ኦዳ ጆርናል/Oda Journal

ኦዳ ጆርናል/Oda Journal hello guys welcome to my official page follow for mor

በኦሮሚያ ክልል በአንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ16 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 23 ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል!!👉በተለይም የሞተር አሽከርካሪዎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መልዕክት ...
28/08/2023

በኦሮሚያ ክልል በአንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ16 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 23 ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል!!

👉በተለይም የሞተር አሽከርካሪዎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መልዕክት ተላልፏል!!

በኦሮሚያ ክልል 2015 ዓ.ም በነሀሴ ወር በመካከለኛ ሳምንት ባሉት ቀናቶች በደረሱ 13 የትራፊክ አደጋዎች የ16 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በ21 ሰዎች ላይ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን የኦሮሚያ ክልል የትራፊክ ቁጥጥር ክፍል ባለሙያ የሆኑት ኢንስፔክተር መሰለ አበራ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል፡፡

አደጋዎቹ በምስራቅ ሸዋ፣በሻሸመኔ ከተማና በተለያዩ የኦሮሚያ ክፍሎች የደረሱ ናቸዉ።

የአደጋዎቹ ሁኔታ ካለፈው ሳምንት ጋር ሲነፃፀር በእጅጉ የጨመረ ሲሆን ፤ መንስኤዎቹ ለእግረኛ ቅድሚያ አለመስጠት፣ ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር ፣በቂ እረፍት ሳያደርጉ ማሽከርከር፣ርቀትን ጠብቆ አለማሽርከር እንዲሁም አሽከርካሪዎች እርስ በእርስ በመሽቀዳደም መሆኑን ኢንስፔክተር መሰለ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

በተለይም በምስራቅ ሸዋ ሲኖትራክ መኪና በዶልፊን የህዝብ ማመላለሻ ላይ በመዉጣት የ5ሰዎችን ህይወት ሲቀጥፍ በሻሸመኔ ከተማ ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ ደግሞ አንድ የሞተር ተሽከርካሪ ላይ የነበሩ ሁለት ሰዎች ወድያዉኑ ህይወታቸዉ ማለፉን በመግለፅ የሞተር አሽከርካሪዎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ሲያሳስቡ አሳዛኝ አደጋዎች መሆናቸዉን ኢንስፔክተሩ ጨምረዉ ለብስራት ሬድዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

ኢንስፔክተሩ አክለዉም በአንድ ሳምንት ብቻ የ16 ሰዉ ህይወት ማለፉ እጅግ አስከፊና አሳዛኝ ነዉ ሲሉ ጠቅሰዉ አሽከርካሪዎች በፍጥነት፣ጠጥተዉ እንዲሁም በመሽቀዳደም የሰዉን ህይወት ከመቅጠፍ እንዲጠነቀቁ ሲያሳስቡ እግረኞችም በተቻላቸዉ አቅም ሁሉ ጥንቃቄ በማድረግ ራሳቸዉን ከትራፊክ አደጋ እንዲጠብቁ በአፅኖት አሳስበዋል።

#ዜና ኦዳ ጆርናል/Oda Journal
ቴሌግራም ላይ ይቀላቀሉን
👇👇👇👇👇👇👇👇👇

28/08/2023

ታማኝ ወቅታዊ መረጃዎችን በቴሌግራም ቻናላችን ይከታተሉ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/Oda_Journal

Journalist

 #ዜና        ከብሄራዊ ባንክ ፍቃድ በማግኘት በቅርቡ በሃገራችን የሞባይል መኒ አገልግሎት መስጠት የጀመረው M-Pesa በዛሬ እለት ደግሞ አድስ አገልግሎትን ለደንበኞቹ ይፋ አድርጓል። ሰ...
28/08/2023

#ዜና

ከብሄራዊ ባንክ ፍቃድ በማግኘት በቅርቡ በሃገራችን የሞባይል መኒ አገልግሎት መስጠት የጀመረው M-Pesa በዛሬ እለት ደግሞ አድስ አገልግሎትን ለደንበኞቹ ይፋ አድርጓል። ሰፋሪ ኮም በዛሬው እለት ይፋ ያደረገውም አገልግሎት የትኛውም ደንበኛው ከባንክ አካውንቱ ወደ M-pesa ዋሌቱ ገንዘብ ማስተላለፍ እንደምችል ይፋ አድርኋል። እነዚህም ባንኮች :- አብሲኒያ ባንል፡ አዋሽ ባንክ እና አባይ ባንክ መሆናቸውንም ጨምሮ ለደንበኞቹ አሳውቋል።

ኦዳ ጆርናል/Oda Journal

አቶ በቀለ ገርባ በአሜሪካ ሀገር ጥገኝነት መጠየቃቸውን አሳወቁ።ለረዥም ዓመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ በግል እና በፓርቲ ደረጃ ተሳታፊ የነበሩት የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ ፓርቲ ተቀዳመ ም...
28/08/2023

አቶ በቀለ ገርባ በአሜሪካ ሀገር ጥገኝነት መጠየቃቸውን አሳወቁ።

ለረዥም ዓመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ በግል እና በፓርቲ ደረጃ ተሳታፊ የነበሩት የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ ፓርቲ ተቀዳመ ምክትል ፕሬዜዳንት አቶ በቀለ ገርባ በፓርቲያቸው የነበራቸውን ተሳትፎ አብቅተው በአሜሪካ ጥገኝነት መጠየቃቸውን ለቢቢሲ አማርኛ ክፍል ተናገሩ።

አቶ በቀለ ፤ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ያለው ፖለቲካዊ ሁኔታ " በሰላማዊ መንገድ ለመታገልም ሆነ በግል በነጻነት መኖር " አሳሳቢ በመሆኑ በሄዱበት አሜሪካ ጥገኝነት መጠየቃቸውን ገልጸዋል።

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ተቀዳሚ ምክትል የሆኑት አቶ በቀለ፣ በውጭ አገር ሆነው ሥልጣኑን ይዘው መቀጠጣለቸው ጠቃሚ ስላልሆነ እራሳቸውን ከፓርቲው ለማግለል መወሰናቸውን ተናግረዋል።

አቶ በቀለ ገርባ ፤ ከአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በኋላ ተፈጥሮ የነበረውን ሁከት ተከትሎ በቁጥጥር ሥር ውለው ለ18 ወራት በእስር ላይ ቆይተው ከተለቀቁ በኋላ ወደ አሜሪካ ተጉዘዋል። አሜሪካ ከሄዱ 1 ዓመት ከሶስት ወር ሆኗቸዋል።

አቶ በቀለ ከእስር ከወጡ በኋላ ወደ አሜሪካ ሲጓዙ ዓላማቸው የእርሳቸውን ከእስር መለቀቅ ሲጠይቅ ለነበረው የዳያስፖራ ማኅብረሰብ ምስጋና ለማቅረብ ነበር።

ነገር ግን አሜሪካ በቆዩባቸው ያለፉት 15 ወራት በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ በመቀየሩ " ወደዚያ አገር መመለሱ አስፈላጊ መስሎ አልታየኝም " በማለት እዛው ጥገኝነት መጠየቃቸውን እና ከፓርቲው ኃላፊነትም እራሳቸውን ማግለላቸውን ለቢቢ አማርኛ አገልግሎት በሰጡት ቃል ገልጸዋል።

ኦዳ ጆርናል/Oda Journal

ትናንት ከፍተኛ ውጊያ የነበረባቸው የላሊበላ እና በሰሜን ሸዋ ዞን አንፆኪያ ገምዛ መኮይ ከተማ ዙሪያ ዛሬ ውጊያ ቆሟል ብለዋል።በተለይ በመኮይ ከተማ በነበረው ውጊያ የንፁሃን ሟቾች ቁጥር አን...
25/08/2023

ትናንት ከፍተኛ ውጊያ የነበረባቸው የላሊበላ እና በሰሜን ሸዋ ዞን አንፆኪያ ገምዛ መኮይ ከተማ ዙሪያ ዛሬ ውጊያ ቆሟል ብለዋል።
በተለይ በመኮይ ከተማ በነበረው ውጊያ የንፁሃን ሟቾች ቁጥር አንድ የ84 አመት አዛውንትን ጨምሮ ከ6 እንደሚበልጥ ተናግረዋል።
👉ላሊበላ ዙሪያ በነበረው ውጊያም ከፍተኛ ጉዳት ሳያደርስ እንዳልቀረ እና በርካታ አምቡላንሶች ወደ ወልዲያ አቅጣጫ ሲመላለሱ ማየታቸውን ምንጭ:-አዩዘሀበሻ
ኦዳ ጆርናል/Oda Journal

ለብሪክስ ስብሰባ ደቡብ አፍሪካ የተገኙት የኢትዮጵያና የኤርትራ መሪዎች ተገናኝተው መምከራቸውን ከምስል ጋር የወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ። ባለፈው በግብፅ ካይሮ በነበረው ስብሰባ ላይ ጠቅላይ ሚ...
25/08/2023

ለብሪክስ ስብሰባ ደቡብ አፍሪካ የተገኙት የኢትዮጵያና የኤርትራ መሪዎች ተገናኝተው መምከራቸውን ከምስል ጋር የወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ።
ባለፈው በግብፅ ካይሮ በነበረው ስብሰባ ላይ ጠቅላይ ሚንስሩ ኢሳያስ አፈወርቂ ወደ አረፉበት ሆቴል በመሄድ እንዳገኟቸው የተገለፀ ሲሆን፣በዚህም ኢሳያስ አፈወርቂ ጠቅላይ ሚንስሩ የሰሩትን ስህተት እንደነገሯቸው ምንጮች ገልጸዋል። በዚህም በወቅቱ አብረው የተጓዙት የጠቅላይ ሚንስትሩ የደህንነት አማካሪ ሬዴዋን ሁሴን ኢሳያስ አፈወርቂ በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ ገልፀው ነበር። ትናንት ደግሞ በደቡብ አፍሪካ እየተደረገ ባለው የብሪክስ ስብሰባ ላይ በተናጠል እንደተገናኙ እና እንደመከሩ የተገለፀ ሲሆን የትኛውም የመንግሥት አካል ግንኙነቱን ይፋ ከማድረግ ተቆጥበዋል።
ኢሳያስ አፈወርቂ ኢትዮጵያን ለመጨረሻ ጊዜ የጎበኙት በጥቅምት 2013 ዓ.ም ነው።
ጠቅላይ ሚንስሩ ባለፈው ጥር ወር ጀምሮ ኢሳያስ አፈወርቂ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ጉብኝት እንዲያደርጉ 3 ጊዜ ጥሪ እንደተደረገላቸው እና ችላ እንዳሉት ተሰምቷል።
Habi Tube

ሰበር ሰበር አሁን ከስፍራው
16/07/2023

ሰበር ሰበር አሁን ከስፍራው

ሰላም እንዴት ናችሁልን በዛሬ ቪዲዮ አርፍ መረጃ እንዳገኛችሁ ተስፋ አደርጋለው ለyoutube ቻናሌ አድስ ከሆናችሁ subscribe አድርጉ ላይክ እንድሁም ሼር አድርጉhello guys i'm habi faf from ethiopia welcome to my ...

አሁን የደረሱን
09/03/2023

አሁን የደረሱን

ሰላም እንዴት ናችሁልን በዛሬ ቪዲዮ አርፍ መረጃ እንዳገኛችሁ ተስፋ አደርጋለው ለyoutube ቻናሌ አድስ ከሆናችሁ subscribe አድርጉ ላይክ እንድሁም ሼር አድርጉhello guys i'm habi faf from ethiopia welcome to my ...

ሰበር ዜናጀግናው መከላከያ ሰራዊት እና ጥምር ጦርጁንታው ላይ እያሳረፈ ባለው ፋታ የለሽ ምትየጁንታው አዋጊዎች ታጣቂውን እና ጀሌውንበትነው እየፈረጠጡ ነው፡ በዛሬው እለት(በ05/01/2015)...
15/09/2022

ሰበር ዜና
ጀግናው መከላከያ ሰራዊት እና ጥምር ጦር
ጁንታው ላይ እያሳረፈ ባለው ፋታ የለሽ ምት
የጁንታው አዋጊዎች ታጣቂውን እና ጀሌውን
በትነው እየፈረጠጡ ነው፡ በዛሬው እለት
(በ05/01/2015)ጁንታው በማይፀብሪ ግንባር
በተወሰደበት እርምጃ አመራሩ በመፈርጠጥና
ህይወቱን ለጊዜው በማትረፍ ታጣቂው ወደ
ኋላ እንዳይሸሽ እና እንዲያልቅ ወስነውበት
ከማይፀብሪ ወደ ሽሬ የሚያሻግረውን የተከዜ
ድልድይ ቡለኑን በመፈታታት ጥለውት ሄደዋል።
በዚህ ምክንያት በአዋጊው የተከዳው ታጣቂውና
ጀሌው ተስፋ በመቁረጥ ለወገን እጅ እየሰጠ
ሲሆን በርካታ ቁጥር ያላቸው ለመሻገር ሲሞክሩ
በተከዜ ወንዝ መወሰዳቸው ከቦታው የደረሰን
መረጃ ያሳያል።

05 01 2015 ECቆቦ ከተማ●●●አሸባሪው የትህነግ ቡድን በዛሬው ዕለት በቆቦ ከተማ ነዋሪዎችን ስብሰባመጥራቱ መረጃዎች እየወጡ ነዉ ።አሸባሪ ቡድኑ ስብሰባውን በማስገደድ የጠራው ከእንግዲህ...
15/09/2022

05 01 2015 EC
ቆቦ ከተማ
●●●
አሸባሪው የትህነግ ቡድን በዛሬው ዕለት በቆቦ ከተማ ነዋሪዎችን ስብሰባ
መጥራቱ መረጃዎች እየወጡ ነዉ ።
አሸባሪ ቡድኑ ስብሰባውን በማስገደድ የጠራው ከእንግዲህ መንግስት ሆነን
የምንመራው እኛ ስለሆንን የድጋፍ ሰልፍ አድርጉልኝ በማለት የፕሮፖጋንዳ
ሥራን ለማከናወን አልሞ ነዉ ።
Ne
ከዚህም ባሻገር ህዝቡን ሰብስቦ ከታጣቂዎች ጋር በማድረግ የአየር ጥቃት
ሰለባ እንዲሆኑ በማድረግ የሀውዜንን ታሪክ ለመድገም ታሳቢ በማድረግ
መሆኑን የደረሰን መረጃ ያመለክታል ።
የአከባቢው ህዝብም ይህን በመረዳት በቡድኑ ስብሰባ ላይ እንዳይታደም
መንግሥት ጥሪውን ያቀርባል።
ምንጭ ፥Horn of Africa Fm

ጀግናው የኢፌዴሪ አየር ሃይል የጁንታው ወታደራዊ አቅሞች ላይ እየወሰደ የሚገኘው እርምጃ ቀጥሏል።ዛሬም በከፍተኛ ጥንቃቄና የኢላማ ጥራት በንፁሃን ላይ ጉዳት እንዳይደርስ በማድረግ የሽብር ቡድ...
14/09/2022

ጀግናው የኢፌዴሪ አየር ሃይል የጁንታው ወታደራዊ አቅሞች ላይ እየወሰደ የሚገኘው እርምጃ ቀጥሏል።

ዛሬም በከፍተኛ ጥንቃቄና የኢላማ ጥራት በንፁሃን ላይ ጉዳት እንዳይደርስ በማድረግ የሽብር ቡድኑ ወታደራዊ ኢላማዎች ላይ እርምጃ ወስዷል።

የሽብር ቡድኑ በጦር ሜዳ እያጋጠመው ያለውን ከፈተኛ ሽንፈት ተከትሎ የሲቪል ተቋማትንና ሰዎች በብዛት የሚገኙባቸውን አካባቢዎች መደበቂያ ለማድረግ እየሞከረ ይገኛል።

ይህ የሽብር ቡድኑ ተግባር አዲስ አይደለም።
ጁንታው ከትግራይም አልፎ በወረራ ይዟቸው በነበሩ የአማራና አፋር አካባቢዎች የእምነት ተቋማትን ትምህርት ቤቶችንና ሆስፒታሎችን የከባድ መሳሪያዎች ማከማቻና ወታደራዊ ማእከላቱ መገኛ አድርጎ እንደነበር ይታወቃል።
አሁንም የትግራይን ህዝብ የፕሮፖጋንዳው ማስፈፀሚያ ለማድረግ ወታደራዊ አቅሙንና የጦርነት መጠቀሚያ ግብአቶቹን ሲቪሉ ህዝብ በሚገኝበት አካባቢ ለመደበቅ እየሞከረ በመሆኑ ህዝቡ ከእነዚህ አካባቢዎች ራሱን ሊያርቅ ይገባል።

መንግስት ከዚህ ቀደም በይፋ ለትግራይ ህዝብ የሽብር ቡድኑ መጠቀሚያ እንዳይሆን ከጁንታው ወታደራዊ አቅሞች ራሱን እንዲያርቅም ማስታወቁ ይታወሳል።

ሩሲያ እስካሁን በአሜሪካ ክስ ዙሪያ ምላሽ አልሰጠችምሩሲያ በሌሎች ሀገራት ፍላጎቷን ለማስጠበቅ 300 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ማድረጓን አሜሪካ ገለጸች።የአሜሪካ የደህንነት ተቋም ባወጣው መረጃ ሩሲ...
14/09/2022

ሩሲያ እስካሁን በአሜሪካ ክስ ዙሪያ ምላሽ አልሰጠችም

ሩሲያ በሌሎች ሀገራት ፍላጎቷን ለማስጠበቅ 300 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ማድረጓን አሜሪካ ገለጸች።
የአሜሪካ የደህንነት ተቋም ባወጣው መረጃ ሩሲያ በተለያዩ የዓለማችን ሀገራት የፖለቲካ ፍላጎቷን ያስፈጽሙልኛል ያለቻቸውን እጩዎች እና ፓርቲዎች በገንዘብ እየረዳች ነው ብሏል።
እንደ ሮይተርስ ዘገባ ከሆነ ሩሲያ በአምስት አህጉራት ለሚገኙ ከ20 በላይ ሀገራት ከ300 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ፈሰስ አድርጋለች ።
በተለይም ከፈረንጆቹ 2014 ጀምሮ ለአውሮፓ፣ እስያ፣ አፍሪካ እና ሁለቱ የአሜሪካ አህጉራት ስር ላሉ ሀገራት በተለያየ መንገድ ገንዘብ ሰጥታለች ተብሏል።
ሩሲያ ገንዘቡን ፈሰስ የምታደርገው በፋውንዴሽን ስም በተቋቀቋሙ ድርጅቶች እና ለይስሙላ በተቋቋሙ የንግድ ድርጅቶች ስም እንደሆነም አሜሪካ ገልጻለች።
አሜሪካ በሩሲያ የገንዘብ ድጋፍ የተደረገላቸውን ሀገራት ለጊዜው ያልጠቀሰች ሲሆን ከአውሮፓ አልባኒያ፣ ቦስኒያ እና ሄርዜጎቪና፣ ሞንቴኔግሮ ሲሆኑ ከአፍሪካ ደግሞ ሜዳጋስካር አንዷ መሆኗን ኤኤፍፒ ከፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ጽህፈት ቤት ያገኘውን መረጃ ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
ሩሲያ ገንዘቡን ወደ ምትፈልጋቸው ሀገራት እና የፓርቲ እጩዎች ቤልጂየም እና ኢኳዶር ከሚገኙት የሩሲያ ኢምባሲዎች በኩል እንደሆነም ተጠቅሷል።
አሜሪካም የፓለቲካ ፍላጎቶቿን ለማስፈጸም በተለያዩ የዓለማችን ሀገራት ላይ በሲአይኤ በኩል ጣልቃ በመግባት መፈንቅለ መንግስት እስከማስፈጸም የሚደርስ ሙከራ ታደርጋለች የሚል ክስ እንደሚነሳባት የጀርመን ድምጽ ዘግቧል።
በተለይም በኢራን እና በቺሊ ሲአይኤ መፈንቅለ መንግስት እንዲፈጸም አድርጓል በሚል የሚቀርብባትን ክስ አሜሪካ ውድቅ አድርጋለችም ተብሏል።
የፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳድር በሩሲያ ላይ ያቀረበውን ክስ ራሷ አሜሪካ በዲሞክራሲ እና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ስም ትፈጽማለች በሚል የቀረበበትን ክስ ውድቅ ማድረጉም ተገልጿል።ሩሲያ በአሜሪካ በቀረበባት ክስ ዙሪያ እስካሁን ምላሽ እንዳልሰጠች
ተገጿል።
የዜና ምንጭ ፡- አል-ዐይን

ዛሬን ለጨመረልህ ጌታ ምስጋናን አቅርብ ነገን የሰጥኋልና🙏
13/09/2022

ዛሬን ለጨመረልህ ጌታ ምስጋናን አቅርብ ነገን የሰጥኋልና🙏

መልካም አድስ አመት🌻🌼🌻🌼🌻🌼
13/09/2022

መልካም አድስ አመት🌻🌼🌻🌼🌻🌼

መልካም አድስ አመት ይሁንልን🌻🌻
13/09/2022

መልካም አድስ አመት ይሁንልን🌻🌻

12/09/2022

ለወቅታዊና አዳድስ ክኑውኖች ይከተሉን

Address

Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኦዳ ጆርናል/Oda Journal posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share



You may also like