14/04/2024
...............................ልሸቀትም ….ውርደትም ነው!!..................
ይገርማል በጣም!!
እኔ እምለው ለምንድ ነው አንዳንድ ሰዎች መንቀፍን እና ማቅለልን ለዕውቀታቸው መለኪያ መሳሪያ አድርገው የሚያስቡት?.......
ዌል ....በቅን ሀሳብ እና በተነጠረ ዕውቀት ይህ ልክ አይደለም …እንዲህ ያለው ነገር ላይ ይህ ግብዓት ቢጨመር እንዲያ ያለ ውጥዓት/output/ ሊያመጣ ይችላል የሚል ቀና እና ገንቢ ሀሳብ መስጠት የአባት ነው፡፡ ከዛ በመለስ ግን አውቃለሁም …አለሁም ለማለት የማያስቅፈውን በመንቀፍ እና በማጥላላት የተጠመዱ ሰዎችን ሳይ ግን ግርምምም ይለኛል!!!
አሁን እንደው ማን ይሙት የበዛ ወርቅ እንዲህ ያለ ልብ ስብር የሚያደርግ መዝሙር ማውጣት ያስነቅፋል?….. አጃኢብ እኮ ባካችሁ!!!
ትላንት ዘፈነች …እኛም …በትዝታዎቿም ተክዘን …በአዝናኙም ስራዋ ተዝናንተን ነበር፡፡ዛሬ ደግሞ መጨረሻዬ አሳሰበኝ …ዓለም በቃችኝ …ብላ አምላኳን ደጅ ጠናች….ጠናችናም ….የልቧን ውስጥ ስጋት …ፍርሃቷን ….እኔ ያንተ ባሪያ ባከበርከኝ ልክ …ሳልከብር …የትም ሜዳ ስዋልል …ስዋትት… ከርሜ …ሲመሽብኝ ….በዓለም ድካም ጉልቤቴ ሲዝል …ከእቅታዬ በፊት ለይቅርታ ደጅህ መጣሁ …እናም ይቅር በለኝ ብሎ ማለት …..ምኑ ነው የሚያስኮንነው?…
አንዱ እኮ ነው ከዚሁ መንደር /ብዙ አውቃለሁ፣አነባለሁ/የሚል ሰው ነው ደግሞ ፡፡
የትም ጨፍራ ሲበቃት …ዘፈኑ ሲያልቅባት …በመዝሙር ልትሸቅል መጣች የሚል የልጅም የጅልም ሀሳብ ብጤ ጫጭሮ …መመለሷን ሊመፃደቅበት ሲሞክር አይቼ በግኜ ነው ይህን መፃፌ ፡፡
እውነት ለማውራት በዛር ወርቅ መዝሙሯን የሰራቸው ለራሷም ብቻ አይመስለኝም፡፡ እንደ እኔ ላለን በዓለም ክፋት በብዙ ለምንመላለስ ሰዎች ነው፡፡ መዝሙሯን ሰምቶ የራሱ ሁኔታ የማያሳስበው አማኝ ቢኖር ይህ የተመፃደቀባት ሰው ብቻ ይመስለኛል፡፡ ሰው እንዴት በራሱ ዕውቀት ይመፃደቃል?….እንደምን የመጀመሪያውን ጠጠር አንስቶ ሊወረውር ተጣደፈሳ?
ወዳጄ ሀጥያታችን እንደጠጉራችን እየበቀለብን የሚታይ ቢሆን ኑሮ ከቤትም አትወጣም ነበር፡፡ ይቅር ይበልህ!!!
እንደ ጴጥሮስ ፀፀት እንደ ማርያም መቅደላዊት ያለ የመማር ፍላጎት /ይቅር የመባል/ ሲኖርህ ሸጋ ነው…ያንተ ዕውቀት …የዚህ ዓለም ንባብ እንዲህ ያለውን የልብ መሰበር እንድትረዳ ካላደረገህ ከፎረሽክ ሰንብተሃል ማለት ነው!!! ወርደኃል ወዳጄ …
ይህ ልሸቀትም ውርደትም ነው….ከንቱ ዕውቀት!!!!