12/08/2022
የሩስያ እና ዩክሬን ጦርነት ከጀመረ ግዜ አንስቶ ለመጀመርያ ግዜ የዩክሬንን እህል ጭኖ ዛሬ ጉዞ የጀመረው ግዙፍ መርከብ የጭነቱ መዳረሻ ኢትዮጵያ እንደሆነ ታውቋል።
የአለም ምግብ ፕሮግራም የገዛው ይህ የእህል ጭነት በኢትዮጵያ ለሚገኙ የድርቅ እና ጦርነት ተጎጂዎች እንደሚከፋፈል ታውቋል። የሩስያ እና ዩክሬን ጦርነት ባስከተለው የምግብ ንረት ብዙ የአፍሪካ እና የላቲን አሜሪካ ሀገራት የመጀመርያውን ጭነት ለማግኘት ቢፈልጉም የአለም ምግብ ፕሮግራም ወደ ኢትዮጵያ እያጓጓዘው እንደሆነ ታውቋል።
ቱርክ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት፣ ዩክሬን እና ሩስያ ለዚህ መሳካት ቁልፍ ሚና ነበራቸው።
"Brave Commander" የተባለው ይህ መርከብ ከ23,000 ሜትሪክ ቶን በላይ እህል የጫነ ሲሆን ከጥቂት ቀናት በኋላ ጅቡቲ ወደብ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
*** የእህሉ መምጣት በርሀብ ለሚሰቃዩት ዜጎቻችንን እጅግ ትልቅ ነገር ነው። ነገር ግን በህዳሴ ግድብ ያየነው ተስፋ እውን ሆኖ የውጭ እርዳታ ሳንጠብቅ ራሳችንን የምንችልበት ወቅት እንዲያመጣልን መስራትም፣ መፀለይም ይገባል።
Photo: File