08/12/2018
ለሁለት ጌቶች መስገድ
• • •
ይህ ሁሉ ማስመሰል፣
ይህ ሁሉ ማጎብደድ፣
ይህ ሁሉ ማወደሥ፣
ይህ ሁሉ እግር መላስ፣
ሕሊናን እንደከብት፣
የድልል ጨው ማላስ፤. .. .. .. ..
(መንገሥ)፤
እና
(መርከስ)።. .. .. .. ..
ውስጥን አስጎንብሶ፣ ውጪን ለማቃናት
በግ-ብስብስ ኑሮ፣ በ"ኮልኮሌው" መቅናት
ምኞትን አንቅቶ፣ እምነትን ማስተኛት
በዘልማድ መስገድ፣ ለታይታ ቁስ ጣዖት
የኖሩትን መድገም፣ የሞቱትን መሞት . .
ጧት ሠርክ ቤተ አምልኮ፣ ምን ቢመላለሱ
በፀፀት ቢወድቁ፣ ትቢያ አፈር ቢልሱ
ፈውስ የለውም ቁስሉ፣እርኩስ ነው ድግሡ
ሁለት ጌቶች ማምለክ፣
በስጋም በነፍስም ሁለቴ ነው ክሱ . .
የመምሰልን ጣዖት፣ "ማልደው" ሳያፈርሱ።
• • •
መምሰልን የሚያህል ጣዖት ተሸክመን
መኾንን የሚያህል ታቦት እንይዝ ብለን
ዘውትር ጎንበስ! ጎንበስ! ልባችንን ጎብጠን
"ራስን" ለመቻል፣ ትከሻ እያነሰን!........
[[ሰይፉ ወርቁ.አ]]•••••
Photo ጆኒ ፀጋዬ.............