Central Hotel Bensa Daye

Central Hotel Bensa Daye EBC ODOO Sidaamu Afoo Facebookete Qoola Hawalle Keerunni Daggini!!
(1)

ዓለማችን በእለቱአሜሪካ አሜሪካ በኒዮርክ እና አንዳንድ የሀገሪቱ ከተሞች   ቲክቶክን በመንግስት  ኮምፒዩተሮች አገልግሎት ላይ እንዳይውል ገደብ ጣለች።ቲክቶክ በመንግሥት መገልገያ ኮምፒዩተሮች...
19/08/2023

ዓለማችን በእለቱ

አሜሪካ

አሜሪካ በኒዮርክ እና አንዳንድ የሀገሪቱ ከተሞች ቲክቶክን በመንግስት ኮምፒዩተሮች አገልግሎት ላይ እንዳይውል ገደብ ጣለች።

ቲክቶክ በመንግሥት መገልገያ ኮምፒዩተሮች ላይ አገልግሎት ላይ እንዳይውል ያገደችው ኒዮርክ ከደህንነት ሥጋት ጋር በተያየዛ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።

ኢሲያ

ህንድ አንዳንድ የሩዝ ምርት ከሀገር ውጭ መላክን አገደች

ምክንያት ደግሞ የእህል ዋጋ ንረት፣የዋጋ ግሽበትና የሩዝ ምርት እጥረት እንዳይገጥማት በመሥጋት መሆኑን አልጀዚራ ዘግቧል።

በዓለማችን ሩዝ በመላክ ቀዳሚ የሆነችው ህንድ የሩዝ ምርት ወደ ወጭ መላክ መቆሟን ተከትሎ በዓለም የሩዝ ዋጋ ጣራ ነክቷል ተብሏል።

መካከለኛ ምስራቅ

በጋዘ ሰርጥ የሚኖሩ 9 ፍልስጤማዊያን ሴቶች ታሪካቸውን ፣ ባህላቸውንና ቅርሳቸውን ለመጠበቅና ለማቆየት ያለ ድካም ይሰራሉ።

በበጎ ፈቃደኝነት ሥራውን የሚከውኑት ሴቶቹ የቆዩ መጽሃፍትን ወደ ዲጂታል በመቀየር ለተመራማሪዎች ምቹ ሁኔታ ይፈጥራልም ብለዋል

አዎሮፓ

ዴንማርክ እና ደች ለዩክሬን ኤፍ 16 የጦር ጀት ድጋፍ አደረጉ
ድጋፉ ለዩክሬን እንዲተላለፍ አሜርካ መፍቀዱን ቢቢሲ ዘግቧል።

የዩክሬኑ ፕሬዝደንት ቭላድምር ዞለንስክ ለተደረገላቸው ድጋፍ አመሥግነው ፣ከራሺያ የሚመጣባቸውን ጦር ለመመከት እንደሚረዳቸው ተናግረዋል።

አፍርካ

የብሪክስ አባል ሀገራት በሚቀጥለው ሳምንት በደቡብ አፍሪካ ጉባኤ ያካሄዳሉ ተባለ ።

በጉባኤው አዳዲስ አባል ሀገራት እንደሚሳተፉ የተጠቆመ ሲሆን የተቋሙ መመሥረት ከምእራባዊያን ጫና ለመላቀቅ ፋይዳው ትልቅ እንደሆነ ስነገርለት ቆይቷል።

በጉባኤው የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድምር ፑቲን እንደማይሳተፉ እየተነገረ ይገኛል። ምክንያቱ ደግሞ በዩክሬን ጦርነት ፈጽመውታል በተባለው የሰብኣዊ ወንጀል የሥር ማዘዣ ስለወጣባቸው ነው ተብሏል።

ደቡብ አፍርካ ከአፓርታይድ ነጻ እንዲትወጣ የያኔዋ የሶቭየት ህብረት የአሁኗ ሩሲያ የማይተካ ሚና መጨዎቱዋን አፍሪካ ኒውስ ዘግቧል

ምክር ቤቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አፀደቀየኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ስብሰባ የቀረበለትን የአስቸኳይ ጊዜ ረቂቅ አዋጅ በአብላጫ ድምፅ...
14/08/2023

ምክር ቤቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አፀደቀ

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ስብሰባ የቀረበለትን የአስቸኳይ ጊዜ ረቂቅ አዋጅ በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል፡፡

14/08/2023

Spoortete Odoo

የአረንጓዴ አሻራ መርሐ -ግብር ለውሃ ሃብት ጥበቃ ካለው ፋይዳ አኳያ ሀገራት ሊተገብሩት እንደሚገባ ተጠቆመኢትዮጵያ እያካሄደችው ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ለዘላቂ የውሃ ጥበቃ ካለው...
14/08/2023

የአረንጓዴ አሻራ መርሐ -ግብር ለውሃ ሃብት ጥበቃ ካለው ፋይዳ አኳያ ሀገራት ሊተገብሩት እንደሚገባ ተጠቆመ

ኢትዮጵያ እያካሄደችው ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ለዘላቂ የውሃ ጥበቃ ካለው ፋይዳ አኳያ ሀገራት በአርዓያነት ወስደው ሊተገብሩት እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) ገለፁ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) እንደተናገሩት ፥ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ እየተተገበረ ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ለዘላቂ ውሃ ሀብት ጥበቃ ከፍተኛ ፋይዳ አለው።

የሚተከሉ ችግኞች ከአካባቢ ጥበቃ ፋይዳቸው ባሻገር ምንጮች እንዲጎለብቱ እና ለወንዞች ፍሰት መጨመር ጉልህ ሚና እንዳለው ጠቅሰው ፥ ይህም ከኢትዮጵያ አልፎ ለሌሎች ሀገራትም ፋይዳው የላቀ ነው ብለዋል።

በአጠቃላይ መርሐ ግብሩ ለአየር ንብረት ለውጥ መቋቋምና ለውሃ ሀብት ጥበቃ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ጠቅሰው፤ ሌሎች ሀገራት በአርዓያት ሊወስዱት እና ሊተገብሩት እንደሚገባ ተናግረዋል።

ሚኒስቴሩ ከተቋማት ጋር በመተባበር የውሃ ሀብት ጥበቃ ስራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችሉ የጥናትና ምርምር ስራዎች ላይ እየሰራ መሆኑንም ነው ያነሱት።

ኢትዮጵያ በመጀመሪያው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር 25 ቢሊየን ችግኝ መትከሏ ይታወቃል።

በሁለተኛው ምዕራፍም 25 ቢሊየን ችግኞች ለመትከል የታቀደ ሲሆን ፥ ከዚህ ውስጥ በዘንድሮው ክረምት ከ 6 ነጥብ 5 ቢሊየን በላይ ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ የዘገበው ኢዜአ

ሕጋዊ እርምጃ መውሰድ ተጀመረበአዲስ አባባ የግብረ-ሰዶም ተግባር በሚፈጸምባቸው ተቋማት ላይ እርምጃ መውሰድ እንደተጀመረ ተገለፀ።እርምጃውን የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ...
10/08/2023

ሕጋዊ እርምጃ መውሰድ ተጀመረ

በአዲስ አባባ የግብረ-ሰዶም ተግባር በሚፈጸምባቸው ተቋማት ላይ እርምጃ መውሰድ እንደተጀመረ ተገለፀ።

እርምጃውን የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በመተባበር እየወሰዱ ነው ተብሏል።

እርምጃ እየተወሰደባቸው ያሉት ሆቴሎች፣ ባሮችና ሬስቶራንቶች መሆናቸው ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ፤ ከነባሩ የሀገሪቷ ባህል፣ ወግ፣ የአኗኗር ስርዓት እና ኃይማኖቶች ባፈነገጠ መልኩ የግብረ-ሰዶም ተግባር በሚያስፈጽሙ ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ ፔንሲዮኖችና መሰል የመዝናኛ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ላይ ከህብረተሰቡ በሚደርስ ጥቆማ መሰረት አስተማሪ እርምጃ እየተወሰደ ነው ብሏል።

ቢሮው ፤ የግብረ-ሰዶም ተግባር መፈጸምና ማስፈጸም በኢትዮጵያ በሥራ ላይ ባሉ ሕጎች የተከለከለ መሆኑ ገልጾ " ይህንን አስጸያፊ በሰውም በአምላክም ዘንድ የተጠላ ደርጊት በሚፈጽሙና በሚያስፈጽሙ የመዝናኛ አገልግሎት መስጫ ተቆማት ላይ ካለ አንዳች ርህራሄ ከህብረተሰቡ በሚደርሰን ጥቆማ መሰረት ከፖሊስ ጋር በመተባበር እርምጃ መውሰዳችንን አጠናክረን እንቀጥላልን " ሲል አሳውቋል።

በዚህም ፤ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 አስተዳደር ውስጥ በሚገኝ " አበባ ገስት ሐውስ " በሚባል የመዝናኛ አገልግሎት መስጫ ተቋም ላይ ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ መሰረት እርምጃ እንደተወሰደበት አሳውቋል።

የተቋሙ ኃላፊም በከተማው ፖሊስ ቁጥጥር ስር እንዲውል በማድረግ ምርመራ እየተከናወነ ይገኛል ተብሏል።

ከግብረሰዶም ፀያፍ ተግባር ጋር የተገናኘ መረጃ እና ጥቆማ ያለው ማንኛውም ሰው በአቅራቢያው በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ በግንባር በመቅረብ እንዲሁም በነፃ የስልክ መስመር 991 እና 987 እንዲሁም በ011-1- 11-01-11 እና 011-5-52-63-02 በመጠቀም መረጃና ጥቆማ መስጠት ይቻላል። (ኢ ፕ ድ)

የመገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች ብሔራዊ ጥቅም የሚያስቀድሙና የሕዝብን አንድነት የሚያጠናክሩ ሊሆኑ ይገባል - ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)የመገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስቀድሙና...
10/08/2023

የመገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች ብሔራዊ ጥቅም የሚያስቀድሙና የሕዝብን አንድነት የሚያጠናክሩ ሊሆኑ ይገባል - ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)

የመገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስቀድሙና የሕዝብን አንድነት የሚያጠናክሩ ሊሆኑ እንደሚገባ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

በኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት እና በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን አዘጋጅነት "መገናኛ ብዙኃን ለአገር ግንባታ" በሚል መሪ ሃሳብ ለፌደራልና ለክልል የመገናኛ ብዙኃን የሥራ ኃላፊዎችና አርታኢያን ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ተጠናቋል፡፡

በማጠቃለያ መርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)፤ መገናኛ ብዙኃን በሕዝቦች መካከል ወንድማማችነት እንዲጸናና አንድነት እንዲጠናከር መሥራት አለባቸው ብለዋል፡፡

መንግሥት ሀገራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እንደምሰሶ የያዛቸው አቅጣጫዎች ከግብ እንዲደርሱ መገናኛ ብዙኃን የራሳቸውን በጎ አስተዋጽዖ ማድረግ እንዳለባቸውም ተናግረዋል፡፡

የብዝኃ-ኢኮኖሚው ምሰሶ በሆኑት ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝም፣ ማዕድን እና አይሲቲ ዘርፎች ላይ ትላልቅ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልፀዋል።

ለአብነትም መንግሥት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ዘመናዊ ግብርናን በማስፋፋት በርካታ ሥራዎች እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

መገናኛ ብዙኃንም ይህ ዕቅድ ከግብ እንዲደርስ ከማገዝ ባሻገር እውነተኛ መረጃዎችን ለሕዝብ ተደራሽ ማድረግ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

በተለይም መንግሥት ሜካናይዜሽንን በመጠቀም በስንዴ ልማት የሚያከናውነው ውጤታማ ሥራ ላይ መሥራት እንዳለባቸው ጠቅሰው፤ በሌማት ትሩፋትና አረንጓዴ አሻራ የተከናወኑ ውጤታማ ተግባራት የዘገባዎች ትኩረት ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡

በሌላ መልኩም በማኑፋክቸሪንግ፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም እና የዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት እየተሰሩ ባሉ ተግባራት ዙሪያ በስፋት መሥራት እንዳለባቸውም ጠቁመዋል፡፡

አካታች ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በኢትዮጵያ እንዲረጋገጥ መንግሥት እየሰራ ያለውን በጎ ሥራ ሕዝቡ ተገንዝቦ የበኩሉን ድጋፍ እንዲያደርግ መገናኛ ብዙኃን የሚጠበቅባቸውን መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡

መገናኛ ብዙኃን ዘላቂና አዎንታዊ ሰላም እንዲረጋገጥ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስቀድሙ ዘገባዎች ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥተው መሥራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡

በሕዝብ መገናኛ ብዙኃን የሚሰሩ ዘገባዎች አካታች ሊሆኑ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡

መገናኛ ብዙኃን ለምርመራ ጋዜጠኝነት ልዩ ትኩረት ሰጥተው መሥራት እንዳለባቸው ጠቅሰው፤ ለስኬታማነቱ መንግሥት አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር መሐመድ እድሪስ በበኩላቸው፤ መገናኛ ብዙኃን በዘገባዎቻቸው ለአገር ግንባታ አስተዋጽዖ ለሚያደርጉ ጉዳዮች ትኩረት ሰጥተው መሥራት እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡

በዚህም ጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት የሚያስችሉ ሚዛናዊ ዘገባዎችን መሥራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል፡፡

10/08/2023
አርቲስት አብነት ዳግም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየአርቲስት አብነት ዳግም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።ለረዥም ጊዜ በህመም ላይ የቆየው አርቲስት አብነት በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡...
09/08/2023

አርቲስት አብነት ዳግም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

አርቲስት አብነት ዳግም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

ለረዥም ጊዜ በህመም ላይ የቆየው አርቲስት አብነት በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡

አርቲስት አብነት በበርካታ ቴአትሮች ፣ ፊልሞች እና ድራማዎች ላይ በተዋናይነት በመሳተፍ እውቅናን ያተረፈ ነበር።

ከዚህ ውስጥ አሉላ አባነጋ፣ የቼዝ ዓለም፣ ዳኛው፣ እስረኛው ንጉስ እና ነቅዕ ቴአትሮች ላይ ተውኗል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ አያስቅም፣ አንድ እድል፣ ላምባዲና፣ ሰበበኛ፣ ባንቺ የመጣ፣ ቁልፉን ስጭኝ፣ የነገርኩሽ እለት፣ ፍቅር እስከ መቃብር እና አትሸኟትም ወይ በተሰኙ ፊልሞች ላይ በመተወን አድናቆትን አግኝቷል።

ስንቅ ፣መለከት፣ ትርታ እና ለወደዱት ደግሞ የተሳተፈባቸው ቲቪ ድራማዎች ሲሆኑ፥ በግሉም የቅብብሎሽ ድራማን ደርሷል።

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በአንጋፋው አርቲስት አብነት ዳግም ህልፈት የተሰማውን ሀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቹ፣ ወዳጅ ዘመዶቹ እና አድናቂዎቹ መፅናናትን ይመኛል፡፡

 ተዋናይ አብነት ዳግም ባደረበት የስኳር ህመም ምክንያት ቀደም ሲል ከባድ ህመም ላይ እንደነበር የሚታወቅ ሲሆን።ትላንት ላይ ህመሙ በመበርታቱ እና በመዳከሙ ምክንያት ወደ ጤና ጣቢያ ቢሄድም ...
09/08/2023



ተዋናይ አብነት ዳግም ባደረበት የስኳር ህመም ምክንያት ቀደም ሲል ከባድ ህመም ላይ እንደነበር የሚታወቅ ሲሆን።

ትላንት ላይ ህመሙ በመበርታቱ እና በመዳከሙ ምክንያት ወደ ጤና ጣቢያ ቢሄድም እሱን ለማትረፍ ሳይቻል ቀርቷል

ተዋናይ አብነት ዳግም በብዙ ቲያትሮች እና ፊልሞች እንዲሁም ማስታወቂያዎች ላይ በብቃት የሚተውን በጣም ትልቅ ባለሙያ ነበር ።

* ለቤተሰቦቹ
* ለአድናቂዎቹ
* ለስራ ባልደረቦቹ

መጽናናትን እንመኛለን

ነፍስ ይማር!!!

😭😭😭

via ጉርሻ pageጉርሻ page

የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች በሲዳማ ክልል የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉየትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች በሲዳማ ክልል ወንዶገነት ከተማ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ እና የችግን ተከላ መርሃ ግ...
09/08/2023

የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች በሲዳማ ክልል የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ

የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች በሲዳማ ክልል ወንዶገነት ከተማ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ እና የችግን ተከላ መርሃ ግብር አካሄዱ፡፡

አመራሮቹ በወንዶ ገነት ከተማ ለሚገኘው ትምህርት ቤት 20 ኮሚፒውተሮች ፣ 3500 መፅሐፍትን ድጋፍ አድርገዋል፡፡

በተጨማሪም አቅም ለአጠራቸው 1000 ለሚጠጉ ተማሪዎች የቦርሳ ድጋፍ እንዲሁም 700 ለሚሆኑ ሴቶች የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን አበርክተዋል።

በዕለቱም የሲዳማ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በየነ ባራሣ ፣ የትምህርት ሚኒስቴር ሚ ዴኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ እና ሌሎች ስራ ሃላፊዎች መገኘታቸውን ከሲዳማ ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

EBC News Sidaamu Afoo

ከኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የተሰጠ መግለጫ********************ኢትዮጵያ በፈተና የምትፀና ሀገር!ኢትዮጵያ በየዘመኑ ከዉስጥና ከዉጭ በሚያጋጥሟት በርካታ ፈተናዎችን አልፋ ዛሬ...
07/08/2023

ከኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የተሰጠ መግለጫ
********************

ኢትዮጵያ በፈተና የምትፀና ሀገር!

ኢትዮጵያ በየዘመኑ ከዉስጥና ከዉጭ በሚያጋጥሟት በርካታ ፈተናዎችን አልፋ ዛሬ የደረሰች ስትሆን አንድነቷና ቀጣይነቷ በጠንካራ አለት ላይ እንዲመሠረት ካደረጉት ጉዳዮች መካከል የህዝቦቿ ህብረትና አንድነት በጉልህ የሚጠቀስ ነው፡፡ በመሆኑም የህዝቦቿ ህልዉናና እጣ ፋንታም በእጅጉ የተሳሰረ ነዉ።

ኢትዮጵያን በጠንካራ መሰረት ላይ ካቆሟት እና የህዝቦቿን አንድነት ካስተሳሰሩ ዘመን ተሻጋሪ ተቋማት መካከል እንዱና ዋነኛዉ የሀገር መከላከያ ነዉ። መከላከያችን ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ሁሉም የኢትዮጵያ ብሔር ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች የተወከሉበት የኢትዮጵያን ህብረብሔራዊነትን አጉልተዉ ከሚያሳዩት ተቋማት መካከል አንዱና ዋነኛው ሆኖ የሀገራችን የግዛት አንድነትና ሉኣላዊነት በመጠበቅ ስያገለግል ቆይቷል፤ እያገለገለም ይገኛል፡፡

ሀገር ወዳዱ፤ ቆራጡ እና ህዝባዊው መከላከያ ሰራዊታችን በሀገር ዉስጥም ሆነ በአለም አቀፍ ደረጃ በተሰጡት ግዳጆች ላይ በመሰማራት በታላቅ የሀገር ፍቅር ስሜትና በጀግንነት አኩሪ ታሪክ የገነባ ህዝባዊ ሰራዊት ነዉ፡፡ የሀገራችን ጋሻ እና የሰላማችን የሁል ጊዜ መከታ የሆነው መከላከያ ሠራዊታችን ኢትዮጵያን በተለያየ ጊዜ ከዉጭ ታሪካዊ ጠላቶቻችንና ከውስጥ በጽንፈኛ ሃይሎች የሚቃጡባትን አደጋዎችን በማክሸፍ ኢትዮጵያን በሙሉ ክብሯ እና አንድነቷ እንድትፀና ደሙን፣ አጥንቱን እና ተኪ የሌላትን ነፍሱን ሲገብር የኖረ ሰራዊት ነው፡፡

ይህንን የሀገሪቱን ታላቅ ተቋም ጽንፈኞች ከዉስጥ እና ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ከዉጭ ተቀናጅተው የተለያዩ የፕሮፓጋንዳ ማሽነሪዎቻቸዉን በመጠቀም ለማጠልሸትና ለማዳከም ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ቢሆንም ሰራዊታችን ህብረብሄራዊነቱን ጠብቆ ግዳጁን እየተወጣ ይገኛል፡፡ በመሆኑም መከላከያን መንካት ማለት የሀገር ሉኣላዊነትን መንካት መሆኑ ሊታወቅ ይገባል፡፡

የኢትዮጵያ ህዝቦች ህልውናና እጣ ፋንታ በእጅጉ ተሳስሮ እያለ ጃውሳው ጽንፈኛ ሀይል በኣማራ ብሄራዊ ክልል የህዝብን ጥያቄ ያነገበ በማስመሰል ነፍጥ አንግቦ መከላከያ ሰራዊታችንን በማጥቃት ክልሉን የጦር አዉድማ እያደረገ ይገኛል፡፡ የክልሉ ህዝብ እራሱን በራሱ የሚያስያስተዳድር ከአብራኩ በወጡ ልጆቹ የሚመራ ሆኖ ሳለ የአማራ ህዝብ ከሀገሪቱ ህዝቦች በተለየ ሁኔታ ጥያቄ ያለው በማስመሰል ነፍጥ ያነሱ እነዚህ በአቋራጭ ስልጣን ለመቆጣጠር ነውጠኛው ሀይል ክልሉን በማህበራዊና በኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ወደ ኋላ እየመለሰው ይገኛል፡፡

ባለፉት ሁለት አመታት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በነበረው ጦርነት ከደረሰበት ከፍተኛ ጉዳት ያላገገመውን የክልሉን ህዝብ ነጣቂው ጃውሳው ዳግመኛ ለከባድ መከራ እየዳረገ ይገኛል፡፡
ከመላው የኢትዮጵያ ህዝቦች ጋር በደም፣ በአጥንት እንዲሁም በአስተዳደራዊ መዋቅር የተሳሰረው የአማራ ህዝብ የእርሻ ወቅትን በጠበቀ መልኩ መሬቱን በአዝርት እንዳይሸፍን መጭው ጊዜ ፈተና እንዲሆንበት ጃውሳው ጽንፈኛው ሀይል ጋሬጣ በመሆኑ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እና ህዝብን በከፍተኛ ሁኔታ ያሳስቧል፡፡

የአማራ ህዝብም ሆነ መላው የሀገራችን ህዝቦች በምርጫ የመሰረቱት መንግስት በእኩልነት ላይ የተመሰረተ የዜጎች የጋራ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ተግቶ እየሰራ ይገኛል፡፡
“እኔ ካልመራኋት” በስተቀር ሀገር አትቀናም በሚል አጉል የጽንፈኞች ነጠላ ትርክት የሚጃጃለው ነውጠኛው ጃውሳ በህዝብ ጥያቄ ስም የራሱን የስልጣን ጥማት ለማርካት የክልሉን መንግስት በማፍረስ እና ክልሉን በማተራመስ የአማራን ህዝብ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚ

የሙሉ ሰዓት ውጤትኢትዮጵያ 4-2 ሎደን ዩናይትድ(30' ሱራፌል ዳኛቸው፣ 54' ሽመልስ በቀለ፣ 63' አስቻለው ታመነ (ፍ)፣ 76' ይሁን እንደሻው)
05/08/2023

የሙሉ ሰዓት ውጤት

ኢትዮጵያ 4-2 ሎደን ዩናይትድ

(30' ሱራፌል ዳኛቸው፣ 54' ሽመልስ በቀለ፣ 63' አስቻለው ታመነ (ፍ)፣ 76' ይሁን እንደሻው)

አሜሪካ ገቡ‼️ 🇪🇹
01/08/2023

አሜሪካ ገቡ‼️ 🇪🇹

በ"ፋኖ" ስም እየተንቀሳቀሱ የሃገር ሰላም ለማወክ በሚሰሩ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል- የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት*************************************አሁናዊ የመከላከ...
01/08/2023

በ"ፋኖ" ስም እየተንቀሳቀሱ የሃገር ሰላም ለማወክ በሚሰሩ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል- የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት
*************************************

አሁናዊ የመከላከያ ሰራዊቱን ያለበትን ሁኔታ በተመለከተ የኢፌዴሪ የመከላከያ ሰራዊት የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት መግለጫ ሰጥቷል።

መግለጫውን የሰጡት የሰራዊቱ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ ኮሎኔል ጌትነት አዳነ፣ መግለጫው በተለያዩ አካላት በሰራዊቱ ላይ እየተናፈሱ ያሉ ብዥታዎችን ለማጥራት የተሰጠ ነው ብለዋል።

ሰራዊቱ ካለፉት ዓመታት በነበረበት ቁመና ላይ እንዳለ የሚያስቡ አካላት ካሉ የቆሙት እነርሱ እንጂ ሰራዊቱ ተራማጅ ነው ያሉት ኮሎኔል ጌትነት፣ ሰራዊቱ ዘርፈ ብዙ ግዳጁን እየተወጣ ነው ብለዋል።

"ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ" የሚል አካል ላይ ሰራዊቱ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል።

ሰራዊቱን መቋቋም ያልቻሉ አካላት በሰራዊቱ ላይ ሰፊ የስም ማጥፋት ዘመቻ ላይ ይገኛሉም ነው ያሉት ኮሎኔል ጌትነት።

በተለይ አሁን ላይ በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ አካላት ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በኦሮሚያ ክልል ሸኔ የመደምሰስ ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን አብራርተዋል።

በአማራ ክልል በመሬት ላይ ካለው ግጭት የገዘፈ የሚዲያ ትግል ተከፍቷል ተብሏል በመግለጫው።

ከሰሞኑ በጎንደር የሰሜን ምዕራብ እዝን ዓመታዊ አፈጻጸም ላይ ለመገምገም ወደ ስፍራው እያቀኑ በነበሩ የሰራዊቱ አባላት ላይ ከጩሂት 2 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሲደርሱ ተኩስ በሰራዊቱ ላይ መከፈቱን ጠቅሰዋል።

የሰራዊቱ አባላትም በመመለስ ላይ ሳለም በቆላድባ አካባቢ በተመሳሳይ ተኩስ ተከፍቷል ነው ያሉት።

ለዚህም ሰራዊቱ ችግሩን በብልሃት ለመፍታት መስራቱንም አስታውሰዋል።

ሐምሌ 23 ቀን 2015 ዓ.ም ከአካባቢው ማህበረሰብ፣ ከወጣቶች እና ከሃገር ሽማግሌዎች ጋር ውይይት ተካሂዶ እንደነበር እና በይቅርታ መዘጋቱን አንስተዋል።

EBC News Sidaamu Afoo

🇲🇦 ሞሮኮአዊቷ ኑሀይላ ቤንዚና በሴቶች አለም ዋንጫ ላይ ሂጃብ በመልበስ መጫወት የቻለች የመጀመሪያዋ ሴት ተጫዋች ሆናለች ! 👏 🧕
30/07/2023

🇲🇦 ሞሮኮአዊቷ ኑሀይላ ቤንዚና በሴቶች አለም ዋንጫ ላይ ሂጃብ በመልበስ መጫወት የቻለች የመጀመሪያዋ ሴት ተጫዋች ሆናለች ! 👏 🧕

ከቀጣዩ አመት ጀምሮ በግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚተገበር አስገዳጅ መመሪያ ተዘጋጀየግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና  ቢያንስ 25 በመቶዎቹን ማሳለፍ ካልቻሉ የትምህርት መስ...
29/07/2023

ከቀጣዩ አመት ጀምሮ በግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚተገበር አስገዳጅ መመሪያ ተዘጋጀ

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ቢያንስ 25 በመቶዎቹን ማሳለፍ ካልቻሉ የትምህርት መስኮቻቸው እንዲታጠፉ የሚያስገድድ መመሪያ ተግባራዊ ሊደረግ ነው።

የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ በግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተግባራዊ የሚደረግ አዲስ መመሪያ መዘጋጀቱን ገልጿል።

በባለስልጣኑ የከፍተኛ ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ክትትል እና ቁጥጥር መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ከፍያለው አድነው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት፥ የመማር ማስተማር ስራው ጥራቱ የተጠበቀ እንዲሆን አዲስ መመሪያ እና መስፈርት ተዘጋጅቷል።

የሚታዩ ክፍተቶችን በመሙላት የሚጠበቀውን ደረጃ እና ጥራት ማስጠበቅ ያስችላል የተባለው አዲስ መመሪያ እና መስፈርትም ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ነው ያሉት።

በመመሪያው የትምህርት ጥራቱን ለማስጠበቅ በርካታ መለኪያዎች የተቀመጡ ሲሆን፥ አንዱ የመውጫ ፈተናን የሚመለከት መሆኑንም አስረድተዋል።

በዚህም እያንዳንዱ ተቋም ለመውጫ ፈተና ከሚያስቀምጣቸው ተማሪዎች በየትምህርት መስኩ ቢያንስ 25 በመቶዎቹ ማለፍ እንደሚጠበቅባቸው በማንሳት ይህ ካልሆነ ግን የትምህርት ፕሮግራሙ ይሰረዛል ብለዋል።

በተጨማሪም የትምህርት ተቋማቱ ለማስተማር የሚመዘግቧቸውን ተማሪዎች ለባለስልጣኑ የማሳወቅ ግዴታ አለባቸው ተብሏል።

ዘንድሮ በተሰጠው የዩኒቨርሲቲ የመውጫ ፈተና ከግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተናውን ከወሰዱ 72 ሺህ ተማሪዎች ውስጥ የማለፊያ ውጤት 50 እና ከዛ በላይ ያመጡት 12 ሺህ 422 ወይም 17 ነጥብ 2 በመቶ ብቻ መሆናቸው ይታወቃል።

EBC News Sidaamu Afoo

ሁላችሁም አዲሱን ገፃችን የሆነውን EBC News Sidaamu Afoo LIKE እና FOLLOW በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!!
29/07/2023

ሁላችሁም አዲሱን ገፃችን የሆነውን EBC News Sidaamu Afoo LIKE እና FOLLOW በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!!

ኢትዮጵያ እና ፓኪስታን በአቪዬሽን ዘርፍ ያላቸውን ግንኙነት የበለጠ ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆናቸውን ጎለጹ ******************** በፓኪስታን የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ጀማል...
27/07/2023

ኢትዮጵያ እና ፓኪስታን በአቪዬሽን ዘርፍ ያላቸውን ግንኙነት የበለጠ ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆናቸውን ጎለጹ
********************

በፓኪስታን የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ጀማል በከር ከፓኪስታን የአቪዬሽን እና የባቡር መንገድ ሚኒስትር ካዋጃ ሰዓድ ራፊቅ ጋር ሁለቱን ሀገራት የአቪዬሽን ዘርፍ ግንኙነት የበለጠ ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።

በዘርፉ ያለው ትብብር የሁለቱን ሀገራት የሕዝብ ለሕዝብ እና የንግድ-ንግድ ግንኙነትን እንደሚያሻሽል ታምኖበታል።

የኢትዮጵያ እና ፓኪስታን መንግሥታትም የንግድ፣ የኢንቨስትመንት እና የቱሪዝም ትሥሥራቸውን ለማሳደግ በዘርፉ ያለውን ሁለገብ ትብብር የበለጠ ለማሳደግ ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

EBC News Sidaamu Afoo

በመዲናዋ የተሰረቁ ተንቀሳቃሽ ስልኮች በሕጋዊ ስም በተከፈቱ የንግድ ሱቆች ውስጥ ተያዙ በተለያዩ አካባቢዎች የተሰረቁ ተንቀሳቃሽ ስልኮች በሕጋዊ ስም በተከፈቱ የንግድ ሱቆች ውስጥ መያዙን የአ...
27/07/2023

በመዲናዋ የተሰረቁ ተንቀሳቃሽ ስልኮች በሕጋዊ ስም በተከፈቱ የንግድ ሱቆች ውስጥ ተያዙ

በተለያዩ አካባቢዎች የተሰረቁ ተንቀሳቃሽ ስልኮች በሕጋዊ ስም በተከፈቱ የንግድ ሱቆች ውስጥ መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

በቦሌ ክፍለ ከተማ በሕጋዊ የሞባይል ስልክ እና የቴሌቪዥን ጥገና ሱቅ ሽፋን ከግለሰቦች የተሰረቁ ስልኮችን እየገዙ ሲሸጡ ከነበሩ ግለሰቦች ሱቅ ውስጥ በርካታ ተንቀሳቃሽ ስልኮች መያዛቸው ተገልጿል፡፡

ኤድናሞል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሞባይል ጥገና ስራ በሚሰሩ 4 የንግድ ሱቆች ላይ በፖሊስ በተከናወነ ብርበራ ነው ከተለያዩ ቦታዎች ተሰርቀው የተከማቹ ሞባይል ስልኮች የተዘያዙት፡፡

ከሞባይል ስልኮቹ በተጨማሪ የወንጀል ፍሬ ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ እና በጥገና ቤቶቹ ውስጥ የተገኙ የተለያየ መጠን ያላቸው ስክሪን ቴሌቪዥኖች መያዛቸው ተጠቁሟል፡፡

ከጉዳዩ ጋር በተገናኘ አራት ግለሰቦች ተይዘው ምርመራ እየተጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ መረጃ ያመላክታል፡፡

ቀደም ሲል በተለያዩ አካባቢዎች በተፈፀመባቸው ወንጀል ተንቀሳቃሽ ስልክ እና ቴሌቪዥን የተወሰደባቸው ግለሰቦች አንበሳ ጋራዥ ጀርባ በሚገኘው የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ እየቀረቡ ማረጋገጥ ይችላሉ ተብሏል፡፡

በወንጀል ምክንያት የተገኙ ንብረቶችን ከወንጀል ፈፃሚዎቹ በሚገዙ ግለሰቦች ላይ ተከታታይነት ያለው እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡

ችግሩ በዘላቂነት እስኪቀረፍ ድረስ በሕግ ተጠያቂ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ፖሊስ አስታውቋል፡፡

በሶማሌ ክልል ለሚገነባው ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመሠረተ ድንጋይ ተቀመጠ*******************የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የሶማሌ ብሄራዊ ክልል ትምህርት ...
26/07/2023

በሶማሌ ክልል ለሚገነባው ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመሠረተ ድንጋይ ተቀመጠ
*******************

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የሶማሌ ብሄራዊ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱላሂ አብዲ አደን በሶማሌ ክልል ፋፋን ዞን ባቢሌ ወረዳ ኦቦሻ ቀበሌ ውስጥ ለሚገነባው የኦቦሻ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የመሰረት ድንጋይ አስቀምጠዋል።

ትምህርት ቤቱ የሚገነባው ሰዎች ለሰዎች በተሰኘ ግብረ ሠናይ ድርጅት መሆኑም ተነግሯል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የመሰረት ድንጋዩን ባስቀመጡበት ወቅት፥ የትምህርት ጥራትን በፍትሀዊነት ለማዳረስ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

የሰዎች ለሰዎች ድርጅት አገር አቀፍ ተጠሪ አቶ ይልማ ታዬ፥ ድርጅታቸው ትምህርት ቤቱን መንግስት ባቀረበው ዲዛይንና በተቀመጠለት ጊዜ መሰረት ሙሉ በሙሉ አስገንብቶ ለማስረከብ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።

አቶ ይልማ አክለውም ድርጅታቸው የፌዴራል መንግስት በቀጣይ አምስት ዓመታት ለማስገንባት አቅዶ እየሰራ ካለው 50 ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል በአገር አቀፍ ደረጃ 16ቱን ለማስገንባት ሀላፊነት ወስዶ እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

ከነዚህም መካከል በዛሬው ዕለት የመሰረት ድንጋዩ የተቀመጠውን ጨምሮ አራት 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶችን በሶማሌ ብሄራዊ ክልል የሚያስገነባ መሆኑን መናገራቸውን ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

EBC News Sidaamu Afoo

konne haaro facebookete qoolankke   NNA   assitinanni ledonkke heedhinoonni daafira lowo geeshsha galanteemmo'ne!ይህን አዲሱ...
25/07/2023

konne haaro facebookete qoolankke NNA assitinanni ledonkke heedhinoonni daafira lowo geeshsha galanteemmo'ne!

ይህን አዲሱን የፌስቡክ ገፃችንን LIKE እና SHARE እንዲሁም FOOLLOW እያደረጋችሁ ከእኛ ጋር ስላሉ ከልብ እናመሰግናለን!!

EBC News Sidaamu Afoo

ሉሲዎቹ በሴካፋ ከ18 ዓመት በታች ሴቶች ውድድር በዩጋንዳ አቻቸው 1 ለ 0 ተሸነፉ ************************ በታንዛኒያ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የምሥራቅ እና መካከለ...
25/07/2023

ሉሲዎቹ በሴካፋ ከ18 ዓመት በታች ሴቶች ውድድር በዩጋንዳ አቻቸው 1 ለ 0 ተሸነፉ
************************

በታንዛኒያ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የምሥራቅ እና መካከለኛው አፍሪካ ዋንጫ (ሴካፋ) ከ18 ዓመት በታች ሴቶች ውድድር የኢትዮጵያ ብሔራዊ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን (ሉሲዎቹ) በመክፈቻ ጨዋታ በዩጋንዳ አቻቸው 1 ለ 0 ተሸንፈዋል።

የዩጋንዳን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ አለንስ ናሳዚ በ68ኛ ደቂቃ ላይ አስቆጥራለች።

ሉሲዎቹ ሁለተኛ ጨዋታውን በቀጣይ ከታንዛኒያ አቻቸው ጋር የፊታችን ዓርብ ያደርጋሉ።

EBC News Sidaamu Afoo

ብርሃኑ ነጋ ፕሮፈሰር - ኢትዮ ትምህርት ሚኒስትር
25/07/2023

ብርሃኑ ነጋ ፕሮፈሰር - ኢትዮ ትምህርት ሚኒስትር

ቻይና ጥቅም ላይ ውለው የተጣሉ ባትሪዎችን በማደስ ለአገልግሎት እያበቃች ነው አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ቻይና በቴክኖሎጂው ዘርፍ ዓለምን እየፈተነ የመጣውን የማዕድናት ...
25/07/2023

ቻይና ጥቅም ላይ ውለው የተጣሉ ባትሪዎችን በማደስ ለአገልግሎት እያበቃች ነው

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ቻይና በቴክኖሎጂው ዘርፍ ዓለምን እየፈተነ የመጣውን የማዕድናት ግብዓት እጥረት ለመቅረፍ ጥቅም ላይ ውለው የተጣሉ ባትሪዎችን በመሰብሰብ አድሳ ዳግም ለአገልግሎት እያበቃች እንደሆነ ተገለጸ፡፡

ቻይና በዘርፉ ከ10 ሺህ በላይ በቴክኖሎጂ የተደገፉ ጣቢያዎችን ከፍታ የተጣሉ ባትሪዎችን በማደስ መልሳ ጥቅም ላይ እያዋለች መሆኑን የሀገሪቷ የኢንዱስትሪ እና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

ከተጣሉ ባትሪዎች÷ የኒኬል፣ ኮባልት እና ሊቲየም ይዘቶችን በጥራት በመለየት ዳግም ጥቅም ላይ ማዋል መቻሉን ሚኒስቴሩ ጠቁሟል፡፡

በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ ከአንድ የተጣለ ባትሪ እስከ 95 በመቶ የኒኬል እና የኮባልት ይዘት መልሶ ማግኘት ሲቻል እንደ ጣቢያዎቹ ዘመናዊነት እና አቅም ከ70 እስከ 90 በመቶ ሊቲየም ከአንድ ባትሪ መልሶ ማግኘት እንደሚቻልም ተመልክቷል፡፡

ከፈረንጆቹ 2021 ወዲህ የተጣሉ ባትሪዎችን ከአቅራቢዎች በአነስተኛ ዋጋ በመረከብ ዳግም ጥቅም ላይ እንዲውሉ ማድረግ መቻሉን ሚኒስቴሩ ጠቁሟል፡፡

ቻይና በፈረንጆቹ 2022 ላይ 277 ሺህ ቶን ያህል ጥቅም ላይ ውለው የተጣሉ ባትሪዎችን ከአቅራቢዎች በአነስተኛ ዋጋ በመግዛት አድሳ ጥቅም ላይ ማዋሏ ተነግሯል፡፡

በዚህ ዓመት የመጀመሪያ ሥድስት ወራት ብቻ እንኳ 115 ሺህ ቶን ባትሪ ሰብስባ በማደስ ጥቅም ላይ ማዋሏን ሲጂቲ ኤን ዘግቧል፡፡

እስከ ፈረንጆቹ 2025 በዓመት 1 ሚሊየን ቶን ጥቅም ላይ ውለው የተጣሉ ባትሪዎችን በዓመት ለመሰብሰብ መታቀዱም ተገልጿል፡፡

ቻይና ካገለገሉ ባትሪዎች መልሳ ማግኘት የምትችላቸውን ሐብቶች በጥራት በመለየት ረገድ ቴክኖሎጂዎቿን እያሻሻለች መሆኑን የኢንዱስትሪ እና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ምክትል ሚኒስትር ዢን ጎቢን ተናግረዋል፡፡

EBC News Sidaamu Afoo

በባቡር የሚጓጓዘው የአፈር ማዳበሪያ በፍጥነት ወደ ማሠራጫ ማዕከሎች እንዲደርስ በትኩረት እየተሠራ ነው ************************** ከጅቡቲ ወደብ በባቡር ተጓጉዞ እንዶዴ ባቡር ...
25/07/2023

በባቡር የሚጓጓዘው የአፈር ማዳበሪያ በፍጥነት ወደ ማሠራጫ ማዕከሎች እንዲደርስ በትኩረት እየተሠራ ነው
**************************

ከጅቡቲ ወደብ በባቡር ተጓጉዞ እንዶዴ ባቡር ጣቢያ የሚደርሰውን የአፈር ማዳበሪያ በፍጥነት ወደ ማሠራጫ ማዕከሎች እንዲደርስ በትኩረት እየተሠራ እና በባቡር ጣቢያው በየቀኑ በአማካይ እስከ 10 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እንደሚሠራጭ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ዴንጌ ቦሩ በእንዶዴ ባቡር ጣቢያ ተገኝተው በባቡር ተጓጉዞ የሚመጣው የአፈር ማዳበሪያ ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚሠራጭበትን ሂደት ተመልክተዋል።

በምልከታቸውም የባቡር ምልልስን በመጨመር የአፈር ማዳበሪያ የማጓጓዝ አቅምን ማሳደግ የተቻለ ከመሆኑም ባሻገር የጭነት ተሽከርካሪዎች ባቡር ጣቢያ ዝግጁ ሆነው እንዲጠብቁ በማድረግ ባቡር ጣቢያ ላይ የደረሰውን የአፈር ማዳበሪያ በአጭር ጊዜ ለማሠራጨት እየተሠራ ስለመሆኑ ማረጋገጥ ችለናል ብለዋል።

ሰሞኑን የአፈር ማዳበሪያን በማጓጓዝ ሂደት የታየው የመፈፀም አቅም በቀጣይ የሎጂስቲክስ ቅልጥፍናን ለማሳደግ በሚሠሩ ሥራዎች ላይ ትልቅ ትምህርት ይሆናል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፣ ባለድርሻ አካላት ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ተቀናጅተው በትጋት መስራታቸው ውጤት ማስገኘቱን ገልጸዋል።

በተጨማሪም የአፈር ማዳደሪያ ተጓጉዞ እስከሚያልቅ ድረስ በከፍተኛ ክትትል የሚሠራ መሆኑን ጠቁመው የተጀመረውን ቅንጅታዊ አሠራር በማጠናከር ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሙሉ አቅማቸውን ተጠቅመው ሊሰሩ እንደሚገባም ማሳሰባቸውን ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

EBC News Sidaamu Afoo

መንግሥት ጀግናው አትሌት አበበ ቢቂላ በሮም ከተማ መታሰቢያ እንዲኖረው በማድረግ ረገድ ውጤታማ የዲፕሎማሲ ሥራ ማከናወኑ ተገለጸ *********************መታሰቢያው  የአትሌቱ ታሪክ ...
23/07/2023

መንግሥት ጀግናው አትሌት አበበ ቢቂላ በሮም ከተማ መታሰቢያ እንዲኖረው በማድረግ ረገድ ውጤታማ የዲፕሎማሲ ሥራ ማከናወኑ ተገለጸ
*********************

መታሰቢያው የአትሌቱ ታሪክ ተጠብቆ ለትውልድ እንዲተላለፍ የሚያደርግ መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው የጀግናው አትሌት አበበ ቢቂላ መታሰቢያ ምስለ ቅርጽን በሮም አኑረዋል።

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ጉዳዩን አስመልከቶ በሰጡት ገለጻ፣ አበበ ቢቂላ በማይመች ሁኔታ ውስጥ በባዶ እግሩ የማራቶን ውድድርን በመሸነፍ ለመላ ጥቁር ህዝቦች የይቻላል መንፈስ ምልክት መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይ ጀግናው አትሌት ያስመዘገበው ድል በርካታ የአፍሪላ አገራት በቀኝ ግዛት ውስጥ እያሉ በመሆኑ ትርጉሙን ልዩ እንደሚያደርገው ተናግረዋል።

መሆኑም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአትሌቱን መታሰቢያ ምስለ ቅርጽ በሮም ለማቆም ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ሥራ ሲየከናውኑ መቆየታቸውን ገልጸዋል።

አብነትም ከሦስት ወራት በፊት ወደ ጣሊያን በመጡበት ወቅትም ይህንን ጉዳይ ትኩረት በመስጠት ከአገሪቷ ከፍተኛ የመንግሥት ሃላፊዎች ጋር መነጋገራቸውን አሰወታውሰው፣በዚህም በአጭር ጊዜ ውስጥ ውጤታማ ሥራ ተከናውኗል ነው ያሉት።

መታሰቢያው ታሪክን ለትውልድ በመዘከር በኢትዮጵያ በየመስኩ የአገር ባለውለታ የሆኑ ጀግኖችን ለማፍራት መነሳሳትን ይፈጥራል ነው ያሉት።

በተጨማሪም በኢትዮጵያና ጣሊያን መካከል ያለውን ወዳጅነት ይበልጥ ለማጠናከር ሚናው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።

የጀግናው አትሌት አበበ ቢቂላ መታሰቢያን በሮም ከተማ በማቆም ረገድ በጣሊያን የኢትዮጵያ ኤምባሲና የጣሊያን መንግሥት ለአከናወኑት ሥራም በኢፌዴሪ መንግሥት ስም ምስጋና አቅርበዋል።

የአርሲ ዩኒቨርሲቲ ለአትሌት ቀነኒሳ በቀለ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ*********************የአርሲ ዩኒቨርሲቲ  በዛሬው እለት ለአትሌት ቀነኒሳ በቀለ  የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጥ...
23/07/2023

የአርሲ ዩኒቨርሲቲ ለአትሌት ቀነኒሳ በቀለ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ
*********************

የአርሲ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው እለት ለአትሌት ቀነኒሳ በቀለ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጥቷል።

አትሌት ቀነኒሳ የክብር ዶክትሬቱን በኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ አማካኝነት ተቀብሏል።

በኦሎምፒክ መድረክ የሶስት ጊዜ የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ እንዲሁም ለአምስት ጊዜ በዓለም የሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና ላይ አሸናፊ በመሆን የሀገሩን ባንዲራ ከፍ አድርጎ ያውለበለበው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በዛሬዉ እለት የክብር ዶክትሬት ተሰጥቷል።

ዩኒቨርሲቲው በዛሬው ዕለት በተለያዩ መርሐ ግብሮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በደማቅ ስነ ስርዓት አስመርቋል።

EBC News Sidaamu Afoo

የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የክብር ዶክትሬት ሰጠ ********************************* የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ...
23/07/2023

የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የክብር ዶክትሬት ሰጠ
*********************************

የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ የ2015 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎችን እያስመረቀ ነው።

ዩኒቨርሲቲው ለቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የክብር ዶክትሬት ሰጥቷል።

የክብር ዶክትሬቱ የተሰጠው ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በትምህርትና የተለያዩ ዘርፎች ላይ ለዜጎች እያበረከቱት ላለው ተግባር እውቅና ለመስጠት እንደሆነ ተገልጿል።

ተመራቂ ተማሪዎች ኢትዮጵያን ከድህነት እና ከኋላቀርነት ለማላቀቅ የበኩላችሁን ሚና እንድትወጡ ሲሉ ስነ-ስርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ አሳስበዋል።

በዘንድሮው ምርቃት ላይ ዩኒቨርስቲው ከፒ.ኤች.ዲ ጀምሮ በማስተር እና በዲግሪ እንዲሁም በዲፕሎማ 1ሺህ 99 ተማሪዎች አስመርቋል።

የዩኒቨርሲቲው 86 በመቶ ተመራቂ ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና አልፈዋል።

EBC News Sidaamu Afoo

በወራቤ ከተማ አንዲት እናት በአንድ ጊዜ 3 ልጆችን በሰላም ተገላገሉ********************* በወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አንዲት እናት ሁለት ሴት ልጆችን እና አንድ...
22/07/2023

በወራቤ ከተማ አንዲት እናት በአንድ ጊዜ 3 ልጆችን በሰላም ተገላገሉ
*********************

በወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አንዲት እናት ሁለት ሴት ልጆችን እና አንድ ወንድ ልጅ በአንድ ጊዜ በሰላም ተገላግለዋል።

ከሆስፒታሉ ማህጸን እና ጽንስ ክፍል የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው ሕፃናቱ 2.7 ፣ 2.6 እና 2.5 ኪሎ ግራም ይመዝናሉ።

እናት ወ/ሮ ሀይሪያ ኑርሰቦ ከአልቾ ውሪሮ ወረዳ በሪፈር ወደ ሆስፒታሉ መሔዳቸው እና በቀዶ ሕክምና ሦስቱን ልጆች መገላገላቸው ታውቋል።

ወ/ሮ ሀይሪያ ከዚህ በፊት በአንድ ጊዜ ከአንድ በላይ ልጅ እንዳልተገላገሉ እና በአንድ ጊዜ 3 ልጅ መውለዳቸው እንዳስደሰታቸውም ገልጸዋል።

ሕፃናቱም ይሁኑ እናትየው በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙም ሆስፒታሉ አረጋግጧል።

Address

Addis Ababa
Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Central Hotel Bensa Daye posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share



You may also like