም አሉን።

ለአስተያየቶቻችሁ በ011 -1- 27 5454 ደውሉልን።

አጫጭር መልዕክቶቻችሁንም :- በ8101 እና በ0939-939393 አኑሩልን!

ሰኞ የካቲት 17/2016 ዓ.ም.  …  የ“ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ  … ከ10:00 እስከ 12:00 ሰዓት ድረስ  መሰናዶዎቹን ያቀርባል።☞  የ"10 ከ 1...
26/02/2024

ሰኞ የካቲት 17/2016 ዓ.ም. … የ“ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ … ከ10:00 እስከ 12:00 ሰዓት ድረስ መሰናዶዎቹን ያቀርባል።

☞ የ"10 ከ 10" ቅንብራችን ከትናንት በስቲያ አዲስ አገልግሎት መስጫ ሕንጻ ገንብቶ ያስመረቀውን "ብሔራዊ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት ኤጀንሲ (ወመዘክር)"ን ያመሰግናል። የዚህ ሳምንት የ"10/10 ባለክብራችን"ም አድርገነዋል!!!

☞ የኦምኒ ሚዲያ የሙዚቃ መረጃዎችን ታገኛላችሁ።

☞ የ“ዘፈን እና ዘመን” መሰናዶአችን ደግሞ …"ተደጋግመው ያልተሰሙ የጌታቸው ካሣ ሙዚቃዊ ጉዳዮች"ንይዳስሳል።

☞ ከየአቅጣጫው ያሰባሰብናቸው የከተማ ወሬዎችም ይኖሩናል።

ለአስተያየቶቻችሁ በ011 -1- 27 5454 ደውሉልን።

አጫጭር መልዕክቶቻችሁንም :- በ8101 እና በ0939-939393 አኑሩልን!

ሰማይ ላይ ያለህ ቢመስልህ .. የመሬቱ እንደሚያስፈልግህ አትርሳ።ወይ አዲስ አበባ!
22/02/2024

ሰማይ ላይ ያለህ ቢመስልህ .. የመሬቱ እንደሚያስፈልግህ አትርሳ።

ወይ አዲስ አበባ!

ዛሬ ሐሙስ የካቲት 14/2016 ዓ.ም.  …  “ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ  … ከ8:00 እስከ 14:00 ሰዓት ድረስ  መሰናዶዎቹን ያቀርባል።☞  ዛሬም "ሰ...
22/02/2024

ዛሬ ሐሙስ የካቲት 14/2016 ዓ.ም. … “ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ … ከ8:00 እስከ 14:00 ሰዓት ድረስ መሰናዶዎቹን ያቀርባል።

☞ ዛሬም "ሰፈራችን" በተሰኘው መሰናዶአችን ስለ"ፒያሳ" የምንላችሁ አለን!

☞ ተጓዡ ጋዜጠኛ ሔኖክ ስዩም "ጉዞ ሔኖክ" በተሰኘ ቅንብሩ "የካቲት ልዩ ወር" ናት ይለናል። ከሀገራችን ጋር የተያያዙ የተለያዩ ታሪካዊ ኹነቶችንም ይዳስሳል።

☞ የተለያዩ ከተማ-ነክ ወሬዎችም አሉን።

ለአስተያየቶቻችሁ በ011 -1- 27 5454 ደውሉልን።

አጫጭር መልዕክቶቻችሁንም :- በ8101 እና በ0939-939393 አኑሩልን!

ሰኞ የካቲት 11/2016 ዓ.ም.  …  የ“ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ  … ከ10:00 እስከ 12:00 ሰዓት ድረስ  መሰናዶዎቹን ያቀርባል።☞  የ"10 ከ 1...
19/02/2024

ሰኞ የካቲት 11/2016 ዓ.ም. … የ“ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ … ከ10:00 እስከ 12:00 ሰዓት ድረስ መሰናዶዎቹን ያቀርባል።

☞ የ"10 ከ 10" ቅንብራችን ፈላስፋውን፣ የሃይማኖት ሊቁንና ዲፕሎማቱን ዶ/ር እጓለ ገብረዮሐንስን ያነሳል፤ ያመሰግናል፡፡ የዚህ ሳምንት የ"10/10 ባለክብራችን"ም አድርገናቸዋል!!!

☞ የኦምኒ ሚዲያ የሙዚቃ መረጃዎችን ታገኛላችሁ።

☞ የ“ዘፈን እና ዘመን” መሰናዶአችን ደግሞ … "የፍቅር ነገር በዜማ አቀማጣዩ አንጋፋ ሙዚቀኛ ሥራዎች ሲቃኝ፤ -- ብሎ በኤፍሬም ታምሩ ሥራዎች በኩል ስለፍቅር ያወጋችኋል።

☞ ከየአቅጣጫው ያሰባሰብናቸው የከተማ ወሬዎችም ይኖሩናል።

ለአስተያየቶቻችሁ በ011 -1- 27 5454 ደውሉልን።

አጫጭር መልዕክቶቻችሁንም :- በ8101 እና በ0939-939393 አኑሩልን!

10ከ 10 ለየትነበርሽ ንጉሴ!
15/02/2024

10ከ 10 ለየትነበርሽ ንጉሴ!

ዛሬ ሐሙስ የካቲት 7/2016 ዓ.ም.  …  “ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ  … ከ8:00 እስከ 10:00 ሰዓት ድረስ  መሰናዶዎቹን ያቀርባል።☞  ዛሬም በ"ሰ...
15/02/2024

ዛሬ ሐሙስ የካቲት 7/2016 ዓ.ም. … “ወይ አዲስ አበባ” የሬድዮ ዝግጅት በሸገር FM 102.1 ላይ … ከ8:00 እስከ 10:00 ሰዓት ድረስ መሰናዶዎቹን ያቀርባል።

☞ ዛሬም በ"ሰፈራችን" መሰናዶ ክፍል 2 ቅንብራችን "ችሎት እና አካባቢው" ላይ እንቆያለን!

☞ ተጓዡ ጋዜጠኛ ሔኖክ ስዩም "ጉዞ ሔኖክ" በተሰኘ ቅንብሩ የአንትሮፖሎጂ ቀንን አስመልክቶ የሚለን አለው። ለዘርፉ አስተዋጽኦ ያደረጉ ምሁራንም ያወሳል።

☞ የተለያዩ ከተማ-ነክ ወሬዎችም አሉን።

ለአስተያየቶቻችሁ በ011 -1- 27 5454 ደውሉልን።

አጫጭር መልዕክቶቻችሁንም :- በ8101 እና በ0939-939393 አኑሩልን!

ዘፈን እና ዘመን  - በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተሰሩ ሙዚቃዎቻችን!
15/02/2024

ዘፈን እና ዘመን - በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተሰሩ ሙዚቃዎቻችን!

13/02/2024
እንኳን ለሬድዮ ቀን አደረሳችሁ!===================እንኳን ለሬድዮ ቀን አደረሰን፤ አደረሳችሁ። ከኢትዮጵያ ሬድዮ ልደት (1928 ዓም) አንስቶ እስካለንበት ዘመን ድረስ የሬድዮ ጉዞ...
13/02/2024

እንኳን ለሬድዮ ቀን አደረሳችሁ!

===================

እንኳን ለሬድዮ ቀን አደረሰን፤ አደረሳችሁ። ከኢትዮጵያ ሬድዮ ልደት (1928 ዓም) አንስቶ እስካለንበት ዘመን ድረስ የሬድዮ ጉዞ በሀገራችን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ውስጥ የላቀ ሚና ነበረው፤ አለውም። --- 88 ደመራዎችን የለኮሰው አረጋዊው "ሬድዮ" ለሀገራችን ሙዚቃ ዕድገትና ሥነ-ጽሑፍ ማበብ ያደረገው አስተዋጽኦ 1፣2 ... ተብሎ ተቆጥሮ የሚዘለቅ አይደለም። ሕዝባችንንም ለዓለም አቀፍ መረጃና ዕውቀት ቅርብ አድርጎታል። በዚሁ ይብቃ ብለን ነው እንጂ .. ሌላም ብዙ፣ ብዙ የሬድዮ በረከቶችን ማውሳት እንችላለን።

በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ!

Address

General Abebe Damtew Street
Addis Ababa

Telephone

+251944747474

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ወይ አዲስ አበባ በሸገር ኤፍኤም 102.1 Wey Addis Ababa on Sheger FM 102.1 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ወይ አዲስ አበባ በሸገር ኤፍኤም 102.1 Wey Addis Ababa on Sheger FM 102.1:

Videos

Share

Category

Nearby media companies