ሱብሀነላህ
እናትና አባቱን ይዞ በሀጅ ላይ
ትግላችን ሙስሊሙን ከሚያከፍሩ የአህባሽ ተክፊሮች ጋር ነው
ኡመር ኮምቦልቻ
ትላንት አንዳንድ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች እየተባለ አስተያየቱን ሲሰጥ የነበረ፣በአወልያ በመፍትሄ አፈላላጊ ኪሚቴዎች ላይ መንግስት እርምጃ ሲወስድ በኢቢሲ ወጥቶ የተናገረ ሰው ነው ። አንዳንድ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች እየተባለ ሲቀርብ የነበረ ሰው ነው ።
ለዚህ ውለታው የቀድሞ ኢህአዴግ ኮሚቴዎችን ካሰረ በኋላ የመጅሊስ ምክትል ፕሬዝዳንት አድርጎ ሾመው
ከዚያስ በየቦታው ስልጠና ሲሰጥ እንዲህ እያለ ይናገር ነበር በድምጽ ማስረጃው ተያይዟል
-ይሁዳውንም ነሷራውንም (ክርስቲያኑንም ) እንቀባለን ነገር ግን ውህብያ ካፊር ነው ። በኢስትግፋር ሳይሆን ሸሃዳ ይዞ ወደ ኢስላምና ይምጣ ።
-ውህብያ ሚስቱ የሆነች ወይም ባል የሆነ ኒካሁ ውድቅ ነው
-ሶላት እነሱንም ተከትሎ መስገድ አይበቃም
እያለ ሙስሊሙን ሲያከፍር የኖረ ሰው ነው ።
በጣም አሳፋሪው ነገር ይሄንኑ ሰው የሸሪዓ ፍርድ ቤት ዳኛ ሁኖ ተሽሟል
አሁን እንግዲህ ከሙፍቲ ጎን ነኝ ብሎ ተሰልፎ ያለው ይሄ ሰው ነው ።
ታዲያ ከነዚህ ሰዎች ምን ይጠበቃል ?
ሙስሊሙን ከሚያከፍር ተክፊር ከዚህ በላይ አይጠበቅም
ለማንኛውም ከንግዲህ ይበቃል ! እውነታው ይኼው ነው ~
የመጅሊስ ችግር የስልጣን እንጂ ሃይማኖታዊ አይደለም!
🔻🔻🔻🔻🔻🔻🔻🔻🔻🔻🔻🔻🔻🔻🔻
በአህመዲን ጀበል
ሙፍቲ ሀጅ ዑመር እድሪስ በጠቅላላ ጉባኤው ዉሳኔ ከመጅሊስ ፕሬዝዳንትነት ተነስተው «ሙፍቲ» ወደ ተባሉበት የፈትዋ ክፍል ሲመደቡ የመጅሊስን ችግር የሱፊ/ሰለፊ በማድረግ ልዩነቱ ሃይማኖታዊ እንደሆነ አድርገው ቢገልጹም ፕሬዝዳንት ተደርገው በተመደቡ ቀን በሚያዚያ 23 ቀን 2011 በሸራተን ሆቴል ግን በዚህ ቪዲዮ እንደሚመለከቱት እንዲህ ብለው ነበር: -
«ከተወሰነ ጊዜያት ወዲህ ወንድሞቻችን ጋር ተለያይተናል። እህቶቻችን ጋር በሀሳብ ተለያይተናል፤ ሃይማኖት አያለያይም፤ የአኪራ ጉዳይ አያለያይም። ከሞት በኋላ ያለው ጉዳይ አያለያይም፤ የሚያለያየ ስልጣን ነው።የሚያለያየው ጥቅም ነው። የሚያለያየው ገንዘብ ነው አዩሀል ዑማ፤እንደዚህ ያለውን ከዉስጣችን ዉልቅ አድርጎ የአኪራ ሰው እንዲያደርገን ዱዓ እናደርጋለን፤»(ሙፍቲ ሐጅ ዑመር እድሪስ፥ሚያዚያ 23 ቀን 2011 በሸራተን ጉባኤ ላይ የተናገሩት)
ትላንትን ዛሬም እየደገሟት ነው
ዛሬ በሱፍያ ስም የሚምሉ የሚገዘቱ ሰዎች የትናንት ማንነታቸው ይህ ነበር ኢንሻአላህ ሱፍያው ነፃ ይወጣል
በጎንደር የተፈጸመውን የሽብር ጥቃት አስመልክቶ በትላንትናው እለት የአሜሪካው ድምጽ ሬዲዮ (VOA) የሰራው ዘገባ
...
በዘገባው እንደተገለጸው፦
...
◾️ከጥቃቱ በኃላ አሁንም ድረስ አላጋጋመችም
◾️ በተለያየ ወቅት ጥላቻን ሲነዙ የቆዩና ለግጭቱ እርሾ የጣሉ የቤተ ክርስቲያን መምህራን "እኛን አይወክሉም" ብለው ስለ ዩራኒየም ያወሩት እራሳቸው የጥቃቱ ዋነኛ መሪ ቀሲስ ዮሴፍ ሲናገሩ ተሰምተዋል።
◾️ ከተማ አስተዳደሩ ከአከባቢው የሚወጡ ገለልተኛ መረጃዎችን በአይነ ቁራኛ ይከታተል እንደነበርና ኢትዮ ቴሌኮምም ኔትዎርኩን በመዝጋት አፈና መፈጸሙን ዘገባው አትቷል።
◾️ የጎንደር እስልምና ም/ቤት ጥቃቱ ለአመታት ሲጠመቅ የቆየ እንደነበር ገልጿል። የነበረውን ስጋት በተመለከተም ለሚመለከተው አካል ቀድመው ማሳወቃቸውን ሳይቀር ገልጸዋል።
◾️ የጎንደር ድባብ አሁንም ቢሆን ውጥረት ያለበት ነው።
..
ሙሉውን ፕሮግራም ከዘገባው ይመልከቱ፦
..
© ሀሩን ሚዲያ
«እንኳንስ የሩቁን ሰዉ የቅርብ ጊዜውን ራሱ መች በወጉ ያስታውስና?»
🔥🔥 🔥 🔥 🔥 🔥
በአህመዲን ጀበል የተፃፈ
በትናንትናው እለት ‹‹አላህ ሽቶብኝ ነው እንጂ እኔ ስልጣን አልፈልግም›› በሚል ርዕስ ባስነበብኩት ጽሑፍ ላይ ከደረሱኝ በርካታ አስተያየቶችና ሀሳቦች መካከል አንድ ወንድም «እንኳንስ የሩቁን ሰዉ የቅርብ ጊዜውን ራሱ መች በወጉ ያስታውስና?» ብሎ አንድ ቪዲዮ ልኮልኛል።
በ2004 ሕዝበ ሙስሊሙ «ድምጻችን ይሰማ» ብሎ ካነሳቸው ሦስት ጥያቄዎች መካከል አንዱ «መሪዎቼን በነጻነት የመምረጥ መብቴ ይከበር» የሚል ነበር። በዚህ ትግል ከ20ሺህ በላይ ሙስሊሞች ታሰረውበታል።በርካቶች ቆስለው ሞተውበታል። በወቅቱ በርካታ ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖች ጭምር ሙስሊሞች በመጅሊስ ላይ በነጻነት መሪዎቻቸውን የመምረጥ መብታቸው ሊከበር ይገባል» ብለው አጋርነታቸውን ለማሳየት በተለያየ መንገድ ደግፈዋል።
የድማጻችን ይሰማ ትግልን በኃይል ማፈን የተሳነው የያኔው የኢህአዴግ መንግስትም የመጅሊስን ምርጫ ጥያቄን ማፈንና ማስቀረት ሲሳነው የደህንነት መሥሪያ ቤቱና የፌደራል ጉዳይ ሚኒስቴር በጋራ ድራማ በመስራት ወሰኑ። ለዚሁ ስኬት ያዘጋጁዋቸውን ካድሬዎችን «ምርጫ ተደረገ» በሚል ስም ሌሎች እነርሱ የሚፈልጓቸውን ሰዎችን ወደ መጅሊስ ለማምጣት ተዘጋጁ።
ሕዝቡ ሲቃወማቸው በነበሩት የያኔው የመጅሊስ አመራሮች በኩል በመስከረም 27 ቀ
አቡበከር ሱለይማን ያለ እውቀት አውርቷል!!
------
ሰለፊዮች ሰነድ የላቸውም ለሚለው ቅጥፈት በቂ ምላሽ በሸይኽ ኢልያስ አህመድ
"እኛ ሱፊ ሰለፊ እያል ስንጓተት ህዝባችንን በየ መንደሩ ሲገደል!!"
ይህ ሳያሳስበን ቀርተን ለግል ፍላጎታችን እና የእኔን ቡድን ከፍ ለማድረግ የምንሄድበት አካሄድ በታሪክ ያስወቅሰናል እና ቆም ብለን እናስብ!!
ኡስታዝ ሙሀመድ ሙስጠፋ
በትላንትናው እለት ምን ተፈጠረ ከሰብሰባው ተካፋይ የተሰጠ