ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem

ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem ሐበሻ ጣዕም ስለ ሁሉም የሚያወራ ስለ ሁሉም የሚያነሳሳ #የመዝናኛ , #የመረጃ ,እና, #የቁምነገር ሬዲዮ ፕሮግራም ነው

አውደርዕዩ "ዓለም አቀፍ ኢትዮ- አውቶሞቲቭ ትራንስፖርት ኤክስፖ" የተሰኘ ሲሆን ከሰኔ 26 እስከ ሰኔ 2 ቀን 2016 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል።ከውደርዕዩ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ...
29/06/2024

አውደርዕዩ "ዓለም አቀፍ ኢትዮ- አውቶሞቲቭ ትራንስፖርት ኤክስፖ" የተሰኘ ሲሆን ከሰኔ 26 እስከ ሰኔ 2 ቀን 2016 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል።

ከውደርዕዩ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ከኢትዮ አውቶ ቴክ ትሬዲንግ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ መሆኑም ተመላክቷል።

የሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ ወይዘሮ አመለወርቅ ህዝቅኤል እንደገለፁት፥ የአውደርዕዩ ዋና አላማ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍ ላይ እየተሰሩ ያሉትን ዋና ዋና ተግባራት ማስተዋወቅ እና ባለድርሻ አካላትን እርስ በእርስ ማገናኘት ነው።

በተጨማሪም ዘርፉን ለማዘመን የሚያግዙ የቴክኖሎጂ የፈጠራ ውጤቶች ያሏቸው ግለሰቦችና ተቋማት የፈጠራ ውጤታቸውን እንዲያሳዩ እድል ለመስጠት ያስችላልም ተብሏል።

ከዚህ ባሻገርም በአጠቃላይ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍና በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪው ላይ ያሉትን ለውጦችና የዘርፉን ማነቆዎች በተመለከተ የፓናል ውይይት የሚካሄደበት መሆኑ ተጠቅሷል።

የኢትዮ አውቶቴክ ትሬዲንግ ላለፈው አንድ አመት ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር አዲስ አለማየሁ ተናግረዋል።

ዋና ስራ አስኪያጁ በዘርፍ የቴክኖሎጂ እና የእውቀት ሽግግርን በማጠናከር ብክለትን የሚቀንሱ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችና ሌሎች አዳዲስ ውጤቶች ለእይታ የሚቀርቡበት ይሆናል ብለዋል።

ሐበሻ ጣዕም

ሳፋሪኮምና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በጋራ ለመስራት የሚስችል ስምምነት ተፈራረሙስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈራው ተሊላና የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ...
29/06/2024

ሳፋሪኮምና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በጋራ ለመስራት የሚስችል ስምምነት ተፈራረሙ

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈራው ተሊላና የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዊም ቫንሄለፑት ተፈራርመዋል።

ስምምነቱ ኤምፔሳ ሳፋሪኮምና የኤሌክትሪክ አገልግሎት የድህረ ክፍያ ደንበኞች ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብን በኤምፔሳ መክፈል የሚያስችል ነው።

የድህረ ክፍያ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞች ጊዜ፣ ገንዘብ እና ጉልበታቸውን በመቆጠብ ፈጣን አማራጭና አስተማማኝ የክፍያ አገልግሎት እንዲያገኙ ይረዳል ተብሏል።

በተጨማሪም የኤምፔሳ ዲጂታል ክፍያ አማራጭን የሚጠቀሙ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የድህረ ክፍያ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞች ከመጀመሪያ አምስት ክፍያዎቻቸው ላይ አስር በመቶ በተመላሽነት የሚያገኙ ይሆናል፡፡

ይህ የሆነው ደንበኞች ዲጂታል የክፍያ አማራጮችን፣ በተለይም ኤምፔሳን እንዲጠቀሙ ለማበረታታት የታቀደ መሆኑን በስምምነት ስነስርዓቱ ላይ ተገልፃል።

ሐበሻ ጣዕም

አሸዋ ቴክኖሎጂ ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልግሎት ይሰጣል የተባለውን ክላውድ አገልግሎትን ወደ ስራ ማስገባቱን አስታወቀ። አገልግሎቱ ለማህበረሰቡ በተለይም አነስተኛ እና መካከለኛ ለሆኑ የንግድ ተ...
27/06/2024

አሸዋ ቴክኖሎጂ ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልግሎት ይሰጣል የተባለውን ክላውድ አገልግሎትን ወደ ስራ ማስገባቱን አስታወቀ።

አገልግሎቱ ለማህበረሰቡ በተለይም አነስተኛ እና መካከለኛ ለሆኑ የንግድ ተቋማት በቀላሉ የሚፈልጉትን አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላል ተብሏል።

ከዚህ ባለፈም በበይነ መረብና በሶስተኛ ወገን አቅራቢነት በአካል መገኘት ሳያስፈልግ ባሉበት ቦታ ሆነው እንዲሰሩ ያስችላልም ነው ያለው።

በተጨማሪም የመረጃ ደህንነትን ለመጠበቅና የፈጠራ ክህሎትን ለመጨመር እንዲሚረዳ ተገልጿል።

ለደንበኞቹ የዶሜን ምዝገባ እና ዝውውር፣ ስቶሬጅ፣ ራም፣ ሲፒዩ፣ በቅርበት የቴክኒክ ድጋፍ ያካተተ እና ደንበኞች ራሳቸውን ማስተናገድ የሚችሉበት የአገልግሎት አቅርቦትም አለው።

የአሸዋ ክላውድ አገልግሎት ለግለሰብ፣ ለመንግስታዊና ለግል ተቋማት አገልግሎት መጠቀም እንደሚቻልም ተጠቁሟል።

ሐበሻ ጣዕም

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የህክምና ማህበር አርቲስት ትግስት ግርማን  አምባሳደር አድርጎ ሾመ።ማህበሩ ዛሬ በሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ በቀጣይ ለሚሰራቸዉ የበጎ አድራጎት እና የህክምና አገልግ...
27/06/2024

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የህክምና ማህበር አርቲስት ትግስት ግርማን አምባሳደር አድርጎ ሾመ።

ማህበሩ ዛሬ በሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ በቀጣይ ለሚሰራቸዉ የበጎ አድራጎት እና የህክምና አገልግሎት አርቲስቷን የክብር አምባሳደር ማድረጉን አሳዉቋል።

ላለፉት ሶስት አመታት ከ35 በላይ የህክምና ጉዞዎችን በሀገሪቱ በማድረግ 26 ሺህ በላይ ሰዎችን የነፃ ህክምና ተጠቃሚ ማድረጉንም ገልፆል።

የኢትዪጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ማህበር የአዲስ አበባ ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ዘላለም እንደገለፁት በቀጣዩቹ አመታት ግዙፍ ሪፈራል ሆስፒታል ለመገንባት እቅድ መያዙን አስታውቋል።

በ2013 ዓ/ ም በሀገረ አሜሪካን ምስረታዉን ያደረገዉ ማእከሉ 2500 በላይ በጎ ፍቃደኛ የህክምና ባለሙያዎች አባላት እንዳሉት ለማወቅ ተችሏል።

ሐበሻ ጣዕም

አምጊፍት ሪልእስቴት አርቲስት አብርሀም ወልዴን ብራንድ አምባሳደር አድርጎ ሾመ።አርቲስት አብርሀም ወልዴ ለሚቀጥሉት ሶስት አመታት የድርጅቱ ብራንድ አምባሳደር ሆኖ የሚያገለግልበትን ስምምነት ...
26/06/2024

አምጊፍት ሪልእስቴት አርቲስት አብርሀም ወልዴን ብራንድ አምባሳደር አድርጎ ሾመ።

አርቲስት አብርሀም ወልዴ ለሚቀጥሉት ሶስት አመታት የድርጅቱ ብራንድ አምባሳደር ሆኖ የሚያገለግልበትን ስምምነት በዛሬው እለት ፈጽሟል።

ላለፉት ሁለት ሶስት አስርት አመታት በቤት ግንባታ ዘርፍ ላይ ተሰማርቶ የሚገኝው ጊፍት ሪልእስቴት ባሁኑ ሰአት ከፍተኛ የቤት ግንባታ እና ሽያጭ እያከናወነ እንደሚገኝ አስታውቋል።

ስምምነቱ በየሶስት አመቱ የሚታደስ ይሆናል ተብሏል።

አርቲስት አብርሀም ወልዴ በመመረጡ ደስ መሰኘቱን ገልጾ እኔም መርጬ ነው አምባሳደር የሆንኩት ብሏል።

ይህንን ስራው በተደራጀ መንገድ እና ኢትዮጵያዊያን በሚገኙባቸው የአለም ሀገራት የጊፍት ቤቶችን እንዲያስተዋውቅ ነው አብርሀም ወልዴ ብራንድ አድርጎ የተመረጠው ተብሏል።

የጊፍት ሪል ስቴት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ገ/የሱስ ኢጋታ ጊፍት ሪል ስቴት በላቀ ጥራት ቤቶቻችን ለመገንባት ዝግጅት ማጠናቀቁን በስምምነቱ ወቅት ተናግረዋል፡፡

ሐበሻ ጣዕም

በናተ ድጋፍ ታጭቻለው ለመጀመሪያ ግዜ በሚካሄደው ሚዲያ አዋርድ ላይ ምርጥ ዲጄ ዘርፍ ታጭቻለው የገባቹ ድምፅ ስጡኝ ወዳጆቼ።👇👇👇https://ethio-mediaaward.com/
26/06/2024

በናተ ድጋፍ ታጭቻለው
ለመጀመሪያ ግዜ በሚካሄደው ሚዲያ አዋርድ ላይ ምርጥ ዲጄ ዘርፍ ታጭቻለው የገባቹ ድምፅ ስጡኝ ወዳጆቼ።
👇👇👇
https://ethio-mediaaward.com/

የ’ፒሬትስ ኦፍ ዘ ካሪቢያን’ ተዋናዩ በሻርክ ተነክሶ ህይወቱ አለፈ የ’ፒሬትስ ኦፍ ዘ ካሪቢያን’ ተዋናዩ ታማዮ ፔሪ በሻርክ ተነክሶ ህይወቱ ማለፉ ተሰማ።የ49 ዓመቱ ተዋናይ በሃዋይ የባህር ...
24/06/2024

የ’ፒሬትስ ኦፍ ዘ ካሪቢያን’ ተዋናዩ በሻርክ ተነክሶ ህይወቱ አለፈ

የ’ፒሬትስ ኦፍ ዘ ካሪቢያን’ ተዋናዩ ታማዮ ፔሪ በሻርክ ተነክሶ ህይወቱ ማለፉ ተሰማ።

የ49 ዓመቱ ተዋናይ በሃዋይ የባህር ስፖርትና መዝናኛ በሆነው ሰርፊንግ እየተዝናና እያለ በሻርክ ተነክሶ ህይወቱ ማለፉ ነው የተገለጸው።

በወቅቱ በሻርክ ከተነከሰ በኋላ ወደ ባህር ዳርቻ ተወስዶ ህክምና ቢደረግለትም፥ መትረፍ እንዳልቻለ የሃዋይ አደጋ ጊዜ ምላሽ አገልግሎት አስታውቋል።

ፔሪ በባህር ቀዘፋና መሰል የባህር መዝናኛዎች ልምድ ያለውና በአካባቢው በህይወት አድን ስራ ተሰማርቶ ይሰራ እንደነበርም ነው አገልግሎቱ የገለጸው።

ሐበሻ ጣዕም

21/06/2024
የተወሰኑ ስፖርታዊ መረጃዎች!ጣልያኑ ክለብ ሮማ የማንችስተር ሲቲ ንብረት የሆነውን ሰርጅዮ ጎሜዝን ለማስፈረም ውሀ ሰማያዊዎቹን አነጋግረዋል።ፋብሪዝዮ ሮማኖ▪️ዊሊያም ሳሊባ ዛሬ ምሽት ሃገሩ ፈ...
21/06/2024

የተወሰኑ ስፖርታዊ መረጃዎች!

ጣልያኑ ክለብ ሮማ የማንችስተር ሲቲ ንብረት የሆነውን ሰርጅዮ ጎሜዝን ለማስፈረም ውሀ ሰማያዊዎቹን አነጋግረዋል።

ፋብሪዝዮ ሮማኖ

▪️ዊሊያም ሳሊባ ዛሬ ምሽት ሃገሩ ፈረንሳይ ከኔዘርላንድ ጋር በምታደርገው ጨዋታ ከኢብራሂማ ኮናቴ ጋር በመጣመር ጨዋታውን እንደሚጀምር ይጠበቃል።

[L'equipe]

አማሪዮ ኮዚየር-ዱቤሪ አርሰናልን ሊለቅ ነው !

የታዳጊ ቡድን ውስጥ እየተጫወተ የሚገኘው አማሪዮ ኮዚየር-ዱቤሪ በሚቀጥሉት 24 ሰዓታት ውስጥ ክለቡን እንደሚለቅ ለአርሰናል አሳውቋል።

ከክለቡ መልቀቅ የፈለገበትን ምክንያት እስካሁን አልታወቀም !

[Arsenal.com]

የኤዲ ኒኪታ አዲሱ ፈላጊ ክለብ !

▪️||በርንማውዞች ሶላንኬን ሚያጡት ከሆነ ሙሉ በሙሉ ትኩረታቸውን ኤዲ ኒኪታ ላይ ሚያረጉ ይሆናል።ልጁ በዚ ክረምት ከአርሰናል መልቀቁ ስለማይቀር በርንማውዞች ዝውውሩ ቀላል ይሆናል ብለው ያስባሉ።

አርሰናል ከተጫዋቹ 30 ሚሊዮን ፖውንድ ብቻ ይፈልጋሉ።[¶Skysport

ሐበሻ ጣዕም

21/06/2024

የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ባለቤት ብሪጅት ማክሮን ጾታቸውን አስቀይረዋል ያሉ ጋዜጠኞች ላይ ክስ መሰረቱ

በዘገባው ምክንያት ስሜ በአውሮፓ እና አሜሪካ ጠፍቷል ያሉት ቀዳማዊ እመቤቷ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ወስደውታል
የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ባለቤት ብሪጅት ማክሮን ጾታቸውን አስቀይረዋል ያሉ ጋዜጠኞች ላይ ክስ መሰረቱ።

የ71 ዓመቷ የፈረንሳይ ቀዳማዊ እመቤት በሙያቸው መምህር የነበሩ ሲሆን አሁን ላይ ባንድ ወቅት ከተማሪዎቻቸው አንዱ የሆኑት ኢማኑኤል ማክሮንን አግብተዋል።

ፕሬዝዳንት ማክሮን ለቀድሞ መምህሩ እና ለባለቤቱ አክብሮት እና ፍቅር እንዳለው በተደጋጋሚ ሲናገሩ ተደምጠዋል።

በፈረንሳይ የዩቲዩብ ጋዜጠኛ የሆኑ ሁለት ጋዜጠኞች ቀዳማዊ እመቤት ብሪጌት ማክሮን በተፈጥሮ ወንድ እንደነበሩ እና ጾታቸውን እንዳስቀየሩ ዘግበዋል።

ከሶስት ዓመት በፊት ተሰራጭቷል የተባለው ይህ ዘገባ ከወጣ በኋላ ጉዳዩ የብዙዎችን ትኩረት የሳበ ሲሆን ቀዳማዊ እመቤቷም ስማቸው መጥፋቱን እና በዘገባው ምክንያት ለፖለቲካ ሴራም ተጋልጫለሁ ሲሉ ክስ መስርተዋል።

የሀገሪቱ ፍርድ ቤት በትናንትናው ዕለት ጉዳዩን መመልከት የጀመረ ሲሆን ክስ የቀረበባቸው ሁለት ጋዜጠኞች እና የቀዳማዊ እመቤቷ ጠበቃ ችሎት እንደቀረቡ ፍራንስ 24 ዘግቧል።

እንደ ዘገባው ከሆነ ጋዜጠኞች የፕሬዝዳንት ማክሮን ባለቤት ብሪጅት ማክሮን ከመባላቸው በፊት ጂያን ማይክል የሚባሉ ወንድ እንደነበሩ ለችሎቱ ተናግረዋል ተብሏል።

ጋዜጠኛዋ አክላም በጉዳዩ ዙሪያ ለሶስት ዓመታት ምርመራ ስታደርግ ከቆየች በኋላ እርግጠኛ ስትሆን ዘገባውን እንደሰራችም ተናግራለች።

የቀዳማዊ እመቤት ብሪጅት ማክሮን ጠበቃ በበኩላቸው ጂያን ማይክል ተብሎ የሚጠራው ሰው የብሪጅት ማክሮን ወንድማቸው መሆኑን እንደተናገረ ተገልጿል።

ጋዜጠኞቹ አሰራጭተውታል በተባለው ዘገባ ምክንያት በቀዳማይ እመቤቷ ላይ ለደረሰው የስም ማጥፋት ወንጀል 10 ሺህ ዩሮ ካሳ እንዲከፈላቸው ጠይቀዋል ተብሏል።

በአውሮፓ እና አሜሪካ ቀዳማዊ እመቤቶች ላይ መሰል ስም ማጥፋት ዘገባዎች ሲሰሩ የብሪጅት ማክሮን የመጀመሪያው ሳይሆን በቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ ባለቤት ሚሼል ኦባማ ላይም ተመሳሳይ ዘገባዎች ሲሰሩ ቆይተዋል።

እንዲሁም በቀድሞ የስዊዘርላንድ ፕሬዝዳንት ጃሲንዳ አርደን ላይም ተመሳሳይ ይዘት ያላቸው ዘገባዎች ሲሰራጩ ቆይተዋል።

ሐበሻ ጣዕም

የ’ዘ ሃንገር ጌምስ’ ተዋናይ ዶናልድ ሱዘርላንድ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ ካናዳዊው እውቅ ተዋናይ ዶናልድ ሱዘርላንድ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።ተዋናዩ ረጅም ጊዜ በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በ88 ...
21/06/2024

የ’ዘ ሃንገር ጌምስ’ ተዋናይ ዶናልድ ሱዘርላንድ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

ካናዳዊው እውቅ ተዋናይ ዶናልድ ሱዘርላንድ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

ተዋናዩ ረጅም ጊዜ በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በ88 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ቤተሰቦቹ አስታውቀዋል።

ዶናልድ ሱዘርላንድ በበርካታ ፊልሞች ላይ በመሪ ተዋናይነት በመተወን እውቅናን ያገኘ ተዋናይ ነበር።

በተለይም ‘ዘ ሃንገር ጌምስ’ እና ‘ዶንት ሉክ ናው’ በተሰኙ ፊልሞች በስፋት ይታወሳል።

ከትወናው ዓለም ቀደም ብሎ በ1950ዎቹ መጨረሻ በለንደን የሙዚቃ እና ድራማዊ ሥነ ጥበብን አጥንቷል።

ከትምህርቱ በኋላ በእንግሊዝ የቴሌቪዥን ድራማዎች ላይ በመሳተፍ ትወና በመጀመር ‘ደርቲ ዶዝን’ እና ‘ኬሊስ ሄሮይስ’ን ጨምሮ በበርካታ ፊልሞች ላይ በመተወን ከኦስካር ውጭ የተለያዩ ሽልማቶችን አሸንፏል።

ከዚህ ባለፈም በፈረንጆቹ 1980 ኦስካር ባሸነፈው ‘በኦርዲናሪ ፒፕል’ ላይ ተውኗል።

ፊልሙ ባለፀጋ ቤተሰብ ውስጥ አንድ ልጁ ራሱን ያጠፋበት ወላጅ አባት ሌላኛውን ልጁን ከዚህ አጋጣሚ ለማራቅ የሚያደርገውን ጥረትና የቤተሰቡን ሁኔታ ይዳስሳል።

ሐበሻ ጣዕም

21/06/2024

በ50ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንዲለቀቁ ተወሰነ

አርቲስት አማኑኤል ሀብታሙ፣ የቴአትር አዘጋጅ ዳግማዊ ፈይሳ እና ፍላጎት አብርሃምን ጨምሮ 17 ግለሰቦች እያንዳንዳቸው በ50 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንዲለቀቁ ፍርድ ቤት ፈቀደ።

ግለሰቦቹ የታሰሩት ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓትን በትጥቅ ትግል ለመቀየር” በመንቀሳቀስ በሚል ነበር፡፡

ዛሬ በጉዳዩ ላይ ብያኔ ለመስጠት የተሰየመው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት፤ በመዝገቡ ከተካተቱት 20 ተጠርጣሪዎች ውስጥ አስራ ሰባቱ እያንዳንዳቸው የ50 ሺህ ብር የገንዘብ ዋስትና በማስያዝ ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

ያሬድ ገብረፃዲቅ በማኅበራዊ ሚዲያ ስሙ ያያ ዘልደታ፣ ፍስሃ እያዩ እና ጌትነት ታከለ የተባሉት ተጠርጣሪዎች ግን 11 ተጨማሪ የምርመራ ቀናት እንደተፈቀደባቸው ጠበቃ አያሌው ገልጸል።

ሐበሻ ጣዕም

21/06/2024

እውቁ ድምጻዊ ጀስቲን ቲምበርሌክ ጠጥቶ ሲያሽከረክር በፖሊስ ተያዘ
እውቁ አሜሪካዊው ድምጻዊ ጀስቲን

ቲምበርሌክ በኒው ዮርክ ውስጥ ጠጥቶ በማሽከርከር በፖሊስ ተይዞ እንደነበር የአካባቢው ባለሥልጣናት ለቢቢሲ ገለጹ።

የፖፕ ሙዚቃ አቀንቃኙ ማክሰኞ ማለዳ ተይዞ በይፋ ክስ እንደተመሠረተበት በኒው ዮርክ የሰፍሎክ አካባቢ አስተዳደር ዐቃቤ ሕግ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ቴምበርሌክ መጀመሪያ ላይ በቁጥጥር ሥር የዋለው በሎንግ አይላንድ ታዋቂ በሆነው የበጋ መዝናኛ ቦታ የሃብታሞች መንደር በሆነችው ሳግ ሃርበር ውስጥ ነው።

ድምጻዊው በይፋ ክስ ከተመሠረተበት በኋላ ያለዋስትና መለቀቁን የሶፍሎክ አካባቢ አስተዳደር ዐቃቤ ሕግ ጨምሮ ገልጿል።

የቲምበርሌክ የክስ መዝገብ እንደሚያስረዳው ከሆነ አቀንቃኙ ሰኞ ከዕኩለ ሌሊት በኋላ ቀይ መብራት የጣሰ ሲሆን በትክክለኛ የመንገድ መስመር ላይ ሳይጓዝ በመቅረቱ በቁጥጥር ስር ውሏል።

የፖሊስ መኮንኖች ባስቆሙት ጊዜም ቲምበርሌክ ዐይን ኑ ከመቅላቱ በተጨማሪ ትንፋሹም ጠንካራ የአልኮል መጠጥ ጠረን እንደነበረው የፖሊስ ሰነድ ያስረዳል።

በተጨማሪም አነጋገሩ ዝግ ያለ እና ፖሊሶች የጠጣ ሰውን ለመለየት የሚጠቀሙበትን ዘዴ እንዲተገብር ሲደረግም በሚጠበቅበት ሁኔታ ተግባራዊ ማድረግ አልቻለም።

ድምጻዊው የአልኮል ትንፋሽ ምርመራ ለማድረግ ግን አሻፈረኝ ብሏል።

ቲምበርሌክ በፖሊሶች በተያዘበት ወቅት አንድ ብርጭቆ ማርቲኒ እንደጠጣ እና ጓደኞቹን ተከትሎ በመሄድ ላይ እያለ እንደነበር መናገሩ ተዘግቧል።

በሐምሌ ወር አጋማሽ በበይነ መረብ አማካኝነት ዳኞች ፊት እንዲቀርብም ቀጠሮ ተይዞለታል።

ጠበቃው ኤድዋርድ በርከር ጁኒየር ደንበኛውን በተገቢው ሁኔታ ለመከላከል እንደሚሠራ የተናገረ ሲሆን፣ አሁን ላይ ከታሰረበት አካባቢ ዐቃቤ ሕግ ጋር በጋራ እየሠራ እንደሆነ ገልጿል።

የ43 ዓመቱ ቲምበርሌክ በቅርቡ ያወጣውን 6ኛ አልበም ተከትሎ ዓለም አቀፍ የሙዚቃ ጉዞ ለማድረግ ዝግጅት ላይ ነበር።

የአንድ ዝነኛ ባንድ አባል የነበረው ቲምበርሌክ ተዋናይ፣ የሙዚቃ ደራሲ እና ምርጥ ሽያጭ ካላቸው አርቲስቶች መካከል ነው።

ድምጻዊው ቀደም ሲል አብዝቶ በመጠጣት ይፈተን እንደነበር በግልጽ ተናግሯል።

በኒው ዮርክ ጠጥቶ ማሽከርከር አንድ ሺህ ዶላር እና ቢያንስ ለ6 ወር መንጃ ፍቃድ መነጠቅን ያስከትላል።

ቲምበርሌክ በቀጣዮቹ የእረፍት ቀናት በቺካጎ በመጪው ማክሰኞ ደግሞ በኒው ዮርክ የሙዚቃ ድግስ ለማቅረብ ቀጠሮ ይዞ ነበር።

አስር ጊዜ ግራሚን የተሸለመው ደምጻዊው በሁለት ፊልሞችም ላይ ተውኗል።
ቴምበርሌል ከታዋቂዋ ተዋናይት ጄሲካ ቢል ጋር በትዳር ውስጥ ያለ ሲሆን ሁለት ልጆችም አሏቸው

ሐበሻ ጣዕም

 #ማስታወቂያዶ/ር ኦሪዮን ስፔሻሊቲ የጥርስ ክሊኒክአድራሻ ካሳችስ ረድኤት ህንፃ 5ኛ ፎቅ ላይ ስልክ 0982640870 ጥርሶትን በልዮነት እናስውባለን።
21/06/2024

#ማስታወቂያ
ዶ/ር ኦሪዮን ስፔሻሊቲ የጥርስ ክሊኒክ
አድራሻ ካሳችስ ረድኤት ህንፃ 5ኛ ፎቅ ላይ ስልክ 0982640870
ጥርሶትን በልዮነት እናስውባለን።

የአርአያ ሰው ሽልማት ሥነሥርዓት ዛሬ ይካሄዳል ተቀማጭነቱን በሀገረ አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ያደረገው ዓድዋ የባህልና የታሪክ ኅብረት ለትርፍ ያልተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በዋናነትም ለ...
21/06/2024

የአርአያ ሰው ሽልማት ሥነሥርዓት ዛሬ ይካሄዳል

ተቀማጭነቱን በሀገረ አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ያደረገው ዓድዋ የባህልና የታሪክ ኅብረት ለትርፍ ያልተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በዋናነትም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን አርአያ የሚሆን ሥራ ለሚሠሩ ግለሰቦችና ተቋማት"የአርአያ ሰው ሽልማት" በሚል ዕውቅና ይሰጣል፡፡

ተቋሙ የሚያዘጋጀው አርአያ ሰው ሽልማት ባለፉት ስድስት ዓመታት ባህል፣ ቅርስና ታሪክ ለተተኪው ትውልድ እንዲተላለፍ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን አጋርነት፣ ድጋፍና ዕውቅና ሲሰጥ ቆይቷል፡፡

ዘንድሮም ለ8ኛ ግዜ በአዲስ አበባ ዮድ አቢሲኒያ የባህል አዳራሽ ዛሬ ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ለሀገር ባለውለታዎች በተለይም በባህል ልማት፣ በተፈጥሮ ጥበቃ፣ በቱሪዝም እና ቅርስ እንዲሁም በታሪክ መስኮች ለሀገራቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት ሽልማት ይሰጣል፡፡

ዛሬ የሚካሄደው የአርዓያ ሰው የሽልማት ሥነሥርዓት በሀገሬ ቴሌቪዥን የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛል ተብሏል።

ሐበሻ ጣዕም

ለመላው የእስልምና ኃይማኖት ተከታይ ኢትዮጵያውያን እንኳን ለአረፋ በዓል አደረሳችሁመልካም በዓልሐበሻ ጣዕም
15/06/2024

ለመላው የእስልምና ኃይማኖት ተከታይ ኢትዮጵያውያን እንኳን ለአረፋ በዓል አደረሳችሁ

መልካም በዓል

ሐበሻ ጣዕም

እማዬ እንዳለች ኑ ቡና ጠጡ ብላለች! በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ ከዛሬ ሰኔ 8 እስከ ነገ ሰኔ 9/2016 ዓ/ም ለአዲስ አበባ ህዝብ ቡና በነፃ እየተጋበዘ ነው። ይህ አዲስ ነገር ...
15/06/2024

እማዬ እንዳለች ኑ ቡና ጠጡ ብላለች!

በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ ከዛሬ ሰኔ 8 እስከ ነገ ሰኔ 9/2016 ዓ/ም ለአዲስ አበባ ህዝብ ቡና በነፃ እየተጋበዘ ነው።

ይህ አዲስ ነገር በአዲስ ዓመት ነፃ ቡና ዝግጅት ሙዚቃ ፣ፋሽን ሾዎችን መዝናኛዎችን እና የተለያዩ አዝናኝ ዝግጅቶችን ማሰናዳታቸውን እና ህብረተሰቡ በነጻ ቡና እየጠጣ እንዲዝናና አዘጋጆቹ ታሜሶል ኮሚዩኒኬሽን አሴቲክስ ሶሉሽን እና ከሊያን ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

ሐበሻ ጣዕም

ኢትዮ ኦርጋኒክ ፉድ ኢምፖርት የሬዲዮ እና የቴሌቪዥን  ኘሮግራም አቅራቢ ጋዜጠኛ የሆነችውን እፀገነት ይልማን የድርጅቱ የብራንድ አምባሳደር አድርጎ በዛሬው እለት ዛሬ  በሳፋየር አዲስ ሆቴል ...
14/06/2024

ኢትዮ ኦርጋኒክ ፉድ ኢምፖርት የሬዲዮ እና የቴሌቪዥን ኘሮግራም አቅራቢ ጋዜጠኛ የሆነችውን እፀገነት ይልማን የድርጅቱ የብራንድ አምባሳደር አድርጎ በዛሬው እለት ዛሬ በሳፋየር አዲስ ሆቴል በተከናወነ መርሐግብር ላይ ተገለጸ።

ኢትዮ ኦርጋኒክ ፉድ ኢምፖርተር ካለፈው ዓመት ጀምሮ በዓለማችን ላይ እጅግ ጠቃሚ የሆነውን የቺያ ዘር ከውጪ አገር አስመጥቶ በማከፋፈል ላይ የሚገኝ ሲሆን የቺያ ዘር ወይም ቺያ ሲድ ለጤና ባለው ከፍተኛ ጥቅም እጅግ ተፈላጊ መሆኑን በማንሳት ኢትዮ ኦርጋኒክ ፉድ ኢምፖርተር
ኦርጋኒክ የሆነውን የቺያ ዘር ቀጥታ ከአምራች ገበሬዎች ጋር ትስስር በመፍጠር እያቀረበ ይገኛል፡፡

ከቺያ ሲድ የደም ውስጥ ስኳርን ለመቆጣጠር፣ ለአእምሮ ጤንነትና ብቃት፣ ለልብ እና ሴሎች ጤንነት ፣ ከካንሰር ራስን ለመጠበቅ፣ የደም ግፊትን ለመቆጣጠር፣ ለክብደት መቀነስ፣ ለአጥንት እና የጥርስ ጤና፣ ለወሊድ (ፈርቲሊቲ)፣ ለቆዳ ጤንነትና ውበት፣ ጥሩ እንቅልፍ ለመተኛት፣ ድባቴንና ጭንቅትን ለመቀነስ፣ ለእርጉዝ እናቶች እና ለፅንስ ዕደገት ጠቀሜታ እንዳለው በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተገልጿል።

ሐበሻ ጣዕም

ካውሰር PLC( ሻሊና ሄልዝ ኬር) 4 የቆዳ መንከባከቢያ ምርቶችን አስተዋወቀካውሰር PLC( ሻሊና ሄልዝ ኬር) በአለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ተቀባይነትን ያተረፈ ድርጅት ሲሆን በኢትዮጵያ ይዟቸው...
14/06/2024

ካውሰር PLC( ሻሊና ሄልዝ ኬር) 4 የቆዳ መንከባከቢያ ምርቶችን አስተዋወቀ

ካውሰር PLC( ሻሊና ሄልዝ ኬር) በአለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ተቀባይነትን ያተረፈ ድርጅት ሲሆን በኢትዮጵያ ይዟቸው የመጣቸውን አዳዲስ ምርቶች ሰኔ 6/2016 ዓ.ም አስተዋውቋል።

ከነዚህ ምርቶች ውስጥ አንዱ ሞናሊሳ ሲባል ይህም የቆዳ እንክብካቤን ለመጠበቅ የሚያስችል ሎሽንና ክሬም ነው

ኤፒግሎው የተሰኘው ደግሞ ለአፍሪካ ቆዳ የተዘጋጀ ሲሆን እንደ ጥቁር ነጠብጣቦች እና ዥንጉርጉር ፊትን እና የተለመዱ የቆዳ ስጋቶችን በ28 ቀናት ውስጥ በመቀነስ ብቻ የሚታይ ለውጥ የሚሰጥ የቆዳ መንከባከቢያ እንደሆነ ተገልጿል

ሌላው ፍሎደንት የተባለው የጥርስ ሳሙና ምርት ሲሆን በፍሎራይድ ለተጠቃ ጥርስ፣ ለአፍ ጤንነት፣ የጥርስ መቦርቦርን የሚታደግ እንደሆነ ተነግሯል።

የመጨረሻው ምርት ጀርሞል የተሰኘ ሳሙና ሲሆን ሰውነትን ከጀርሞች ለመከላከል የሚረዳ ነው ተብሏል።

ሻሊና ሄልዝ ኬር 40 አመትን ያስቆጠረ ድርጅት ሲሆን እስካሁን በ22 የአፍሪካ ሀገራት ላይ ሰርቷል።

ድርጅቱ በአሁን ሰአት በአዲስ አበባ ላይ 6 ክፍለ ከተሞች ላይ ስራ የጀመረ ሲሆን 1000 ለሚደርሱ ሰዎች የስራ እድል ፈጥሯል።

ሐበሻ ጣዕም

የኔ መኪና የትራንስፖርት ዘርፉን ከማዘመን አኳያ በርካታ ጥቅሞች እንደሚሰጥ የተነገረ ሲሆን በተለይም በመንገድ እና ትራንስፖር ባለስልጣንና በተሽከርካሪ ባለንብረቶች መካከል ያለውን ግንኙነት ...
13/06/2024

የኔ መኪና የትራንስፖርት ዘርፉን ከማዘመን አኳያ በርካታ ጥቅሞች እንደሚሰጥ የተነገረ ሲሆን በተለይም በመንገድ እና ትራንስፖር ባለስልጣንና በተሽከርካሪ ባለንብረቶች መካከል ያለውን ግንኙነት ያለምንም ክፍተት በመናበብ ስራቸውን ምቹ እና ቀልጣፋ እንዲሆን ከማድረግም በላይ የተሽከርካሪ ባለንብረቶችን ማሳደስ ያለባቸውን ነገሮች በማስታወስ ከቅጣት እና አላስፈላጊ እንግልት የሚያድን ሶፍትዌር እንደሆነ ተገልጿል።

አንድ የተሸከርካሪ ባለቤት የተሸከርካሪው ኢንሹራንስ፣ አመታዊ ምርመራ፤ የመንጃ ፈቃድና የመንገድ ፈንድ ቀነ ገደባቸው ከማብቃቱ በፊት በሞባይል ስልካቸው ላይ አጭር መልእክት እንዲደርሳቸው የሚያስታውስ፣ ከመክፈያ ዘዴ፤ እንዲሁም ተለጣፊና ሌሎች መረጃዎችን የማድረስ አገልግሎቶችን በአንድ ላይ የሚያጣምር የዌብና የሞባይል መተግበሪያ ነው።

ኢቲቦሎ ዴስክቶፕ፣ ዌብ እና ሞባይል መተግበሪያ ይህ መተግበሪያ መረጃዎች ደህንነታቸውን በጠበቁ መልኩ ያለ ሶስተኛ ወገን ጣልቃ ገብነት በቀጥታ ከምርመራ ተቋማት የተገኘውን ውጤት ወደ ማዕከላዊ የመረጃ ቋት በማስገባት ለሚመለከተው አካል በቀጥታ እንዲደርስ በማድረግ የነበረውን የመረጃ ከፍተት በዘላቂነት የሚፈታ ሶፍትዌር ሲሆን ለትራፊክ ፖሊስና ለመንገድ ትራንስፖርት ተቆጣጠሪዎች የሚሆን የራሱ የሞባይል መተግበሪያ አለው፡፡

ሌላኛው የኔ ዴሊቨሪ ሶፍትዌር ሲሆን የተለያዩ ዶክመንቶችን፣ ሰነዶችን፣ እቃዎችን እንዲሁም የተሽከርካሪ መለዋወጫ እቃዎችን ቴከኖሎጂ በመጠቀም ለግለሰቦች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለሆስፒታሎች ለማድረስ የበለጸገ ሶፍትዌር እንደሆነ የቲዎስ ቴክኖሎጂ ስራ አስፈፃሚ አቶ ቴዎድሮስ አጥናፉ ተናግሯል።

ቲዎስ ቴክኖሎጂ ሶልሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር የተለያዩ ሶፍትዌር መተግበሪያዎችን በማበልጽግ እየሰራ የሚገኘ ድርጅት ነው።

ሐበሻ ጣዕም

በጣፋጭ ህይወት መልቲሚዲያ በየዓመቱ የሚዘጋጅው "የጣፋጭ ህይወት የምስጋና ሽልማት" ዘንድሮ ለአራተኛ ጊዜ  ግንቦት 30 2016 ዓ.ም በስካይላት ሆቴል ተካሄዷል።አርብ አመሻሽ ላይ የተካሄደው...
08/06/2024

በጣፋጭ ህይወት መልቲሚዲያ በየዓመቱ የሚዘጋጅው "የጣፋጭ ህይወት የምስጋና ሽልማት" ዘንድሮ ለአራተኛ ጊዜ ግንቦት 30 2016 ዓ.ም በስካይላት ሆቴል ተካሄዷል።

አርብ አመሻሽ ላይ የተካሄደው"የጣፋጭ ህይወት የምስጋና ሽልማት" በስድስት ዘርፎች ልዩ ልዩ ተሸላሚዎችን ሸልሟል።

የዘንድሮው የአራተኛው የጣፋጭ ህይወት የምስጋና ሽልማት የተሸላሚዎች ዝርዝር የሚከተለውን ይመስላል

1.ስራ ፈጠራን ተግባር ዘርፍ ተሸላሚ: ኢ/ር ቢጃይ ናይከር

2. ተስፋ የሚጣልበት/የሚጣልባት ስራ ፈጣሪ ዘርፍ ተሸላሚ: ቤተልሔም ደሴ

3.በበጎ አድራጎት ተቋማት ዘርፍ ተሸላሚ: ይመለከተኛል የበጎ አድራጎት ተቋም

4. በበጎ አድራጎት ተቋማት ዘርፍ (በግል): ሚኪያስ ለገሰ

5.የህይወት ክህሎት አሰልጣኝ (በተግባር ዘርፍ ) ተሸላሚ: ሔኖክ ሐ/ማርያም (ኒው ላይፍ )

6.ተስፋ የሚጣልበት/የሚጣልባት የህይወት ክህሎት አሰልጣኝ ተሸላሚ: ሰላም አታላይ (ቡና ፖድካስት)

7.ዝናን ለመልካም ምግባር በመጠቀም ዘርፍ ተሸላሚ: አርቲስት መቅደስ ፀጋዬ

8.ሚዲያውን ለሥነልቦና ግንባታ ዘርፍ ተሸላሚ: መጽሔተጥበብ የሬድዮ ፕሮግራም

9.ማህበራዊ ሚዲያውን ለበጎ ምግባር በመጠቀም በቲክቶክ ዘርፍ ተሸላሚ : መምህርት ዙፋን ታምር (ሚስ ዙፋን)
10.ማህበራዊ ሚዲያን በበጎ በመጠቀም በዩቲዩብ ዘርፍ ተሸላሚ: መሪ ፖድካስት
11. ልዩ ተሸላሚ: ማስተር ካርድ ፋውንዴሽን

በተጨማሪም የጣፋጭ ህይወት የምስጋና ሽልማት አዘጋጆች ግንቦት 30 በመላው ሀገሪቱ ብሎም በአፍሪካና ዓለምአቀፍ ደረጃ የመመሰጋገኛ ቀን ሆኖ እንዲከበር ለማድረግ አልመው እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በዚሁ ዕለት በሀዋሳ ሐረርና አዳማ መምህራን የጤና ባለሙያዎች እንዲሁም የመንገድ ላይ ፅዳት ሰራተኞች ተመስግነዋል።

ሐበሻ ጣዕም

ክርስቲያን ላቃቸውየአርቲስት ዘሪቱ ከበደ የመጀመሪያ ልጅ አረፈ የአርቲስት ዘሪቱ ከበደ የ 17 ዓመት የመጀመሪያ ልጅ ክርስቲያን ላቃቸው በድንገተኛ ህመም፣ በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ከዚህ ዓለም ...
05/06/2024

ክርስቲያን ላቃቸው
የአርቲስት ዘሪቱ ከበደ የመጀመሪያ ልጅ አረፈ

የአርቲስት ዘሪቱ ከበደ የ 17 ዓመት የመጀመሪያ ልጅ ክርስቲያን ላቃቸው በድንገተኛ ህመም፣ በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ተሰምቷል።

ባለቤቷ፤ ( የ3 ልጆቿ አባት ) የተወዳጁ የምንጊዜም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ተጫዋች የመንግስቱ ወርቁ ልጅ ላቃቸው መንግስቱ ነው።

በድንገት ያረፈው
ክርስቲያን ላቃቸው - የ11ኛ ክፍል ተማሪ ነበር።

ሐበሻ ጣዕም
ለመላው ቤተሰብ መጽናናትን እንመኛለን።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251923484891

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem:

Share

Category



You may also like