Memher Yohannes Eshetu

Memher Yohannes Eshetu በዚህ ገፅ ላይ መንፈሳዊ ትምህርቶችና የቴክኖሎጂ ዕውቀቶች ይተላለፋሉ።

👉 ሰሉስ የብሉይ ኪዳን ትርጓሜ አርብ ደግሞ ቅኔ ዘአርብ በሚል ስያሜ የቅኔ ቀን ነው።

+አደራ ተቀባዩ+ዮሐንስ ተብለው የተጠሩ ብዙ ቅዱሳን አሉ ከእነዚያም ውስጥ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ፤ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ለአብነት ያህል ይጠቀሳሉ ። ዮሐንስ ተብለው የተሰየሙ ሁሉ...
12/01/2024

+አደራ ተቀባዩ+

ዮሐንስ ተብለው የተጠሩ ብዙ ቅዱሳን አሉ ከእነዚያም ውስጥ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ፤ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ለአብነት ያህል ይጠቀሳሉ ። ዮሐንስ ተብለው የተሰየሙ ሁሉም ቅዱሳን ማለት ይቻላል የስማቸው ትርጓሜ እያስገደዳቸው ነው መሰል ሁሉም ለቤተ ክርስቲያን ደስታ ሁነዋታል ።

ኮከብ ከኮከብ ጣትም ከጣት እንደሚበልጥ ሁሉ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ከሁሉ ልቆ ክብሩ እንደ ጠዋት ጮራ ሲያበራ እናየዋለን ። ዮሐንስ በእድሜው ከሐዋርያት ሁሉ በጊዜው ትንሹ
ሲሆን በሕይወተ ሥጋ በመኖር እና በክብሩ ደግሞ ትልቁ ነው ።

ቅዱስ ወንጌል > ብሎ የቀጸለውም ለዮሐንስ ነው ። ይኽን ሲል ግን ጌታ ሌሎቹን ሐዋርያቶቹን አይወዳቸውም ማለት አይደለም ። ዮሐንስ ጌታን እጅግ በጣም በመውደዱ ሲሆን የጌታ ፍቅርም በእኛ ላይ የሚታየው በወደድነው መጠን ነው ሲል ነው ።

ጌታ እና ሐዋርያቱ የፋሲካውን እራት እየበሉ ሳለ ጌታ > ዮሐ 13:21 ብሎ ስለይሁዳ በተናገረበት ሰዓት ሁሉም ሐዋርያት ስለማን እንደተናገረ ተጠራጥረው እርስ በእርሳቸው ተያዩ ። ዮሐንስም ከጌታ አጠገብ ተቀምጦ ነበር ። ከሐዋርያት በእድሜ አንጋፋው እና አለቃቸው ጴጥሮስም ዮሐንስን ጠቀሰና > ዮሐ 13:24 ከአንድ ሰው የምንፈልገውን ነገር ለማግኘት በሚወደው ሰው በኩል እንደምናስጠይቀው ሁሉ ጴጥሮስም ይህንን መንገድ ነበር የተጠቀመው ።

ከእራቱ በኋላም > ሲል የተደመጠው ጴጥሮስ ከዶሮ ጩኸት አስቀድሞ ሦስት ጊዜ ሲክደው ልጅ እግሩ ዮሐንስ ግን እስከ መቃብር ተከተለው ።

ጌታ በመስቀል ላይ የተቀበለውን መከራ አይቶ የዓይን ምስክር ሁኖ በመጻፉ ዮሐንስን ከሌሎቹ ወንጌላውያን ልዩ ያደርገዋል ።

መከራውን ካየ በኋላ ዮሐንስ የምድር ላይ ቀሪ ዘመኑን በሐዘን ነው የጨረሰው ። ይኽንን ሐዘኑን ይረሳና ይጽናና ዘንድ እንዲሁም እስከ መስቀል ለደረሰው ፍቅሩ ሽልማት ይሆነው ዘንድ ጌታ አቻ የማይገኝላትን በምድር አንድ ያለችውን እናቱን > ብሎ ሸለመው ።

እመቤታችን እንደ ዮሐንስ አይነት ላሉ ጌታ የወደዳቸው እነሱም የወደዱት ስጦታ ናት ። እንደ ዮሐንስ ጌታን ስትወደው እርሱም ሲወድክ ከጌታ የሚበረከትልክ ስጦታ ቢኖር እመቤታችን ናት ። እመቤታችን ሩጫክን ስትጨርስ የምትበረከትልክ ሜዳልያ ፤ የምትቀዳጃት ዘውድ ናት ።

ለዮሐንስ ጌታ እናቱን ከመስጠቱ አስቀድሞ የጌታን ፊት ለማየት በብረት መደብ አፈር አስሞልቶ 40 ዘመን ተሸክሞ ከዞረው ከሙሴ እና ከኤልያስ ጋር በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን አሳይቶታል ።

ጌታ ዮሐንስንም ይስመው እንደነበር የመልክአ ኢየሱስ ደራሲ > የልቡ እና የሕሊናው ንጽሕና ለዓይንኽ ባማረው ጊዜ ዮሐንስን ለሳመው አፍኽ ምስጋና ይገባል እያለ በምስጢር አዋዝቶ ያመሰግናል ።

ዲያቆን ኃ/ኢየሱስ በሻህ (Kin Bebi
ጥር ዮሐንስ 2016 ዓ.ም

ዘመናተ ከፈለ ፣ ወአውረደ ልዑለዓመተ ዓለም ለሁለት ለተከፈለበት ፣ ዘኢይትረአይ ወዘኢይትዓወቅ የሚባል ጌታ አምላክ ወሰብእ ለተባለበት በዓለ ልደት እንኳን በሰላም አደረሰን። ድንግል በጽንሷ ...
07/01/2024

ዘመናተ ከፈለ ፣ ወአውረደ ልዑለ

ዓመተ ዓለም ለሁለት ለተከፈለበት ፣ ዘኢይትረአይ ወዘኢይትዓወቅ የሚባል ጌታ አምላክ ወሰብእ ለተባለበት በዓለ ልደት እንኳን በሰላም አደረሰን።

ድንግል በጽንሷ ጊዜ ወደ ማኅጸኗ አጎንብሳ የምትሰማው የመላእክትን ዝማሬ ብቻ ነበር። ጌታን በወለደች ጊዜ ግን የመላእክትን ብቻ ሳይሆን አዝማደ መለኮት መላእክት ፣ አዝማደ ትስብእት ኖሎት በአንድ ሆነው ሲያመሰግኑ ሰማች።

አአምን በልደተ ወልድከ እምአንቀጸ ማኅፀን ንሱግ
ወበተገዝሮቱ በሐፂን ዘከመ አዘዘት ሕግ
እግዚአብሔር አሐዱ አምላከ ሠለስቱ አዕሩግ
ግዝር ሕዋሳትየ እምቁልፈተ እከይ ወጹግ
በመጥባሕተ መንፈስ የዋህ ወአኮ ፀዋግ

ከድንግል እናትነት ከጌታ ልደት የሚገኘው በረከት አይለየን። መልካም በዓለ ልደት።

በህይወታችን ልንሰማቸው የምንጓጓላቸው ነገሮች ብዙ ናቸው። ተማሪው ውጤቱን ሰምቶ ስለማለፉ ፣ ነጋዴው ስለማትረፉ ፣ ሰራተኛው ስለ ዕድገቱ ለመስማት ከልብ ይጨነቃል ይጓጓል። የደስታውን ነገር ...
29/12/2023

በህይወታችን ልንሰማቸው የምንጓጓላቸው ነገሮች ብዙ ናቸው። ተማሪው ውጤቱን ሰምቶ ስለማለፉ ፣ ነጋዴው ስለማትረፉ ፣ ሰራተኛው ስለ ዕድገቱ ለመስማት ከልብ ይጨነቃል ይጓጓል። የደስታውን ነገር በሰማ ጊዜ ደግሞ ውሳጣዊ ደስታ ይሰማዋል።

የቅዱስ ገብርኤል ዜና ብስራት ግን ያስደሰተው አንድን ሰው ብቻ አይደለም። መላውን የአዳም ልጅ ነው እንጂ። "ትወልዲ" የሚለውን ቃል ለሀና ልጅ ሲያሰማ የአዳም ነፍስ በፍጹም ደስታ ላይ ሆና የቀራንዮን ስቅለት ትጠብቅ ነበር። ብስራቱን ሲነግር "ፍስሐ ኩሉ ዓለም" ብሎም አይደል?

ዳግመኛም ሞት የተሸነፈበትን ፣ መቃብር ድል የተነሳበትን የጌታን ትሳኤ በዕለተ ዓርብ ለሴቶች የሰበከላቸው ገናናው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው። ኋላም በጊዜ ምጽዓት ሰማይና ምድር በሚያልፉበት ጊዜ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት ሆኖ ለሰው ልጆች ምህረትን የሚለምነው የአምላክን የተዋህዶ ስም የያዘው ቅዱስ ገብርኤል ነው።

አመ ሐወጸ ዓለመ መኮንነ ሥጋ ወነፍስ
ገብርኤል ተለውኮ እምነ ምጽናዕ ኃምስ
እምፅንሰ ኤልሳቤጥ ጠንቂቆ ኁልቆ ወርኅ ሳድስ

ጌታን እስከ አምስተኛው ሰማይ ድረስ ከተከተለው ፣ ሠለስቱ ደቂቅን ከእሳት ካወጣ ቅዱስ ገብርኤል በረከትና ረድኤት ይክፈለን። አሜን!

"መቅደስ ዘይኬልልዋ ኪሩቤል"ሰማይና ምድርን በማኅጸኗ የተሸከመች ንጽህት ድንግል በሶስት ዓመቷ ወደ ቤተ መቅደስ ልትገባ ባለች ጊዜ "የምግቧ ነገር" ጥያቄ ሆኖ ተነሳ። እንዴት የህይወት እንጀ...
13/12/2023

"መቅደስ ዘይኬልልዋ ኪሩቤል"

ሰማይና ምድርን በማኅጸኗ የተሸከመች ንጽህት ድንግል በሶስት ዓመቷ ወደ ቤተ መቅደስ ልትገባ ባለች ጊዜ "የምግቧ ነገር" ጥያቄ ሆኖ ተነሳ። እንዴት የህይወት እንጀራን የምታስገኝ መሶብ ላይ የምግብ ነገር ጥያቄ ሆኖ ይነሳል?

እርሷማ ሰማያዊ ምግብና መጠጥን እንደ ዕለት እንጀራ ስትመገብ አድጋለች። ያውም መልዓኩ ቅዱስ ፋኑኤል ክንፉን ጋርዷት ፣ ሰማያዊ መዓዛ መላዕክትን እያሸተተች ፣ ውዳሴ መላዕክትን እየሰማች ፣ መላእክት በቤተ መቅደስ እየጎበኟት ነው እንጂ።

የመላእክት ደስታቸው የሚላት አንድም ለዚህ አይደል። በንጽህና የሚመስላቸው ከፍጡራን ወገን አንድ እሷን አግኝተው እኮ ነው። ዛሬም በመቅደሱ እንደ ልጅነቷ ትኖራለች። ኪሩቤል የሚጋርዷት አማናዊቷ መቅደስ ድንግል ማርያም የእኛን የልጆቿን ጸሎትም ትሰማለች።

05/12/2023

አምላክነሰ ኀይልነ ወጸወንነ

የደማስቆ እና የአራም (ጠበቅ ተደርጎ የሚነበብ) ንጉስ እንዲሁም የኤፍሬም ልጆች በአካዝ ላይ በተነሱበትና መከራን ባበዙበት ጊዜ ንጉሱ አካዝ ወደ እግዚአብሔር አመለከተ። እግዚአብሔርም የጠላቶቹን መውደቅ ሳይውል ሳያድር አሳየው። ይህንን ክስተት አስቀድሞ በዓይነ መንፈስ የተመለከተው የእሴይ ልጅ ዳዊት "አምላክነሰ ኀይልነ ወጸወንነ" እያለ "በእንተ አካዝ ወሕዝቅያስ" ዘምሯል።

በመዝሙር 45 ላይ የሚገኘው ይህ ሀይለ ቃል እግዚአብሔር ለታመኑበት ሰዎች መሸሸጊያ የሚሆን ተራዳዒ አምላክ መሆኑን በሰፊው ይተነትናል። በመከራችን ፣ በችግራችን ፣ በተለያዩ አስቸጋሪ የህይወት መንገዶቻችን ላይ ሳለን አምላካችን ሃይላችን እና መሸሸጊያችን እንደሆነ ልናምን ይገባል።

የክርስቶስን አዳኝነት በልባችን መዝገብ ላይ ጽፈን በተረዳን ጊዜ ከንጉሱ ከዳዊት ጋር "እግዚአ ኀያላን ምስሌነ ፣ ወምስካይነ አምላኩ ለያዕቆብ" እያልን እንዘምራለን።

"ማርያም ጽዮን ታቦተ ቃለ ጽድቅ መንፈቀ እስራ"እንኳን ለበዓለ ጽዮን ማርያም በሰላም አደረሰን!
30/11/2023

"ማርያም ጽዮን ታቦተ ቃለ ጽድቅ መንፈቀ እስራ"

እንኳን ለበዓለ ጽዮን ማርያም በሰላም አደረሰን!

https://m.youtube.com/watch?v=Ac8qBhgOH-Q
18/11/2023

https://m.youtube.com/watch?v=Ac8qBhgOH-Q

ዛሬ የተሰጠን አንደበት ነገ በመቃበር ይዘጋል ፤ ዛሬ የምናወራበት ምላስ ነገ በአፈር ይታሰራል ፤ ቀኑ አጥሮብን ሌሊቱንም የምንራወጥበት እግርም በሳጥን ይገደባል፤ በትንሹ የግንባር ሜ....

በዓለ ቁስቋም (ጊዜ ዕረፍት ወሚጠት)ሰላም ለኅንብርትኪ ወለድንግልናኪ ሕኑጽለሐቈኪ ሰላም ቀዳሜ አብራክ አቁያጽማርያም ኅድሪ ውስተ ቤትየ ሕጹጽአኮኑ ኀደርኪ በቁስቋም ወአንሶሰውኪ በግብጽእንዘ ...
16/11/2023

በዓለ ቁስቋም (ጊዜ ዕረፍት ወሚጠት)

ሰላም ለኅንብርትኪ ወለድንግልናኪ ሕኑጽ
ለሐቈኪ ሰላም ቀዳሜ አብራክ አቁያጽ
ማርያም ኅድሪ ውስተ ቤትየ ሕጹጽ
አኮኑ ኀደርኪ በቁስቋም ወአንሶሰውኪ በግብጽ
እንዘ ውስቴታ ጣዖት ዘብሩር ወዕፅ

ደራሲ እመቤታችንን ሲጠራ እንዲያው በደፈናው ሳይሆን ምስጢርን ከምስጢር አያይዞ ነው። ይህንንም ሲያስረዳ እንዲህ ይላል።

እመቤቴ! ግብጽ በውስጧ የብርና የእንጨት ጣዖት የሞላባት ሆና ሳለች ፥ በእርሷ ተመላልሰሻልና በቁስቋምም አድረሻልና ፤ በጎዶሎ ቤቴ ገብተሽ እደሪ።

እመቤታችን በህይወታችን ገብታ ጎዶሎውን ሁሉ ትሙላልን።

አመ ሰሙኑ ለህዳርየሥላሴን መለኮታዊ ጥበብና በየዘመናቱ የነበሩትን አበው እያነሳ ፣ አሁን ላለነው ምዕመናን ትምህርት የሚሰጠን "ጠቢበ ጠቢባን" የተሰኘው ጥንታዊ መጽሐፍ በወንድማችን ዲያቆን ...
13/11/2023

አመ ሰሙኑ ለህዳር

የሥላሴን መለኮታዊ ጥበብና በየዘመናቱ የነበሩትን አበው እያነሳ ፣ አሁን ላለነው ምዕመናን ትምህርት የሚሰጠን "ጠቢበ ጠቢባን" የተሰኘው ጥንታዊ መጽሐፍ በወንድማችን ዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው በአማርኛ ግጥም ተተርጉሞ ቀርቦልናል። መጽሐፉ ህዳር ፰ ቀን ይመረቃልና ሁላችንም በቦታው ተገኝተን የጠቢባን ሥላሴን ድንቅ ምስጢር እንስማ።

"እስመ ገብር ኩለሄ ዘወሀበ እዶ" ነውና እጅ አትስትጥ!👉🏽 የሰው ልጅ "እጅ መስጠትን" ብዙ ጊዜ ከጦርነት ጋር ያይዘዋል። በስጋዊ ህይወታችን እጅ የምንሰጥባቸው ሽንፈቶቻችን ግን ብዙ ናችው።...
23/10/2023

"እስመ ገብር ኩለሄ ዘወሀበ እዶ" ነውና እጅ አትስትጥ!

👉🏽 የሰው ልጅ "እጅ መስጠትን" ብዙ ጊዜ ከጦርነት ጋር ያይዘዋል። በስጋዊ ህይወታችን እጅ የምንሰጥባቸው ሽንፈቶቻችን ግን ብዙ ናችው። አሁን አሁን የምንሰማው ራስን የማጥፋት እና እግዚአብሔርን የመበደል ፣ ብሎም ክብርት የሆነችውን ዘለዓለማዊት ነፍስ ያለማክበር ተግባር የሚመጣው ለችግሮቻችን እጅ ከመስጠት ነው። የችግሮቻችን ልኬቶችና መጠኖች በእጅጉ የከበዱና የሚያስፈሩ ቢሆኑ እንኳን ፤ በአምላካችን ዘንድ ቀሊላን እንደሆኑና እርሱ በቀላሉ ሊያሻግረን እንደሚችል ማመን ደግሞ የሚያድነን መፍትሄ ነው።

👉🏽 አንዳንድ ጊዜ የችግሮችን ልክ ስናስብ ፤ እንድማንጽርያ እንኳን ለመውሰድ የማይመች ቢሆንም ከእመቤታችን በላይ መከራን ፣ ችግርን ፣ ስቃይን ፣ መገፋትን ፣ መቁሰልን ፣ መድማትን ያየ ሰው አይኖርም። እመቤታችን ስደትን እና መገፋትን ገና በልጅነቷ አንድያ ልጇን ይዛ በግብጽ በረሃ ፣ በማታውቀው ሀገር ፣ ሐሩረ ፀሀዩና ቁረ ሌሊቱ በጸናበት ፣ አክይስት እና አቃርብት በሞሉበት ጎዳና ስትጓዝ በዓይነ ህሊናችን ስናስብ "እንዴት" የሚል ጥያቄ ያጭርብናል። ምክንያቱም ሰማይና ምድርን የፈጠረ ፣ ሁሉን ማድረግ የሚቻለውን ጌታ ይዛ ነበርና።

👉🏽 እመቤታችን ይህን ሁሉ ችግር በትእግስት ሲብስም በሀዘነ ልብ እና በለቅሶ ታሳልፈው ነበር። የደረሰባት መከራ እንደኛ በሀሳብ ላይ የተጫነ ብቻ አልነበረም አካላዊም (በእሾኽ መወጋት ፣ በድንጋይ መደናቀፍ ፣ መውደቅ መነሳት ፣ ረሀብ ፣ ጥም...) ጭምር ነው። ታዲያ ድንግል በዚህ ሁሉ መከራና ሀዘን ልጇን ወዳጇን አምላኳን ተስፋ አድርጋ ትኖር ነበር እንጂ ለመከራውና ለመገፋቱ "እጅ አልሰጠችም"። እኛም የሚመጣብንን ችግር ሁሉ በጌታ እርዳታ ማሸነፍ እንደምንችል ማሰብ ይገባናል። ያለን አንድ አማራጭ ይህ ብቻ ነው።

👉🏽 በዛሬው ቅኔያችን ያማረውን መጽሐፋዊ መንገድ ተከትለን ዘመነ ስደትን ከአሁናዊ ህላዌ ጋር ዳስሰንበታል። ንጉሰ ይሁዳ ያለው "ወተቀንየ ኢዮአቄም ንጉሰ ይሁዳ ለንጉሰ ግብጽ ሠለስተ ዓመተ" ያለውን ይዞ ነው።

መወድስ ዘዮሐንስ
ዓይነ ማርያም ድንግል ንጉሰ ይሁዳ
በሀዘነ ልብ ተቀንየ ለንጉሰ ግብጽ ተሰዶ
ሠለስተ ዓመተ እንዘ ያደንን ክሳዶ
ለእመ ነሀትት እምቀዳሚ
እስመ ገብር ኩለሄ ዘወሀበ እዶ
ወገዳመ ዕዝራ እንተ ያውኢ
ነደ ሰማርያ ረሀብ ለዮሴፍ ያነድዶ

ተቀብረሂ ታህተ ማኅረጽ እንዘ የሀድግ ማኅፈዶ
እግረ ሰሎሜ ሴዴቅያስ እንተ ደም የዓውዶ
ወለተገፍዖ ይስማኤል እምነ አመት ወለዶ
ፀሐየ ዘአምለከ አብርሃም ተዋርዶ

21/10/2023

"ሰአሉ ለነ ኢያቄም ወሐና ዘፈረይክሙ በቅድስና መሶበወርቅ እንተ መና"

👉🏽 በገድል በፆም በጸሎት የጸናችሁ በመና የተመሰለ ኢየሱስ ክርስቶስን የወለደች እርሷም በመሶብ ምሳሌነት በደጋግ አባቶች እና ሊቃውንት በደገኛው ምሳሌነት የተጠቀሰች ድንግል ማርያምን የወለዳችሁ ቅዱስ ኢያቄም እና ቅድስት ሐና በቃል ኪዳናችሁ ለተማጸንን ለእኛ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ በሚሰማ ጸሎታችሁ ከክፉ ሁሉ እንድን ዘንድ ለምኑልን!!! አማልዱን!!!

👉🏽 የቅዱስ ኢያቄም እና የቅድስት ሐና ጸሎት ልመና እና በረከት በሐገራችን እና በአማላጅነታቸው በምናምን በሁላችን ይደርብን አሜን!!!

ያማረውን ጣዕመ ዜማ ባማረ ላህይ ወንድማችን ሊቀ መዘምራን ዘርይሁን ወርቅነህ እንዲህ አሰምቶናል።

14/10/2023

ሊቀ ጠበብት ተስፋ አስማረ ዘማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ

 ቀደምት እረኞች የበጎቻቸው ነገር በእጅጉ ያሳስባቸዋል። የዘመናችን እረኞች በየቦታው ያሉ በጎቻቸው ሲታረዱ ከመመልከት ውጪ ምንም ማድረግ አለመቻላቸው የሚያሳዝናቸው ይመስለናል። ነገር ግን የ...
06/10/2023



ቀደምት እረኞች የበጎቻቸው ነገር በእጅጉ ያሳስባቸዋል። የዘመናችን እረኞች በየቦታው ያሉ በጎቻቸው ሲታረዱ ከመመልከት ውጪ ምንም ማድረግ አለመቻላቸው የሚያሳዝናቸው ይመስለናል። ነገር ግን የበጎቻቸው ሀሳብ ምን እንደሆነ መረዳት በራሱ ያሉትን መሰረታዊ ችግሮች ለመፍታት ቀዳሚ መንገድ መሆኑ የማይካድ ሀቅ ነው።

በብሉይ ዘመን ለነበረው ሊቀ ካሕናት "ደብተራ ኦሪት" መኖርያው ፣ መሸሸጊያው ብሎም መመኪያው ሀገሩ ነበረች። በእርሷ ክብር ውስጥ የእርሱ ክብር ጎልቶ ይታያል። ካሕን በየትኛውም ሀገር ፣ በየትኛው ሁኔታና አስተሳሰብ ክቡር ነው። የእግዚአብሔር ልዑክ ነውና።

በዘመናችን ግን ለካሕን የህይወቱ መሰረት ፣ የኑሮው ምልክት የሆነችው ቤተ መቅደስ የሞቱ ምክንያትና መቃብሩ ከሆነች ሰነባብተናል። ካሕን በጠራራ ፀሐይ ይዋረዳል ፣ ይገደላል። ይህ የትውልድ ክሽፈት ፣ የህሊና ንቅዘት ያመጣው አባዜ ከእረኞቻችን እንቅልፍ ጋር ተዳምሮ የተለመደ የዕለት ተዕለት ዜና ሆኗል።

ቅኔያችን በዚህ ሀሳብ ላይ ያጠነጥናል።

መወድስ ዘዮሐንስ

ኖሎተ ሳምኒት ዘመን እንዘ ይነውሙ
ውስተ ፍና ሰናክሬም ሞት አባግዓ ቤቶሙ ተሰወሩ
እመ ኖላዊ ይነውም ውስተ ውሳጢት ማኅደሩ
እስመ ለአባግዕ ይበልዖሙ
መቃብር አርዌ አደንግጾ ዘቀሊል እግሩ
ወእንዘ ኖሎተ ይሰመዩ
ፍና አባግዕ አዕላፍ እምነ ልቦሙ ኢያእመሩ

ቀዳሚትሰ ደብተራ ስምዕ ለሊቀ ካህናት ሀገሩ
አምጣነ ካሕናት በውስቴታ ፍጹመ ይከብሩ
ባህቱ ዘመንነ ሀልቀ ወተወለጠ እምድሩ
እስመ ቤተ መቅደስ ደኃራዊት ለካህን መቃብሩ

ዘበመስቀልከ አቅረብከነ ኀበ አቡከ መልዕልተ ሰማያትበመስቀልህ በጌትነት ወደአለ ወደአባትህ አቀረብከን
28/09/2023

ዘበመስቀልከ አቅረብከነ ኀበ አቡከ መልዕልተ ሰማያት
በመስቀልህ በጌትነት ወደአለ ወደአባትህ አቀረብከን

25/09/2023

ማኅደረ ስብሐት ልዕልት እምነ አድባር ልዑላን

👉 የጌታን መዋዕለ ሥጋዌ ረቂቅ በሆነ ምስጢረ መለኮት ከጻፈው ፣ 👉 ጌታችን አብዝቶ ከሚወደው ፣ 👉 በመስቀሉ ስር ከእናቱ ከድንግል ማርያም ጋር እስከመጨረሻው በታማኝነት ከተገኘው ፣ 👉 የጌታ...
15/09/2023

👉 የጌታን መዋዕለ ሥጋዌ ረቂቅ በሆነ ምስጢረ መለኮት ከጻፈው ፣
👉 ጌታችን አብዝቶ ከሚወደው ፣
👉 በመስቀሉ ስር ከእናቱ ከድንግል ማርያም ጋር እስከመጨረሻው በታማኝነት ከተገኘው ፣
👉 የጌታን እናት "ነያ እምከ" ተብሎ በመስቀል ስር በአደራነት ከተቀበለው ፣
👉 ከሞት ፊት ከተሰወረው ፣

ከዮሐንስ ወንጌላዊ በረከትና ረድኤት ይክፈለን።

ነገረ ጳጉሜን ነዓስጉባኤ ቃና ዘዮሐንስኢተአምርኑ ጳጉሜን አሐቲ በአስተራህቆ ወሊደዲበ ኀምስቱ ውሉድ እስመ ወሰከት አሐደ👉🏽 ዓለም የተፈጠረው መጋቢት 29 ቀን ፣ በዕለተ እሁድ ፣ በዘመነ ዮሐ...
09/09/2023

ነገረ ጳጉሜን ነዓስ

ጉባኤ ቃና ዘዮሐንስ

ኢተአምርኑ ጳጉሜን አሐቲ በአስተራህቆ ወሊደ
ዲበ ኀምስቱ ውሉድ እስመ ወሰከት አሐደ

👉🏽 ዓለም የተፈጠረው መጋቢት 29 ቀን ፣ በዕለተ እሁድ ፣ በዘመነ ዮሐንስ ወንጌላዊ ነው። ዕለተ እሁድ ጥንተ ዕለት (የዕለት መጀመርያ) ፣ ጥንተ መላእክት (መላእክት የተፈጠሩበት) ፣ ጥንተ ቅዳሴ (ምስጋና የተሰማበት) እንዲሁም የሌሎች ጥንታት መሰረት ነው። ከእርሱ ቀጥሎ ያለው ሁለተኛው ቀን ሰኑይ (ሰኞ) ይባላል። ይህ ዕለተ ሰኑይ ጥንተ ሳኒታ (የመጀመርያው ማግስት) ተብሎ ይጠራል። በእነዚህ ሁለት ቀናት ውስጥ "ቁጥር" የተባለው ፤ የሰው ልጆች ዘመናትን እና ሌሎች ሂሳባዊ ስሌቶችን የሚሰሩበት ቀመራዊ ሐሳብ ባለመገኘቱ ምክንያት እነዚህን ዕለታት ቀደምት አባቶቻችን "ዕለተ ጠቢባን" (በጠቢባን ሥላሴ ብቻ የሚታወቁ ዕለታት) ብለው ሰይመዋቸዋል።

👉🏽 ከእነዚህ ዕለታት ቀጥሎ የሚመጣው ዕለት ሠሉስ (ማክሰኞ) የሚባል ሲሆን ፤ የዘመን መለወጫ ሚያዝያ ነውና ዮሐንስ ዘመኑን ፈጽሞ ሚያዝያ 1 ቀን ፣ በዕለተ ሠሉስ ለተቀባዩ ወንጌላዊ ለማቴዎስ ዘመኑን አስረክቧል። ለዚህም ነው ማክሰኞ ጥንተ ቀመር (የቀመር መጀመርያ) ከመባሉ ባሻገር ጥንተ ቀመሩ ለማቴዎስ የሚባለው። በዕለተ ረቡዕ የዘመን መቁጠሪያና መክፈያ የሚሆኑ ፣ በዑደታቸው (በዙረታቸው ዘመንን የሚከፍሉ) ፀሐይ ፣ ጨረቃና ከዋክብት ተፈጥረዋል ዕለቱም ጥንተ ዖን (የፀሐይ ጥንት) ተብሎ ተሰይሟል።

👉🏽 እንግዲህ እኒህ ከላይ የጠቀስናቸው ሐሳቦች ለዘመን ቀመር መሰረቶችና መነሻ ስሌቶች ናቸው። የዛሬው ሐሳባችን ግን ጳጉሜን ላይ ያተኮረ ነው። ዘመን በዕለት ፣ በወርኅ እና በዓመት ይለካል ይሰፈራል። ፀሐይ ዑደቷን ለመፈጸም (ከመነሻ መስመሯ ተነስታ ፣ በክብነት ዞራ ፣ በቀደመው በመነሻ መስመሯ ላይ ተመልሳ ለመድረስ) 365 ዕለታት ፣ ከ15 ኬክሮስ ፣ ከ6 ካልዒት ያስፈልጋታል። ጠቅለል ባለ አጠራር 1 ዓመት ብለን እንጠራዋለን።

👉🏽 12ቱ አውራኅ (ከመስከረም እስከ ነሐሴ ያሉት) 30 ዕለታትን በውስጣቸው ሲይዙ ጳጉሜን ግን ተለይታ አምስት ዕለታትን ትይዛለች (በዘመነ ሉቃስ ስድስት ትሆናለች)። ለዚህም ነው በመርሐ ዕውር አዋጅ ላይ "ወንጌላውያን በዓመት ፣ ጳጉሜን በዕለት" ተብሎ የተጠቀሰው። ወርኃ ጳጉሜን እንደማነሷ አይደለችም። በአምስቱም ሆነ በስድስቱ ዕለታት ሂደቷ ውስጥ መንፈሳዊና ቀመራዊ ምስጢራትን ይዛለች። ከእነርሱ ውስጥ ጥቂቶቹን እንመለክታለን።

1. በአንድ ዓውደ አበቅቴ ዑደት ውስጥ ሶስት ጊዜ የልደተ አበቅቴ መጀመርያ ትሆናለች (ይኸውም በአራተኛው አንቀጸ አበቅቴ በጳጉሜን 3 ፣ በ12ኛው አንቀጸ አበቅቴ በጳጉሜን 5 እና በ15ኛው አንቀጸ አበቅቴ በጳጉሜ 2 ማለት ነው።)

2. በዘመን ቀመር መሰረት አራቱ ክፍላተ ዓመት (ጸደይ ፣ ክረምት ፣ መፀው ፣ ሐጋይ) ዘጠና ዘጠና ቀን ከ315 ኬክሮስ ይደርሳቸዋል። 90 ቀን ለአራት ሲባዛ 360 ይሆናል (ይኸውም ከመስከረም 1 እስከ ነሐሴ 30 ያሉት ዕለታት ናቸው)። ከ315 ኬክሮስ 300 ወስደን 300ን ለ60 ብናካፍል 5 ዕለታት ይተርፋሉ (የጳጉሜን አምስቱ ዕለታት)። ከ315 ኬክሮስ ላይ 300 ኬክሮስ ነስተን 15 ኬክሮስ ይቀረናል። ይኽችውም ከዮሐንስ ጀምራ ሉቃስ ላይ ስትደርስ 60 ትሆናለች (15 ሲባዛ በ4 ስልሳ ይሆናልና)። በሉቃስ 60 ኬክሮስ ስትሞላ 1 ዕለት ተብላ ትቆጠራለች (በሉቃስ ጳጉሜን 6 መሆኗ ለዚህ ነው)

N.B፡ 1 ዕለት = 60 ኬክሮስ

3. አምስተኛይቱ ጳጉሜን ዕለተ ምርያ(ዕለተ መድኃኒት) ትባላለች። ጌታችን የተወለደባትን ዕለት ስለምታስታውቅ ነው። ጳጉሜ አምስት የዋለበት ዕለት እና የጌታችን ልደት የሚውልበት ዕለት አንድ ነውና። ለምሳሌ ጳጉሜ አምስት ሰኞ ቢውል ፣ የጌታ ልደት በዓልም ሰኞ ይሆናል። ለዚህም ነው ጳጉሜ 6 በሆነችበት ዓመት የጌታን ልደት በታህሳስ 28 የምናከብረው።

4. ስድስተኛይቱ ጳጉሜን መጠነ ራብዕት ትባላለች። መጠነ ራብዕት ማለት አራቱ ወንጌላውያን በየዓመታችው ያተርፏት 15 ኬክሮስ ፣ በአራት ዓመት ዑደታቸውን ሲያደርጉ በመገኘቷ ነው። ሠግረ ዮሐንስም ትባላለች። ጳጉሜን ስድስት ስትሆን ከወትሮ በተለየ ዮሐንስ አንድ ዕለት ተራምዶ ዓመቱን ስለሚጀምር ነው።

ለምሳሌ ፦
👉🏽 መስከረም 1 በዘመነ ዮሐስን እሁድ ቢሆን በዘመነ ማቴዎስ መስከረም 1 ሰኞ ይሆናል።
👉🏽 መስከረም 1 በዘመነ ማቴዎስ ሰኞ ቢሆን በዘመነ ማርቆስ መስከረም 1 ማክሰኞ ይሆናል።
👉🏽 መስከረም 1 በዘመነ ማርቆስ ማክሰኞ ቢሆን በዘመነ ሉቃስ መስከረም 1 ረቡዕ ይሆናል።
👉🏽 መስከረም 1 በዘመነ ሉቃስ ረቡዕ ቢሆን በዘመነ ዮሐንስ መስከረም 1 አርብ ይሆናል።

በዚህም መስረት ከሉቃስ ወደ ዮሐንስ ዘመን ሲሸጋገር ፣ ዮሐንስ አንድ ዕለት ተራምዶ መስከረም 1 ላይ መዋሉን ያሳያል።

5. በወርኃ ጳጉሜን የክርስቶስ ምጽዓት ይነገርበታል። በቅኔ እና በትርጓሜ ጉባኤዎች ፣ ከምጽዓቱ ጋር የተያያዙ ትምህርቶች እና ቅኔያት ይነገሩበታል።

6. ጳጉሜን የርኅወተ ሰማይ መጀመሪያ ናት። ርኀወተ ሰማይ በጳጉሜ 2 አልያም በጳጉሜ 3 ጀምሮ በ52 ቀናት ልዩነት ፤ በዓመት 7 ጊዜ ይውላል።

7. ጳጉሜን የሰንበተ ወንጌላውያን መጠሪያ ፣ አምሳል ናት (ዓውደ ጳጉሜን በመባል)። በአራት ዓመት ዑደት እንድትመላ ወንጌላውያንም በአራቱ አጽናፈ ዓለም ወንጌልን ዞረው የማስተማራቸው ምሳሌ ናትና።

8. ጳጉሜ በልደተ አበቅቴ ቀመር ላይ እንደሚጠቀሰው በአልቦ አበቅቴ ጊዜ ፀሐይና ጨረቃ እኩል ዑደታቸውን መስከረም አንድ ይጀምሩ ዘንድ ፤ ያለፈውን ዑደታቸውን የሚፈጽሙባት ወር ናት። በበነጋው መስከረም አንድ ሁለቱም በተፈጠሩበት ኆኅት ተራክቦ ያደርጋሉና።

የቀመር ነገር እንዲህ በቀላሉ አይፈጸምምና ጊዜ ያለው ማንኛውም ሰው በጉባኤያችን በመገኘት ሰፋ ያለውን ትምህርት ማግኘት ይችላል።

ቸር ቀን ይሁንልን።

መጋቤ ብሉይ ዮሐንስ እሸቱ

ርኅወተ ሰማይ (ግንቦት ፲፰)በ365 (366) ዕለታት ወይም በአንድ ዓመት ዐውደ ፀሐይ ውስጥ "ኅሩያን ዕለታት" ከምንላቸው ውስጥ ፤ ቀመራቸውን ከጳጉሜን 3 እየጀመሩ በየ52 ዕለታት ልዩነት ...
08/09/2023

ርኅወተ ሰማይ (ግንቦት ፲፰)

በ365 (366) ዕለታት ወይም በአንድ ዓመት ዐውደ ፀሐይ ውስጥ "ኅሩያን ዕለታት" ከምንላቸው ውስጥ ፤ ቀመራቸውን ከጳጉሜን 3 እየጀመሩ በየ52 ዕለታት ልዩነት የሚውሉ ዕለታት አሉ። እሊህ ዕለታት በጥቅል ቀመራዊ አጠራራቸው "ዕለታት ዘርኅወተ ሰማይ" ይባላሉ።

በነዚህ ዕለታት የሰማይ መስኮት የሚከፈት ሲሆን የሰው ልጆች ጸሎትም ያርጋል። ካህናትም በነዚህ ዕለታት በዘይትና በውሃ ላይ እየጸለዩ ለህሙማን ፈውስን ይሰጣሉ።

በርኅወተሰማዩ ሀገራችንን እንዲጠብቅልን ፣ ክፉውን እንዲያርቅልን ፣ መላዕክትም ጸሎታችንን አሳርገው ከአምላካችን ዘንድ ምህረትን እንዲያሰጡን የሰማይ አምላክ መልካም ፈቃዱ ይሁንልን።

ርኅወተሰማይ የሚውልባቸው እለታት ጳጉሜ 3 ፤ ጥቅምት 20 ፤ ታኅሳስ 12 ፤ የካቲት 4 ፤ መጋቢት 26 ፤ ግንቦት 18 ፤ ሐምሌ 10 ናቸው።

እግዚአብሔር አባታችን ከታላቁ መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል በረከትና ረድኤት ይክፈለን።

በረከተ ብጹዕ አባ ሣዊሮስ ጳጳስ ዘደቡበ ኢትዮጵያ ዘሐነጻ ለማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ይኩን ምስለ ኩልነ ውሉደ ሃይማኖት ርትዕትታላቂቱን ደብር ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማ...
07/09/2023

በረከተ ብጹዕ አባ ሣዊሮስ ጳጳስ ዘደቡበ ኢትዮጵያ ዘሐነጻ ለማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ይኩን ምስለ ኩልነ ውሉደ ሃይማኖት ርትዕት

ታላቂቱን ደብር ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያምን ካነጹት ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ከነበሩት ብጹዕ አባታችን አቡነ ሣዊሮስ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን።

ተክለ ሃይማኖት ሠዋዒ ለእግዚአብሔር ካህኑአድኅነኒ እምጸብአ ከይሲ ዘዐሥር ቀርኑወእምብእሲ ዘክልኤ ልሳኑየእግዚአብሔር ካህን የምትሆን በዓለ መስዋዕት ተክለ ሃይማኖት ሆይ ፣ቀንዱ አስር ከሆነ ...
30/08/2023

ተክለ ሃይማኖት ሠዋዒ ለእግዚአብሔር ካህኑ
አድኅነኒ እምጸብአ ከይሲ ዘዐሥር ቀርኑ
ወእምብእሲ ዘክልኤ ልሳኑ

የእግዚአብሔር ካህን የምትሆን በዓለ መስዋዕት ተክለ ሃይማኖት ሆይ ፣
ቀንዱ አስር ከሆነ ከዲያብሎስ ጥል ፣ ዳግመኛም አንደበቱ ሁለት ከሚሆን ሰው አንተ አድነኝ።

የአባታችን በረከትና ረድኤት ከሁላችን ጋር ይሁን።

 👉🏻 እግዚአብሔርን ለማወቅ እና ለመረዳት በምትነሳበት ቅጽበት እርሱ ወደ አንተ ይቀርባል። ፍጹም ረቂቅ በሆነው ፍቅሩ ስትጠመድ ፣ እርሱን ለማየት ስትጓጓ ፣ ስለ አምላክነቱም ቀናዒ ስትሆን ...
19/08/2023



👉🏻 እግዚአብሔርን ለማወቅ እና ለመረዳት በምትነሳበት ቅጽበት እርሱ ወደ አንተ ይቀርባል። ፍጹም ረቂቅ በሆነው ፍቅሩ ስትጠመድ ፣ እርሱን ለማየት ስትጓጓ ፣ ስለ አምላክነቱም ቀናዒ ስትሆን ጥልቅ የሆነውን የአባትነቱን ፍቅር ያሳይሃል።

👉🏻 የልቡናህ ተምኔት እርሱን ማየት ሆኖ ሳለ ሞት እንኳን ቢቀድምህ ከሙታን መካከል አስነስቶ የመለኮቱን ብርሃን ያሳይሃል። ሞትን ሳትቀምስ በብሄረ ሕያዋን እንኳን ብትኖር "እትአመን ከመ እርአይ ሠናይቶ ለእግዚአብሔር በብሔረ ሕያዋን" እያልክ በነቢዩ ቃል እየዘመርክ በታቦር ተራራ ላይ እንድትገኝ የጸጋውን ሸማ ያለብስሃል።

👉🏻 እርሱ የፍቅር አምላክ ነውና ከአሳ አስጋሪነት አውጥቶ በጥርጣሬ ባህር ላይ የሚዋኘውን ልብህን ፤ ከጨለማው ዓለም በመለኮቱ ብርሃን አውጥቶ ወደ ዕረፍት መንገድ ይመራሃል። የፍቅሩ ማዕበል ከወዲያና ከወዲህ እያማታ ቢያስጨንቅህ "ጌታ ሆይ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው" እያልክ ፤ የምትናገረውን እንኳ እስከማታውቅ ድረስ የልብህን ተምኔት ለእርሱ ትገልጣለህ።

በአማናዊቷ ደብረ ታቦር ቤተ ክርስቲያን ሁልጊዜ እንድንኖር እርሱ ይርዳን።

ዋዜማ ዘዮሐንስ

እፎኑመ ተመነይከ
ዘምስለ ኤልያስ ትንበር ደቂቀ ቤቱ ለዮና
ላዕለ ደብር እምድኅረ ሰማዕከ ዘኤልያስ ዜና፣
እስመ በረሀብ ኤልያስ ይቀትለከ በፍና
ባህቱ ኢትህዝን እምደብረ ሲና
እስመ ሀሎ ዘያወርድ መና

ዘከመ ጸሐፎ ዮሐንስ

04/08/2023



ሀገራችን ኢትዮጵያ የጭንቅ ጊዜ ላይ ትገኛለች። የምንሰማው ነገር በሙሉ የሚያሳዝን ከሆነ ሰነባብቷል። ጥንት በታሪክ ሰላሟን ፣ ፍቅሯን እና የደግ ሰው መኖሪያ መሆኗን የሰማንላት ኢትዮጵያ እንደ ህልም ብሎም እንደ ጢስ ቀትር ታይታ ፣ ምሴት ላይ የጠፋች መስላለች።

ወጣቱ ትውልድ መስራትና ማገልገል በሚችልበት በዚህ ጊዜ በጭንቀት ሲባዝን መታየቱ እንደ ክሽፈት የሚታይ ነገር ነው። ብዙ ቢያወጉ ይዘነጉ ነውና ነገሩ ፣ የኔታ ጠቅለል አድርገው የአሁኒቷን ኢትዮጵያ ገጽታ በቅኔያቸው መስታወት ያሳዩናል። ተቀበል!!!

መወድስ ዘመምህር ዘካርያስ አምባው

ነቂሐነ ንስማዕ ዘመሀረተነ
ቀዳሚተ ኩሎን አህጉር እምኄውተ ሃይማኖት ኢትዮጵያ
ነገረ ቀዳሚ ወድኅር በአዕይንቲሃ ርእያ
እንተ ርእየ አምጣነ የዐቢ እምዘ ሰምዐ ነያ
ወይጻዑ እምኔሃ
ለኢትዮጵያ ባዕዳን ትምይንት ወሕብልያ

ኢሀለወሂ ክብረ ልዕልና እንተ አወፈያ
ከመ አክበረቶ ለዳዊት ብዕሲተ ናባል አቤግያ
ወህላዌሃ ይመስል ዕለተ ምርያ
ከመ እለ ይብሉ ሙዳሱጣ እስመ ትብል ሙኪርያ

አሜን ይጻዑ ለነ ትምይንት ወሕብልያ እምሀገርነ ኢትዮጵያ!!!

24/07/2023

ኢየሉጣ ወለደት ነቅዓ ጽጌ ረዳ
ፀሐየ ጽድቅ የዓውዳ

ሠናይ በዓለ ቂርቆስ ወኢየሉጣ ወበዓለ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል

ለወንድማችን ሊቀ መዘምራን ዘርይሁን ወርቅነህ ዕድሜን ከጤና ጋር ይስጥልን።

22/07/2023

"ከዚህ በኋላ ጥቂት ቀን ነው የተቀመጠ አርፏል የነገረችውም በዝቶ ተርፎ አግኝቶታል።"

REPOSTED

ይህ ከዚህ በላይ ያለው የትርጓሜያችን ቃለ ንባብ በጣም አንጀት የሚበላ ሲሆን ፤ ቅዱስ ኤፍሬም ለእመቤታችን ያለውን ፍቅር በእጅጉ ይገልፃል። የመጨረሻዋን የትርጓሜ ሀረገ ንባብ ታነቧት ዘንድ እጋብዛችኋለሁ።

ወእምዝ አሀዘ ይትቀነይ በሰለስቱ ጸዋትወ ዜማ ይላል ፤ በዚህም ቀን በዜማ በግዕዝ በእዝል በአራራይ ሲያመሰግናት አድሯል። በሀገራቸው ምን ዜማ አለ ቢሉ እንደኛ ባይጸና ቀለል ቀለል ያለ ዜማ አለ። በዚያ ሲያመሰግናት አድሯል። አንድም ለያሬድ የገለጸች እመቤት ገልጻለት በዜማ ሲያመሰግናት አድሯል። በዛሬውም ዕለት በዘጠኝ አናቅጽ አስደርሳዋለች። በዘጠኙ ክፍለ ሐመረ ኖህ በዘጠኙ መዓርገ መላእክት ቁጥር አምሳል እመሰገናለሁ ስትል ነው።

እንደቀደመውም ዝም ብላው አልቀረችም "በከመ አንተ አስተፍሳህከኒ በዲበ ምድር ከማሁ አነሂ አስተፌስሀከ በመንግስተሰማያት" አንተ በዚህ አለም ስሜን ጠርተህ አመስግነህ ደስ እንዳሰኘኸኝ እኔም በወዲያኛው አለም በመንግስተሰማያት ደስ አሰኝሀለሁ ብላ ተስፋውን ነግራው አርጋለች።

"ወእምዝ አዕረፈ ለብሀዊ" ይላል ከዚህ በኋላ ጥቂት ቀን ነው የተቀመጠ አርፏል። የነገረችውም በዝቶ ተርፎ አግኝቶታል።

ከቅዱስ ኤፍሬም በረከትና ረድኤት ይክፈለን።

16/07/2023

"ቅኔው ይቅርና ...."

#የግል እይታ

በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን የአስተምህሮ ስርዓት ውስጥ "ብዛት" ሳይሆን "ጥራት" ትልቅ ቦታ አለው። ቀደምት አባቶቻችን የአብነት ትምህርቶችን በየቅደም ተከተላቸው ቀርጸው ትውልድን እያነጹና እነርሱን የመሰሉ ጥራት ያላቸውን መምህራን እየተኩልን አልፈዋል።

በቤተ ክርስቲያናችን የመጨረሻውና ትልቁ የሚባለው የትምህርት ዘርፍ የትርጓሜ መጻህፍት ጉባኤ ነው። እንደሚታወቀው በዩኒቨርስቲ ትምህርት አንዳንዱ ኮርስ "perquisite" (ቀዳሚ ኮርስ) ያስፈልገዋል። ይህ መንገድ በጥንታዊቷ ኦርቶዶክሳዊት ጉባኤ ያለና የነበረ ነው።

አንድ ሰው ወደ መጽሐፍ ቤት ገብቶ ለመማርና ብቁ ሆኖ ለመውጣት አስቀድሞ ቅኔን ከነአገባቡ ከነ እርባ ቅምሩና ከነ አዋጁ ጠንቅቆ መማር ይገባዋል። እንደው ቅኔው ይቅርና የግስ እርባታና አመልን ከንባብ ጋራ ጠንቅቆ ሊማር የተገባ ነው።

አሁናዊ የመጻህፍት ጉባኤዎቻችን የሚሄዱበት መንገድ ግን ቤተ ክርስቲያናችን ከጥራት ይልቅ ብዛት ላይ እንድታተኩር እያስገደዳት ይገኛል። ችግሩ ደግሞ ጎልቶ የሚታየው ከዓመታት በኋላ መሆኑ አድማሱን ለማስፋቱ ጥሩ ምልከታ ነው።

ትርጓሜ ራሱ የቅኔ መንገድ ነውና "አባቱን አያውቅ አያቱን ይናፍቅ" ዓይነት እንዳይሆንብን ቢያንስ ከቅኔዋ ውሃ ትንሽ ጎንጨት እንበል። መጽሐፍና ቅኔ አባትና ልጅ መሆናቸውን እናውቅ ዘንድ የቀደምቶቹን ሊቃውንት የነ የኔታ ውብሸትን ፣ የነ አለቃ ገብረ ሥላሴ ክንፉን ፣ የነ አለቃ ጥሩነህን ፣ የነ አለቃ አድማሱ ጀንበሬን ቅኔ መመልከት በቂ ነው።

እንደ መዝጊያ እንዲሆን

ማዕበል ደስታ በአንድ ወቅት ለራስ ወልደ ጊዮርጊስ ቅኔ ሲሰጡ በመጨረሻዎቹ የመድስ ቤቶች ላይ እንዲህ ይላሉ።

ወእንዘ ዳዊት ሰይፍከ ቀታሌ አእላፍ ወእልፍ
ናቡከደነጾር ፈረስከ አኮኑ ተውላጠ ዖፍ

ይላሉ። ታዲያ ይህን ቅኔ ከብዙ ዓመታት በፊት ተመለከትኩትና ንባቡንና ያመጡበትን መንገድ አድንቄ አለፍኩት። መጻሕፍትን በጥንቃቄ ከሚያነበው ወንድሜ ሊቀ መዘምራን ዘርይሁን ወርቅነህ ጋር "ተውላጠ ዖፍ" ያሉት እንዴት ነው በሚል ስንነጋገር የናቡከደነጾርን ታሪክ መመርመር ግድ ሆነብን። ከዚያም እርሱ ከድርሳነ ጽዮን እኔ ደግሞ ከኢሳይያስ ትርጓሜ ላይ አገኘነው። እስኪ ይህንን ታሪክ የሰማችሁ አጋሩን?

ዋናው ነገር እንደ ጌዴዎን ሰራዊት ዳግመኛም "ወኀረየ ዐሰርተ ወክልዔተ ሐዋርያተ" እንደተባለለት እንደ ጌታ ፣ ጉባዔዎቻችን ጥራት ላይ ቢያተኩሩ መልካም ነው።

14/07/2023

ዓለማትን የፈጠሩ ቅድስት ሥላሴ ለፍጥረታት ሁሉ በተለያየ አምሳል አንድነታቸውን እና ሶስትነታቸውን ይገልጣሉ። ይኸውም ይታወቅ ዘንድ በመምሬ ዛፍ ስር ለአብርሃም የሥላሴና የዋህድና ምስጢርን ከገለጹለት በኋላ "አመ ከመ ዮም እገብእ ኀቤከ" ብሎ እግዚአብሔር ወልድ ከእርሱ ባህርይ በስጋ እንደሚገለጥ አስታውቆታል።

ወደ አብርሃም ቤት በእንግድነት የገቡ ቅድስት ሥላሴ ሃይማኖታችንን እና ሀገራችንን ይጠብቁልን። አሜን!!!

እንደተለመደው ወንድማችን ሊቀ መዘምራን ዘርይሁን ወርቅነህ ለዕለቱ የሚስማማውን ቀለም እንዲህ አሰምቶናል።

👉 Like the page
👉 Share the post
👉 Telegram : https://t.me/gubaeQene

11/07/2023

ውሉደ ብርሃን ጴጥሮስ ወጳውሎስ

የብርሃን ልጆች የተባሉ ጴጥሮስና ጳውሎስ የክርስቶስን ሃይማኖት በዓለም ዙርያ ያደረሱ የቤተ ክርስቲያን አዕማድ ናቸው። ሐምሌ አምስት ቀን በሮም አደባባይ የሰማዕትነትን ጽዋ አንዱ ቁልቁል ተዘቅዝቆ ፣ አንዱ ደግሞ በሰይፍ ተከልሎ ተቀብለዋል። የቅዱሳን አባቶቻችን የሐዋርያት በረከት እና ረድኤት ከሁላችን ጋር ይሁን።

ወንድማችን ሊቀ መዘምራን ዘርይሁን ወርቅነህ በዓሉን የተመለከተ ወረብ እንዲህ ያሰማናል።

06/07/2023

ጌታችን በወንጌል ሴቶች ከወለዷቸው ልጆች ሁሉ የሚበልጠው እንደሌለለ የመሰከረለት ፣ የመንገድ ጠራጊው የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የልደት በዓል በእጅጉ የከበረ ነው።

የቅዱስ ዮሐንስ መመረጥ የሚያስደንቀው በማኅጸን ለጌታና ለእመቤታችን ክብር ፤ ምስጋናን ማቅረቡ ብቻ ሳይሆን የክርስቶስ መንገድ ጠራጊ መሆኑ ጭምር ነው። ክብሩ በዚህ ብቻ ሳይወሰን "ነዋ በግዑ" ብሎ አምላኩን አጥምቋል። ከመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ረድኤትና በረከት ይክፈለን።

ወንድማችን ሊቀ መዘምራን ዘርይሁን ወርቅነህ ዘማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለዕለቱ ከተመረጡት ቀለማት አንዱን እንዲህ አሰምቶናል።

28/06/2023

ገነይነ ለኪ ኦ ወለተ ዳዊት
ጽርሐ ቅድሳቱ ለወልድ
ዘወርቅ ማኅፈድ
ወሡራሬሃ ዘመረግድ

Watch "🔴አዲስ  ዝማሬ👉መልአከ ምክሩ ቅዱስ ሚካኤል ‼️ዘማሪ ዲያቆን ፋሲል አለማየሁ ዘልደታ💥New Mezmur 2023 Zemari Deacon Fasil Alemayehu" on YouTube
21/06/2023

Watch "🔴አዲስ ዝማሬ👉መልአከ ምክሩ ቅዱስ ሚካኤል ‼️ዘማሪ ዲያቆን ፋሲል አለማየሁ ዘልደታ💥New Mezmur 2023 Zemari Deacon Fasil Alemayehu" on YouTube

🆂🆄🅱🆂🅲🆁🅸🅱🅴_____________/Connect With Me On Social Media\____________► Telegram:➜► Tiktok:➜► Facebook:➜https://www.facebook.com/Rama-T...

Address

Addis Ababa

Telephone

+251921625794

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Memher Yohannes Eshetu posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Memher Yohannes Eshetu:

Videos

Share

Nearby media companies

  • Edo.T

    Edo.T

    Lideta Addis Ababa


You may also like