15/02/2023
ከአዋሽ ባንክ ጋር ተያይዞ በማህበራዊ ሚዲያ የሚነዛው ወሬ መሰረተ ቢስና ሀሰተኛ ነው
ሰሞኑን በአዋሽ ባንክ ላይ ሲወሩ ከነበሩ ና እየተወሩ ካሉ መሰረተቲስና ሀሰተኛ ወሬዎች ጋር ተያይዞ የማጣራት ስራ አካሂደናል::
እዉነት እና ንጋት እያደር ይጠራል እንደሚባለው ሰሞኑን አዋሽ ባንክ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሐይማኖት ተከታይ የሆኑ ሰራተኞቹ ቅዱስ ሲኖዶሱ ባስተላለፈው መመርያ መሰረት ጥቁር የለበሱ ሰራተኞቹን ነጭ ልበሱ ብሏል ተብሎ በማህበራዊ ሚዲያ የተነዛው ወሬ ፍፁም ከእውነት የራቀ የስም ማጥፋት ዘመቻ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡
እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ በባንኩ ላይ የተከፈተው የማጥላላት ዘመቻ አገርንም ሆነ ኢንዱስትሪውን የሚጠቅም አይደለም፡፡ በሐይማኖት ሽፋን ሌላ ተልዕኮ የማራመድ ድብቅ ሴራ እንዳለውም የሚያሳብቅ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡
አዋሽ ባንክ የኢትዮጵያ ህዝቦች ያለ ዘር፣ ሐይማኖትና የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ከሁሉም አቅጣጫ ተሰባስበው የመሰረቱትና ያሰደጉት ከአገር አልፎ አህጉራዊና አለምአቀፋዊ ዝናን ያተረፈ የአገር ኩራት የሆነ የአገርና የኢትዮጵያ ህዝቦች አለኝታ የሆነ ባንክ ነው፡፡ ለዚህም መጠነ ሰፊ የሆነ ማህበራዊ ተሳትፎው ህያው ምስክር ነው፡፡ ስለሆነም እንደዚህ ዓይነቱን ህዝባዊ ተቋም በሀሰት ስም ማጥፋት ትልቅ ስህተት ነው ብለን እናምናለን። የማህበረሰብ አንቂዎችም የተከታይ ቁጥር ለመጨመር ብቻ ሳይሆን ተአማኒነት ያለውን ትክክለኛ መረጃ ለህዝቡ ለማቅረብ መስራት እነዳለባቸው በዚሁ አጋጣሚ ለመጠቆም እንወዳለን፡፡