Jemberu Times

Jemberu Times updated news for at any times

18/01/2023

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!- አቶ ዮሐንስ በየነ

የጥምቀት በዓል በማይዳሰስ ቅርስነት ከተመዘገቡ ድንቅ የኢትዮጵዊነት ማሳያ፣ውድ ሃብታችን፣ ድምቀታችንና የሀገራዊ ኩራት ምንጭ ከሆኑ በዓሎቻችን አንዱ ነው፡፡

ሁሉን ቻይ፤ ሁሉን አድራጊ፤ ሁሉን ፈጣሪና ሁሉን ወሳኝ የሆነው አምላክ በውኃ መካከል ተገኘ። በዮሐንስ እጅ፣ በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠመቀ። ይህም ለሰው ልጆች ትህትናን ለማስተማር ራሱን ዝቅ አድርጓል፡፡

ኢየሱስ ክርስቶስ በፈለገ ዮርዳኖስ ከመጠመቁ በፊት የሰው ልጅ ውኃን የሚያውቀው በመዓትነቱና በዕንቅፋትነቱ ነበር። በኖኅ ዘመን የሰው ልጅ የጠፋው በውኃ ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ በማዕከለ ዮርዳኖስ ሲቆም ግን ለመዓት የነበረው ውኃ ለበረከት ሆነ። ይሄው ዛሬም በየዓመቱ ወደ ውኃ ወርደን የጥምቀት በዓልን እናከብራለን።

ክርስቶስ ከውልደቱ እስከ ጥምቀትና ስቅለቱ፣ ትንሳኤና እርገቱ ያለው ሂደት ተስፋውን ሲጠባበቁ ለነበሩ ሁሉ፥ በእያንዳንዱ ምዕራፍ ውስጥ ክርስቶስ የፈጸማቸው ተግባራት፥ የአዳምን ዘር የመዳን ተስፋ ያለመለሙና ጠላት ዲያቢሎስን ያሸነፈበት በመሆናቸው ለሰዎች ልጆች ሁሉ ትልቅ ብስራት ናቸው፡፡ ታላቅ ደስታም አስገኝተዋል፡፡

የሥራ ባህላችንን በማሻሻል በሁሉም የልማት መስኮች ተሠማርተን ለማሸነፍ በቁጭት መስራትና መትጋት አለብን። የኋላቀርነት ቅርፊቶችን ከኋላችን ጥለን ድህነታችንን በየቀኑ የምናባብልና ስለድህነት ሠርክ የምናለቅስ ሳንሆን በተስፋና በእልህ ወደ ብልጽግና የምንገሰግስ መሆን ይገባል፡፡

በኢኮኖሚውም፣ በማህበራዊውም፣ በፖለቲካውም መስክ የበለጸገችና በሁሉም ረገድ ስልጡን ህዝብ የሚኖርባት ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ሁላችንም የወንድማማችነትን እሴት ተላብሰን ለአንድ ዓላማ መቆም አለብን፡፡

ከሚያለያዩን ጉዳዮች ይልቅ በጋራ ያለፍናቸው እና ወደፊትም የምናልፋቸው የአብሮነትና የወንድማማችነት መንገድ ለመከተል ጠባብ እይታችን በአድማስ ማስፋት ያስፈልጋል፡፡

እሳት ምግብ ለማብሰያም ለጥፋትም ይውላል። ወሳኙ ተጠቃሚው ሰው ነው። እሳትን ለጥቅም ለማዋል እሳቱን ወደ ውኃነት መቀየር አያስፈልግም፤ የእሳቱን አጠቃቀም መቀየር እንጂ።

በማህበራዊ ሚዲያ የምናሰራጫቸው መረጃዎች ከአሉባልታ ይልቅ ጀግንነታችንን፣ ልማታችንን፣ የሀገራችንን ሉአላዊነት፣ የህዝባችንን አንድነትና ብሩህ ተስፋችንን የሚያጎሉ ሊሆኑ ይገባል፡፡ በአመጽና ጥላቻ ንግግር የሚመጣ ልማት ትላናትም፣ ዛሬም፣ ነገም አይኖርምና፡፡

እንደ ጥምቀት ያሉ ታላላቅ ክብረ በዓላትን እንደ አንድነታችን ማጠናከሪያ መሣሪያ ይዘን በአጭርና በረዥም ጊዜ የያዝነውን የብልፅግና ጉዟችንን ለማደናቀፍ የሚሯሯጡ ሁሉንም ጥሰን በማለፍ የያዝነውን ራእይ ለማሳካት በአንድነት እንድንሠራ በዚህ አጋጣሚ ጥሪዬን አቀርባለሁ።

አዲሱ የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች የክልል አደረጃጀት ህዝበ ውሳኔ ጥር 29 በሚካሄዳው ሁሉም ህብረተሰብ ክፍሎች ድምጽ በመስጠት የዜግነት ግዴታችሁን እንዲትወጡ እያሳሰብኩ የድምጽ አሰጣጡ ሂደት ፍጽም ሠላማዊ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ኃላፊነታችሁን በተግባር እንዲታረጋግጡ አሳስባለሁ፡፡

ጥምቀት ልዩ ገፅታን የሚያላብስ ከአይን ማረፍያ በአሎቻችን አንዱ በመሆኑ በዓሉ በድምቀት እንዲከበር፣ በሰላም ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ አስተዋዩ፣ ጨዋዉና ሰላም ወዳዱ የዞናችን ህዝብ ወትሮም እንደምናደርገው ሁሉ በትብብርና በአብሮነት አካባቢያችንን በንቃት በመጠበቅ፤ ከፀጥታ ሃይሎቻችን ጋር በትብብር በመስራት፤ እንድናሳልፍ ዘንድ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ!!

ጥምቀቱን ስናከብር ቅንነትን ተላብሰን፣ በልዩ ልዩ አጋጣሚዎች የተጎዱ ወገኖቻችንን በቸርነት ዓይናችን እያየን፣ የተቸገሩትን በድጋፍ እጃችን እየጎበኘን መሆን እንደሚገባ ላሳስባችሁ እወዳለሁ፡፡

በድጋሚ፣ መልካም የከተራና የጥምቀት በዓል እንዲሆን እመኛለሁ።

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!

ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!

ዮሐንስ በየነ
የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ

23/09/2022

ዮ ዮ ጊፋታ!
የ2015 የወላይታ ብሔር የዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል አስመልክቶ የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ዮሐንስ በየነ ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልካም ምኞት መልዕክት፡፡

የተወደዳችሁ መላው የወላይታ ህዝቦች! እንኳን ለ2015 የወላይታ ብሔር የዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል በሠላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን!!

ጊፋታ በዓሉ የአዲስ ዓመት ብርሃን ማብሰሪያ፣ በተለያየ ምክንያት ከአካባቢው ርቀው የሚኖሩ ወገኖች ከወላጆቻቸው ጋር የሚገናኙበት፣ የተጣላ የሚታረቅበት ታላቅ ክብረ በዓል ነው።

ጊፋታ የወላይታ ብሔር ከጥንት ጀምሮ ሲያከብሩ የነበረ የአሮጌው ዓመት ማብቂያና የአድሱ ዓመት መጀመሪያ የዘመን መለወጫ በዓል ነው፡፡

በወላይታ ህዝብ ዘንድ ጊፋታ ሰዎች ብቻ ሳይሆኑ አእዋፋትና የቤት እንስሳትም ጭምር በጋራ የሚያከብሩት በዓል እነደሆነ በዚሁ አጋጣሚ ልገልጽላችሁ እፈልጋለሁ፡፡

የጊፋታ በዓል በውስጡ ማህበራዊ፣ ባህልዊ፣ ፖለቲካዊና ስነልቦናዊ ፋይዳዎችን የያዘ ሲሆን በህዝቦች መካከል ያለው የአብሮነት፣ የአንድነትና የመቻቻል እሴቶች በውስጡ የሚገለጹበት ነው፡፡

በዞናችን ውስጥ ባለፉት ዓመታት ውስጥ የተከናውኑ የልማት፣የዴሞክራሲና የመልካም አስተዳደር ተግባራትን በማጠናከር በቀጣይም ከህዝባችን ጋር በመሆን ለመሥራት ያቀድናቸውን ተግባራት ከህዝባችን ጋር በመወያየት ጠንካራ የለዉጥ እንቅስቃሴ የምንመራበት ወቅት ሊሆን ይገባል፡፡

ጊፋታ የተጣሉ የሚታረቁበት የእርቅና የሠላም በዓል ነው፡፡ በወላይታ ብሔር ማንም የተጣላ ሰው ሳይታረቅ አዲሱን ዓመት መሻገር ነውር ነው፡፡

መላዉ የወላይታ ህዝብ ይሄ ብርቅዬ ባህል ሳይበረዝና ሳይከለስ ከትዉልድ ወደ ትዉልድ እንዲተላለፍና ከነሙሉ ክብሩ ተጠብቆ እንድቆይ የሁል ጊዜ ትጋታችሁን አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ እጠይቃለሁ፡፡

የወላይታ ህዝብ ሀብትና ንብረት የሆነውን የጊፋታን በዓል በቀጣይ የኢትየጵያ ህዝብ በዓል በማድረግ በዓለም ከሚገኙ ከማይዳሰሱ የሰው ልጆች ወካይ እንድታበርክቱ ቅርሶች አንድ አድርገን ለማስመዝገብ ለምናደርገው ጥረት ሁላችሁም የበኩላችሁን አስተዋፆኦ እንድበረከቱ ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡

ተፈጥሮ ህጓን ጠብቃ፤ ክረምት በጋውን ስታፈራርቅ፣ መሄር በልጉን ስታመጣ፣ ፀሃይ ብርሃኗን፣ ስማይ ዝናቡን፣ መሬት ቡቃያዋን እንዳትከለክል ፈጣሪያችን እንዲረዳን ምኞተም ጸሎቴም ነው፡፡

ሠላም የሁሉም መሠረት ነው። ሠላም ማለት ሰው፣ ሀገር፣ ይቅርታ፣ ፍቅርና አንድነት ነው። ሠላም ካለ ሁሉም አለ። የሀገራችንን ሠላም በጋራ እንጠብቅ። ጥላቻን አርቀን በፍቅር እንኑር።

የኢትዮጵያዊነት የመጨረሻው መዳረሻው ሠላም፣ ፍቅርና አንድነት ነው። እያንዳንዳችን ለሀገራችን ሠላም የየድርሻችንን እንወጣ።

መረዳዳትና መደጋገፍ የብልፅግና አንኳር እሴት ነው!! ስለዚህ በዓሉን ስናከብር የተቸገሩትን በመርዳት፣ በመተሳሰብ፣ በይቅር-ባይነት፣ በመግባባት፣ በወንድማማችነትና በአብሮነት መንፈስ ልናከብር ይገባናል፡፡

በዓሉ የሠላም፣ የፍቅር፣ የጤና፣ የአንድነትና የብልጽግና እንዲሆን በራሴና በዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ስም በድጋሚ መልካም ምኞቴን እገልጻለሁ፡፡

ዮ ዮ ጊፋታ!
ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን እግዚአብሔር ይባርክ!

10/09/2022

“አዲሱ ዓመት አቅደን የሚንፈጸምበትና ሰርተን የሚንለወጥበት፣ ሠላምና ፍቅር የሚነግስበት እንዲሆንልን እመኛለሁ”፡- አቶ ዮሐንስ በየነ

የተወደዳችሁ መላው የኢትዮጵያ ሕዝቦች!!

የተወደዳችሁ መላው የዞናችን ህዝቦች፤ የፓርቲያችን አባላትና ደጋፊዎች!

እንኳን ለ2015 አዲሱ ዓመት/እንቁጣጣሽ/ በዓል በሠላም አደረሳችሁ! አደረሰን!!

አሮጌው ዓመት አልፎ አዲስ እየተተካ የክረምት፣ የጭቃ፣ የዝናብ፣ የብርድና የጨለማ ጊዜ አልፎ የብርሃን ጊዜ እየመጣ ሁሌም እየተደሰትን ከአንዱ ዘመን ወደ ሌላ ዘመን በየእድሜያችን ቁጥር ልክ ተሸጋግረናል። ይህንን ዕድል ሳያገኙ ወደ አዲሱ ዘመን መሻገር ያላቻሉ ብዙዎች አሉና።

አዲስ ዘመን ሲመጣ ዘመኑ ካለፈው ዘመን የተለየና እንደ ስያሜው አዲስ እንዲሆንልን ከፈለግን በሚመጣው ዘመን ውስጥ አዲሰ ሆነን ሲንገኝ ነው። ስለ አዲስ ዘመን ስናወራ ራሳችንም ማደስ ይገባናል።

ከዘመን ወደ ዘመን ስንሸጋገር አሮጌ ባህሪያችንንና አስተሳሰባችንን ቀብረን አዲስ ሕይወት ይዘን አዲሱን ዓመት ልንቀበለው ይገባል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከብዙ ውጣ ውረዶች ውስጥ አልፈን ትላልቅ ስኬትና ውጤት እንድናስመዘግብ በሀሳብ፣ በሞራል፣ በጊዜና በዕውቀት እንዲሁም በሁሉም መስክ ያላሰለሰ ድጋፍ ያደረጋችሁ በሙሉ በያለችሁበት ቦታ ሁሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናና አክብሮት ይደርሳችሁ፡፡

የምንፈልገውን ልማት፣ ዴሞክራሲ፣ሁለንተናዊ ሠላምና ብልጽግናን በአጭር ጊዜ ዕውን ለማድረግ የድል ብልጽግናን የሚያበሰሩ ነባራዊ እውነቶች ላይ ቆመን በአዲስ መንፈስ መረባረብ እንዳለብን ይሰማኛል፡፡

ውድ የፓርቲያችን አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲያችን ብልጽግና በምርጫ ወቅት ለህዝባችን ቃል የገባውን ማኒፌስቶን ወደ ተግባር ለመቀየር የሚጠበቅባችሁን ኃላፊነት በትጋት እንድትወጡ በዚህ አጋጣሚ ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡

ከወግ አጥባቂነትና ከጽንፈኝነት ዝንባሌዎች እንዲሁም አፍርሰን ከመገንባት አስተሳሰቦች ተላቅቀን መካከለኛውን መንገድ ይዘን ለሁለንተናዊ ብልጽግና መትጋት አለብን፡፡

የተከበራችሁ የዞናችን ህዝቦች፡- በዞኑ ውስጥ የሚደረጉ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና የልማት እንቅስቃሴዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የድርሻችሁን ያልተቆጠበና የላቀ ተሳትፎ እንድታደርጉ ላሳስባችሁ እወዳለሁ፡፡

የምንወዳትና እንደዐይናችን ብሌን የምንሳሳላት ሀገራችን ኢትዮጵያ የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት እንድትሆን የሚያለያዩ ሁኔታዎችን ከማጉላት ይልቅ የሚያቀራርቡና የሚያስተሳስሩንን እውነታዎች ላይ ማተኮርና መጠንከር ያስፈልጋል፡፡

ጥላቻን ነቅለን ፍቅርን እየተከልን፤ አንዳችን ለሌላችን ዋልታ እና ማገር፣ ድርና ማግ ሆነን የጀመርነውን የብልጽግና ጉዞ እውን እንዲሆን መላው የዞናችን ማህበረሰብ ተግቶ እንዲሰራ ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡

አሸባሪው ህወሐት የሠላም አማራጮችን አሻፈረኝ ብሎ ለ3ተኛ ጊዜ የከፈተብንን ጦርነት ለመቀልበስ ውድ ህይወታቸውን ሳይሰስቱ በዱርና በበረሃ እየተዋደቁ ላሉ ለሀገር መከላከያ ሠራዊትና ለጥምር ጦሩ የዞኑ ህዝብ ላደረገው ድጋፍ ልዩ ክብር አለኝ።

ሰላም የሁሉ መሠረት ነውና ሰላማችንን እንጠብቅ፣ ያላወቅነውን ለማወቅ፣ ያወቅነውን በጎ ነገር ለሌሎች ለማሳወቅ እንትጋ፣ አካባቢያችንን ብሎም አገራችንን ለማልማትና ወደ ብልፅግና ማማ ለማውጣት ተግተን እንሥራ የሚለው ዋና መልዕክቴ ነው፡፡

በዓሉን ስናከብር የተቸገሩትንና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ውስጥ ለሚገኙ ወገኖቻችንን በመርዳት፣ በመተሳሰብ፣ በይቅር-ባይነት፣ በመግባባት፣ በወንድማማችነት፤ በእህታማማችነትና በአብሮነት መንፈስ ልናከብር ይገባል፡፡

በድጋሚ ለመላው የሀገራችንና የወላይታ ህዝብ አዲሱ አመት የሰላም፣ የጤና፣ የብልጽግናና የከፍታ ዓመት እንዲሆን ልባዊ ምኞቴ ነው፡፡

እንኳን በሠላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ!! መልካም አዲስ ዓመት!!

ዮሐንስ በየነ
የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!

31/08/2022

ኢትዮጵያ 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

Address

Wolaita
S**o

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Jemberu Times posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Nearby media companies


Other News & Media Websites in S**o

Show All