
03/02/2025
ብልፅግና ፓርቲ 2ኛ ጉባዔዉን የአቋም መግለጫ በማውጣት አጠናቋል።
በአቋም መግለጫዉ የተነሱ ዋና ዋና ጉዳዮች፡-
-የተሰጣቸውን ተልዕኮ በውጤታማነት እየፈጸሙ የህዝቡን ሕይወት የሚለውጡ፤ የጠንካራ ዲሲፕሊን እና የመልካም ስነ ምግባር መገለጫ የሆኑ፤ የኢትዮጵያን ህልም ዕውን የሚያደርጉ አመራርና አባላትን ለማፍራት እንሰራለን፡፡
-የሃሳብና የታሪክ ውህደት በመፍጠር፣ መዋቅራዊ ልህቀት በማረጋገጥ፣ የፖለቲካ ስክነትን ዕውን በማድረግ እና የውጤት ዘላቂነትን በቁርጠኝነት ለመፈፀም ዳግም ቃል እንገባለን።
-ነጻና ገለልተኛ ተቋማትን በማብዛት ለጠንካራ የሀገረ መንግስት እና የደሞክራሲ ባህል ግንባታ ላይ እንሰራለን።
-የፍትህ ስርዓትን የማዘመን፣ ባለሙያዎችን የማብቃት፣ የዳኝነት አገልግሎት ነጻነትን እና ተጠያቂነት ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እንታገላለን።
-ኢኮኖሚው ነባር አቅሞችን የሚያጠናክር፣ ወደ አዳዲስ ዘርፎች የሚሸጋገር እና ወደ መጪው የፈጠራ ዘመን የሚያስፈነጥር ይሆን ዘንድ ለመታገል ወስነናል።
-ዘላቂ የልማት ፋይናንስ ስርዓት በመፍጠር ኢኮኖሚውን ከብድር ጫና የሚያላቅቅ አቅጣጫ አስቀምጠናል።
-ገቢ የመሰብሰብ አቅም በማጎልበት የህዝቡን አዳጊ የልማት ፍላጎት ለመመለስ እንሰራለን።
-አረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ባህል ሆኖ እንዲቀጥል ለማስተባበር አቋም ወስደናል።
-በቀጣይ ሶስት ዓመታት የተቃና የኢኮኖሚ ለመገንባት ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝም፣ ማዕድንና ዲጂታል ኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ አበክረን እንሰራለን።
-ማህበረሰቡ ሁለተናዊ ብልፅግና ተረጋገጦለት ሁለንተናዊ ክብሩ እንዲጠበቅ አካታቸ ማህበራዊ ልማት ዕውን እንዲሆን እንሰራለን።
-ትውልዱ ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኝ እና የወንድማማችነት፣ የመቻቻል፣ ሕብረ ብሔራዊ አንድነት እና አርበኝነት እሴቶች እንዲማር የተጀመሩ ስራዎች ይጠናከራሉ።
-በጤና መድህን አገልግሎት፣ በጤና ተቋማት ተደራሽነት እና ጥራት የማሻሻል እንዲሁም አካታች የሆኑ ሰው ተኮር ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ።
-የተጀመሩ የማህበራዊ ልማት ስራዎቻችንን ሁለንተናዊ ማህበራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ አጠናክረን እንቀጥላለን።
-ሕብረ ብሄራዊ አንድነት እንዲጠናከር ከነጣጣይ ትርክቶች ይልቅ አስተሳሳሪ ትርክቶች አሸናፊ ሆነው ወጥተው ገዥ ትርክት እንዲሆኑ እንሰራለን።
-ለሕብረ ብሔራዊ አንድነትና ገዥ ትርክት ለማስረጽ በመላ ሀገሪቷ በተለያዩ አማራጮች ህዝባዊ ውይይቶች ይደረጋሉ።
-የሃሳብ ነጻነት መከበር እንደተጠበቀ ሆኖ ማህበራዊ ሚዲያ ከአፍራሽ ተልዕኮ ይልቅ ለገዥ ትርክት እና ህብረ ብሄራዊ አንድነት ግንባታ እንዲሁም የኢትዮጵያን ዕውነት ለመግለጥ እንዲውል አበክረን እንስራለን።
-በሲቪል ሰርቪስ ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮች እና ብልሹ አሰራሮች ህዝብን ለእንግልትና ለሮሮ እየዳረጉ በመሆ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የመንግስትን የማስፈጸም አቅም ለማጠናከር ጠንከራ አቋም ወስደናል።
-በቴክኖሎጂ የታገዘ የአሰራር ስርዓት በመዘርጋት እና ገቢር ነበብ ሪፎርም በማከናወን የቅሬታ ምንጭ በሆኑ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ላይ የተጀመረው ሪፎርም ተጠናክሮ ይቀጥላል።
-ዘላቂ የባሕር በር የማገኘት ፍላጎት በሰላማዊና በዲፕሎመሲያዊ መንገድ ምላሸ እንዲያገኝ በተገኘው የዓለም መድረከ ሁሉ ለመታገል ቆርጠን መነሳታችንን እናረጋግጣለን።
-ዘላቂ ሰላም የሁለንተናዊ ብልጽግና ወሳኝ በመሆኑ አካታች ሀገራዊ ምክከር ተደርጎ የኢትዮጵያ የዘመናት የችግር ስንክሳር በዘላቂነት መፍትሄ እንዲያገኝ የተጀመረውን ጥረት እንደግፋለን።
-የተጀመረው የሽግግር ፍትህ ሂደት ተግባራዊ እንዲሆን የተጣለብንን ሃላፊነት በብቃት ለማስፈጸም እንሰራለን።
-ከታጣቂ ሃይሎች ጋር የሚደረግ ውይይትና ድርድር ተጠናክሮ እንዲቀጥል እና ግጭት እንዲቀር ተጨማሪ አቅጣጫ አስቀምጠናል።
-ሁሉም የፓርቲው አመራርና አባላት ለሰላም ግንባታ እንዲሰራ ተስማምተናል።
-የጉባዔውን ውሳኔዎች በመተግበር ሀገራዊ ሰላም ለማረገጋጥና ህብረ ብሄራዊ አድንድነታችንን አጠናክረን ለማስቀጠል ሁላችንም በአንድነትና በጽናት እንቆማለን።
ጥር 26/2017 ዓ.ም
#የኢትዮጵያሬድዮ
………….
Follow us
ፌስቡክ ፡- https://www.facebook.com/radioethiopia11?mibextid=ZbWKwL
በዌብሳይት ቀጥታ ፡- http://www.ebc.et/videolink.aspx?id=3
በዜኖ fm ቀጥታ ፡- https://zeno.fm/radio/ebc-ethiopia-radio/
መደበኛ ስርጭታችንን አዲስ አበባን ጨምሮ በአብዛኛዎቹ የአገሪቱ አካባቢዎች በFM 93.1 ፣ ባህር ዳር እና ሀገረ ሰላም (ሲዳማ) በFM 104.7 እንዲሁም ጎንደር በFM 97.1 መከታተል ትችላላችሁ፡፡ በተለያዩ ከተሞች የሚገኙ የመካከለኛ ሞገድ ማሰራጫ ጣቢያዎቻችንም ሥራ ላይ ናቸው።
ሳተላይት ላይ ደግሞ፡- ethio sat 11165 / symbol rate 4500 / vertical ላይ ያገኙናል ፡፡
እናመሰግናለን