12/04/2022
#ወልድያ‼…
አሁን ለወልዲያ የሚበጃት ይሄነው!!!
ለጣይቱ ብጡል ትምህርት ቤት የተደረገ ድጋፍ
=============================
አባታቸው ስለወልዲያ ከተማ እንዲሁም ስለ ጣይቱ ቡጡል ት/ቤት እየነገሯቸው ያደጉ ልጆች ዛሬ ለጣይቱ ቡጡል ትምህርት ቤት ድጋፍ አድርገዋል።
ነዋሪነታቸውን በአሜሪካን ሀገር ያደረጉት በጎ አድራጊ ወይዘሮ ብሌን ተከስተ_ብርሀን ገብረ_ሚካኤል በወልዲያ ከተማ አስተዳደር ለሚገኙ ትምህርት ቤቶች 319,012.33 ብር የሚገመት የትምህርት መማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ።
የበጎ አድራጊዋ አባት አቶ ተከስተብርሀን ገብረ_ሚካኤል 1950ዎቹ የእቴጌ ጣይቱ ብጡል አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ እንደነበሩ ከበጎ አድራጊዋ ልጃቸው ለማወቅ የተቻለ ሲሆን አባቴ ለተማረበት ትምህርት ቤት ድጋፍ እንዲያደርጉ ለተባበሯቸው ሁሉ ከፍተኛ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን በቀጣይም ተመሳሳይ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
ለትምህርት ቤቶቹ የተደረጉትም ድጋፎች
👉60የመማሪያ ወንበሮች
👉48 የጥቁር ሰሌዳ፣
👉15 ካርቶን ወረቀት እንዲሁም በዚህ ሴሚስተር ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ለሚወጡ ተማሪዎች የሚሆን ሽልማት አበርክተዋል።
ድጋፉን የተረከቡት የወልዲያ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ እና የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ የሆኑት አቶ ለተደረገው ድጋፍ በወልድያ ከተማ አስተዳደር ስም ከፍ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበው የተደረገው ድጋፍ በወረራው ምክንያት በመማር ማስተማሩ ሂደት ላይ የተፈጠረውን ችግር አንደሚቀርፍም ገልጸዋል።
በመጨረሻም ድጋፉን ላደረጉት በጎ አድራጊ ለወይዘሮ ብሌን ተከስተ_ብርሀን ገብረ_ሚካኤል ከወልድያ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ እና የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ከአቶ እጅ የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል ።
ከተባበርን እናሸንፋለን!!!
በቴዎድሮስ አያሌው (ሀብታሙ)
ሚያዚያ፬ ቀን፳፻፲፬ዓ/ም ተጣፈ።
04/07/2014ዓ/ም