15/06/2020
የሪከርድ ሰበራ ሰበር ዜና።
*~★★~*
• የፌስቡክ ባለቤት ጋሽ ማርቆስን እግዚአብሔር ይስጠው። ገፍቶ ገፍቶ ፈረንካ ላይ ጣለኝ እኮ። ሸሩን ትተህ በፌስቡክም አድርግልኝማ።
| ~ ይሄንንም በምስጋና ልጀምር !!
• "ጌታ ሆይ! ከዚህ በፊት በሆነው፤ አሁንም እየሆነ ባለው እና ወደፊትም በሚሆነው ነገር ፤ ክብሩን ሁሉ አንተ ውሰድ።" አሜን !
"ድንግል ሆይ እናቴ ! አዛኝቱም አማላጂቱም ሆይ! ዛሬም እንደትናንቱ ቅደሚ ከፊት ከኋላዬ።" አሜን።
•••
እኔ ዘመዴ ዘመዳችሁ ስመ ጥምቀቴ አክሊለ ገብርኤል የድንግል አሽከር የአምላኬ የልዑል እግዚአብሔር ባርያ ኃጥእ አገልጋይ ልጁም የምሆን እኔ ዛሬም ሳይገባኝ አዲስ ሪከርድ መስበሬ ተነግሮኛል። ክብር ለመድኃኔዓለም ይሁን። አሜን።
•••
ታስታውሱ እንደሆን ባለፈው ጊዜ 200 ሺ ሰው ለሚፈልገው“ ማዕዶት ዘ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የትናንቱን ለነገ ማኅበራችን የቴሌግራም ግሩፕ ይሆኑ ዘንድ ለባለ ማዕተቦቹ ባቀረብኩት ጥሪ መሠረት በ36 ሰዓታት ውስጥ የሚፈለገው የሰው ብዛት ተሟልቶ እኛን እጃችንን በአፋችን አስጭኖ ሀገር ምድሩን ደግሞ ጉድ ማሰኘቱ ይታወሳል። ሪከርድም ነበር የሰበርነው።
•••
ዛሬ ደግሞ ወደ ዩቲዩብ መንደር መጥተን ያን የተለመደ 36 ሰዓት ሪከርድ ደግመነዋል። ③⑥ ቁጥር ተደጋገመብንሳ? ሠላሳ ስድስቱ ቅዱሳት አነስትን አስታወሰኝ።
① ዩቲዩብ ለመሥራት፣ ቀጥታ ለመቀረጽ የሚያስፈልገውን 1ሺ ሰብስክራይበርስ የዩቲዩብ ቻናሌን አክቲቭ ባደረግኩ በ4 ደቂቃ ውስጥ የተባለውን ቁጥር አሟልተን ሪከርዱን ሰብረናል።
https://www.youtube.com/c/ZemedkunBekele?sub_confirmation=1
② ዩቲዩብ ክፍያ ለመፈጸም የሚጠይቀውን የ4ሺ ሰዓት፣ የ240,000 ሺ መመሪያም በ36 ሰዓታት ውስጥ አሟልተን የዩቲዩብ ተከፋይ ለመሆን ማረጋገጫ አግኝተናል። ይሄም ሪከርድ ነው። https://www.youtube.com/c/ZemedkunBekele?sub_confirmation=1
③ አሁን ዩቲዩብ 30,200 ሰብስክራይበርስ ወዳጆች እንዳገኘሁ ነግሮኛል። በአንድ የ34 ደቂቃ ቪድዮ 4099 ሰዓት ወይም 240,000 ሺ ደቂቃ የዕይታ ሰዓት ማሟላቴን አረጋግጦልኛል። በቀጣይ የተላከልኝን ፎርምም ሞልቼ ለዩቲዩብ ልኬአለሁ። አሁን ለእኔ ለዘመዴ የዩቲዩብ ካምፓኒ ቀጥታ ክፍያ ይፈጽምልኛል ማለት ነው። አከተመ።
https://www.youtube.com/c/ZemedkunBekele?sub_confirmation=1
★ ከዚህ በኋላ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በሀገረ ጀርመን የራሴን ቤት ተከራይቼ ከስደተኝነት ጡረታ እገላገላለሁ ማለት ነው። ቢያንስ ቢያንስ በጀርመን የገዛሁትን ቴሌቭዥን ከፍቼ አያለሁ ማለት ነው። ጉድ እኮ ነው እንናንተው። አሁን እንዲህ ስል ማን ያምነኛል? ሆኦ። በጀርመን ትለኝ እኮ ይሆናል? አዎ በጀርመን።
•••
በቀጣይ ያሉኝን ዕቅዶቼን እንደሚከተለው እገልጻለሁ።
፩ኛ፥ • 592,318 ወዳጆችና ጎዶኞች ያፈራሁበት ፌስቡኬም እንዳለ ነው። ተጠናክሮም ይቀጥላል።
፪ኛ፥ • 120.2k ወዳጆችና ጎዶኞች ያፈራሁበት የቴሌግራም ቻናሌም እንዳለ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
፫ኛ፥ • 25.3k ወዳጆችና ጎዶኞች ያፈራሁበት የቴሌግራም ቻናሌም እንዳለ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
• ዌብሳይቴም ዋነኛውን ሥራ እንደ አዲስይሠራል። ወደፊት ራሱ የፌስቡክ ካምፓኒው በራሱ ችግር ቢዘጋ እንኳ ዌብሳይቴ ፌስቡክን ተክቶ ይሠራል ማለት ነው። ይቀጥላል።
• አሁን 30ሺ ወዳጆችን ያፈራው የዩቲዩብ ቻናሌም ወደፊት በከፍተኛ ዝግጅትና ጥራት በብዙ ዐዋቂዎች እየታገዘና ብዙ ባለሙያዎችን እያሳተፈ በጋራ እየሠራን የምናገኘውንም በጋራ እየተካፈልን ቻናሌ የሁላችንም ሆኖ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
•••
ለዩቲዩብ ሥራዬ የሚያስፈልጉኝን ማቴሪያሎች በተመለከተ።
① የእያንዳንዳቸው ዋጋ 3ሺ ዶላር የሆኑ ሁለት ኮምፒዩተሮች ያስፈልጉኝ ነበር። ይሄንንም በቀደም ተናግሬ ነበር። እናም ሁለቱም ላፕቶፖች ከመቅጽበተ ዓይን አይኔን ጨፍኜ ሳልገልጥ በማላውቃቸው ወዳጆቼ ተሟልተውልኛል። አይ ወላዲተ አምላክ እናቴ። ትቀድሚልኛለሽ እኮ ከፊት ከኋላዬ።
• አንዱ ላፕቶፕ ፌስቡክ ከጀመርኩ ዕለት አንስቶ ለሚረዳኝ ሀገር ቤት ላለው የአይቲ ቲሞቼ የሚያስፈልግ ሲሆን እሱን አንድ ባለማዕተብ ባለተስፋ ወዳጄ 3 ሺ ዶላር አውጥተው እንደሚያስረክቡኝ ቃልገብተውልኛል። ሁለተኛዎቹ የዱባይና የአማሪካ የአይቲ ቲሞቼ አይፈልጉም። እሱም ተሳክቷል።
• ሌላኛው ለእኔ የሚያስፈልገኝ ላፕቶፕ ሲሆን እሱን ደግሞ አማሪካ ያሉት እስከአሁን የስልክ ካርድ የሚሞሉልኝ ወዳጆቼ እነ ሀረግ፣ እነ ቲጂ፣ እነ አህመዲን ሱሌይማን አብርሽ ወንድሜ፣ ይገዙልኝ ዘንድ ተፈርዶባቸዋል። ከምር ማስታወሻውን ለእነሱ ሰጥቻለሁ። አለቀ። ሰሞኑንም ይደርሰኛል። እረከበዋለሁም።
② ካሜራ ነው።
• እውነትና ሩት የሚባሉ በሀገረ ኖርዌይ የሚኖሩ ባለ ማዕተብ እህቶች ዋጋውን ንገረንና እኛ ነን የምንገዛው ብለው ፈጥርቀው ይዘውኛል። አሁን ይሄን እየጻፍኩ ሁላ እውነት የምትባለው እህት ደውላ ከካሜራው ጋር አብረው ያሉትን ማይክራፎኖችም ጥሩ የሚባለውን አብረን ነው የምንገዛው ብለውኛል። በአንድ አፍ ብያለሁ። ቀልድ የለም።
③ የሞባይል ስልክ
• ሌላው የሚያስፈልገኝ የእጅ ስልክ ነው። ካሜራው ግሩም የሆነ የሞባይል ስልክ ነው የሚያስፈልገኝ። እኔ ደግሞ የሳምሰንግ ወዳጅ ነኝ። እናም አንድ ሳምሰንግ ስልክ እፈልጋለሁ ማለት ነው። ከራየን ወንዝ ዳር ሆኜ እየተቀረጽኩ የምበጠረቅበት ስልክ ያስፈልገኛል።
• በፊት ጊዜ ወዳጄና የሐገር ልጅ ደሩ ዘሀረሩና የዛሬን አያድርገውና ዮኒማኛ ሁለቱ እኛው ነን የምንገዛልህ ብለው ነበር። ያው ዮኒ ባርቆብኛል የቀረው ደሩ የሀገሬ ልጅ ነው ከእሱ ጋር አወራለሁ ማለት ነው። ኤትአባቱንስና አስተፋዋለሁ።
•••
200 ሺ የማዕዶት ቤተሰብ ሰብስክራይብ ካደረገኝ፣ 600 ሺው የፌስቡክ ወዳጆቼ ሰብስክራይብ ካደረጉኝ፣ በቅርቡ 1 ሚልዮን ሰብስክራይበር ይኖረኛል ማለት ነው።
• እውነት ከምሬ ነው የዩቲዩብን መንደር አሳምረን እንቀይረዋለን። ውብ እናደርገዋለን። ከዚያ በሚገኘው ገንዘብም በሁሉ ሰው ፊት የባለማዕተቦችን ህይወት እንቀይርበታለን። ታሪክም ተዓምርም እንሠራለን። ዩቲዩብን ወደ ቴሌቭዥን ቻናል የመንደርደሪያ ሜዳ እናደርገዋለን። ቱ ምን አለ ዘመዴ በሉኝ።
•••
ዩቲዩብን በተመለከተ ሌላ ዕቅድም አለኝ።
• በፀረ ተሃድሶ ትግሉ ላይ ዓይነተኛ ሚና የነበራቸውን መምህራንና ዘማርያን ፔጆችን እየመረጥኩ ከያሉበት ለቅሜ ሁላችንም ባለማዕተቦች ሰብስክራይብ የምናደርግበትን የዘመቻ ቀንም አዘጋጃለሁ። የእነ ማንን እንደማስደርግ ግን እኔው ራሴ አውቀዋለሁ። ወትዋች፣ ጎትጓችም አያስፈልገኝም። አለቀ። ደግሞስ ፈረንጅ ለሚከፍለው ዶላር የምን ምቀኝነት ነው። እንዲያውም ተመካክረን፣ ተጠቃቅሰን፣ ተረዳድተን፣ በጋራም ተካፍለን እንበላለን። ኦርቶዶክሳውያን ምቀኝነትን፣ ሸርን፣ አስወግደን በመደጋገፍ በኢኮኖሚም እንፈረጥማለን። ይሄ ግን የራበውን መንገደኛ ጆቢራ ግን አይመለከትም። አለቀ።
•••
ካነሰ እያየሁ እጨምራለሁ።
•••
ሻሎም ! ሰላም !
ዘመድኩን በቀለ ነኝ።
ሰኔ 8/2012 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ።