09/03/2024
ወላይታ ለየትኛውም ስፖርት Untaped Potential እምቅ አቅም ያላትና የስፖርተኞች መፍለቂያ ምድር መሆኗ እየተረጋገጠ መጥቷል፤ አሁንም ትኩረት ለስፖርት ልማት !
ባለፉት 6 ወራት ውስጥ ከወላይታ አከባቢ ክለቦች ወደ ሌላ እግር ኳስ ክለቦች የተዘዋወሩ ባለልዩ ተስጥኦ ጥበበኛ እግር ኳስ ተጨዋቾች ዝርዝር፦
1, ናትናኤል ዳንኤል (አጥቂ)፦ ከቦዲቲ ከነማ ወደ ፕርሚየር ሊጉ ክለብ ድሬዳዋ ከነማ፣
2, ዙርባቤል ፈለቀ (አማካይ) ከቦዲቲ ከነማ ወደ ፕርሚየር ሊጉ ክለብ ሀምባሪቾ ዱራሜ፣
3, ተመስገን ተፈሪ (ሸገር) ከቦዲቲ ከነማ ወደ ነቀምት ከነማ፣
4, ማሞ አየለ፣ ከድር ዳንስ እና ሙሉቀን ተስፋዬ(ዲማሪያ) ለደብረብርሃን ከነማ፣
5, ግሩም በለጠ (ጭርዱ) ከቦዲቲ ከነማ ወደ
አየር ኃይል(ንብ)፣
6, ከአረካ ከተማ ወደ ሱሉልታ ከነማ፣ (ከበዴሳ ከነማ የተገኘ)
7, ዘካሪያስ ጆብሮ (ዛክሩ) አረካ ከነማ ወደ ቦዲቲ ከነማ፣
8, ውብሸት ወልደ እና ሳዳም ዳንሳ ከአረካ ከተማ ወደ ቦዲቲ ከነማ፣
9, (ፐፕሲ) ከሶዶ ከነማ ወደ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ከነማ፣ (ከበዴሳ ከነማ የተገኘ)፣
10, አማኑኤል ኦልሳ፣ ዝናቡ ዳመነ እና ውብሸት ክፍሌ ከቦዲቲ ከነማ ወደ አዲስ አበባ ከነማ፣
11, ሌሎች የእግር ኳስ ተጨዋቾች ወደ ተለያዩ የኢትጵያ ፕርሚየር ሊግ እና ከፍተኛ ሊግ ክለቦችን በወላይታ አከባቢ ካሉ ክለቦች መዘዋወር ችለዋል።
ከዚህ በፊት በረከት ወልዴ፣ ሽመክት ጉግሳ፣ ቸርነት ጉግሳ፣ እዮብ ዓለማየሁ፣ አላዓዛር ፋስካ፣ ወዘተ የመሳሰሉ ስመጥር ተጨዋቾች ከክለብ አልፎ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድናችን ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውና እያበረከቱም መሆናቸው ይታወቃል።
የመጫወቻ ሜዳዎች፣ የታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀክት፣ ስልጠናና ውድድር መድረክ፣ የስፖርት ትጥቅና አልባሳት አቅርቦት፣ ወዘተ በልዩ ትኩረት ቢሠራበት Investment Return በአጭር ጊዜ በተጨባጭ የሚታይ ስለሆነ የከተማና ወረዳ መዋቅሮች ስፖርት ምክር ቤቶች ልዩ ድጋፍ ለዘርፉ ቢሰጡ መልካም ነው።