መረጃ ከነምንጩ - ምጥን

መረጃ ከነምንጩ  - ምጥን በአሳማኝ ምንጭ ላይ የተመረኮዙ ወቅታዊ ሁነቶችን በአጭር እና
(2)

15/06/2024

ሰበር ዜና
የጄኔራል አሳምንው ፅጌ ልጆች
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ነውረኛው የአቢይ አመድ አገዛዝ ስመ ጥር የሀገርና የህዝብ ሀብት የሆኑትን የኢትዮጵያ አየር መንገድንና የኢትዮጵያ ቴሌ ኮሙኒኬሽን ለስልጣኑ ማስጠበቂያ በመጠቀም ፋኖ ከህዝቡ በሚያገኘው መረጃ እያጠቃን ነው በሚል ሙሉ ለሙሉ የኔትወርክ ማጥፋት ሥራ በመስራት ፋኖን ከመሸገበት አጠፋዋለሁ በማለት ከሚያዚያ መጨረሻ ጀምሮ በመደበኛ ሠራዊቱ ያልቻለውን ውጊያ ከአስራ አራቱ ክልል ያውጣጣውን ሠራዊት ያዘመተ መሆኑ ይታወቃል። ነገርግን በሁለቱ ኮማንዶዎች በዋና አዛዥ አምሳ አለቃ ወንድሙ ማሩ እና በም/ል አዛዥ አምሳ አለቃ ፍቅሩ ሙሉዬ የሚመራው የዐማራ ፋኖ ወሎ ዕዝ ላስታ አውራጃ የጄ/ል አሳምነው ፅጌ ክፍለ ጦር ፋኖዎች ጨለማን ለብሠው ጠላት ከመሸገበት ቦታ ድረስ በመሄድ አርብ ለቅዳሜ ዛሬ ግንቦት 8/2016ዓም ከማለዳ ጀምሮ መቄት ወረዳ ፍላቂትና ገረገራ ከተማ ውስጥ የመሸገውን የጠላት ጦር ሙሉ ለሙሉ በመደምሠሥ ከተማውን የተቆጣጠሩ ሲሆን ከአስታጥቄ ብሬንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችን መታጠቃቸውን ገልፀዋል። ለጠላት ሽፋን ሊሠጥ በውር ድንብር በሁለት ኦራል ተጭኖ ሲከንፍ የነበረ ተጨማሪ የጠላት ጦር በደፈጣ መሀንዲሶቹ ገረገራ ከተማ አቅራቢያ ላይ እምሽክ ሲደረግ የተወሠኑ ብሬን ከእነ ተተኳሻቸው እና ከአምሳ በላይ ጥቁር እና ቀይ አዲስ ክላሽም መገኘቱን የላስታ አውራጃ የጄ/ል አሳምነው ክፍለ ጦር የሜጄር ጄኔራል ውብአንተ አባተ ብርጌድ አዛዥ ኮማንዶ አማን ተናግሯል።

በከተማው ውስጥ የሚገኙ የህዝብ መገልገያ ባንኮች ምንም እንኳን ለጨካኙ ስርዓት መሳሪያ ከሆኑት ባንኮች መካከል ግንባር ቀደሙ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መሆኑ ቢታወቅም መደበኛ የህዝብ አገልግሎታቸውን እንዲቀጥሉ በማሠብ
- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
- የፀደይ ባንክ (አብቁተ)
- ዓባይ ባንክ
- አቢሲኒያ ባንክ
ከውድመትና ከዝርፊያ በፋኖዎቹ ጥበቃ እየተደረገላቸው ይገኛል።

በከፍተኛ የፋኖ አመራሮች የተመራው ልዩ ኦፕሬሽን ጠላት ባላሰበው ስዓትና ጊዜ በመድረስ ድባቅ በመምታቱ በኩል በግዙፉ የላስታ አውራጃ የጄ/ል አሳምነው ፅጌ ክፍለ ጦር ስር ከሚንቀሳቀሱ በርካታ ብርጌዶች መካከል በአምሳ አለቃ ጌታዬ የሚመራው ጄ/ል ተፈራ ማሞ ብርጌድና በኮማንዶ አማን የሚመራው የሜ/ጄ/ል ውብአንተ አባተ ብርጌድ ጣፋጭ ድል ማስገኘታቸውን አምሳ አለቃ ኮማንዶ ወንድሙ ማሩ ገልጿል።

በተመሳሳይ ቀን በተሠጠ ወታደራዊ ግዳጅ እና ተልዕኮ የላስታ አውራጃ የጄ/ል አሳምነው ክፍለ ጦር ኃይሉ ከበደ ብርጌድ በበርካታ ሻለቃዎች ጥምረት ውጊያ እየተደረገ ይገኛል። የማኩሽ ሻለቃ መሪ በፋኖ ዘላለም እየተመራ በሠቆጣ እና በአምደ ወርቅ ከተማ መካከል የምትገኘውን የቀውዝላ ከተማን የተቆጣጠሩ ሲሆን በጠላት ላይ የበላይነቱን በመውሰድ ውጊያው የዋግኽምራ ዞን መቀመጫ ለሠቆጣ ከተማ በ17ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ እንደሆነ የክፍለ ጦሩ የህዝብ ግንኙነት ፋኖ መጎስ ተናግሯል።

አሳምነው አሳምነው ፅጌ‼️‼️
ድል ለፋኖ ድል ለአማራ ህዝብ

15/06/2024

ሰኔ 8/2016 ዓ.ም

የድረሱልኝ ጥሪ ከወለጋ!
የወለጋ አማራዎች እየተጨፈጨፉ ነው።

በዚህ ምሽት ህፃናትን ጨምሮ በርካታ አርሶ አደሮች ተገድለው አስከሬናቸው በየመንገዱ ወድቋል።

በሆሮጉድሩ ወለጋ ዞን አቤ ደንጎሮ ወረዳ መንደር 20 እና መንደር 21 ላይ በርካታ የአማራ ተወላጆች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል።

ግድያውን የፈፀመው መከላከያ ሰራዊት መሆኑንም ህይወታቸውን ለማትረፍ እየሸሹ ያሉ ሰዎች ለአማራ ድምፅ ሚዲያ ገልፀዋል

የአማራ ድምፅ ሚድያ ያነጋገራቸው የአከባቢው ነዋሪ የሆኑ አንዲት እናት "አከባቢው በሞርተር እና በዙ23 እየተደበደበ ነው፣ አስከሬን ማንሳት አልቻልንም። በርካታ ሰዎች በከባድ መሣሪያ ተመተው በቦታው ወድቀው የሲቃው ድምፅ እያሰሙ ነው" ሲሉ ቃል በቃል ተናግረዋል።

ጣቢያችን ያነጋገራቸው ሌላኛው የመንደር 21 አከባቢ ነዋሪ ደግሞ "አቅሙ የፈቀደለት መከላከያ ሰራዊቱ የከፈተውን ጥቃት ለመመከት አንገት ላንገት ተናንቆ እየተዋደቀ ነው።እኔና የመንደሬው ሰው መሳሪያ ያለው መሳሪያውን ይዞ፡ የሌለን ደግሞ ዱላ ይዘን ጥቃቱን ለመከላከል የቻልነውን ሁሉ እያደረግን የዋልን ቢሆንም ነገር ግን ከአቅማችን በላይ ሁኗል" ብለዋል።

ህፃናትን ጨምሮ የቆሰሉ አርሶ አደሮች የሚያነሳቸው የሚያነሳቸው አካል የለም።መከላከያ ሰራዊቱ እግር በእግር እየተከታተለ የቆሰሉትን ሰዎች በእሳት እያቃጠላቸው መሆኑንም ሌላኛው የአይን እማኝ ለአማራ ድምፅ ተናግረዋል።

ዘገባው የአማራ ድምፅ ነው!

7/10/16 ዓ ም 🔥 …‼️ #ከደብረብርሃ ከተማ ወደ መሃል አምባ፣ ናስና ዘንደጉር የገባው የኦነግ ብልፅግና መከላከያ ድባቅ ተመቶ ሙትና ቁስለኛ ተደርጏል:: ባንዳ አድማ ብተናና ሚሊሻን አግ...
14/06/2024

7/10/16 ዓ ም 🔥 …‼️

#ከደብረብርሃ ከተማ ወደ መሃል አምባ፣ ናስና ዘንደጉር የገባው የኦነግ ብልፅግና መከላከያ ድባቅ ተመቶ ሙትና ቁስለኛ ተደርጏል:: ባንዳ አድማ ብተናና ሚሊሻን አግተልትሎ የገባውየኦሮሙማ መንጋ በአማራ ፋኖ ሸዋ እዝ ነጎድጓድ ክፍለጦ አንበሳው ብርጌድ ነብሮ ሻለቃ፣ ፊት አውራሪ ገበየሁና ኃይለማርያም ማሞ ሻለቃ ነበልባሎች ሲረግፍ የቆየ ሲሆን ከሞት የተረፈው አማራዎችን ንብረት በመዝረፍና በማቃጠል ወደ ደብረብርሃን ፈርጥጧል።

በተመሳሳይ #ደብረብርሀን ዙሪያ ቀይት ላይ ዛሬ ጠዋት ጀምሮ እየተደረገ በቆየ ውጊያ የኦነግ ብልፅግና ጎመንና የባንዳው ስብስብ የፋኖ ጥይት ሲሳይ ሲሆን አርፍዷል:: የኦሮሙማው መንጋ በአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ክፍለጦር ደጃዝማች ተሰማ ብርጌድ ሻለቃ 2 አስቻለው ደሴ ሻለቃ እሬሳው ተከምሮ ከሞት የተረፈው ጎመን ንፁሃን ላይ እየተኮሰ ወደ ደብረብርሃን ፈርጥጧል::

💪
💪

12/06/2024

ምጥን መረጃ : ቅምሻ ፦ ሰኔ 5/2016 ዓ.ም

1) በደቡብ ጎንደር በአምስት ግንባሮች ከባድ ውጊያ እየተደረገ ነው።

ጠንካራ የፋኖ ይዞታዎች ከሚባሉት አንዱ በሆነው ደቡብ ጎንደር ዛሬ ማለዳ በአምስት ግንባሮች ውጊያ ተከፍቷል።

የመጀመሪያው ከደብረ ታቦር ከተማ ወደ ማኅደረ ማርያም አቅጣጫ ገና መጫወቻ ግንባር

ሁለተኛው ከጭስ ዓባይ በወንቅሸት አይሰድ ማርያም ታምሬ አቦ ግንባር

ሦስተኛው አንዳቤት አቅጣጫ በቅሎ ፍለጋ ግንባር

አራተኛው ከእስቴ በዓለም ማያ እና ጅብ አሥራ ግንባር

አምስተኛው ከደራ ዓ/ገብያ ልጫ ግንባር ነው

በተለይ በማኅደረ ማርያም በኩል ገና መጫወቻ ግንባር ያለው ውጊያ ገና በማለዳው ከፍተኛ የሆነ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጉዳት ተመዝግቦበታል።

በቦታ ሸፋን ከፍተኛ ቦታ የሸፈነ ነው በተባለው ውጊያ የደረሰውን ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጉዳት እንደደረሰ ይቀርባል !

02/06/2024

ምጥን ፦ ግንቦት 25/2016 ዓ.ም

1) ሸዋ ይፋት
በይፋት ቀጠና የኤፍራታ ግድም ወረዳ አስተዳዳሪ ግንቦት 24/2016 ዓ.ም በመኖሪያ ቤቱ በተከፈተበት ጥቃት ተገድሏል።

2) ጎጃም
ከብቸና ከተማ አቅራቢያ ዛሬ ረፋድ ውጊያ ሲደረግ መመልከታችን የመረጃ ምንጮች ገልፀዋል።

ውጊያው የተደረገባቸው ዛንበራ፣በቆል፣ወብ አላት፣ቆቅ ውሃ እና ተስካረ ማርያም ናቸው የሚሉት የዓይን እማኞች መንግሥት ኃይሎች በአካባቢው ከሚንቀሳቀሱት የደጀን ዛንበራ የፋኖ ብርጌድ እነማይ በላይ ዘለቀ የፋኖ ብርጌድ እና ዲቢሳ ሻለቃ ጋር ነው ብለዋል። በውጊያው የደረሰውን ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጉዳት በዝርዝር አልታወቀም።

3) የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ የኢትዮጵያ መንግስት ከግሎባል ፈንድ የሚያገኘውን እርዳታና ድጋፍ ዱባይ ውስጥ የዶላር ሒሳብ ቁጥር በመክፈት ለከባድ ምዝበራ አጋልጠዋል ተባለ።

ሚኒስትር ድኤታው የድርጅቱን አመራሮች እጅ በመጠምዘዝ ዱባይ ልዩ የጥቅም ሰንሰለት በመዘርጋት ነው የማጭበርበር ሥራ አየሰሩ ያሉት።

በግሎባል ፈንድ ለተላላፊ በሽታዎች ቁጥጥር የሚያገለግሉ የግብዓት አቅርቦቶችን ግዥ ከሚፈፅመው የኢትዮጵያ የፋርማሲዩቲካል ግብዓቶች አገልግሎት (EPSS) ድርጅት ሰራተኞችና ኃላፊዎች ጋር ትስሰር በመፍጠር በውጭ ሀገር ከሚፈፀሙ ግዥዎች ላይ ዘረፋ እየፈፀሙ እንደሆነ ተጨባጭ መረጃዎች ተገኝተዋል።

በተጨማሪም ሰውዬው ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ለተለያዩ የመ/ቤቱ እና የኤጀንሲ ኃላፊዎች በሚል ከመንግሥት የተቀበለውን ኮንዶሚኒየም መኖሪያ ቤቶች ለሚመለከታቸው አካላት ሳይደርስ በአቋራጭ ለእናት አባቱ ለቅርብ ዘመዶቹ አከፋፍሏል።

31/05/2024

ዜና ቅምሻ ፦ በሸዋ ቀጠና/ግንቦት 23/2016 ዓ.ም/

1)ባልጭ

ከሌሊቱ 10- ንጋት 2:30 ድረስ በባልጭ ከተማ ውጊያ ተደርጓል። በዚህ ውጊያ ከፍተኛ ሰብዓዊ ጉዳት ተስተናግዷል።

እስከ ረፋድ 3:00 የፋኖ ኃይሎች ባልጭ ከተማን ይዘው እንደነበር የሚገልፁት ምንጮች በማለዳ ውጊያ ከፍተኛ ጉዳት ያስተናገደው መከላከያ እንደገና ኃይል አሰባስቦ ወደ ከተማዋ መመለሱን ጠቁመዋል። የፋኖ ኃይሎች ቀደም ብለው ከከተማ ወጥተዋል።

2) በረኸት

የረኸት ወረዳ ዋና ከተማ መተህ ብላ ከተማ ከባድ ውጊያ እየተደረገባቸው ካሉ አካባቢዎች አንዷ ነች ያሉት የመረጃ ምንጮች በሌሊት የፍኖ ኃይሎች ከተማዋን በአራት አቅጣጫ ከበባ አድርገው አደሩ።

ማለዳ ወደ ከተማው በመግባት በፖሊስ ጣቢያ እና በመንግሥት ኃይሎች ካምፕ ላይ ጥቃት ሰነዘሩ። ይህንን ተከትሎ በከተማዋ ውስጥ ከባድ ውጊያ ተቀሰቀሰ። የመንግሥት ኃይሎች በተከታታይ የቡድን መሣሪያዎችን እየተኮሱ ነው።

ውጊያው በከተማ ውሰጥ የተደረገ በመሆኑ በሲቪሎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሳይደርስ አይቀርም የሚሉት ምንጭ በተፋላሚ ኃይሎችም ሆነ በንፁሃን ላይ የደረሰው ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጉዳት አልታወቀም። ውጊያ እስከ እኩለ ቀን ቀጥሎ እንደዋለ የዓይን እማኞች ገልፀዋል።

3)ደ/ሲና

ደ/ሲና በደብረሲና ከተማ ከማለዳ ጀምሮ ለአራት ሰዓታት የዘለቀ ከባድ ውጊያ ተደርጓል። በመከላከያ ካምፕ አካባቢ የተቀሰቀሰውን ውጊያ ተከትሎ የስልክና የትራንስፖርት አገልግሎት ለግማሽ ቀን ተቋርጦ ነበር ተብሏል። እስከ ረፋድ ድረስ ወደ ከተማው የፋኖ ኃይሎች ዘልቀው ገብተው ነበር ተብሏል።

እንደገና መከላከያ ከካምፕ የተበተነውን ኃይሉን አሰባስቦ ከሸዋሮቢት እንዲሁም ከሰላ ድንጋይ ተጨማሪ ኃይል ይዞ 5:30 ወደ ከተማዋ መግባቱን ገልፀዋል።

ከዚያ ቀደም ብሎ የፋኖ ኃይሎች ከከተማ መውጣታቸውን ተመልክተናል ሲሉ ያከሉት የዓይን እማኞች በተለይ በመንግሥት የኃይሎች ላይ በማለዳው ጥቃት ጉዳት ሳይደርስ አይቀርም ብለዋል።

4) ደብረ ብርሃን

ከደብረ ብርሃን አቅራቢያ በዋናው መንገድ ላይ ቀይት በተባለች ቦታ ግንቦት22/2016 በተፈጸመ የደፈጣ ጥቃት ጉዳት በወታደራዊ ተሽከርካሪ ላይ ጉዳት ደርሷል።

ሰበር ዜና !ነበልባሉን የአማራ ፋኖ ከበባ አድርጎ ጥቃት ለመፈፀም ያቀደው የአብይ አህመድ ወታደር እንደእባብ ተቀጥቅጦ ተመልሰ።   ግንቦት 22/2016 ዓ.ም      የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝከደ...
30/05/2024

ሰበር ዜና !

ነበልባሉን የአማራ ፋኖ ከበባ አድርጎ ጥቃት ለመፈፀም ያቀደው የአብይ አህመድ ወታደር እንደእባብ ተቀጥቅጦ ተመልሰ።

ግንቦት 22/2016 ዓ.ም
የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ

ከደብረብርሀን 13 ኪ.ሜ ርቀት ላይበእምዬ ምኒልክ ቀዬ በአንኮበር መስመር ልዩ ቦታው ዲቡት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኙ የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ጀግኖች ላይ የህልም እንጀራ ለመብላት ከአንኮበር እና ከደብረብርሀን ከተማ ተሰባስቦ ያለውን ሁሉ ሜካናይዝድ የጦር መሳሪያ በመያዝ ጥቃት ለመፈፀም እሳቱን የሸዋ ምድር የረገጠው የብርሀኑ ጁላ ፀረ አማራ ፍዝ መንጋ ቡድን በጀግናው የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ በ ኢንጅነር ፋኖ ደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ የተመራው በተለያዩ የብርጌድ ሻለቆች በደረሰበት መብረቃዊ የመልሶ ማጥቃት ምት አስከሬኑን ሳይሰበስብ እግሬን በሰበረኝ እያለ ወደ መጣበት ፈርጥጧል።
ግንቦት 21/2016 ዓ.ም ከሌሊቱ 9:00 ጀምሮ ጥቃት እንዲፈፀምበት በሸዋ ባንዳዎች ሴራ የተሸረበት የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ለልዩ ኦፕሬሽን የተዘጋጁ የተለያየ የብርጌድ ሻለቆች በየአቅጣጫው ዲሽቃና ዙ-23 ተሸክሞ በሁለት አቅጣጫ የመጣውን የአብይ አህመድ አሽከር ባደረጉት አስደማሚ እና ተወርዋሪ የማጥቃት ኦፕሬሽን ፀረ አማራው የአገዛዙ ወንበር ጠባቂ የጠላት ሀይል ጥቁር አስፓልቱን ተከትሎ ወደ ደብረብርሃን ከተማ ፈርጥጦ የተመለሰ ሲሆን ሀቅን ከህዝባቸው፣ ጀግንነትን ከአባታቸው የወረሱት የአማራ ፋኖ የሸዋ አናብስቶችም ታላቅ ጀብዱ በመጎናፀፍ የጠላትን ሀይል እግር በእግር እየተከተሉ ወደ ደብረብርሃን እየገሰገሱ ይገኛሉ።

ድል ለአማራ ፋኖ
የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት ክፍል

15/05/2024

የማይደራደረውና የተደራዳሪው ፋኖ አመራር ጎራ ነገር !!
========================
የመላው አማራ ህዝብን ህልውና ከመጥፋት ታድጎ፤ አፅመርስቱን በማስከበር የአማራ ትውልድ ቀጣይነት የሚወሰንበት የአማራ ህልውና ትግል መዳረሻ ግብ እንዳይዛነፍ ለመጠበቅ፤

ፋኖ ውድ ሂወቱን የሚሰዋበትና ደሙን የሚያፈስበት የአማራ ህልውና ትግል በ11ኛው ሰአት ላይ የአሸናፊነት የድል መንገዱን እንዳይስት ለማድረግ እና

ለተቀደሰ አላማና ግብ የሂወትና የአካል መስዋትነት የሚከፈልበት የአማራ የህልውና ትግል በድል የሚጠናቀቅበትን ጊዜ ለማሳጠር የፋኖ አመራሮች እየተፈተኑ የሚለዩበት 2 አሰላለፎችን (የማይደራደርና ተደራዳሪ አመራሮች ጎራ) በመረዳት አቋም መያዝ ውዴታ ሳይሆን ግዴታ እንደሆነ የህልውና ትግሉ ያስገድዳል።

ከላይ የቀጠለ

#1ኛ. የማይደራደረው የፋኖ አመራር ጎራ

የዚህ ጎራ አመራር አሰላለፍ አራት ኪሎን ከመቆጣጠር በፊት ውይይት፣ ንግግርና ድርድር ማድረግ የህልውና ትግሉን መክዳትና ለመሸጥ መሆኑን ያሰመረ ነው።

ይህ የማይደራደረው አመራር ጎራ አማራ ጠል አደረጃጀቶችን፣ ቡድኖችን፣ ግለሰቦችን (ብአዴንን፣ ወያኔ ትህነግን፣ ኦሮሙማ ብልፅግናን፣ ግንቦት 7/ኢዜማን፣ Fake Ethiopawent aramajoche..የሻብዕያ agents የወንጀል ተባባሪዎቻቸውንና የጥቅም ሸሪኮቻቸውን ወዘተ) የሚደራደራቸው ሳይሆኑ በፈፀሙትና ባስፈፀሙት ዘር ማጥፋት፣ አገር ማፍረስ፣ ዘረፋና ሰባዊ መብት ጥሰት ወንጀል ልክ ለፍርድ የሚያቀርብ ነው።

ይሄ በቆራጥነትና በጀግንነት ለአማራ ጠሎችና ለባንዳዎች የእግር እሳት የሆነው አመራር አሰላለፍ መላው አማራ ፋኖ፣ መላው የአማራ ህዝብ፣ ሰላምና ደህንነቱ አደጋ የተደቀነበትና ሰላምና ደህንነት ናፋቂ የሆነው ኢትዮጵያዊ በሙሉ በነፃ አውጪነት የሚደግፉት ሲሆን አብዛኛው የአፍሪካና የምስራቁ አለም አገራት ደግሞ የሚከተለውን መርህና አቋሙን የሚገዙለት ጎራ ነው።

#2ኛው. ተደራዳሪው የፋኖ አመራር ጎራ

የዚህ አመራር ጎራ በግልፅ አማርኛ ሲገለፅ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለውጭም ለውስጥም በቅጥረኝነት የሚሰራ የባንዳ ስብስብ ጎራ ነው

ተደራዳሪውን የአመራር ጎራ ቀጣሪዎች ዋና ግባቸው በዘር ማጥፋት አረመኔ ተግባር ህልውናው እየጠፋ የሚገኘው አማራ በማንነቱ ተደራጅቶ በአማራ ብሄርተኝነት ንቅናቄ የተወለደውን የህልውና ትግል በመጥለፍ የፋኖን ግብ አሰናክሎ በመጣል የአማራ ጠል አደረጃጀቶች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከመክሰም እራሳቸውን ለማዳንና የአሜሪካንና የምራባውያን ጥቅምና ፍላጎትን ማስከበር ነው።

ይህ ተደራዳሪ አመራር የፋኖ ጎራ ሁለት አይነት አካሄድ ሲኖረው #አንደኛው ከፋኖ ድል አድራጊነት በፊት የሽግግር መንግስት በመመስረት የፋኖን ትግልና ድል ለመንጠቅ የተቀጠረ ሲሆን #ሀለተኛው ደግሞ ፋኖ ከክልሉ እንዳይወጣ በመገደብ ከተሳካለት ከብአዴን ጋር ተደራድሮ ካልቻለ ብአዴንን ተክቶ ከወያኔ ትህነግና ከኦሮሙማ ብልፅግና ጋር በመደራደር የአማራን የህልውና ትግል ለመሸጥ የተቀጠረ የባንዳ ስብስብ ነው።

የዚህ ተደራዳሪ አመራር ጎራ በልሳንነት የሚያገለግሉት የህግ ባለሞያዎች፣ ጋዜጠኞች፣ አክቲቪስቶች ወዘተ የብአዴን ቅጥረኛ የነበሩ መሆናቸው የስብስቡን ማንነት አስረጂ ሆኖ ተገኝቷል።

ይህ ተደራዳሪ አመራር ጎራ አንደኛው ወገን በፀረ አማራዎቹ ስብስብ በግንቦት 7 ሰዎች/ኢዜማ ወዘተ ሌላኛው ወገን በደም ነጋዴዋ ሰላያ በነመአዛ መሀመድ፣ በፀረ አማራው በነጌታቸው በየነና ቡድናቸው በኩሉ ከአሜሪካና ምራባውያን ጋር ዝምድና የፈጠረ ነው።
👉አካፋን አካፋ ዶማን ዶማ አለማለት ባንዳነት ነው።
@የየአማራ ተማሪዎች ማህበር / Amhara Students Associationተ/ማየአማራ ተማሪዎች ማህበር / Amhara Students Associationየአማራ ተማሪዎች ማህበር / Amhara Students Associationየአማራ ተማሪዎች ማህበር / Amhara Students Association

02/05/2024

ሚያዝያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም
በዐምሓራ ሳይንት(የጥንቱ ቤተ ዐምሓራ) የምትገኘውን ጥንታዊቷ የተድባበ ማርያም ገዳም ውድመት ሊደርስባት ነው።

የመንግሥት ወታደሮች የጦርነት ሕግ በመተላለፍ ደብረ ኤሊያስ ገዳም የፈፀሙትን ገዳም የመዝረፍ የማውደም እና መነኩሳትን መግደል ተግባር ሊፈፅሙ ወደ ገዳሙ በከባድ መሣሪያዎች በመታገዝ ከበባ አድርገዋል የሚል መረጃ ከአካባቢው ነዋሪዎች የመጣ ነው።

ድምፅ ሁኑን ይላሉ የገዳሙ አባቶች!

02/05/2024

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ ዛሬ ሚያዚያ 24/2016 ዓ.ም ከመኖሪያ ቤታቸው በጸጥታ አካላት መወሰዳቸው ታውቋል።

የሁለቱ አገልጋዮች መኖሪያ ቤት መፈተሹም ተገልጿል።

በአሁኑ ሰዓት ሜክሲኮ ፌዴራል ፓሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ የሚገኙ ሲሆን የተያዙበት ምክንያት አልታወቀም።

ዝርዝር እንደደረሰን እናቀርባለን።

28/04/2024
27/04/2024

የግንባር መረጃዎች
**///**
1) በምስራቅ ጎጃም ስናን ወረዳ ረቡዕ ከተማ ሰፍሮ የሰነበተው የብርሃኑ ጁላ ሰራዊት በቅኝ ጌታ ዮፍታሄ ክፍለጦር ስናን አባጅሜ ብርጌድ ሲወቃ ውሏል፡፡

2) የአማራ ፋኖ በጎጃም የአገው ምድር ክፍለጦር በእንጅባራ ከተማ ጥቃት ከፍቶ ሲያርበደብደው እምሽተዋል፡፡ በተመሳሳይ በሳትማ ዳንጊያና በፋግታ ወረዳ አዋሳኞች ከፍተኛ ውጊያ ሲያደረግ ውሏል፡፡

3) የቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ክፍለ ጦር አባል የሆነው የደንበጫው ኢንጂነር ክበር ተመስገን ብርጌድ በአንጀኒ ከተማ በብርሃኑ ጁላ ጦር ላይ በወሰደው እርምጃ ከ80 በላይ ሙትና ቁስለኛ ተደርጓል፡፡

4) በምዕራብ ጎጃም ከደምበጫ ከተማ የሚመጣለትን ሬሽን ለመቀበል ከደጋዳሞት ፈረስቤት ከተማየተንቀሳቀሰው የጠላት ሀይል ቅቤ ገደል አካባቢ ሲደርስ በዳሞት ፋኖ ተቀትቅጦ ማሟሙቷል፡፡ ሁለት FSR መኪና ሎጅስቲክስ ከነ ወታደሮቹ ተደምስሷል፡፡

5) በሸዋ አንኮበር ወረዳ ከአልዩ አምባ ከተማ በቅርብ እርቀት ጎርጎ ወደ ዞማ ከተማ ለመንቀሳቀስ የሞከረው የፋሽስት ስርዓት ዙፋን አስጠባቂ ሀይል በጀግኖች ተገርፎ ሙት እና ቁስለኛ ሆኗል።

6) በደቡብ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ ኮሬብ ከተማ ታሪክ ተሰርቷል፡፡ በአካባቢው የሚንቀሳቀሰው ፋኖ የበሽሎ ሻለቃ ጦር በብርሃኑ ጁላ ሰራዊት ላይ በወሰደው ማጥቃት 38 ሲደመሠሥ ከ25 በላይ ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነዋል፡፡ በዚህ ውጊያ ከወገን በኩል አራት ጀግኖቻችን በክብር ተሰውተዋል፡፡

ወያኔ፣ 29 ሺህ አምሓሮች ከራያ አፈናቀለች‼️ኦቻየተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርት 29 ሺህ አማራወች ከራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መፈናቀላቸውን አስታውቋ...
20/04/2024

ወያኔ፣ 29 ሺህ አምሓሮች ከራያ አፈናቀለች‼️
ኦቻ
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርት 29 ሺህ አማራወች ከራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መፈናቀላቸውን አስታውቋል፡፡
የህወሓት ታጣቂዎች ለከርሶሌና ለዋጃ አማካኝ ቦታ በሆኑት ሀሞገደል፣ጎቱና ታፌ በሚባሉ አካባቢዎች ከሀሙስ ጀምሮ በብዛት ሰፍረዋል ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በርተኽላይ አካባቢ እንዲሁም ባንዲራ በሚባል ቦታ ጊዚያዊ የጦር መሳሪያ መጠገኛ ሰርተው መሳሪያ ጥገና ጀምረዋል ሲሉ የመረጃ ምንጮቼ ገልፀዋል። የሰሞኑን የህወሃት ታጣቂዎች እንቅስቃሴን መሰረት በማደረግ በፋሽስቱ ኦህዴድ ብልፅግና የሚመራው የአማራ ክልል ተላላኪ ሹምባሽ የአድማብተና አባላት በብዛት ወደ አካባቢው እንዲንቀሳቀሱ ተደርጓል።

ባለፈው ሳምንት የህወሓት ታጣቂዎች በአላማጣ ወረዳ እና በኦፍላ ወረዳዎች በፈጠሩት ትንኮሳና ግድያ ምክንያት ከ29,000 በላይ አምሓራዎች በግፍ ተፈናቅለዋል።

#ድል፣ ለመላው አምሓራ ፋኖ🙏
media moresh

20/04/2024

ቀን 11/08/2016
ሰበር ዜና
ከአማራ ፋኖ ሽዋ እዝ
በመርሀቤቴ ወረዳ በባንዳነት ተሰማርቶ ህዝብን ሲያምስ የነበረው ባንዳ የሚኒሻ አባል እና የአገዛዙ መርጃ እና ዋና መንገድ መሪው ጌታው የሚባል ግለሰብ በፋኖ የመረጃ ደህንነት ክትትል ሲደረግበት ቆይቶ በአይበገሬው የህዝብ ልጅ የሆነው ናደው ክፍለ ጦር ከለሚ እንሳሮ ከሚንቀሳቀሰው ልጅ ስዩም ሻለቃ ጋር መረጃ በመለዋወጥ ባንዳውን ለመጨረሻ ጊዜ ተሰናብቷል። ይህ ባንዳን የመግርፍ ስራ በጥብቅ የሚቀጥል ሲሆን ማንኛውም ለአገዛዙ የሚላላክ አካል ላይ ጥብቅ እርምጃ መውሰዳችን ይቀጥላል።
በሻምበል እወይ የሚመራው በልጂ ስዩም ሻለቃ ስር የምትገኜው 3ኛ ሻምበል በእንሳሮ በሬሳ በተባለ ቦታ በተደረገ ውጊያ በርካታ የአገዛዙ ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ ሲሆን ከሶስት አንቡላንስ በላይ ቁስለኛ አንስቷል።ከ 5 በላይ ክላሽ እንዲሁም በርካታ ተተኳሽ መማረክ ተችሎል ።

በሌላ ዜና የብልፅግና አገዛዝ በክልሉ ያሰማራቸው ደህንነት ውስጥ በመርሃቤቴ ከተሰማሩት ውስጥ ሁለት ሴቶች በአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ናደው ክፍለጦር እጅ ከፈንጅ የተያዙ ሲሆን ከተያዙት አንዲቷ ሴት ከትግራይ ክልል የመጣች ስትሆን ሌላኝዋ ሴት የአገዛዙ ልዩ ኦፕሬሽን መረጃ ናት ።ሁለቱም አይተዋወቁም በተለያየ ቦታ ነው የተያዙት ።ከተሰጣቸው ተልእኮ ውስጥ አንዱ የፋኖን አመራር መያዝ ስላልቻልን በፍቅር መቅርብ እና ለአገዛዙን ለማሲያዝ ማመቻቸት ሲሆን ሌሎች የተሰጣቸው ሙሉ ተልእኮ መርጃውን ለፋኖ መርጃ ክፍል አስረድተዋል ።የተለያዩ እፆችንም እንደሚያስጠቅማቸው ተናግርዋል ።

በዚህም የአገዛዙን መስመር የወደቀ መሆኑን ገምገመንበታል ።መላው የአማራ ፋኖ በሁሉም ከተሞች የተሰማሩ ሰለሆነ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲታደረጉ እናሳስባለን አስፈላጊውን መረጃ በውስጥ መስመር ለሁሉም የፋኖ አደረጃጀቶች እናደረሳለን።

አማራ በክንዱ ነፃነቱን ያረጋግጣል !!
>

ድል ለአማራ ፋኖ!
ድል ለአማራ ህዝብ!

18/04/2024

ሚያዚያ 9/2016
ብዙ የድል ዜና ከአማራ ፋኖ በሸዋ ...
የአማራ ፋኖ በሽዋ ከሰም ክፍለጦር ተስፋ ብርጌድ ዛሬ ታላቅ ድል ተቀዳጀ።

በበረኸት ወረዳ የሚንቀሳቀሰው እና በ ፶/አለቃ ጎሽመው ኃይሌ የሚመራው ተስፋ ብርጌድ ዛሬ ከጠዋቱ 1:00 ሰዓት እስከ ቀኑ 9:00 ሰዓት ድረስ ለተከታታይ 8 ሰዓት እራሱን ጥምር ጦር ብሎ ከሚጠራው የአገዛዙ ጠባቂ ሰራዊት ጋር ከፍተኛ ትንቅንቅ በማድረግ እንዲሁም የአገዛዙን ሰራዊት በመደምሰስ ከፍተኛ ሙት እና ቁስለኛ ያደረገ ሲሆን በርካታ ቁጥር ያለው ግትልትል የኦህዴድ ሰራዊትም ተማርኳል ።

በዕለቱ ጦርነት በተደረገባቸው 09 ቀበሌ፣ 02 ቀበሌ፣ ዋንሴ፣ ፍርዱ ሃገር፣ደመወዜ፣ አቤቶ እና መሃል በረኸት ላይ ወራሪው ሃይል ተደምስሶ 3000 (ሶስት ሽህ) የክላሽ ጥይት፣50 የጀርባ ቦርሳ እና በርካታ ክላሽ ኮፍ መሳሪያዎችን ተኩሰው የማይስቱት ብቻ ሳይሆን ጭንቅላት የሚመቱት የበረኸቶቹ የበረሃ ነብሮች በምርኮ ገቢ ያደረጓቸው የጠላት ሃብትም ወደ ተስፋ ብርጌድ ገቢ ተደርጓል።

በምንጃር አረርቲ ከተማ የስርዓቱ ጠባቂ ጥምር ሃይል በካምፕነት በሚጠቀምበት የምንጃር ሸንኮራ የወረዳው ፖሊስ ጣቢያ ላይ አዳሩን የነበልባል ብርጌድ እርምጃ ወስዷል።

ትናት ከለሊቱ 6:00 ሰዓት ላይ የምንጃር ሸንኮራ ክንደ ብርቱዎቹ የነበልባል ብርጌድ ፉኖዎች በከተማዋ ሰርጎ በመግባት በወራሪው የሃገር መከላከያ ፣ የአማራ አድማ ብተና እና የአማራ ሚሊሻ ላይ እርምጃ በመውሰድ እራሱን ጥምር ጦር ብሎ በሚጠራው ሃይል ላይ ድንገተኛ ጥቃት በማድረስ በርካቶችን ገድለው እና አቁስለው እቅዳቸውን ሙሉ አሳክተው በፋኖ ላይ ምንም ጉዳት ሳይደርስ ከአረርቲ ከተማ ለቀው ወተዋል።

በተያዘ ዜና በከሰም ክፍለ ጦር በነበልባል ብርጌድ በሸንኮራ ንኡስ ወረዳ በባልጪ ከተማ የአገዛዙ ሃይል በካምፕነት በሚጠቀምበት ፖሊስ ጣቢያ ላይ ከለሊቱ 6:00 ሰዓት ላይ ፋኖዎቹ ሰርገው በመግባት እራሱን ጥምር ጦር ብሎ በሚጠራው ሃይል ላይ እርምጃ በመውሰድ በርካቶችን በመግደል እና በማቁሰል የነበልባል ብርጌድ ባቀደው መሰረት ኦፕሬሽኑን ሰርቶ ምንም ጉዳት ሳያስተናግድ የባልጪ ከተማን 9:00ሰዓት ላይ ለቆ ወቷል።

አዳሩን ከፍተኛ ጉዳት ያስተናገደው ወራሪ ሃይል በደረሰበት ጉዳት በእጅጉ በመናደዱ የበቀል በትሩን ዛሬ ቀኑን ሙሉ በምንጃር አረርቲ ከተማ የሚኖሩ ንፁሃን አማራዎችን፣ የባጃጅ አሽከርካሪዎችን እና የከተማዋን ነዋሪ ሲደበድብ እና ሲያስር ውሏል።

ይህ የሚያሳየው የስርዓቱን ተስፋ መቁረጥ እና የውድቀት ዋዜማ ላይ መሆኑን ነው።

የአማራ ፋኖ የከሰም ክፍለ ጦር የሃይለማርያም ማሞ ብርጌድ በሃገረ ማርያም ከሰም ወረዳ በሾላ ገበያ ከተማ ክንደ ነበልባሎቹ የአርበኛው የሃይለማርያም ማሞ የመንፈስ ልጆች ከለሊቱ 9:00 ሰዓት ወደ ከተማዋ በመግባት በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ጥቃት አደርሰዋል።

ፋኖዎቹ ጥምር ጦሩ በሰፈረበት ቦታ በመጠጋት በተለምዶ ካንቦ ማርያም በሚባል አካባቢ እና አስተዳደር ግቢ በመግባት ጥቃት በማድረስ የስርዓቱን አስጠባቂ ሃይል ሙት እና ቁስለኛ አድርገው ተልእኳቸውን አሳክተው ያለምንም ጉዳት ስራቸውን ሰርተው ከተማዋን ለቀው ወተዋል።

የከሰም ክፍለጦር በስሩ ካሉት አራት ብርጌዶች ውስጥ ሶስቱን አናቦ ስራ በመስራቱ የተሻለ ውጤት እንዲገኝ አድርጓል። አማራ ሲናበብ እና ሲተባበር ጠላቱን ያሸንፋል።

ድል ለአማራ ፋኖ !!
ድል ለአማራ ህዝብ!!

የድል ዜና፦ በአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ በአፄ ይኩኑ አምላክ ክፍለ ጦር በፕ/ር አስራት ወልደጌስ ብርጌድ በተደረገ ውጊያ ከፍተኛ ድል ተመዘገበ።   ሚያዚያ 7/2016 ዓ·ም የስርዓቱን አስጠባቂ ሰ...
15/04/2024

የድል ዜና፦
በአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ በአፄ ይኩኑ አምላክ ክፍለ ጦር በፕ/ር አስራት ወልደጌስ ብርጌድ በተደረገ ውጊያ ከፍተኛ ድል ተመዘገበ።

ሚያዚያ 7/2016 ዓ·ም የስርዓቱን አስጠባቂ ሰራዊት በሸዋ ምድር በይፋት ልዩ ቦታው አርብ ገበያ በተባለ አካባቢ እራሱን ጥምር ጦር ብሎ የሚጠራውን ወራሪ ሃይል በማጀቴ አናብስት ፋኖዎች አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቶ ከፍተኛ ኪሳራ አስተናግዶ ወደ መጣበት ተመልሷል።

የወራሪው ሃይል የማጀቴን ከተማ ለመያዝ ሃይሉን ከአጣዬ፣ ከመንዝ እና ከኬሚሴ አውጣጥቶ እና አደራጅቶ ከትላንት ቀን 10 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12 ሰዓት እንዲሁም ዛሬ ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ቀኑ 6 ሰዓት ድረስ ከፍተኛ ትንቅንቅ ቢያደርግም ጠላት ያሰበው ሳይሳካ ቀርቶ ከፍተኛ ሽንፈት አስተናግዷል።

በአርበኛ እና ደራሲ አሰግድ መኮንን የሚመራው የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ የአፄ ይኩኖ አምላክ ክፍለጦር የፕሮፌሰር አስራት ብርጌድ ሶስት ሻለቃዎችን ማለትም አይሻ ሰይድ ሻለቃ ፣ ደጅአዝማች መሸሻ ሻለቃ እና ደጃዝማች ዳምጠው ሻለቃን በማሰለፍ የማጀቴ ከተማን ለመውረር የመጣውን እራሱን በሃገር መከላከያ፣ በአማራ ሚሊሻ እና በአማራ አድማ ብተና አደራጅቶ ከባባድ መሰሰሪየዎችን ታጥቆ ማጀቴን ለመያዝ ዙሪያውን ከበባ ለማድረግ ያሰበውን እና በከፍተኛ አሰላለፍ በአርብ ገበያ በኩል ወደ ማጀቴ ሰብሮ ለመግባት የሞከረውን ወንበር ጠባቂ ሃይልን ከፍተኛ ትንቅንቅ በማድረግ ክንደ ነበልባሎቹ የጀነራል አሳምነው መንፈስ ወራሾቹ የማጀቴ ፋኖዎች አይቀጡ ቅጣት ቀጥተው ብትንትኑን አውጥተው ወራሪው ሃይል ወደ ኋላው ሙት እና ቁስለኛውን በተገቢው ሳያነሳ እንዲሸሽ በማድረግ ድል ተቀዳጅተዋል።

ድል ለአማራ ፋኖ
ድል ለአማራ ህዝብ

14/04/2024

የጥንቃቄ መረጃ !
ለአዲስአበባ

በአዲስአበባ ውስጥ ከ3000 በላይ የአሸባሪው ድህንነት መዋቅር አሉት። አብዛኞቹ የአማራ ተወላጅ ናቸው። ተልዕኮውን የሚወጡት ደግሞ መጠጥ ቤት እና ወጣት በሚሰበሰብባቸው ቦታዎች ሲሆን የፋኖን ትግል የሚደግፉ በመምሰል አቦ ፋኖ በመጣ እና ይህንን መንግሥት ባስወገደልን የሚል ጭዌ በማስነሳት እና መሰል ወሬዎችን በማናፈስ መሆኑን ደርሰንበታል።

መውጫ:- ጀግናው የአማራ ፋኖ ሰምኑን የሰራው ጀብድ ካሳለፍንው ሳምት በእጥፍ የበለጠበት ሁኔታ አለ ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል።

ደም በደም ብቻ ይጠራል‼️
🦅

13/04/2024

መረጃ
የሞት ሽረት የተባለው የመጨረሻውን ትንቅንቅ እስከ ሰኔ 30/2016 ዓ.ም ሊደረግ መሆኑ ተሰማ‼️

12/04/2024

03/08/16 ዓ.ም
አጫጭር መረጃዎች!

◦ በቤተ አማራ ወሎ #ገነቴ ከተማ ካምፕ ውስጥ በተደረገ ድንገተኛ ጥቃት በርካታ የኦነግ ብልፅግና ጎመን በቦረና ገነቴ መክት ሻለቃ አናብስት ታጭዷል::

◦ በሸዋ #ጎሸባዶ ከተማ አካባቢ በተደረገ የደፈጣ ጥቃት 4 የአገዛዙ ቀይ ቦኔት (ቀይ ሽንኩርት) በአንበሳው ብርጌድ ፊት አውራሪ ገበየሁ ሻለቃ ነበልባሎች ታጭዷል፣ 6 በከባድ ቆስሏል::

◦ በጎጃም #አዴት ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ ላይ በተደረገ ድንገተኛ ኦፕሬሽን በባንዳ የብአዴን ካድሬዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል፤ በግፍ የታሰሩ ወጣቶች በአሳምነው ፅጌ ብርጌድ 1ኛ እና 3ኛ ክፍለ ጦር አናብስት ነፃ ወጥተዋል::

◦ በጎንደር #ደምቢያ አይንባ ልዩ ቦታው አርሴማ ላይ 37 የኦነግ ብልፅግና ጎመን በአይሸሽም ብርጌድ ነበልባሎች አመድ ተደርጏል።
💪
💪

09/04/2024

ሰበር ዜና 1/08/2016 ዓ.ም
ከአማራ ፋኖ ሽዋ እዝ

በደብረብርሃን ዙሪያ በተለያዩ የጦር ግንባሮች የነበሩ ድሎች

ሀ) የአማራ ፋኖ ሽዋ ዕዝ ነጎድጓድ ክፋለጦር አንበሳው ብረጌድ አስራት ሻለቃ እና ባሩድ ሻለቃ ከፊት አውራሪ ገበየሁ (አባ ጎራው)ክፋለጦር አረበኛ አሊ ሻለቃ በጋራ በመሆን በደብርብርሃን ጠባሴ ክፋለ ከተማ ጎሾባዶ በሚባል ቦታ ከጥዋት 12:00 ጀምሮ እስከ ምሽት ሁለት ስአት ድረስ በተደረገ ዉጊያ አሸባሪው የአገዛዙ ቡድን ሙትና ቁስለኛ ሲሆን ቁስለኛውን በአንቡላንስ እያጋዘ እሬሳውን ጥሎ ፈረጥጦል።

ለ)የአማራ ፋኖ ሽዋ እዝ ነጎድጓድ ክፍለጦር አንበሳው ብርጌድ ነብሮ ሻለቃ በደብርብርሃን ጣይቱ ክፋለ ከተማ ዘንደጉር እና ቀይት በተባለ የተለያዩ ቦታወች የአገዛዙን ጥምር ጦር ተብሎ የሚጠራ ቡድን ብትንትኑን በማውጣት በቆረጣ አናብስቶቹ ጠላትን እንደቅጠል አረግፈውታል።

ሐ) ሚንሊክ ክፈለ ከተማ ወሻውሽኝ በሚባል ቦታ ነጎድጓድ ክፈለጦር ጋተው ብረጌድ የማጥቃት ውጊያ ሲያደረግ የጥምረ ጦሩ ቡድን በድንገት ሲመታ ፈርጥጦ ደብርብርሃን ከተማ ውስጥ ጎብቶል አናብስቶቹም ለከተማቸው ለህዝባቸው ደህንነት ወደ ሃላ በመውጣት በከተማው ጫፋ ይገኛሉ በቀጣይ በከተማ ለሚደረገው የሽምቅ ውጊያ ህዝባችንን ለጥንቃቄ አስገንዝበን የምንደመስሰው ይሆናል።

መ) የአማራ ፋኖ ሽዋ እዝ መብረቁ ብርጌድ አሳምነው ሻለቃ ከቀኑ 11:00 ጀምሮ እስከ ምሽት 2:00 ስአት በሞጃና ወደራ ወረዳ ሰላድንጋይ ከተማ የማጥቃት ውጊያ እያደረገ ሲሆን ውጊያው ይህ ዘገባ እስከተሰራበት ስአት ውጊያው እንደቀጠለ ሲሆን ጠላትን መውጫ መግቢያው እስኪጠፋው እየተገረፈ ነው።

የአገዛዙ ሰራዊት በቡዙ አቅጣጫ ውጊያ ሲከፈትበት መፈርክርኩን እና አቅም የሌለው መሆኑን ያየንበት ሲሆን ጠላት በሁሉም አውደ ውጊያወች ክፉኛ የተመታ ሲሆን በአካባቢው ሚንሻ መሪነት አገዛዙ የፋኖ ቤተሰብ እና የፋኖ የብረጌድ አመራር የመኖሪያ ቤት አቃጥሏል። በሰፈሩት ቁና መሰፈር አይቀረም
አማራ በክንዱ ነፃነቱን ያረጋግጣል !!
> ናትናኤል እክሊሉ
የአማራ ፋኖ ሽዋ እዝ ም/ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሃላፊ

ድል ለአማራ ፋኖ!!
ድል ለአማራ ህዝብ!!

08/04/2024

30/07/16 ዓ.ም

🔥 !

የኦነግ ብልፅግና አሸባሪዎች ደሴ ላይ መስጂድ በቦንብ ሊያፈነዱ ሱሉ ተያዙ...‼️

#የመከላከያ መታወቂያ የያዙ እና ብልፅግና ኦነግ የላካቸዉ #የኦሮሞ ተወላጆች አሁን በዚህ ሰዓት ወሎ ደሴ ፉርቃን መስጊድ ቦንብ ይዘዉ ለማፈንዳት ሊገቡ ሲሉ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል።

የመከላከያ ሚሊተሪ ልብስ አዉልቀዉ ከደሴ ሙስሊም ጋር በሽርጥ ተመሳስለዉ ከከሚሴ አስተዳደር በጀት ተሰጥቷቸዉ የመጡት የኦነግ አባሎች ዐማራ ነን ለዲናችን ለሃቃችን እንሞታለን ባሉ ሙስሊም ወንድም
እህቶቻችን እርብርቦሽ መያዛቸዉ የተሰማ ሲሆን!

ዕቅዱ የከሸፈበት እና ሴራዉ የተነቃበት ብልፅግና ጉዳዮን ላለማራገብ ኦነግ መራሹን መከላከያ በአካባቢው በፍጥነት በመላክ በቁጥጥር ስር የተያዙትን ሰዎች ለለማስመለጥ ጥረት እያደረገ ቢሆንም። እኛ በህይወት እያለን እነዚህን አሸባሪዎች አንለቅም በማለታቸዉ እስከ አሁን ድረስ በአካባቢው ከፍተኛ ዉጥረት ነግሷል!

ድል ለፋኖ!
ድል ለአማራ ህዝብ!

08/04/2024

ሰበር ዜና – ከአማራ ፋኖ ሽዋ እዝ

ቀን 29/07/2016

የአማራ ፋኖ ሽዋ ዕዝ ናደው ክፋለጦር ፈለቀ እጂጋየሁ ብርጌድ ተወርዋሪ ሃይል በመርሃቤቴ ሰባጌ በተባለ ቦታ ላይ በተደረገ ደፈጣ የአገዛዙ ቡድን በሁለት መኪና እና 1 ፓትሮል ያሉው ሙሉ ሲደመሰስ በሌላ መኪና ያለው በከፍተኛ ሁኔታ ሙት እንዲሁም በርካታ ቁስለኛ ሲሆን ከሞት የተረፈውም ተበታትኗል። ጠላት ሲጓጓዝበት የነበረ መኪና በንስሮቹ ተመቷል በርካታ የተለያዩ ትጥቆች እና ተተኳሽ ለመማረክ ተችሎል ።
በሌላ ዜና የአማራ ፋኖ ሽዋ እዝ ነጎድጓድ ክፋለጦር አምበሳው ብርጌድ ነብሮ ሻለቃ ከደብርብርሃን ከተማ 40 ኪ.ሜትር ወጣ ብሎ በቀይት እና በጉዶ በረት መካከል በተደረገ ደፈጣ የአገዛዙ ቡድን በመኪና ወደ ይፋት ቀጠና ሲንቀሳቀስ አንዱ መኪና ላይ ያለው በሚገባው ቋንቋ አናብስቶቹ አስተናግደውታል በዚህም በተመታው መኪና ላይ ያለው ሙሉ በሙሉ ሙት ሆኗል።በዚህ የተናደደው የአገዛዙ ቡድን ወደ ደብር ብርሃን ከተማ ዙሪያ ዙ 23 እየተኮሰ ህዝብ ማሸበሩን ቀጥሎበታል።

አማራ በክንዱ ነፃነቱን ያረጋግጣል !!
>

ድል ለፋኖ!
ድል ለአማራ ህዝብ!

06/04/2024

28/07/16 ዓ.ም🔥 #ደብረማርቆስ…‼️

በዛሬው ዕለት በደብረማርቆስ ከተማ በተደረገ ድንገተኛ ኦፕሬሽን የፋኖ አናብስት #በአራት አቅጣጫ በመግባት መጠነ ሰፊ የመከላከያ ጎመን አጨዳ እና የባንዳ ፅዳት ሲያደርጉ አርፍደዋል:: በርካታ ባንዳ አድማ ብተና ፖሊስ እና ሚሊሻ ተሸኝቷል:: የደብረማርቆስ ሆስፒታል በጠላት ተጥለቅልቋል:: ቆንጆዎቹ ያቀዱትን አድርገው የስትራቴጂክ ቦታቸው ተመልሰዋል::
💪
💪

06/04/2024

የአማራ ፋኖ ሽዋ እዝ ታላቅ ጀብድ

ቀን 28/07/2016

የአማራ ፋኖ ሽዋ ዕዝ ከሰም ክፍለጦር ሃይለማርያም ማሞ ብርጌድ በሽዋ ምድር ምንጃር ቀጠና ታላቅ ጀብዱ ፈፀመ። ሚያዝያ 27/2016 ዓ·ም የአማራ ፋኖ ሽዋ እዝ በምንጃር በበረኸት ወረዳ እና በሃገረ ማርያም ከሰም ወረዳ ከአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ጋር በሁለቱም ቀጠና ወጊያወች የተካሄዱ ሲሆን ።በሃገረ ማርያም ልዩ ስሙ ኮረማሽ በሚባል ቦታ በሃይለማርያም ማሞ ብርጌድ ሻለቃ 3 እና በአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ ጥምር ጦር መካከል ውጊያ ሲደረግ በዚህ ጦርነት የአገዛዙ ሃይል አሸባሪው የአስር አለቃ ብርሃኑ ጁላ ሰራዊት ፣ባንዳ የክልሉ ብልፅግና ሚሊሻ፣ባንዳ የክልሉ ብልፅግና ፖሊስ እና የኦሮሚያን ልዩ ሃይልን ያሰለፈ ሲሆን በከተማዋ በአምስት አቅጣጫ ለዘረፋ እና ህዝብ ለመጨፋጨፍ ቢመጣም ከጠዋቱ 2 ሰዓት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ከፍተኛ ትንቅንቅ ሲደረግ የስርዓት አስጠባቂው ሃይል በክንደ ነበልባሎቹ በሃይለኛው ተመቶ ተመልሷል። በዚሁ ጦርነት ላይ የአገዛዙ ሃይል ከባድ መሳሪያዎችን የተጠቀመ ቢሆንም በዚህም ጦርነት ጠላት እንደተለመደው በበቂ መልኩ ተመቶ ወደ መጣበት የቱለፋ ከተማ እና የሸኖ ከተማ ተመልሶ ፈርጥጦል።
በሌላ ዜና የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ በበረኸት ወረዳ በተስፋ ብርጌድ በሻለቃ 1 በደምረው በሻህ የምትመራው ሻንበል 3 ተወረዋሪ ሃይል በአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ላይ በተደረገ የደፈጣ ውጊያ አንድ ሙሉ ፓትሮል ሰራዊት ልዩ ስሟ ጦዳ በምትባል ቦታ እስከወዲያኛው ተሸኝቷል ።

አማራ በክንዱ ነፃነቱን ያረጋግጣል !!
>

ናትናኤል እክሊሉ
የአማራ ፋኖ ሽዋ እዝ ም/ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሃላፊ

ድል ለፋኖ!
ድል ለአማራ ህዝብ!

05/04/2024

እነኚህ ጂኦፖለቲካዊ ይዘት ያላቸው መረጃዎች ምን ይናገራሉ?

1. ሶማሊያ በሀገሯ የሚገኘው የኢትዮጵያ አምባሳደር በ72 ሰዓት ውስጥ ለቅቆ እንዲወጣ አስጠንቅቃለች። በፑንትላንድ እና ሶማሊላንድ ያሉ የኢትዮጵያ ቆንስላዎችም እንዲዘጉ አዝዛለች።

2. ሶማሊያ የኢትዮጵያ አየርመንገድ በሀገሯ ያሉትን 3 መዳረሻዎች ( ሞቃዲሾ፣ ሀርጌሳ፣ ገረዌ) እንዳይጠቀም ልትከለክል እንደምትችል ዝታለች።

3. በ55ኛ የተመድ የሰብዓዊ መብት ካውንስል መደበኛ ጉባኤ ላይ 44 ሀገራት በኢትዮጵያ አማራና ኦሮሚያ የሚፈፀመው የሰብዓዊ መብት ጥሰት እና በአማራ ላይ የተራዘመው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንደሚያሳስባቸው ገልፀዋል። አሜሪካን ጨምሮ የአውሮፓ ሀገራት ፈርመው ባቀረቡት ሰነድ ላይ ሩሲያና ቻይና ይህንን ጥሪ አልተቀላቀሉም።

4. Human Rights Watch ስለመራዊ ጭፍጨፋ ባወጣው የምርመራ ሪፖርት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የጦር ወንጀል ፈፅሟል ብሏል። በዚህም የተነሳ ኢትዮጵያ የሰላም አስከባሪ ሃይል እንዳታዋጣ ለ ተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና ለአፍሪካ ህብረት ጥሪ አቅርቧል። በተጨማሪም የተመድ ሰብዓዊ መብት ካውንስል በኢትዮጵያ ላይ መርማሪ ቡድን እንዲያቋቁም ጠይቋል።

5. IMF ከአብይ መንግስት ጋር በአዲስ አበባ ሲያደርግ የነበረው ድርድር ያለስምምነት ተጠናቋል። IMF የግብር ማሻሻያ፣ የውጭ ምንዛሬ ማሻሻያ፣ ከበጀት አሰራር ውጭ ያለው የአብይ ፕሮጀክቶች ግልጽነት የጎደለው አሰራር እንዲስተካከል ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡ ተነግሯል።

6. የኢትዮጵያ የውጭ ንግድ ገቢ ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት አንፃር በ 1.79 ቢሊዮን ዶላር ቅናሽ አሳይቷል።

ድል ለፋኖ!
ድል ለአማራ ህዝብ!
-በምስጋናው ዘ-ግዮን

03/04/2024

አንድ አማራ ሰበር ዜናዎች:
ዕለታዊ መረጃዎች

መረጃ-1
የነጓድጓድ ክፍለ ጦር አምበሳዉ ብርጌድ በደብረብርሃን ከተማ በጠላት ላይ እርምጃ መዉሰዱን ገለጸ!

በደብረ ብርሃን ከተማ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ደፈጣ በማድረግ እና ከበባ ዉስጥ በማስገባት ጥቃት በማድረስ በርካታ የወራሪዉ አባላት ሲደመሰሱ ሌሎች በርካቶች ቁስለኛ እና ምርኮኛ መሆናቸዉን የአማራ ፋኖ ሸዋ እዝ የህዝብ ግንኙነት ፋኖ ንጋቱ አረጋግጠዋል

መረጃ -2
በጎንደር ከተማ ማራኪ ክ/ከተማ ትላት ከምሽቱ 3:20 እስከ 5:30 የተሳካ ኦፕሬሽን በጀግኖች ተፈፅሟል።

በዚህ የጠና ኦፕሬሽን ማራኪ ክፈለ ከተማ ሰፍሮ የነበረውን ባንዳ ሚሊሻና አድማ ብተና ሙሉ በሙሉ በጀግኖች ተደምስሷል።

በከተማው ውስጥ ለአገዛዙ የሚያሸረግዱ የጎንደር የቀበሌ ሊቀመንበር ካድሬዎችን ከየቤታቸው በጀግኖች ተለቃቅመው ተወስደዋል።

ጀግኖች ይህንን የተሳካ ኦፕሬሽን ያለምንም መስዋትነት ያጠናቀቁ ሲሆን አሁን ላይ ገዢ ቦታቸውን ይዘው እንደሚገኙ እና ይህ አይነት ኦፕሬሽን ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስገንዝበዋል።
የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ

መረጃ -3
የድል ዜና

በአዊ ዞን በግምጃ ቤት ከተማ በተመረጡ ቦታዎች ላይ ማለትም የግምጃ ቤት ወረዳ አስተዳደር ፅ/ቤት እና የአራዊት ሰራዊቱ፣ የአድማ ብተና፣ የሚሊሽያና ፖሊስ ጥርንፍ ኃይል ካምፕ ባደረገበት ቦታ በፋኖ አዳነ አንዷለም የሚመራው የጓጉሳ ብርጌድ በድንች ናቃ ፈፅመዋቸዋል።

እጅግ በርካታ የወዳደቀ የፋሽስት ኃይል አሁን ድረስ እንዳልተነሳ የታወቀ ሲሆን ኮማንደር ወርቁ የተባለ የወረዳው ፖሊስ አዛዥም የሆስፒታል አልጋ ላይ እንዳለ ለማወቅ ተችሏል።

በግምጃቤት ያለው የፋሽስት ኃይል ሙሉበሙሉ ከምድርበታች መሆኑን ተከትሎ ከኮሶበር/እንጅባራ አዲስ ኃይል የተንቀሳቀሰ ቢሆንም አሁን ዘግየት ብሎ እንደደረሰን መረጃ ከሆነ ይህ አዲስ ኃይልም በተወርዋሪዎቹ መብረቃዊ ምት ትቢያ መሆኑ ተረጋግጧል።

መረጃ -4
የድል ናዳ ዜናው ቀጥሏል!

በደቡብ አቸፈር ሃሙሲት አካባቢ የዱርቤቴና የዳንግላ የፋኖ ጥምር ኃይል በፈፀመው ኦፕሬሽን፣ በርካታ አራዊት ሰራዊት፣ ሚሊሽና ፖሊስ የተጠና ከምድር በታች መሆኑ ተረጋግጧል።

በሚያስገርም ሁኔታ በህይወት የተረፈው አራዊት ሰራዊት የእራሱን አባላት አስክሬን ብቻ ለቅሞ መውጣቱ ታውቋል፤ ይህ አብረውት ለተዋጉትና አብረውት ለወደቁት አድማብተና፣ ፖሊስና ሚሊሽያ ውለታ መሆኑ ነው¡።

በትናንትናው ዕለት እንደዘገብነውም የደቡብ አቸፈር ወረዳ የሚሊሽያ ጽ/ቤት ኃላፊን ጨምሮ 37 የፖሊስና ሚሊሽያ አባላት ከምድር በታች መሆናቸውን እስካሁን የተጠናቀረው መረጃ ያስረዳል። እምሽክ ብሏል። መከላከያ የእራሱን አስከሪየን ብቻ ለቅሞ መውጣቱ አስደንጋጭ ነው።
ድል ለፋኖ!
ድል ለአማራ ህዝብ!!

ሰበር መረጃ ነው…!"…ሰሞኑን በአምባሰል ተራሮች ላይ ከፋኖ ጋር በውጊያ ላይ የከረመው የብራኑ ጁላ ሠራዊት በግሸን ደብረ ከርቤ ላይ የጅምላ ጭፍጨፋ ለማካሄድ መወሰኑ ተሰምቷል። "…ለዚሁም ከ...
03/04/2024

ሰበር መረጃ ነው…!

"…ሰሞኑን በአምባሰል ተራሮች ላይ ከፋኖ ጋር በውጊያ ላይ የከረመው የብራኑ ጁላ ሠራዊት በግሸን ደብረ ከርቤ ላይ የጅምላ ጭፍጨፋ ለማካሄድ መወሰኑ ተሰምቷል።

"…ለዚሁም ከቆጋት ተስቦ ግሸን ድረስ የተዘረጋውን የውኃ ቧንቧ ቆርጦታል። ውኃው ከተቋረጠ ግሸን ላይ ያሉት ነዋሪዎች በሙሉ በውኃ ጥም ይሞታሉ።

"…ሌላው እታች አውቶቡስ ማቆሚያው ጋር ያለውን ወፍጮ ቤት ነቅሎ በአይፋ መኪና ጭኖ መውጣቱም ተነግሯል።

"…ታቦተ ጽዮንን ፍለጋ በአክሱም፣ በትግራይ የተደረገው ጦርነት እንዳለ ሆኖ፣ አሁን ደግሞ የክርስቶስን መስቀል ፍለጋው በአረመኔው የኦሮሙማ ኢሉሚናቲ አገዛዝ ቀጥሏል።

"…ቀጥሎ የሚከሰት ነገር ካለም መረጃው ሲደርሰኝ እነግራችኋለሁ።
@ዘመዳችን

01/04/2024

በአጣዬና አካባቢው የታቀደው አገዛዙ የሚመራው እልቂት‼

ዛሬ በሰንበቴ፣ በከሚሴ እና በልዩ ዞኑ አዋሳኝ ቦታወች ኦነጋዊ ቡድን እንቅስቃሴ እያደረገ እንደሆነ ተጨባጭ መረጃወች ደርሰውናል።

ስለሆነም በአጣዬ፣ በአንጾኪያ ገምዛ፣ በሽዋሮቢትና በቀጠናው ያላችሁ ውድ አምሓራውያን ሆይ ከበፊቱ የበለጠ በተጠንቀቅና በመናበብ ህዝባችን ላይ ለማድረስ የታቀደውን እልቂት ትከላከለለ አስቼኳይ ጥሪ እናስተላልፋለን።

መረጃውን ይዛመት ማህበረሰባችንን እናንቃ‼

01/04/2024

23/07/16 ዓ.ም

#ጮቄ ተራራ አካባቢ አገዛዙ የላካት የጦር ጀትት ተከሰከሰች‼️

ዛሬ ማለዳ ኦነግ ብልፅግና የአማራን ህዝብ ለመጨፍጨፍ የላከው በቢቡኝ እና ስናን ወረዳ አካባቢ በሚገኘው ጮቄ ተራራ #ተከስክሶ አመድ መሆኗን የአሻራ ምንጮች ገልፀዋል።

ድል ለፋኖ!!!
ድል ለአማራ ህዝብ!!!

ሰበር ዜና – ላስታ ላሊበላ #ዘመቻ  #ውባንተሰኞ መጋቢት 23 ቀን 2016 ዓ.ምዛሬ መጋቢት 23/2016 ዓም ጠዋት ላይ የአሸባሪው የአብይ አህመድ ወታደር በእያንዳንዱ ወረዳ የሚገኝ የፋኖ ...
01/04/2024

ሰበር ዜና – ላስታ ላሊበላ

#ዘመቻ #ውባንተ

ሰኞ መጋቢት 23 ቀን 2016 ዓ.ም

ዛሬ መጋቢት 23/2016 ዓም ጠዋት ላይ የአሸባሪው የአብይ አህመድ ወታደር በእያንዳንዱ ወረዳ የሚገኝ የፋኖ ኃይልን መደምሰስ በሚል አዲስ የማጥቃት ተልዕኮ ተቀብሎ ከሠቆጣ እና ከአስከተማ የሚገኘውን ጦሩን በማንቀሳቀስ በላሥታ አውራጃ የጄ/ል አሳምነው ፅጌ ክፍለ ጦር ኃይሉ ከበደ ብርጌድን ለማጥቃት መንቀሳቀሱን የፋኖ የደህንነት ምንጮች አድርሠዋል። ይህ መረጃ የደረሳቸው ትንታጎቹ ዘመቻ ሜጄር ጄኔራል ውብአንተ አባተን በማስቀጠል የታሠበውን የማጥቃት እንቅስቃሴ ወደ ጥሩ አጋጣሚ በመቀየር ነበልባሎቹ በደፈጣ እና በመደበኛ ውጊያ ብትንትኑን በማውጣት በጠላት ተይዛ የነበረችውን የላልኪው ከተማን ነፃ አውጥተዋል። ከቦታው ለንሥር ብሮድካስት በደረሰው መረጃ ከአስታጥቄ የብርሐኑ ጁላ ጦር እንደ ክላሽ ያሉ የነፍስ ወከፍና እንዲሁም የቡድን መሳሪያ ብሬን ማርከው መታጠቃቸውንና ብዛት ያለው ምርኮኛ መያዛቸውን ውጊያውን የመራው የክፍለ ጦሩ ዘመቻ መምሩያ ኃላፊ ፋኖ ታዘበው ገልጿል።

አሁንም ሌሎች ከተሞችን ለመያዝ ውጊያው እደቀጠለ ይገኛል!…

ድል ለፋኖ!!!!
ድል ለአማራ ህዝብ!!!

Address

Main
Debre Birhan

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when መረጃ ከነምንጩ - ምጥን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to መረጃ ከነምንጩ - ምጥን:

Videos

Share

Category