25/05/2023
የዓለም ምግብ ፕሮግራም WFP በትግራይ ክልል ከፍተኛ የሆነ የምግብ ዕርዳታ በአገር ውስጥ ገበያ መሸጡን የሚያሳይ ማስረጃ በማግኘቱ የምግብ አቅርቦቱን ማቆሙን አስታውቋል::
WFP በትግራይ ክልል ምርመራ መጀመሩንም የገለጸ ሲሆን WFP አስፈላጊው እርዳታ በጣም ተጋላጭ ለሆኑ ሴቶች፣ ወንዶች እና ህጻናት በትክክል መድረሱን ለማረጋገጥ አዳዲስ የመከላክያ እና ቁጥጥርን ዘዴዎች ለማዘመን እየሰራ እደሆነም ገልጿል::
WFP ዋና ዳይሬክተር ሲንዲ ማኬን በትግራይ ክልል የእርዳታ ምግቦች ለተራቡ ለተቸገሩ ሰዎች እንዳይደርስ ለሚደረገው ትልቅ ስርቆት ላይ WFP ከዚህ በኃላ ትዕግስት የለውም ብለዋል ። በትግራይ ክልል ይህን ዘረፋ የሚያደርጉ ሰዎች ክልልሉ ኃላፊነት በመውሰድ በህግ መጠየቅ አለበትም ብለዋል ዋና ዳሬክተሯ:: WFP ይህን መልስ የሰጠው ትናት በትግራይ ክልል እርዳታ ለምን ቆመ በማለት ህዝቡ በሰላማዊ ሰልፍ ለጠየቀው ጥያቄ መልስ እደሆነም ተገልጿል:: ሙሉ ዝርዝሩን ከመግለጫው ላይ ያንቡ 👇 https://www.wfp.org/news/wfp-statement-strengthened-actions-address-food-diversion-ethiopia