Nahoo Sport

Nahoo Sport ለፈጣን ሀገራዊ እና የባህር ማዶ ስፖርታዊ መረጃዎች ምርጫዎ ያድርጉ ።

🇪🇹🇪🇹🇪🇹
04/01/2024

🇪🇹🇪🇹🇪🇹

ዋይኒ ሩኒ ከአሰልጣኝነት መንበሩ ተሰናብቷል !የሻምፒዮን ሺፑን ክለብ በርሚንግሀም ሲቲን ሲያሰለጥን የነበረው ዋይኒ ሩኒ ከክለቡ አሰልጣኝነት ተሰናብቷል። 5ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ የነበረውን ክ...
02/01/2024

ዋይኒ ሩኒ ከአሰልጣኝነት መንበሩ ተሰናብቷል !

የሻምፒዮን ሺፑን ክለብ በርሚንግሀም ሲቲን ሲያሰለጥን የነበረው ዋይኒ ሩኒ ከክለቡ አሰልጣኝነት ተሰናብቷል። 5ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ የነበረውን ክለብ ከተረከበ በኋላ ባደረጋቸው 15 ጨዋታዎች 2ቱን ብቻ ያሸነፈው ሩኒ በርሚንግሀምን በደረጃ ሠንጠረዡ 20ኛ ደረጃ ላይ ካስቀመጠ በኋላ ከሀላፊነቱ ተነስቷል።

ክሪስቲያኖ ሮናልዶ 2023 ን በከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ማጠናቀቅ ችሏል ።
31/12/2023

ክሪስቲያኖ ሮናልዶ 2023 ን በከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ማጠናቀቅ ችሏል ።

የሊጉ ክለቦች ከዩናይትድ ጋር መች እንደሚጫወቱ ለማየት ...😁😁
30/12/2023

የሊጉ ክለቦች ከዩናይትድ ጋር መች እንደሚጫወቱ ለማየት ...😁😁

ማንችስተር ዩናይትድ እንደተለመደው ሽንፈት አስተናግዷል !!በሀያኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንችስተር ዩናይትድ ከኖቲንግሀም ፎረስት ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2 ለ 1 በሆነ...
30/12/2023

ማንችስተር ዩናይትድ እንደተለመደው ሽንፈት አስተናግዷል !!

በሀያኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንችስተር ዩናይትድ ከኖቲንግሀም ፎረስት ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ተሸንፈዋል።

የኖቲንግሀም ፎረስትን የማሸነፊያ ግቦች ዶምኒጉዌዝ እና ጊብስ ዋይት ሲያስቆጥሩ ለማንችስተር ዩናይትድ ማርከስ ራሽፎርድ ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።

ማንችስተር ዩናይትድ በዘንድሮው የውድድር ዘመን በሊጉ ዘጠነኛ እንዲሁም በሁሉም ውድድሮች አስራ አራተኛ ሽንፈታቸውን አስተናግደዋል።

ሸገር ደርቢ በቡናማዎቹ አሸናፊነት ተጠናቀቀ !!በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የሰባተኛ ሳምንት ተስተካካይ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ቡና ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1ለ0 በሆነ ውጤት ማሸ...
30/12/2023

ሸገር ደርቢ በቡናማዎቹ አሸናፊነት ተጠናቀቀ !!

በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የሰባተኛ ሳምንት ተስተካካይ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ቡና ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

ቡናማዎቹን አሸናፊ ያደረገች ብቸኛ ግብ ጫላ ተሺታ በሁለተኛው አጋማሽ ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።

ጫላ ተሺታ በውድድር ዘመኑ ያስቆጠራቸውን ግቦች ወደ ሶስት ከፍ ማድረስ ችሏል።

ፈረሰኞቹ በውድድር ዘመኑ ሁለተኛ የሊግ ጨዋታቸውን ተሸንፈዋል።

ኢትዮጵያ ቡና ማሸነፉን ተከትሎ ነጥቡን አስራ አንድ በማድረስ ሰባተኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ቅዱስ ጊዮርጊስ በአስራ ስድስት ነጥቦች አራተኛ ደረጃን ይዟል።

'' ፖሊስ ደጋፊዎቼ ላይ በሚወስደው እርምጃ ተባባሪ እሆናለው '' የኢትዮጵያ ቡና ክለብ ደጋፊዎች ማህበር !!የኢትዮጵያ ቡና ክለብ ደጋፊዎች ማህበር ዛሬ መግለጫ አውጥቷል በመግለጫው ከቅርብ ...
27/12/2023

'' ፖሊስ ደጋፊዎቼ ላይ በሚወስደው እርምጃ ተባባሪ እሆናለው ''

የኢትዮጵያ ቡና ክለብ ደጋፊዎች ማህበር !!

የኢትዮጵያ ቡና ክለብ ደጋፊዎች ማህበር ዛሬ መግለጫ አውጥቷል በመግለጫው ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለይም ከዘንድሮ የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ ውድድር ጅማሮ አንስቶ የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ በሚሳተፍበት በታላቁ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግና በኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ዋንጫ ውድድሮች ላይ የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ እንዳይሳተፍ ! የቦርድ ሊቀመንበር፣ የክለቡን ስራ አስኪያጅ፣ የደጋፊ ማህበሩን ስራ አስፈጻሚዎችን፣ አስተባባሪዎችን እና ለስታዲየማችን ድምቀት በመሆን አስጨፋሪዎች ለክለቡ ውጤት የሚለፉትን ያለ በቂ ማስረጃ በመዝለፍ እና በማስፈራራት ስራ እንዳይሰራ መከልከል ስራዎች ላይ ጥቂት ደጋፊዎች ተሰማርተው ተገኝተዋል።

በተጨማሪም በማህበራዊ ሚዲያና በውድድር ስፍራዎችም በተቀናጀና ከፍተኛ ድጋፎችን በማስተባበር ከስም ማጥፋት እስከ ንብረት የማውደምና ክለቡን ለከፍተኛ የህልውና አደጋ እየዳረጉት ይገኛሉ ብለዋል በመግለጫው።

በመሆኑም የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ደጋፊዎች ማህበር እስካሁን የተጓዘባቸው ርቀቶች መፍትሄ ለማምጣት ባለመቻላቸው ከዚህ በኋላ ክለባችን ጨዋታ በሚያደርግባቸው የውድድር ስፍራዎች የሚከሰቱ የጸጥታ መደፍረሶች ለማስተካከል የሚመለከተው የአገሪቱ የጸጥታ አካል ለሚወስዳቸው ማናቸውም ህጋዊ እርምጃዎች ተባባሪ መሆኑን ያስታውቃል።

በተጨማሪም በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያያዎች ላይ የተለያዩ የስም ማጥፋት እና ደጋፊዎችን ላልተፈለገ አመጽ የሚገፋፉ በስመ የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ደጋፊነት ሽፋን ህገ-ወጥነትን የሚያበረታቱ ጥቂት ግለሰቦችን ቡድኖችን የሚመለከተው የፀጥታ ኃይሉ አስፈላጊውን የእርምት እርምጃ እንዲወስድ ቅድመ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን እናሳውቃለን ሲል በመግለጫው መልዕክት አስተላልፏል።

ጋናዊዉ አማካይ ወደ ሜዳ ተመልሷል !!ቶማስ ፓርቴ ከጉዳቱ አገግሞ ወደ ሙሉ ልምምድ የተመለሰ ሲሆን አርሰናል ነገ ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር በሚኖረው ጨዋታም የስብስቡ አካል እንደሚሆን ይጠበቃ...
27/12/2023

ጋናዊዉ አማካይ ወደ ሜዳ ተመልሷል !!

ቶማስ ፓርቴ ከጉዳቱ አገግሞ ወደ ሙሉ ልምምድ የተመለሰ ሲሆን አርሰናል ነገ ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር በሚኖረው ጨዋታም የስብስቡ አካል እንደሚሆን ይጠበቃል።

ወሳኙ የጉዲሰን ፓርክ ፍልሚያ !!✔️ኤቨርተን ከ ማንችስተር ሲቲ ጋር ባደረጋቸው ያለፉት 20 የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው በአንዱ ብቻ ነው።✔️ማንችስተር ሲቲ ወደ ጉዲሰን ፓርክ ...
27/12/2023

ወሳኙ የጉዲሰን ፓርክ ፍልሚያ !!

✔️ኤቨርተን ከ ማንችስተር ሲቲ ጋር ባደረጋቸው ያለፉት 20 የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው በአንዱ ብቻ ነው።

✔️ማንችስተር ሲቲ ወደ ጉዲሰን ፓርክ አቅንቶ ኤቨርተንን በገጠመባቸው ያለፉት ስድስት የሊጉ ጨዋታዎች በሁሉም ማሸነፍ ችሏል።

✔️ኤቨርተን በዛሬው ጨዋታ ድል የሚያደርግ ከሆነ ከመስከረም 2021 በኋላ በሜዳቸው ያደረጓቸውን ሶስት ተከታታይ የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች በማሸነፍ ጥሩ ሪከርዳቸውን ይደግማሉ።

✔️ሲቲዝኖቹ በፕሪሚየር ሉጉ ካደረጓቸው ያለፉት ስድስት መርሃ ግብሮች ማሸነፍ የቻሉት በአንዱ ብቻ ነው።

✔️ማንችስተር ሲቲ በፕሪሚየር ሊጉ ባደረጓቸው ያለፉት ሰባት ጨዋታዎች በእያንዳንዱ ግብ አስተናግደዋል።

✔️የኤቨርተኑ አሰልጣኝ ሲያን ዳይች ማንችስተር ሲቲን በተቃራኒው በገጠመባቸው ያለፉት 13 የሊጉ ጨዋታዎች በ12ቱ ሽንፈት አስተናግደዋል።

✔️አብደላይ ዶኩሬ በጉዲሰን ፓርክ በተደረጉ ያለፉት ሁለት የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች ግብ ማስቆጠር ችሏል።

✔️ጃክ ግሪሊሽ በፕሪሚየር ሊጉ ባደረጋቸው ያለፉት ሶስት ጨዋታዎች ሶስት ግቦችን ማስቆጠር ችሏል : ይህም ተጨዋቹ ከዚህ በፊት ባደረጋቸው 23 ጨዋታዎች ካስቆጠረው የግብ ብዛት ጋር እኩል ነው።

አዲስ አበባ ከተማ በከፍተኛ ሊግ ምድብ ሀ  ያለመሸነፍ ግስጋሴውን አስቀጥሏል !!የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ ሀ ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው አዲስ አበባ ከተማ በስምንተኛ ጨዋታ መርሀግብር ሀላ...
27/12/2023

አዲስ አበባ ከተማ በከፍተኛ ሊግ ምድብ ሀ ያለመሸነፍ ግስጋሴውን አስቀጥሏል !!

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ ሀ ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው አዲስ አበባ ከተማ በስምንተኛ ጨዋታ መርሀግብር ሀላባ ከተማን አንድ ለባዶ በማሸነፍ ያለመሸነፍ ጉዞውን አስቀጥሏል። በአሰልጣኝ ፖውሎስ ጌታቸው ማንጎ እየተመራ ምንም ሽንፈት ሳያስተናግድ ካለፉት ስምንት ጨዋታ አምስቱን አሸንፎ በስስቱ አቻ ተለያይቶ አስራ ስምንት ነጥብ ይዞ በአንድ የግብ ክፍያ ከኢትዮ ኤሌትሪክ ቀጥሎ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

አምና ይዞት ከነበረው ስብስብ ውስጥ አስራ አንድ የቡድኑን ተጨዋቾች አዲስ ፈራሚ አስራ ሁለት ተጨዋቾች እንዲሁም አራት ተጨዋቾች ከታዲጊ ቡድኑ አካቶ ጥቅምት ወር የቅድመ ዝግጅት ጊዜውን በአዲስ አበባ በማድረግ ሁለት የወዳጅነት ጨዋታ አንድ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ አድርጎ ነበር የውድድር ጊዜውን የጀመረው።

ከከፍተኛ ሊጉ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ክለቦች በማሳደግ የሚታወቀው ፖውሎስ ጌታቸው ማንጎ ዘንድሮስ ምን ሊያስመለክተን ይችላል የሚለው ከወዲሁ የሚጠብቅ ይሆናል።

ማንቸስተር ዩናይትድ በኦልትራፎርድ በቦክሲንግ ደይ ባደረጋቸው ያለፉት 20 ጨዋታዎች ሽንፈት አላስተናገደም ።17 አሸንፎ 3 አቻ ተለያይቷል።
27/12/2023

ማንቸስተር ዩናይትድ በኦልትራፎርድ በቦክሲንግ ደይ ባደረጋቸው ያለፉት 20 ጨዋታዎች ሽንፈት አላስተናገደም ።

17 አሸንፎ 3 አቻ ተለያይቷል።

ማንችስተር ዩናይትድ ከ2ለ0 መመራት ተነስቶ ማሸነፍ ችሏል !!በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ አስራ ዘጠነኛ ሳምንት መርሐ ግብር ማንችስተር ዩናይትድ ከአስቶን ቪላ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 3ለ2 በሆነ...
27/12/2023

ማንችስተር ዩናይትድ ከ2ለ0 መመራት ተነስቶ ማሸነፍ ችሏል !!

በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ አስራ ዘጠነኛ ሳምንት መርሐ ግብር ማንችስተር ዩናይትድ ከአስቶን ቪላ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 3ለ2 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

የማንችስተር ዩናይትድን የማሸነፊያ ግቦች አሌሀንድሮ ጋርናቾ ሁለት እና ራስሙስ ሆይሉንድ ከመረብ ማሳረፍ ሲችሉ ለአስቶን ቪላ ማክ ጊን እና ዴንዶንከር አስቆጥሯል።

የማንችስተር ዩናይትድ የፊት መስመር ተጨዋች ራስሙስ ሆይሉንድ የመጀመሪያ የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ግቡን ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።

ሊቨርፑል የሊጉን መሪነት ተረክቧል !በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ የአስራ ዘጠነኛ ሳምንት መርሐ ግብር የ ሊቨርፑል ከበርንሌይ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።የሊቨርፑልን...
26/12/2023

ሊቨርፑል የሊጉን መሪነት ተረክቧል !

በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ የአስራ ዘጠነኛ ሳምንት መርሐ ግብር የ ሊቨርፑል ከበርንሌይ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

የሊቨርፑልን የማሸነፊያ ግቦች ዳርዊን ኑኔዝ እና ዲያጎ ጆታ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል ፤ ይሄንንም ተከትሎ ሊቨርፑል የሊጉን መሪነት በጊዜያዊነት ከአርሰናል መረከብ ችሏል።

በየ 23 ጨዋታዉ አንድ ዋንጫ !!አሰልጣኝ ፔፕ በአቬሬጅ በየ23 ጨዋታዉ አንድ ዋንጫ አሸናፊ ሆኗል ፤ እስከአሁን በአሰልጣኝነት 8️⃣4️⃣9️⃣ ጨዋታዎችን የመራ ሲሆን የትላንት ምሽቱን ጨምሮ...
23/12/2023

በየ 23 ጨዋታዉ አንድ ዋንጫ !!

አሰልጣኝ ፔፕ በአቬሬጅ በየ23 ጨዋታዉ አንድ ዋንጫ አሸናፊ ሆኗል ፤ እስከአሁን በአሰልጣኝነት 8️⃣4️⃣9️⃣ ጨዋታዎችን የመራ ሲሆን የትላንት ምሽቱን ጨምሮ 3️⃣7️⃣ ዋንጫዎችን አሸንፏል ።

🏆🏆🏆🏆🏆 Premier League
🏆🏆🏆🏆 Club World Cup
🏆🏆🏆🏆 EFL Cup
🏆🏆🏆🏆 UEFA Super Cup
🏆🏆🏆 Champions League
🏆🏆🏆 La Liga
🏆🏆🏆 Bundesliga
🏆🏆🏆 Supercopa España
🏆🏆 Community Shield
🏆🏆 Copa del Rey
🏆🏆 DFB Pokal
🏆🏆 FA Cup

🙄🙄ለፔፕ ጋርዲዮላዉ ቡድን እጅጉኑ መጥፎ ዜና !!የማንቸስተር ሲቲዉ አማካይ ሮድሪ ጎዳት አስተናግዶ ተቀይሮ ወጥቷል ። እንደሚታወቀው ሲቲ ያለ ሮድሪ ያደረጋቸዉን 5 ጨዋታዎችን ማሸነፍ አለመቻ...
22/12/2023

🙄🙄
ለፔፕ ጋርዲዮላዉ ቡድን እጅጉኑ መጥፎ ዜና !!

የማንቸስተር ሲቲዉ አማካይ ሮድሪ ጎዳት አስተናግዶ ተቀይሮ ወጥቷል ። እንደሚታወቀው ሲቲ ያለ ሮድሪ ያደረጋቸዉን 5 ጨዋታዎችን ማሸነፍ አለመቻሉ ይታወሳል ። 😁😁

ማንችስተር ሲቲ ሻምፒዮን ሆኗል 🏆🏆ማንችስተር ሲቲ ከብራዚሉ ክለብ ፍሉሚኔንስ ጋር ያደረገውን የአለም ክለቦች ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ 4ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሻምፒዮን መሆን ችለዋል።በአሰልጣኝ...
22/12/2023

ማንችስተር ሲቲ ሻምፒዮን ሆኗል 🏆🏆

ማንችስተር ሲቲ ከብራዚሉ ክለብ ፍሉሚኔንስ ጋር ያደረገውን የአለም ክለቦች ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ 4ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሻምፒዮን መሆን ችለዋል።

በአሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ የሚመራው ማንችስተር ሲቲ በአንድ አመት ውስጥ አምስት ዋንጫዎችን ማሳካት የቻለ የመጀመሪያው የእንግሊዝ ክለብ መሆን ችለዋል።

 የማያረጀዉ አንበሳ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በ2023 በአመቱ አጠቃላይ 51ኛ ጎሉን ማስቆጠር ችሏል።ንጉሱ ለአልናስር በዚህ የውድድር አመት ለአልናስር 21 ጨዋታ አድርጎ 21 ግቦችን ሲያስቆጥር 1...
22/12/2023



የማያረጀዉ አንበሳ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በ2023 በአመቱ አጠቃላይ 51ኛ ጎሉን ማስቆጠር ችሏል።

ንጉሱ ለአልናስር በዚህ የውድድር አመት ለአልናስር 21 ጨዋታ አድርጎ 21 ግቦችን ሲያስቆጥር 10 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል።

ስዋሬዝ በይፋ ኢንተር ሚያሚን ተቀላቅሏል !የአሜሪካ ሜጀር ሊግ ሶከሩ ክለብ ኢንተር ሚያሚ የቀድሞ የባርሴሎና እና ሊቨርፑል ፊት መስመር ተጨዋች ሉዊስ ስዋሬዝ ማስፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል።ዩ...
22/12/2023

ስዋሬዝ በይፋ ኢንተር ሚያሚን ተቀላቅሏል !

የአሜሪካ ሜጀር ሊግ ሶከሩ ክለብ ኢንተር ሚያሚ የቀድሞ የባርሴሎና እና ሊቨርፑል ፊት መስመር ተጨዋች ሉዊስ ስዋሬዝ ማስፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል።

ዩራጋዊው የፊት መስመር ተጨዋች ሉዊስ ስዋሬዝ በኢንተር ሚያሚ ቤት የአንድ አመት ኮንትራት መፈረሙ ተገልጿል።

ፋሲል ከነማ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ ተሸንፏል !በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የስምንተኛ ሳምንት መርሐግብር ሀድያ ሆሳዕና ከፋሲል ከነማ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ ሀድያ 2ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏ...
15/12/2023

ፋሲል ከነማ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ ተሸንፏል !

በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የስምንተኛ ሳምንት መርሐግብር ሀድያ ሆሳዕና ከፋሲል ከነማ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ ሀድያ 2ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።

የሀድያ ሆሳዕናን የማሸነፊያ ግቦች ተመስገን ብርሀኑ እና ግርማ በቀለ ከመረብ ሲያሳርፉ ለፋሲል ከነማ ናትናኤል ገ/ጊዮርጊስ አስቆጥሯል።

በውድድር ዘመኑ ፋሲል ከነማ አስራ ሁለት እንዲሁም ሀድያ ሆሳዕና ስምንት ነጥቦችን መሰብሰብ ችለዋል።

ሸገር ደርቢ ተራዝሟል ! በነገው ዕለት በኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ መካከል ሊደረግ የነበረው ተጠባቂው የሸገር ደርቢ ጨዋታ ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙ ይፋ ሆኗል።አወዳዳሪው አካል ባወጣው...
08/12/2023

ሸገር ደርቢ ተራዝሟል !

በነገው ዕለት በኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ መካከል ሊደረግ የነበረው ተጠባቂው የሸገር ደርቢ ጨዋታ ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙ ይፋ ሆኗል።

አወዳዳሪው አካል ባወጣው መረጃ " በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ ስታዲየም የሚደረገው የኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ጨዋታ ላልተወሰነ ጊዜ ተራዘሟል " ሲል አሳውቋል።

አፄዎቹ ሽንፈት አስተናግደዋል !!በ7ተኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ወላይታ ዲቻ ፋሲል ከነማን 2ለ0 በሆገ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል።
07/12/2023

አፄዎቹ ሽንፈት አስተናግደዋል !!

በ7ተኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ወላይታ ዲቻ ፋሲል ከነማን 2ለ0 በሆገ ዉጤት ማሸነፍ ችሏል።

የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ  የዋናውን ቡድን አውቶብስ ርክክብ አካሄደ !!ከዛሬ አምስት አመት በፊት በአጋሩ ሃበሻ ቢራ አ•ማ ቃል ተገብቶ የነበረው የዋና ቡድን አውቶብስ በዛሬው ዕለት ለክ...
07/12/2023

የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ የዋናውን ቡድን አውቶብስ ርክክብ አካሄደ !!

ከዛሬ አምስት አመት በፊት በአጋሩ ሃበሻ ቢራ አ•ማ ቃል ተገብቶ የነበረው የዋና ቡድን አውቶብስ በዛሬው ዕለት ለክለቡ ርክክቡ ተከናዉኗል።

ባሱን ለመግዛት 17,5 ሚሊዮን ብር አጠቃላይ የወጣ ሲሆን BkG በላይነህ ክንዴ ግሩፕ ጎልደን ድራገን (Golden Dragon) የተሰኘውን 51 ሰው የሚጭን ባስ በዛሬው ዕለት ርክክብ ተካሂዷል ።

ርክክቡን የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ የቦርድ ስራ አስፈጻሚዎች ፣የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ የደጋፊ ማህበር ስራ አስፈጻሚዎች ፣የክለቡ ስራ አስኪያጅ በጋራ በመሆን የዘመናዊ አውቶብሱን ቁልፍ ዛሬ በካሌብ ሆቴል በተካሄደ ስነ-ስርዓት ተረክበዋል።

ሀሪ ማጓየር የወሩ ምርጥ ተጨዋች !አስራ አራተኛ ሳምንቱ ላይ የሚገኘው የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ የወርሀ ህዳር የወሩ ምርጥ ተጨዋች በመባል መመረጡ ተገልጿል።በዚህም መሰረት እንግሊዛዊው የማን...
06/12/2023

ሀሪ ማጓየር የወሩ ምርጥ ተጨዋች !

አስራ አራተኛ ሳምንቱ ላይ የሚገኘው የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ የወርሀ ህዳር የወሩ ምርጥ ተጨዋች በመባል መመረጡ ተገልጿል።

በዚህም መሰረት እንግሊዛዊው የማንችስተር ዩናይትድ የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ሀሪ ማጓየር የወርሀ ህዳር የፕርሚየር ሊግ የወሩ ምርጥ ተጨዋች በመሆን መመረጡ ታውቋል።

06/12/2023



ትላንት ምሽት በተደረገው የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የምድብ አራተኛ ዙር ጨዋታ የፈረንሳዩን ክለብ ሎንስ በሜዳዉ 6ለ0 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ የቻለዉ አርሰናል ከ2017 የውድድር አመት በኋላ ለመ...
30/11/2023

ትላንት ምሽት በተደረገው የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የምድብ አራተኛ ዙር ጨዋታ የፈረንሳዩን ክለብ ሎንስ በሜዳዉ 6ለ0 በሆነ ዉጤት ማሸነፍ የቻለዉ አርሰናል ከ2017 የውድድር አመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የጥሎ ማለፍ አስራ ስድስቱን መቀላቀል ችሏል።

አምስቱ ክለቦች ከሶስት ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ !!በህመም ምክንያት በቱርክ ሀገር በህክምና ላይ ለሚገኘዉ አንጋፋዉ አሰልጣኝ አስራት ሀይሌ ህክምና የሚዉል ገንዘብ የኢትዮጵ...
29/11/2023

አምስቱ ክለቦች ከሶስት ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ !!

በህመም ምክንያት በቱርክ ሀገር በህክምና ላይ ለሚገኘዉ አንጋፋዉ አሰልጣኝ አስራት ሀይሌ ህክምና የሚዉል ገንዘብ የኢትዮጵያ ፕሮፌሽናል እግርኳስ ተጫዋቾች ማህበር በማሰባሰብ ላይ ሲገኝ በዚህም በክለብ ደረጃ ፋሲል ከነማ ፣ ኢትዮጵያ ቡና ፣ ባህርዳር ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና መቻል ከሶስት ሚሊየን ብር በላይ ለመስጠት ቃል መግባታቸው ታዉቋል።

የአምስቱም ክለብ ተጫዋቾች በወር 1710 ብር ለአሰልጣኙ ለመለገስ ቃል መግባታቸው የተገለፀ ሲሆን ፤ ከዚህ በተጨማሪም ቅዱስ ጊዮርጊስ ከዋናዉ ቡድን በተጨማሪ የወጣት ቡድኑን ተጫዋቾች ጨምሮ በድጋፉ ላይ በወር ሁለት ሺ ብር እንደሚሰጡ ተነግሯል።

ይህንን ድጋፍ በማስተባበር ላይ የሚገኘዉ የኢትዮጵያ ፕሮፌሽናል እግርኳስ ተጫዋቾች ማህበር ትልቅ ምስጋና እንደሚገባዉ እየገለፅን ፤ ለአሰልጣኙ ህክምና የሚደረገዉ ድጋፍ በሌሎች ክለቦችም በአዳማ ቀጥሎ እንደሚከናወን ለማወቅ ተችሏል።

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ አስታወቀ !!ኢትዮጵያዊው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ከቀናት በኋላ  በፈረንጆቹ ታሕሳስ 3 ቀን በሚካሄደው የቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ አስ...
29/11/2023

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ አስታወቀ !!

ኢትዮጵያዊው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ከቀናት በኋላ በፈረንጆቹ ታሕሳስ 3 ቀን በሚካሄደው የቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ አስታወቀ፡፡

አትሌቱ ከደቂቃዎች በፊት በማህበራዊ ትስስር ገፁ ባሰፈረው ጽሑፍ ከብዙ ጊዜ ጉዳት በኋላ በቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ አስታውቋል።

22/11/2023

- በቀን ተጋለጡ ሲለን ....
- ከዚህ በኋላስ....? ምሽት 2:30 ሰዓት ይጠብቁ


 #ተሸንፈናል ዓለም ዋንጫ ማጣርያ 2ኛ የምድብ ጨዋታ !             ተጠናቀቀ🇪🇹 ኢትዮጵያ  0-3 ቡርኪና ፋሶ 🇧🇫                                           ...
21/11/2023

#ተሸንፈናል

ዓለም ዋንጫ ማጣርያ 2ኛ የምድብ ጨዋታ !

ተጠናቀቀ

🇪🇹 ኢትዮጵያ 0-3 ቡርኪና ፋሶ 🇧🇫

69' ብላቲ ቶውሬ
78' በርትራንድ ትራኦሬ (ፍ)
90' ዳንጎ ኦታራ

ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የዓለም ዋንጫ ማጣርያ የ3ኛ ዙር የመልስ ጨዋታ ዉጤት !🇪🇹 ኢትዮጵያ 4-0 ማሊ 🇲🇱 ⚽️35' እሙሽ ዳንኤል⚽️45' እሙሽ ዳንኤል⚽️ 65' መዓድን ሳህሉ ⚽...
19/11/2023

ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የዓለም ዋንጫ ማጣርያ የ3ኛ ዙር የመልስ ጨዋታ ዉጤት !

🇪🇹 ኢትዮጵያ 4-0 ማሊ 🇲🇱

⚽️35' እሙሽ ዳንኤል
⚽️45' እሙሽ ዳንኤል
⚽️ 65' መዓድን ሳህሉ
⚽️ 69' መሳይ ተመስገን

ኢትዮጵያ በድምር ውጤት 6-0 አሸንፋ ወደ መጨረሻው የማጣርያ ዙር ማለፏን አረጋግጣለች።

ኢትዮጵያ በመጨረሻው የሴቶች ከ20 ዓመት በታች ዓለም ዋንጫ ማጣርያ ዙር ሞሮኮን ትገጥማለች።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Nahoo Sport posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share