17/05/2022
** ኤልሳቤት ቦርን የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ **
ኤልሳቤት ቦርን በ30 አመታት ውስጥ የመጀመሪየዋ የፈረንሳይ ሴት ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን በፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ተሾመዋል፡፡ በሀገሪቱ የሰራተኛ ሚኒስትር የነበሩት ኤልሳቤት ቦርን÷ የ61 አመቱን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዣን ካስቴክስን ተክተው የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚንስትር ሆነው መሾማቸው ተሰምቷል፡፡
ተሰናባቹ የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዣን ካስቴክስ የፕሬዚዳንት ማክሮን ዳግም መመረጥን ተከትሎ ለአዲሱ መንግስት የለውጥ አካል ለመሆን በሚል ስልጣናቸውን በገዛ ፈቃዳቸው መልቀቃቸውን አናዶሉ ዘግቧል፡:
Via Fana