Onesimus Publisher

Onesimus Publisher Offering theological books in vernacular languages for the Ethiopian church. Empowering local clergy and believers with culturally resonant resources.

Explore our Ethiopian church-focused theological publication. We are guardians of Biblical truth. አናሲሞስ አሳታሚ በወንጌላዊያን የሥነ-መለኮት ትምህርት ቤቶች ውስጥ ለሚማሩ ተማሪዎች እንዲሁም አገልጋዮች ደረጃዎቻቸውን የጠበቁ አጋዥና ማጣቀሻ መጻሕፍትን ለማዘጋጀት የተቋቋመ ተቋም ነው።

Finally, I am holding my first book in English on my hand! Tekalign Duguma Negewo
30/03/2024

Finally, I am holding my first book in English on my hand! Tekalign Duguma Negewo

καὶ ἡ ἐξουσία τοῦ σκότους ‘and the power of darkness’ "እና የጨለማው ኃይል ጊዜ ነው።”Darkness refers to Satan, the ruler of evil [...
04/03/2024

καὶ ἡ ἐξουσία τοῦ σκότους ‘and the power of darkness’ "እና የጨለማው ኃይል ጊዜ ነው።”

Darkness refers to Satan, the ruler of evil [Arn, ICC, NAC, NICNT, TG, WBC]. Or, darkness characterizes the rule or domain of evil [BECNT]. The expression ‘the darkness’ almost personifies the darkness as possessing a power as though it were a monster of evil [Lns]. It is the hour in which the power of darkness is revealed and exercises its force [NIGTC]. Darkness and all it symbolizes will hold sway [AB].
1. This hour is theirs and also it is the hour of the power of darkness [Gdt, ICC, Lns, MGC, NIC, TH, TNTC; NET]. Their hour coincides with the hour allowed to the power of darkness [ICC]. This hour is not only the hour of Jesus’ human enemies, it is also the hour for the activity of the devil who rules in the darkness [TH]. Their hour is also the hour that the power of darkness operated in and through them [Lns, MGC]. They will succeed in their evil plans because in that hour Satan and his henchmen were being permitted by God to bring the Son of God into humiliation, suffering, and death [NIC]. Nighttime is when Satan puts forth his power over humanity, so it is his hour, and it is their hour because they are Satan’s instruments [Gdt].
2. This hour is theirs and it is characterized by being the power of darkness [BNTC, NIBC, Su, WBC; CEV, GW, NASB, NCV, NIV, NLT, REB, TEV]. The crowd has selected the hour of darkness to arrest Jesus and it was an appropriate time because darkness typified the nature of their act [Su]. The authorities who came to arrest Jesus were acting as representatives of Satan, the ultimate darkness [WBC]. The darkness of that night symbolizes the moral and spiritual darkness of that hour [NIBC].
LEXICON—a. aorist act. participle of συλλαμβάνω (LN 37.109) (BAGD 1.a.α. p. 776): ‘to seize’ [Arn, BAGD, BECNT, LN, Lns, NTC; HCSB, NIV, NRSV], ‘to take’ [KJV], ‘to arrest’ [AB, BAGD, LN, WBC; GW, NASB, NCV, NET, NLT, REB, TEV]. This active voice is also translated passively with ‘Jesus’ as the subject: ‘to be arrested’ [CEV]. This verb is a technical term for making an arrest [NAC]. The verb does not necessarily imply violence [TNTC].
QUESTION—What was the house of the chief priest?
It was the official residence of the high priest [TH]. It was part of the total temple structure

24/02/2024

(ከማቴዎስ ወንጌል ማበራሪያ 1-7 የተወሰደ)

የዋህነትና ብፅዕና

ይህ ጥቅስ የተወሰደው ከመዝ 37፥11 የሰብዓ ሊቃናት የብሉይ ኪዳን መጽሐፍ ሳይኾን አይቀርም። πραΰς ‹‹የዋሆች›› የሚለው ቃል በዐዲስ ኪዳን ጥቅም ላይ የዋለው አራት ጊዜ ብቻ ሲኾን፣ ሦስቱ የሚገኙት በማቴዎስ ወንጌል ነው (ማቴ 5፥5፤ 11፥29፤ 21፥5)። ቀሪው በ1ጴጥ 3፥4 ይገኛል። በማቴ 11፥29ና 21፥5 ላይ ኢየሱስ በእግዚአብሔር ፊት እንደ ሙሴ (ዘኍ 12፥3) πραΰς ‹‹የዋህ›› እንደኾነ ተግልጾአል። ማለትም፣ ነፍሱንና ሥጋውን አራቊቶ በእግዚአብሔር ፊት ባዶውን ቀርቧል፤ ሙሉ ለሙሉ በእግዚአብሔር ላይ መደገፉን ያሳያል። ይህም ተግባሩ የዋህ አሰኝቶታል።

በማቴዎስ ወንጌል πραεῖς ‹‹የዋሆች›› የሚለው ቃል፣ በዓለም ፊት ምንም ኀይል የሌላቸው፣ በሌሎች ኀያላን ነን በሚሉ የተጨቈኑ፣ ፈሪሃ እግዚአብሔር በሌላቸው ሰዎች ፍትሕ የተጓደለባቸውን፣ ነገር ግን በዚህ ኹኔታ እንኳ ኾነው ከእግዚአብሔር ብድራታቸውን የሚጠባበቁ ሰዎችን የሚያመለክት ነው።

በመቀጠልም፣ የየዋሆች ብፅዕና ወይም ታላቅ ደስታ ምስጢሩ ምን እንደኾነ በማቴ 5፥5ለ ላይ እንዲህ ይገልጽልናል ὅτι αὐτοὶ κληρονομήσουσιν τὴν γῆν ‹‹ምድርን ይወርሳሉና።›› በቁምራን ማኅበረሰብ ዘንድ መዝ 37 ከፍተኛ ስፍራ እንደነበረው ለመዝ 37 ከሰጡት ማብራሪያ መመልከት ይቻላል (4QpPs 37)። በዚህ ማብራሪያ ውስጥም በመሲሑ አማካኝነት እግዚአብሔር ይታደገናል ብለው ያምኑ እንደነበር እናያለን።
የዋሆች ይወርሷታል የተባለላትን ምድር በተመለከተ የሥነ መለኮት ምሁራን የተለያዩ አስተያየቶችን ሰንዝረዋል። አንዳንዶች፣ የእስራኤልን መሬት ያመለክታል ይላሉ። ሌሎች ደግሞ፣ አጠቃላይ ምድርን ነው በማለት ይሞግታሉ። ከእነዚህ ኹለቱ በተቃራኒ ደግሞ፡- ‹‹መንፈሳዊዋን መንግሥተ ሰማያትን›› የሚያመለክት ነው የሚሉ አሉ።

ይወርሷታል የተባለችው የእስራኤል ምድር ናት የሚሉ ሰዎች ለመከራከሪያ በእማኝነት የሚያነሡት አንዱ መረጃ፣ የማቴዎስ ወንጌል ጸሓፊ የሰው ልጅ የኾነው መሲሕ በእስራኤል እንደሚነግሥ የሚያመለክቱ ዐሳቦች በማቴ 8፥11ና 19፥28 መቀመጣቸውን ነው። ይኹን እንጂ፣ በመጀመሪያ ደረጃ በማቴ 19፥28 የተሰጠው የተስፋ ቃል የሚፈጸመው ἐν τῇ παλιγγενεσίᾳ ‹‹በዳግም ልደት›› መኾኑ የሚያመለክተው አጠቃላይ የምድርን ዳግም ልደት ወይም መታደስን እንጂ የእስራኤልን ምድር አለመኾኑን መመልከት ይቻላል።

ኹለተኛ፣ በማቴዎስ ወንጌል τὴν γῆν ‹‹ምድር›› የሚለው ቃል ጥቅም ላይ በዋለባቸው ስፍራዎች ሁሉ የሚያመለክተው አጠቃላይ ምድርን እንጂ የእስራኤልን ምድር ብቻ አይደለም (5፥13፡18፡35፤ 6፥10፡19፤ 9፥6፤ 11፥25፤ 12፥42፤ 16፥19፤ 18፥18-19፤ 23፥9፤ 24፥30፤ 28፥18 ይመ.)። ምንም እንኳ በመዝ 37 ላይ የሚገኘው τὴν γῆν ‹‹ምድር›› የሚለው ቃል የሚያመለክተው የእስራኤልን ምድር፣ እግዚአብሔር ለአይሁድ ከአብርሃም ጊዜ አንሥቶ የገባላቸውን የቃል ኪዳን ምድር ቢኾንም፣ በማቴዎስ ዐውድ ግን የዋሆች ይወርሷታል የተባለቸው ምድር በመሲሑ አማካኝነት እንደምትታደስ በኢሳ 65-66 የተነገረላት ምድር ናት።

ስለዚህ፣ ከነበሩበት ጭቈና የተነሣ የተዋረዱት፣ ፈሪሃ እግዚአብሔር በሌላቸው ገዢዎች ፍትሕ የተጓደለባቸው፣ ምድር ዐልባ የኾኑት በዚህ ኹኔታ ውሰወጥ እንኳ ኾነው ከእግዚአብሔር ዘንድ ብድራታቸውን እንደሚቀበሉ ተስፋ የሚያደርጉ የዋሆች ናቸው። መሲሑ አኹን ይዞት የመጣውን መንግሥት ሙሉ ለሙሉ በምድር ላይ በሚመሠርትበት ወቅት የታደሰችው (ዳግም ልደት ያገኘችው) ምድር የእነርሱ ትኾናለች። ከጨቋኞቻቸው የተነሣ ምንም እንኳ ያኹኗ ምድር የእነርሱ ባትኾንም፣ ተስፋ የሚያደርጉት መሲሕ መንግሥቱን በምድር ላይ ሲመሠርት ያን ጊዜ የታደሰችው ምድር ሁሉ የእነርሱ ትኾናለች፣ እርሷንም ይወርሷታል።

As some scholars have posited, the striking similarity between Jesus rebuking and calming tumultuous waves and Yahweh's ...
13/02/2024

As some scholars have posited, the striking similarity between Jesus rebuking and calming tumultuous waves and Yahweh's actions in the Old Testament (evidenced in passages like Psalms 18:16, 104:7, and 106:9) cannot be easily dismissed as mere coincidence. It's as if, through the person of Jesus Christ, Yahweh is once more facing off against his ancient adversary Yamm amidst the turbulent waters of the Sea of Galilee.

12/02/2024

በእግዚአብሔር መንግስት እና በጨለማው ዓለም መካከል የተደረገ ፍልሚያ

የእግዚአብሔር አገዛዝ ዘላለማዊ እና ሁሉን አቀፍ ነው፤ እርሱ የሁሉ ገዥ ነበር፣ ነውም ይኾናልም። ምንም እንኳ እርሱ የሰማያት፣ የመላእክት፣ የዓለማት፣ የተፈጥሮ እና የታሪክ ገዥ ቢኾንም የእርሱን አገዛዝ በዕለት ተዕለት ሕይወታችን ላንለማመድ እንችላለን። የእግዚአብሔር መንግስት መምጣት በሰው ልጆች ታርክ ውስጥ እግዚአብሔርን ጣልቃ መግባቱን የሚያሳይ ነው። ይህ የሰው ልጆች ጉዳይ ውስጥ እግዚአብሔር ጣልቃ በመግባት ሰዎችን በእስራት እና ኃይል ከያዙት ኃይላት ጋር ፍልሚያ በማድረግ የተለመደውን የሰው ልጆችን የአኗኗር ዘይቤ መለወጡን ያመለክታል።

እስራኤላዊያን በግብጽ ምድር በባርነት በነበሩ ጊዜ የኾነውም ይኼው ነው። ክፉ በኾነው የፈርኦን አገዛዝ አማካኝነት ይሠራ በነበሩ ክፉ ኃላት ባርነት ሥር ነበሩ። የግብጻዊያን አምላክ፣ ፈርኦን እና ሠራዊቱ እስራኤላዊያን ባርያ አድርገው ይገዟቸው ነበር። እነርሱም በባርነት ሳሉ የእግዚአብሔር መንግስት መጥታ የግብጻዊያንንም አማልክት በተለያዩ መቅሰፍቶች መታች። በግብጻዊያን አማልክት እና በመጣችው እግዚአብሔር መንግስት መካከል ፍልሚያ መደረጉን፤ ይሁን እንጂ የእግዚአብሔርም መንግስት በድል አድራጊነት ነጻ መወጣቷን ታርኩን በመመልከት መረዳት ይቻላል።

እስራኤላዊያን ወደ ከነዓን ምድር በገቡ ጊዜም በከነዓን ምድር ከነበሩ ሰዎቸ ጋር ጦርነት በገጠሙ ጊዜም እግዚአብሔር ቀድሞዋቸው መውጣቱ፤ ለእነርሱ ድልንም እንደሰጣቸው እንመለከታለን።

በተጨማሪም በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ውስጥ በተጠቀሱ የነገሥታት ታሪክ ውስጥም የእስራኤልም አምላክ በነገሥታት አማካኝነት እስራኤልን ይገዛ እንደነበር እንያለን። የእግዚአብሔር መንፈስ ዳዊትን የእስራኤል ንጉሥ አድርጎ በመሾም እስራኤላዊያን ካስጨነቁ ኃይላት ኹሉ ነጻ ማውጣቱ፤ በዳዊት አገዛዝ ዘመን የሠፈነው ሠላም ከእግዚአብሔር መንግስት ሠላም ጋር ተመሳሳይ መኾኑን እናያለን። ይህ ሠላም ፍጹም የኾነው እና እስራኤል ከጦርነት ያረፈችው የዳዊት ልጅ በኾነው በንጉሥ ሰለሞን ዘመን ነበር። የእስራኤልም አምላክ በነገሥታት አማካኝነት እስራኤልን ይገዛ ነበር።

እንዲህ ዓይነቱ የእግዚአብሔር ስለእስራኤል በነገሥታቱ አማካኝነት ጣልቃ መግባት እንዲህ በማለት እንዲናገሩ አደርጓቸዋል፦ እግዚአብሔር ንጉሣች ነው! እስራኤላዊያን የእግዚአብሔር አገዛዝ እየተለማመዱ በሄዱ ቁጥር እግዚአብሔር አገዛዝ በተፈጥሮ፣ በሌሎች ነገሥ በተፈጥሮ እና በአጠቃላይ በኹሉም ላይ እንደኾነ ወደ ወደ ማወቅ መምጣታቸውን እንመለከታለን። ይህም እስራኤል ቃል ኪዳኗን ስትጠብ ንጉሧ እግዚአብሔር ከጠላቶቿ ኹሉ ይታደጋት፣ በበረከትም ያትረፈርፋት እንደነበር ኹሉ ከንጉሧን ከእግዚአብሔር በራቀች መጠን ግን እግዚአብሔር ይቀጣት ነበር። ቅጣቱም የአሕዛብ ነገሥታትንም በማስነሣት ለባሪነት/ለግዞት አሳልፎ ሰጥⶆዋቸዋል።

እስራኤላዊን በኀጢአታቸው ምክንያት ወደ ግዞት በሄዱበት ዘመንም ወደፊት ስለሚትመጣዋ እግዚአብሔር መንግስት/ አገዛዝ ተስፋ ተሰጥቶዋቸዋል። ይሁን እንጂ ይህ ተስፋ እግዚአብሔርም በሙሴ ዘመን እስራኤላዊያን ከግብጽ ባርነት ነጻ ባወጣበት ዘመን እንደኾነው የእርሱ ወዲያው የሚኾን ጣልቃ ገብነቱ ሳይኾን ለወፊት የሚኾን የእግዚአብሔርን ጣልቃ ገብነት ወይም እግዚአብሔር በእስራኤል ፈንታ ጣልቃ የሚገባበትን ዘመንንን የሚያመለክት ነው። ይህ ተስፋ እግዚአብሔር በእስራኤል ታሪክ ውስጥ እንዳደረገው እንደገና ጣልቃ እንደሚገባ የሚያሳይ ነው። እግዚአብሔር ወደ ሰው ልጆች ታርክ ውስጥ እንደገና ጣልቃ በመግባት እንደገና አገዛዙን በምድር ላይ ይመሠርታል።

ለወደፊት ሊኾን ስላለው የእግዚአብሔር ጣልቃ ገብነት አስደናቂነት ነቢያት በምሳሌም ሲገልጹት ድንጋይ ከሰማይ ይወድቃል፣ የዚህን ዓለም መንግሥታት ሁሉ ያደቃቸዋል፤ የእግዚአብሔር ክብርም ከጸሐይ ብርሃን ይልቅ ያበራል፤ የእግዚአብሔር መንፈስ ምድረ በዳውን ወደ ኤደን ገነት ያደርገዋል፤ እየሰፋም ሄዶም ምድርን ኹሉ ይሸፍናል በማለት ተናግረዋልረ። ይህም የሚኾነው በመጨረሻ ኹሉን እንዲገዛ የእግዚአብሔር ቅባት በእርሱ ላይ በሚኾነው በዳዊት ልጅ አማካኝነት ነው። በዚያ ቀን ሕዝቦች ሁሉ በእግሩ ሥር ይሰግዳሉ፤ የታሠሩ ነጻ ይወጣሉ፤ ዓይነ ስውራን ያያሉ፤ አንካሳው ይራመዳል፤ እንዲሁም አዲስና ልዩ ሰላምም ለእግዚአብሔር ሕዝብም ይኾናል። ይህ እግዚአብሔር ኹሉ ለመግዛት እና ለማስተካከል በሚመጣበትን በመጨረሻው ዘመን የሚኾን ነው። በመምጣቱም በአዲስቱ ዓለም ውስጥ ለራሱ አዲስ ሕዝብን ይፈጥራል። በመጨሻ እግዚአብሔር ጠላቶቹን ኹሉ ድል በማድረግ እርሱ ብቻ ገዥ የሚኾንበት አዲስ ዘመን ይኾናል።

እስራኤል በተለያዩ የአሕዛብ ነገሥታት ያለማቋረጥ እየተገዙም ሳለም ነብያቱ በአዲስ ኪዳን ዘመን ሊኾን ስላለው አዲሱ ክህነት፣ አዲሲቱ ኢየሩሳሌም፣ አዲስ አገር፣ እና አዲስ ቀን ይናገሩ ነበር። ነቢያቱ ስለመጪው የተስፋ ዘመን እንዲህ ባሉ የተስፋ ቃላት ይናገሩ እንጂ ሕዝቡ እግዚአብሔር በእኛ ላይ ቁጣው የበረታ ነው፤ ፍቱኑም ከእኛ አዙሯል ይሉ ነበር። በዚህ ዘመናትን ባስቆጠረ ተስፋ መቁረጥ ውስጥም ቢኾን የነበያቱ የተስፋ ድምጽ እየጨመረ ሄዷል። በመጨረሻም በዕዝራ እና ነህሚያ እንዲሁም ከዚያ በኋላ በተደረገው የማቃባዊያን ጦርነት ውስጥም ይህንን በነቢያቱ የተነገረው የተስፋ ቃል ጭላንጭ ማየት ይቻላል። ይህ የተስፋው ቃል ጭላንጭል ብቻ ከኾነ የሚጠበቀው የእግዚአብሔር መንግሥቱ የሚመጣው መቼ ነው?

ከዘመናት በኋላ ያልተጠበቁ እንግዳ እና ምስጢራዊ የኾኑ ነገሮች በድንገት መኾን ጀመሩ። አንድ ከምድረ በዳ የጣ ነቢይ የሚትጠብቁት መስሑ፣ የተቀባው መምጣቱን እያወጀ መጠ። ከናዝሬት የኾነው የአናጢው የዮሴፍ ልጅ እስራኤላዊያን ለዘመናት ይመጣል ብለው ሲጠብቁት የነበረው መስሑ እንደኾነ ተናገረ። በእርሱም እጅ አዲስ ነገር መኾነ ጀመረ። አንካሶች መራመድ፣ መስማት የተሳናቸው መስማት፣ አካለ ስንኩል መራመድ፣ ኃጢአተኞች ይቅር መባል፣ አጋንንት መውጣት፣ ሙታን ከሙት መነሣት፣ አውሎ ነፋሳት በአንድ ቃል ጸጥ ማለት እንዲሁም የእግዚአብሔርም መንግስት ከዬትኛው ዘመን ይልቅ ቅርብ መኾኑን መታወጁ በእርሱ የተከናወኑ አዳዲስ ነገሮቸ መካከል ጥቂቶቹ ናቸው።

ብዙ ሰዎችም ይህ ሰው የሚለውን ለመስማት ወደ እርሱ ይመጡ ነበር። እርሱ ያደረጋቸው እና የተናገራቸው ነገሮች ኹሉ የእግዚአብሔር መንግስት መምጣት የሚመሰክሩ ናቸው። በትምህርቶቹ እና በምሳሌዎች ስለ እግዚአብሔር መንግስት አብዝቶ ይናገር ነበር። እነዚህም በዚያ ወቅት አንድ ወሳኝ ነገር ስእለመኾኑ ያለጥርጥር ምስክሮች ናቸው። የእግዚአብሔር መንግስት በመካከላችን ናት እንዲሁም ለወደፊት ትመጣለች እያለ የእግዚአብሔር ምስጥር ይናገር ነበር። በአንደ በኩል ነቢያቱ አስቀድመው ስለእግዚአብሔር መንግስት/አገዛዝ የተነበዩት ነገር እየተፈጸመ መኾኑን ይናገራል በሌላ በኩል ደግሞ የተነገረው ነገር ሁሉ ሙሉ ለሙሉ ፍጻሜ እንዳላገኘና ወደፊት የመጨረሻው የእግዚአብሔር ጣልቃ ገብነትን እንደሚኾን ይጠቁማቸው ነበር።

ምንም እንኳ ኢየሱስ የእግዚአብሔር መንግስት መምጣት ሚስጥር የገለጸ ቢኾንም እስራኤላዊያን እና መሪዎቻቸው ይህንን እውነት ለማየት ዐይናቸው ተውሮ ነበር። በእርግጥ እርሱ እንደሚመጣ የተነገረው መስሑ ነበር? ወይስ መስሑ እንደኾነ የሚናገር አስመሳይ ሰው ነበር? እግዚአብሔር በመስሑ በኢየሱስ ሕይወት እና አገልግሎት አማካኝነት የተለያዩ ነገሮች በማድረግ የእርሱን ትክክለኛ መስሕነት አረጋግጧል። በመጨረሻ የእግዚአብሔር መንግስት ስትመጣ ይኾናሉ ተብለው በነቢያት የተነገሩ ነገሮች ኹሉ ክርስቶስ በኾነው በኢየሱስ በኩል ፍጻሜን አግኝተዋል። የዚህ ግለሰብ ማንነት ሚስጥራዊነቱ እና የእስራኤል እውነቱን ለማየት ዕውር መኾኗ በእርሱ ላይ ከፍተኛ ተቃውሞን አስነስቷል፤ ይሁን እንጂ ይህ ተቃውሞ ያልተጠበቀ እና እንግዳ የኸነ ነገር አልነበረም። መስሑን የሚቀበሉት እና ይዞት የመጣው መልዕክት የሚረዱት ጥቂቶች እንደኾኑ ነቢያቱ አስቀድመው ተናግረዋል። ከዚህም የተነሣ እርሱ ባስተማራቸው ትምህርቶቹ እርሱ ራሱ እንዲሁም ደቀ መዛሙርቱ ከሃይማኖት መሪዎች ይጋጩ ነበር።

በአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ውስጥ ኢየሱስ ስለእስራኤል መከራን ይቀበላል ተብሎ አስቀድሞ የተነገረውንና በኢሳያስ ትንቢት ውስጥ የተጠቀሰውን ባሪያ/አገልጋይ ሚና ይዞ እንደነበር ተገልጾ እናገኛለን። ምንም አንኳ የመስቀል ሞትን ቢሞትም ከሞት ተነሥቷል። ይህ ከሞት መነሣት እንደሚመጣ የተነገረው የአዲሱ ዘመን መምጣት መገለጫ ነው። ከትንሣኤ በኋላም ኢየሱስ ክርስቶስ ስለእግዚአብሔር መንግስት መናገሩን አላቆመም። ምንም እንኳ የእግዚአብሔር መንግስት ብትመጣም በትንሣኤው የአዲስ ዘመን መጀመሩን ቢያመለክትም የእግዚአብሔር መንግስት በኃይል ኹሉን የሚትገዛበት ዘመን ለወደፊት እንደሚትመጣ ከትንሣኤው በኋላም ይናገር ነበር። ይህንንም የእግዚአብሔር መንግስት መምጣት ወደ ዓለም ኹሉ ሄደው ያውጁ ዘንድ ደቀ መዛሙርቱን ካዘዘ በኋላም ወደ ሰማይ አርጓል። ከዚያም በኋላ ደቀ መዛሙርቱ የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ተቀብለዋል።

ከጴንጤቆስጤ ቀን በኋላም የኾኑት ነገሮች በኢየሱስ ሕይወት እና አገልግሎት ዘመን ከኾኑት ነገሮች ጋር ተመሳሳይ መኾናቸውን መመልከት ይቻላል። በዚህም ዘመን የኾነው ነገር የእግዚአብሔር መንግስት መምጣት ከጠላቶቹ ጋር ፍልሚያ እያደረገ መኾኑን በሚያሳዩ ቃላት ተገልጾ እናገኛለን። የወንጌል ብርሃን በዚያ ዘመን የነበረው ጨለማ እያስወገደ፣ አጋንንት ከሰዎች ውስጥ እየወጣ፣ የታመሙ እየተፈወሱ፣ ሙታን እየተነሡ፣ ኃጢአተኞች የኃጢአት ይቅርታን እያገኙ በመኾናቸው በኢየሱስ ክርስቶስ ተከታዩች እና በጨለማው ዓለም ገዥ ጋር ፍልሚያ መኖሩን ያሳያል። ከዚህም የተነሣ ኢየሱስ ንጉሥ መኾኑ በታወጀባቸው ከተሞች እና መደሮች ውስጥ ታላቅ ነውጥ ይኾን ነበር። የነዚህ ነገር ምስክሮች የኾኑነት ደቀ መዛሙርቱ ስለ እግዚአብሔር መንግስት የሰጡት ምስክርነት በወንጌላት፣ በሐዋርያት ሥራ፣ በጳውሎስ እና በሌሎች የአዲስ ኪዳን ደብዳቤዎች፣ በራዕይ መጽሐፍ ተጽፎ እናገኛለን።

10/02/2024

"[T]heological systematization is hardly the concern of the biblical narrators"
(Wenham, 1987:144)

ዛሬ የተማሪዎቼን ጥናታዊ ጽሑፍ ሳነብ ከአንድ ተማሪ አንድ እንደገና እንዳስብበት የሚያደርግኝ ሀሳብ አገኘው። አንዳንዴም የተማሪ ወረቀትም አስተማሪ ነው ለማለት ያኸል ነው፦
07/02/2024

ዛሬ የተማሪዎቼን ጥናታዊ ጽሑፍ ሳነብ ከአንድ ተማሪ አንድ እንደገና እንዳስብበት የሚያደርግኝ ሀሳብ አገኘው። አንዳንዴም የተማሪ ወረቀትም አስተማሪ ነው ለማለት ያኸል ነው፦

29/01/2024
25/01/2024

Theology evolves, not universally fixed, but a perpetual process to consistently engage in.

16/01/2024

ነገረ ቅድመ ውሳኔ

In the grand tapestry of existence, the personal God is an intimate companion, understanding individual nuances, while the philosophical deity is a meticulous mathematician defining the very essence of everything with cosmic precision.

ሁለተኛው ከመጸሐፍ ቅዱሳዊነቱ ይልቅ ምናባዊነቱ ያደላል

29/12/2023

የአስተምህሮ ግልጽነት ባሌለበት ሁሉ ኹሉ ልክ ወይም ኹሉ ስህተት ይኾናል።
ሰሞነኛ አጀንዳ በተመለከተ ሁለተኛ ጎልቶ እየወጣ መሰለኝ

የማይታይ አምላክ ምሳሌ (ቆላ. 1፥15)
21/12/2023

የማይታይ አምላክ ምሳሌ (ቆላ. 1፥15)

14/12/2023

ክፍል -2 - የዓለሙን ወዷልና ትርጓሜ

ከዚህ በፊት ባለው የፉስቡክ ልጥፍ በዮሐ. 3፡16 ውስጥ የተጠቀሰው “ዓለም” የሚለው ቃል ትርጉም ምን እንደኾነ ለማስረዳት ጥረት አድርጌላሁ። አውዳዊ ትርጉምም እግዚአብሔር ለሰዎች ልጆች በአደራ የሰጠው ፍጥረተ ዓለምን የማስተዳደር፣ የመግዛት ስልጣን ሲኾን ይህ በኋላ ላይ ግን የሰው ልጅ ይህንን የተሰጠውን ስልጣኑን በዳብሎስ የተነጠቀውን የማስተዳደር፣ የግዛት ስልጣኑን የሚያመለክት ነው። እግዚአብሔር አንዲያ ልጁን የሰጠውንም ይህንን ይህንን ለሰዎች ሰጥቶ በዳብሎስ የተነጠቀው ፍጥረት ዓለሙን የማስተዳደር እና ፍጥረተ ዓለሙን እንደ እግዚአብሔር መንግስት ፈቃድ የማስተዳደር ስልጣን በማስመለስ በእግዚአብሔር እና በሰዎች ፍጥረተ ዓለሙን በመግዛት በማስተዳደር ረገድ አንድነት እንዲኖር፣ አንድ ዓላማ እንዲኖር ነው የሚል ሀሳብን በዚህ ልጥፍ ለማካፈል እሞክራለሁ። አስቀድሞ ከእኔ ጋር ለማሰብ፣ ሀሳባችሁክ ለማካፈል ስለወደዳች ለማመስገን እወዳለሁ።

“እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና”

በዮሐ. 3፡16 ላይ እግዚአብሔር ዓለሙን የወደድበትን መንገድ ለመረዳት በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ የእግዚአብሔር መውደድ በምን መንገድ እንደተገለጠ ማወቅ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። በተለይም ዮሐ. 17 ላይ የተገለጸው ሀሳብ ቁልፍ ሚና አለው ብዬ አስባለሁ። እንዲህ ይላል፦
1-2ኢየሱስም ይህን ተናግሮ ወደ ሰማይ ዓኖቹን አነሣና እንዲህ አለ፦ “አባት ሆይ፥ ሰዓቱ ደርሶአል፤ ልጅህ ያከብርህ ዘንድ፥ በሥጋም ሁሉ ላይ ሥልጣን እንደ ሰጠኸው፥ ለሰጠኸው ሁሉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸው ዘንድ ልጅህን አክብረው። 3እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት። 4እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ፤ 5አሁንም፥ አባት ሆይ፥ ዓለም ሳይፈጠር በአንተ ዘንድ በነበረኝ ክብር አንተ በራስህ ዘንድ አክብረኝ። 6ከዓለም ለሰጠኸኝ ሰዎች ስምህን ገለጥሁላቸው። የአንተ ነበሩ ለእኔም ሰጠሃቸው፤ 7ቃልህንም ጠብቀዋል። የሰጠኸኝ ሁሉ ከአንተ እንደ ሆነ አሁን ያውቃሉ፤ 8የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸዋለሁና፤ እነርሱም ተቀበሉት፥ ከአንተም ዘንድ እንደ ወጣሁ በእውነት አወቁ፥ አንተም እንደ ላክኸኝ አመኑ። 9እኔ ስለ እነዚህ እለምናለሁ፤ ስለ ዓለም አልለምንም ስለ ሰጠኸኝ እንጂ፤ የአንተ ናቸውና፤ 10 የእኔም የሆነ ሁሉ የአንተ ነው የአንተውም የእኔ ነው፤ እኔም ስለ እነርሱ ከብሬአለሁ። 11ከዚህም በኋላ በዓለም አይደለሁም፥ እነርሱም በዓለም ናቸው፥ እኔም ወደ አንተ እመጣለሁ። ቅዱስ አባት ሆይ፥ እነዚህን የሰጠኸኝን እንደ እኛ አንድ እንዲሆኑ በስምህ ጠብቃቸው። 12ከእነርሱ ጋር በዓለም ሳለሁ የሰጠኸኝን በስምህ እኔ እጠብቃቸው ነበር፤ ጠበቅኋቸውም መጽሐፉም እንዲፈጸም ከጥፋት ልጅ በቀር ከእነርሱ ማንም አልጠፋም። 13አሁንም ወደ አንተ እመጣለሁ፤ በእነርሱም ዘንድ ደስታዬ የተፈጸመ እንዲሆንላቸው ይህን በዓለም እናገራለሁ። 14እኔ ቃልህን ሰጥቻቸዋለሁ፤ እኔም ከዓለም እንዳይደለሁ ከዓለም አይደሉምና ዓለም ጠላቸው። 15ከክፉ እንድትጠብቃቸው እንጂ ከዓለም እንድታወጣቸው አልለምንም። 16እኔ ከዓለም እንዳይደለሁ ከዓለም አይደሉም። 17በእውነትህ ቀድሳቸው፤ ቃልህ እውነት ነው። 18ወደ ዓለም እንደ ላክኸኝ እንዲሁ እኔ ወደ ዓለም ላክኋቸው፤ ፤ 19እነርሱም ደግሞ በእውነት የተቀደሱ እንዲሆኑ እኔ ራሴን ስለ እነርሱ እቀድሳለሁ። 20-21ሁሉም አንድ ይሆኑ ዘንድ፥ ከቃላቸው የተነሣ በእኔ ስለሚያምኑ ደግሞ እንጂ ስለ እነዚህ ብቻ አልለምንም፤ አንተ እንደ ላክኸኝ ዓለም ያምን ዘንድ፥ አንተ፥ አባት ሆይ፥ በእኔ እንዳለህ እኔም በአንተ፥ እነርሱ ደግሞ በእኛ አንድ ይሆኑ ዘንድ እለምናለሁ። 22-23እኛም አንድ እንደ ሆንን አንድ ይሆኑ ዘንድ፤ እኔም በእነርሱ አንተም በእኔ ስትሆን፥ በአንድ ፍጹማን እንዲሆኑ፥ የሰጠኸኝን ክብር እኔ ሰጥቻቸዋለሁ፤ እንዲሁም ዓለም አንተ እንደ ላክኸኝ በወደድኸኝም መጠን እርሱን እንደ ወደድሃቸው ያውቃል። 24አባት ሆይ፥ ዓለም ሳይፈጠር ስለ ወደድኸኝ የሰጠኸኝን ክብሬን እንዲያዩ እኔ ባለሁበት የሰጠኸኝ እነርሱ ደግሞ ከእኔ ጋር ይሆኑ ዘንድ እወዳለሁ። 25ጻድቅ አባት ሆይ፥ ዓለም አላወቀህም፥ እኔ ግን አወቅሁህ እነዚህም አንተ እንደ ላክኸኝ አወቁ፤ 26 እኔንም የወደድህበት ፍቅር በእነርሱ እንድትሆን እኔም በእነርሱ፥ ስምህም አስታወቅኋቸው አስታውቃቸውማለሁ።”

ይህ ክፍል ከዮሐ. 3፥ ጋርየሚያመሳስሉት ነገሮች እንዳሉት መመልከት ይቻላል፦ (1) የዘላለም ሕይወት (2) የእግዚአብሔር መውደድ። እንዲሁም በዮሐ. 17 አጠቃላይ ሀሳብ መሠረት እግዚአብሔር ኢየሱስን የወደደበት መውድድ የዓላማ፣ የሀሳብ አንድነት የሚያመለክት ነው። የእግዚአብሔር መውደድ የሚያመለክተው በዓላማ፣ በሀሳብ አንድነ መኾንን የሚያመለክት ከኾነ በዮሐ. 3፡16 ላይ ያለው እግዚአብሔር “ዓለምን ስለወደደ” የሚለው ሀረግ ትርጓሜ እግዚአብሔር ከዓለም ጋር በዓላማ፣ በሀሳብ አንድ መኾንን በመፈለጉ ምክንያት አንዲያ ልጁን መስጠቱን ያመለክታል ማለት ነው። ከዚህ በፊት በለጠፍኩት የፌስቡክ ልጥፍ ውስጥ ደግሞ በዮሐ. 3፡16 ላይ የተጠቀሰው “ዓለም” እግዚአብሔር በኤደን ገነት ለአዳም ሰጥቶት የነበረው ነገር ግን በዳብሎስ የተወሰደው ፍጥረተ ዓለሙን የማስተዳደር ግዛት ነው (ሉቃ. 45-6 ጋር ያነጻጽሩ)። ስለዚህ እግዚአብሔር ይህንን በዳብሎስ የተነጠውን በአደራ ለሰው ልጅ ሰጥቶት የነበረውን ግዛቱን በመውደዱ ይህንን ለማስመለስ አንድ ልጁን አሳልፎ ሰጥቷል። ማለትም የእርግዚአብሔር መንግስት አገዛዝ እና ለሰዎች በአዳራ ተሰጥቶ የነበረው ነገር ግን በሴጣን ቁጥጥር ሥር የገባው ፍጥረተ ዓለሙን የመግዛት ስልጣንን ከሴጣን በልጁ ሞት እና ትንሳኤ በመዋጀት የእግዚአብሔር አገዛዝ እና የፍጥረት ዓለሙን የመግዛት ሀሳብ አንድ እንዲኾን ነው።
ይህንን ሀሳብ ይበልጥ የሚያረጋግጠው ደግሞ በዮሐ. 17፥ 6፣ 11፣ 12 እና 26 ላይ የተጠቀሱው “ስምህን ገለጥሁላቸው የሚለው ሀሳብ ነው። ይህ የብሉይ ኪዳን ታርካዊ ዳራ አለው። በብሉይ ኪዳን መጽሐፍት ውስጥ የእግዚአብሔር ስም መገለጥ ከእግዚአብሔር መንግስት መገለጥ ጋር ተመሳሳይ ነው። ለምሳሌ የእግዚአብሔር መንግስት/አገዛዝ ምንነት የዘጸአት መጽሕፍ ጸሐፊ በመጀመሪያ የገለጸው በኹለት ኃይላት መካከል በሚደረግ ፍልሚያ በሚያሳይ ስዕላዊ መግለጫ ነው።
የግብጻዊያንን አማልክት አሸናፎ እስራኤላዊያንን ከባርነት ነጻ ያወጣ ንጉሥ የኾነው ያሕዌ እና በእስራኤል መካከል በተደረገው ቃል ኪዳናዊ ትስስር ውስጥ የእግዚአብሔር መንግስት የተገለጠበትን ኹለተኛ ስዕላዊ መግለጫ እናገኛለን።
እንዲሁም እስራኤላዊያን ወደ ከነዓን ምድር የገቡ ጊዜ የነበረውን ኹኔታም በኹለት ኃይላት መካከል ፍልሚያ እንደነበር እናያለን። በዚህም ሳያበቃ የዳዊት ሥርዎ ንግስት በዳዊት ንግሥና ከመጀመረበት ጊዜ አንስቶ በልጁ በንጉሥ ሰለሞን አማካኝነት ጠላቶቹን ኹሉ ድል እስከ ነሣበት ጊዜ ያለው ታሪክ ደግሞ እግዚአብሔት ከሌሎች ኃይላት ጋር ባደረገው ፍልሚያ ኹሉን ድል በመንሣት አሸናፊ መኾኑን፤ ከዚህም የተነሣ የሰለሞን የንግሥና ዘመን ወርቃማው ዘመን መኾንን እናያለን።
እስቲ እነዚህን ታሪካዊ ክስተቶች በጥልቀት እንመርምርና ጸሐፍቱ ያዩትን መመልከት እንጀምር፤ ክስተቶቸ ኸሉ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት/አገዛዝ የሚያመላክቱ ናቸው።
ምንም እንኳ ስለእግዚአብሔር ንጉሥነት/ ገዥነት የሚያመለክት ሀሳብ በተዘዋዋር መልኩ በዘፍጥረት 1፡26 የሚገኝ ቢኾንም በግልጽ ስለእግዚአብሔር መንግስት ለመጀመሪያ ጊዜ ተጠቅሶ የሚናገኘው በዘጸአት መጽሐፍ ውስጥ ነው።
በዘጸአት መጽሐፍ ውስጥ ስለእግዚአብሔር መንግስት/ንግሥና የቀረበበት መንገድ ከታሪኩ አወቃቀር ጋር ብዙ መልኩ ግንኙነት አለው። በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ስለ እግዚአብሔር አገዛዝ በገልጽ የተጠቀሰው በዘጸ. 15፡18 ላይ እንዲህ በሚል ቃል ነው፦ “እግዚአብሔር ለዘላለሙ እስከ ፍጻሜ ይነግሣል”። ይህም በዚህ መጻሐፍ ውስጥ የተዘረዘረው ታርክ የመጨረሻ ግብ መመልከት ይቻላል። ይህንንም ለመረዳት የእግዚአብሔርን ንግሥና የተጠቀሰበትን ክፍል ሥነ-ጽሑፋዊ አውድ መመርመር ይጠቅማል።

የዘጸአት ታሪክ አጠቃላይ የታሪክ ፍሰቱ መሠረቱ የእግዚአብሔር ሥም የተገለጠበት ክስተት ነው (ዘጸ። 3፡14 ይመልከቱ)። ታርኩም የእግዚአብሔር ስም ከተገለጠብ ጊዜ ተነስቶ የታሪኩ ፍሰት የጡዘት ጫፍ ወደ ኾነው የእግዚአብሔር መንግስት/ አገዛዝ ወይም ንጉሥነት መገለጥ ላይ ይደረሳል (ዘጸ. 15፡18 ይመልከቱ)። ይህም በእግዚአብሔር ስም እና በእግዚአብሔር መንግስት/ንጉሥነቱ ጥብቅ ቁርኝነት መኖሩን አመለካች ነው። የእግዚአብሔር ስም መገለጥ ስለ መጪው የእግዚአብሔር አገዛዝ ዘመን የሚነገር ነገር አለውና። እግዚአብሔር በእስራኤላዊያን ታርክ ውስጥ የሚያደርገውን ጣልቃ ገብነት ምን እንደሚመስል የተገለጠው በዋናነት በእግዚአብሔር ስም አማካኝነት ነው። የእግዚአብሔር ጣልቃ ገብነት ኹለት ገጽታዎች አሉት፡ አንደኛው መንፈሳዊ እና የማይታይ ሲኾን፤ ኹለተኛው ወታደራዊ እና የሚታይ ነው። ይህ ኹለት ገጽታ ያለው ጦርነት እግዚአብሔር እስራኤላዊያን ከግብጽ ምድር ነጻ ባዋጣበት ታሪክ ውስጥ በግልጽ ይታያል። እግዚአብሔር በእነርሱ ፈንታ ተዋግቶ ከባርነት ነጻ አወጣቸው። ስለዚህም እስራኤለዊያንም ከግብጽ ምድር ባርነት ነጻ ከወጡ በኋላ በዘጸ. 15፥18 ላይ “እግዚአብሔር ለዘላለሙ እስከ ፍጻሜ ይነግሣል” ብለው አዜሙለት። ይህም የዘጸአት መጽሐፍ በአጠቃላይ ከምዕራፍ ሦስት አንስቶ እስከ 15፥18 ድረስ ያለው እግዚአብሔርን እንዴት እስራኤላዊያን ባሪያ አድርጎ የገዛቸውን ጠላት በማሸነፍ እንዴት ንጉሣቸው እንደኾነ የተገለጠበት ኾኖ እናገኘዋለን። ስለዚህ ከዘጸ. 15፡18 በፊት የተጻፈው ኹሉ እግዚአብሔር ለእስራኤላዊያን እንዴት ንጉሣቸው ሊኾን እንደቻለ ለማብራራት ነው።

ስለዚህ በዮሐ. 17 ላይ ኢየሱስ የገለጠላቸው ስም የእግዚአብሔር መንግስት ነው። ይህንን ስም ወይም የእግዚአብሔር መንግስት ማወቅ የዘላለም ሕይወት ነው። እግዚአብሔርም ልጁን የላከበት ዋነኛ ዓላማ በዮሐ. 17፥26 ላይ የተገለጸው “እኔንም የወደድህበት ፍቅር በእነርሱ እንድትሆን እኔም በእነርሱ፥ ስምህም አስታወቅኋቸው አስታውቃቸውማለሁ።” እግዚአብሔር ከኢየሱስ ጋር በሀሳብ፣ በዓላማ አንድ እንደኾነ ኹሉ ኢየሱስን ከሚያምኑት ጋር በሀሳብ፣ በዓላማ አንድ እንዲኾኑ ነው። ማለትም የሰው ልጅ በሴጣን የተነጠቀውን ፍጥረት የመግዛት ስልጣን ከሴጣን እጅ ቀምቶ ሊሰጠው እግዚአብሔር መንግስት እና ሰዎች ፍጥረተ ዓለሙን በእርሱ ፈንታ፣ እንደ እርሱ ኾነው፣ እንደ እርሱ ዓላማ እና ሀሳብ እንዲገዙ፣ የሰማዩ መንግስት እና የምድሩ መንግስት አንድ እንዲኾኑ ወደድዶ ልጁን አሳልፎ ሰጥቶታል።
እኛም “መንግስት በሰማይ እንደኾነች እንዲሁ በምድር ትሁን” እንላለን።

ክፍል አንድ፡ የ”ዓለም” አውዳዊ ትርጓሜመዝገበ ቃላዊ ፍችκόσμος, ου, ὁ ① that which serves to beautify through decoration, adornment, adornin...
12/12/2023

ክፍል አንድ፡ የ”ዓለም” አውዳዊ ትርጓሜ
መዝገበ ቃላዊ ፍች
κόσμος, ου, ὁ
① that which serves to beautify through decoration, adornment, adorning
② condition of orderliness, orderly arrangement, order
③ the sum total of everything here and now, the world, the (orderly) universe
④ the sum total of all beings above the level of the animals, the world
⑤ planet earth as a place of inhabitation, the world
ⓐ Land
ⓑ the world as the habitation of humanity
ⓒ earth, world in contrast to heaven
ⓓ the world outside in contrast to one’s home
⑥ humanity in general, the world
ⓐ humanity in general
ⓑ of all humanity, but especially of believers
⑦ the system of human existence in its many aspects, the world
ⓐ as scene of earthly joys, possessions, cares, sufferings
ⓑ the world, and everything that belongs to it, appears as that which is hostile to God, i.e. lost in sin, wholly at odds with anything divine, ruined and depraved
⑧ collective aspect of an entity, totality, sum total
William Arndt et al., A Greek-English Lexicon of the New Testament and Other Early Christian Literature (Chicago: University of Chicago Press, 2000), 561–563.

በዮሐ. 3፡16 ላይ “ዓለም” ተብሎ የተተረጎመው ቃል κόσμος ከስምንት በላይ ትርጓሜዎች ሲኖሩት በብዙ ወንጌላዊያን አማኞች እና በሥነ-መለኮት ምሁራን ዘንድ ለአውዱ ተስማሚ ተደርጎ የሚወሰደው በስድስተኛው ተራ ቁጥር ላይ ያለው “የሰው ልጆች” ወይን “ አማኞች”የሚል ያለው ትርጓሜው ነው። እኔ ለምን ይህ ትርጉም ተመራጭ ኾነ? የሚል ጥያቄ አነሳለሁ። ከአማራጭ ትርጓሜዎቹ መካከል የቃሉ ትርጉም ይህ መኾን እንዳለበት የሚጠቁመን ምን ነገር አለ? ብዬ እጠይቃለሁ። እስካሁን ድረስ በዚህ አውድ ውስጥ የቃሉ አውዳዊ ትርጓሜ “የሰው ልጅ” ወይም “አማኞችን” የሚል እንደኾነ የሚያሳይ ሥነ-ጽሑፋዊ፣ ታርካዊ፣ ባሕላዊ እና ማህበረሰባዊ አውዳዊ አላየሁም። ይልቁንም በተራ ቁጥር 7 ላይ የተጠቀሰው የቃሉ ትርጓሜ በኀጢአት ምክንያት ከእግዚአብሔር ጋር የተቃቃረውን ዓለምን እና በውስጡ ያሉትን ኹሉ የሚያመለክት ይመስለኛል።
ምክንያት አንድ፡ ይህ ቃል የተነገረው ኒቆዲሞስ የተባለው የአይሁድ መምህር “ከእግዚአብሔር ዘንድ የመጣህ መምህር እንደ ሆንክ እናውቃለን” አለው።“ በማለት ለጠየቀው ጥያቄ ኢየሱስ በሰጠው መልስ ውስጥ ነው። ኢየሱስ በሰጠው መልስ ውስጥም “የእግዚአብሔር መንግስት” ጉዳይ ተነሥቷል። ይህ የእግዘዚአብሔር መንግስተ ርዕሰ ጉዳይ ደግሞ በመጥመቁ ዮሐንስ እንዲሁም በኢየሱስ የተሰበከ እንዲሁም ኢየሱስ ወደዚህች ምድር ይዟት የመጣች መኾኗን ከተመሳሳይ ወንጌላት ንባባችን እንረዳለን። የእግዚአብሔር መንግስት ማለት እግዚአብሔር ንጉሥ፣ ገዥ ኾኖ የሚያስተዳድርበት ማለት ነው። የኒቆዲሞስም ጥያቄ ወደዚህ መንግስት መግብት እንዴት ይቻላል ነው። የኢየሱስም መልስ - ‘ሰው እንደገና ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም” የሚል ነው። ኢየሲስ በመቀጠል ኢየሱስ የእግዚአብሔርን መንግስት የሚመሠርትበትን መንገድ ይነግረዋል፤ ይኼውም 14“ሙሴ በበረሓ እባብን ከፍ አድርጎ እንደ ሰቀለ እንዲሁም የሰው ልጅ ከፍ ብሎ ሊሰቀል ይገባዋል” ማለትም በዋጆዋዊ ሥራው ነው። ኢየሱስ በዋጆዋዊ ሥራው የዘላለም ሕይወት የሚገኝበትን መንገድ እንደሚያዘጋጅ መናገሩን ልብ ይለዋል። የኒቆዲሞስ ጥያቄ ወደ እግዚአብሔርን መንግስትን እንዴት መግባት ይቻላል ሲኾን የኢየሱስ መልስ ደግሞ የሰው ልጅ በኾነው በኢየሱስ ሞት የዘላለም ሕይወት ማግኛ መንገድ ይዘጋጃል የሚል ነው። ስለዚህ በዘላለም ሕይወት ማግኘት እና ወደ እግዚአብሔር መንግስት መግባት ተመሳሳይ ሀሳብ ናቸው ማለት ነው። ነገሩ እንዲህ ከኾነ ገና ከጀምሬው አንስቶ የእግዚአብሔር መንግስት/ አገዛዝ በምድር ላይ እንዲኾን የእግዚአብሔር ፈቃድ እንደኾነ የዘፍጥት መጽሐፍ ይነግረናል። የሰው ልጅን “በመልኩ እና በምሳሌው” አድርጎ መፍጠሩም ለዚሁ ዓላማ ነው። የሰው ልጅ በእግዚአብሔር መልክ እና ምሳሌ ተፈጠረ ማለት በእግዚአብሔር ፈንታ የእግዚአብሔር አገዛዝን ገዥ ኾኖ እንዲያስተዳድር የተፈጠረ ነው ማለት ነው። ለዚህ ማስረጃው አንደኛው በዚያ ዘመን ነገሥታት አንድን አከባቢ በጦርነት ከተቆጣጠሩ በኀላ ያ ግዛት የእነርሱ መኾኑን ለማሳየት መልካቸውን እና ምሳሌያቸውን የሚያሳይ ሀውልት ያቆሙ ነበር፤ ግዛቴ ነው ለማለት። እንዲሁም በዚያ ዘመን ነገሥት የአማልክቶቻቸው ወኪሎች ኾነው ምድራቸውን ያስተዳድራሉ የሚል እምነት ነበር። ለዚህም እስራኤላዊያን በዙሪያቸው ካሉ ነገሥታት ጋር ተዋግተው ሲያሸንፉ አምላካችን እግዚአብሔር አሸነፈ የጠላቶቻችል አማልክት ተሸነፉ የሚሉት። እንዲሁም እስራኤላዊያን በጦርነት ሲሸነፉ ጠላቶቻቸውን አማልክቶቻችን የእስራኤልን አምላክ አሸነፉ የሚሉት። ስለዚህ ነገሥታት የአማልክቶቻች መልኮች ናቸው፤ የአማልክቶቻቸው ልጆች ነው። በተመሳሳይ መልኩም የሰው ልጅ የእግዚአብሔር ወከል ኾኖ የእግዚአብሔር ፍጥረትን እንዲገዛ ተፈጠረ፤ የእግዚአብሔር ልጅ ኾነ። ይሁን እንጂ የሰው ልጅ የተሰጠውን ውኪልና መወጣት አልቻለም። የእግዚአብሔርን ፍጥረት በውኪልና ለማስተዳደር ስልጣን በሴጣን ተቀማ። ከዚህም የተነሣ ሴጣን የዚህ ምድር ገዥ ኾነ። እግዚአብሔርም በዘመን መጨረሻ አንድ ልጁን ልኮ በሴጣን የተቀማውን ግዛቱን አስመለሰ። ስለዚህ በዚህ አውድ ውስጥ κόσμος “ዓለም” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የእግዚአብሔር ግዛት የነበረው፣ ለሰው ልጅ ያስተዳድር ዘንድ የተሰጠው የእግዚአብሔር ግዛት (ፍጥረትን ኹሉ ያካትታል፥ ሰውንም ጨምሮ) ነገር ግን በሴጣን ተቀሚቶ የነበረው ግዛት ያመለከትታል። በመኾኑም የቃሉ ትርጉም የሰው ልጅ ሳይኾን በኀጢአት ምክንያት ከእግዚአብሔር ጋር ተቃቅሮ የነበረው ፍጥረት ዓለሙን ያመለክታል። እግዚአብሔር አንድ ልጁን የመላኩ ምክንያት ግዛቱን ለማስመለስ፣ ከእርሱ ጋር ተቃቅሮ የነበረው ፍጥረተ ዓለሙን ለመዋጀት ነው። ይህንን ያደረገው ለፍጥረት ዓለሙ፣ ግዛቱን ከመውደዱ የተነሣ ነው - እግዚአብሔር “ዓለምን ስለ ወደደ” ይላልና።ዓለምን ወደደ ማለት ግን ምን ማለት ነው? እመለስበታለሁ።

በትክክል አለመረዳቴን አወቅኩትአንዳንዴ ደጋግመን ከመናገራችን፣ ቃላቱን በአእምሮዋችን ከመያዛችን የተነሣ ትርጉማቸውን የሚናውቅ የሚመስለን ግን የማናውቃቸው ብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች አሉ። ...
10/12/2023

በትክክል አለመረዳቴን አወቅኩት

አንዳንዴ ደጋግመን ከመናገራችን፣ ቃላቱን በአእምሮዋችን ከመያዛችን የተነሣ ትርጉማቸውን የሚናውቅ የሚመስለን ግን የማናውቃቸው ብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች አሉ። ከእነርሱ መካከል አንዱ ዮሐ. 3፡16 ይመስለኛል። ቢያንስ እኔ ዛሬ ምሽት አለማወቄን አውቄያለሁ!

Enacted Eschatology
07/12/2023

Enacted Eschatology

05/12/2023

ማቴ 12፡ 38 “ከዚያም አንዳንድ የአይሁድ ሃይማኖት መምህራንና ፈሪሳውያን፣ “መምህር ሆይ፤ ከአንተ ታምራዊ ምልክት ማየት እንፈልጋለን” አሉት፝
የአይሁድ መምህራን ወደ ኢየሱስ ቀርበው እርሱ ሲጠብቁት የነበረው መስሕ መኾኑን፣ የእግዚአብሔርን መንግስት ይዞ የመጣው እርሱ መኾኑን የሚያረጋግጥ “ታምራዊ ምልክት”ን ያሳያቸው ዘንድ ጠየቁት።
የጠየቁት ምልክት በዘመናት መካከል የእግዚአብሔር መንግስት፣ አገዛዝ፣ ኃይል እስራኤላዊያን ለመታደግ በመጣች ጊዜ የተመለከቱትን ዓይነት ምልክት ነው። ታዲያ በጥንቱ ዘመን የእግዚአብሔር መንግስት፣ አገዛዝ ሲትመጣ ለእስራኤላዊያን መታደግ፣ ነጻ መውጣት ምልክት ሲትኾን ለጠላቶቻቸው ግን ቅጣት እና ጥፋት ምክንያት የኾነች ምልክት ናት። ስለዚህ ጥያቄያቸው ለእስራኤል የመዳን፤ ለአሕዛብ ደግሞ የመጥፋት ዘመን መምጣቱን የሚያሳይ “ታምራዊ ምልክትን” አሳየን የሚለው ነው።
በማቴ. 12፡38-48 ውስጥ በትክክል እንደተገለጸው ኢየሱስ ግን ለአይሁድ መምህራን የመለሰላቸው መልስ እናንተ ከንሰሓ ይልቅ ልባችኹን ስላደነደናችሁ የእግዚአብሔርን መንግሰት መምጣቷ ምልክት ይሰጣችኳል። ነገር ግን እንደ ቀድሞ ዘመን ለእስራኤል ድነትን፣ ነጻ መውጣትን የሚያመለክት ምልክት ሳይኾን ቅጣትን፣ ፍርድን የሚያመለክት ምልክት ነው። ይህ ፍርድ ደግሞ በብሉይ ኪዳን ዘንድ እግዚአብሔር የአሕዛብ ነገሥታትን የቀጣበት ፍርድ ጋር ተመሳሳይ ነው።
ስለዚህ በዚህ ክፍል ውስጥ የተገለጠው የዮናስ ምልክት - በእስራኤል ላይ ፍርድ መምጣቱን የሚያመልክት ምልክት ነው።

ለእኛም እንዲኹ ይመስለኛል ምክንያቱም ያለንሰሓ፣ ያለ መመለስ መታደስን ስለምንናፍቅ!

10/06/2023

የአስትንተኖ ተከታታይ ማብራሪያ፦
የሉቃስ ወንጌል ጥራዝ 1
እና ትንብተ ሚክያስ
እስካሁን 8 ማብራሪያዎች ተጀምረዋል!!!!!!

Address

Addis Ababa

Telephone

+251913518234

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Onesimus Publisher posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Onesimus Publisher:

Share

Category