Hadiya.TV

Hadiya.TV Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Hadiya.TV, Media, hossana, Hossana.
(40)

ከባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊና ውጤታማ የውይይት መድረክ አካሂደናል:- አቶ ተሾመ አናሞበአዲስ መልክ ተግባራዊ የሚደረገውን ስትራቴጂክ ፕላንን በማስመልከት ከባለድርሻ አካላት ጋር የተደርገው የ...
27/06/2024

ከባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊና ውጤታማ የውይይት መድረክ አካሂደናል:- አቶ ተሾመ አናሞ

በአዲስ መልክ ተግባራዊ የሚደረገውን ስትራቴጂክ ፕላንን በማስመልከት ከባለድርሻ አካላት ጋር የተደርገው የውይይት መድረክ ውጤታማና አስፈላጊ ሃሳቦች የተገኙበት ነው ሲሉ የሀዲያ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ተሾመ አናሞ ገለፁ።

ህብረተሰብ ያልተሳተፈበት የከተማ ፕላን ብዙ ጉድለት እንዳለው የገለጹት አቶ ተሾመ ከባለድርሻ አካላት ጋር ያደረግነው ሰፊ ውይይት ብዙ ግብዓት ያገኘንበት ነው ብለዋል።

አዲሱን የአስር ዓመት ስትራቴጂክ ፕላን በማስመልከት በዋና ዋና ችግሮች ዙሪያ ከተሳታፊዎች የተነሱትን ሰፋፊ ሀሳቦች በሚገባ ይዘናል ያሉት አቶ ተሾመ:-

ለፕላን ትግበራ አስፈላጊ ናቸው የተባሉ ግብዓቶችን በማሰባሰብ ፕላኑን እየተሰራ ባለው አግባብ በአጭር ጊዜ ሰርተን ይፋ እናደርጋለን ብለዋል።

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አበራ በዶሬ እንደገለጹት ፕላኑ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንዲደረግ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በቁርጠኝነት ትብብሩን እንዲገልጽ በማሳሰብ:-

በባለሙያ ስህተት ምክንያት የሚፈጠረውን የፕላን ስህተት እና ጥሰት ለመከላከል እንዲሁም በህግና ስርዓት አስይዞ ከመምራት አኳያ ህግ እየተከበረ እንደሚሄድ ተናግረው:-

ሾኔ ውብ፣ጽዱ፣ለነዋሪዋ ምቹ ከተማ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልፀዋል።

ለፕላን ያስፈልጋሉ የተባሉ የሶሺዮ ኢኮኖሚ፣የሰርቬይ ስራዎች፣የመሬት አጠቃቀም መረጃ፣የፍልድ ስራዎች ሁሉ ከሞላ ጎደል በመጠናቀቅ ላይ መሆናቸውን የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተማ ፕላን እና ኮንስትራክሽን ቢሮ ከፍተኛ ፕላነር የሆኑት አቶ ተስፋዬ ፊጦራ አብራርተዋል።

በሀዲያ ዞን ሾኔ ከተማ አስተዳደር ከዚህ ቀደም ሲሰራበት የቆየው መዋቅራዊ ፕላን ጊዜው እንዳበቃም ተገልጿል።

በቀጣይ አስር አመታትን የሚዘልቅ አዲስ ስትራቴጂክ ፕላንም በዝግጅት ሂደት ላይ ይገኛል።

ፕላኑ በክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ፣በሃዲያ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያና በከተማ አስተዳደሩ የጋራ ትብብር እየተሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል።

በሀዲያ ዞን ሾኔ ከተማ አስተዳደር በቀጣይ በሚተገበረው የአስር ዓመት ስትራቴጂክ ፕላን ዝግጅት እና ችግሮች ልየታ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የተደረገው ሰፊ ውይይት ለፕላኑ አተገባበር የተሻለ ሀሳብ ተሰጥቶበት በታላቅ መግባባት ተጠናቋል ሲል የሾኔ ከተማ አስተዳደር የመንግስት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው የዘገበው።

በሀድያ ዞን በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በመሳተፍ የበኩሉን እንዲወጣ ተጠየቀ።በሀድያ ዞን ቦኖሻ ከተማ አስተዳደር ዞናዊ  የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ...
27/06/2024

በሀድያ ዞን በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በመሳተፍ የበኩሉን እንዲወጣ ተጠየቀ።
በሀድያ ዞን ቦኖሻ ከተማ አስተዳደር ዞናዊ የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሄዷል።

የማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የሀድያ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ ዶ/ር በፈቃዱ ገ/ሀና የሀድያ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ እቴነሽ ሙልጌታ፤ የሀድያ ዞን የመንግስት ረዳት ተጠሪዎች፤የሁሉም ወረዳ አስተዳዳሪዎችና የፓርቲ ኃላፊዎች፤ የተለያዩ የዞንና የወረዳዎች አመራሮችና ባለድርሻ አካላት በተሳተፉበት ተካሄዷል።

በመርሃ ግብሩ የተገኙት የሀድያ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ እቴናሽ ሙልጌታ ወጣቶች ለህልውና እርካታ የተለያዩ በጎ አድራጎት ተግባራት ላይ በባለቤትነት መሳተፍ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

በተለይም በትምህርት ላይ ያጋጠመውን ስብራት ለመጠገን ከዩኒቨርስቲዎች የተመለሱ ወጣቶች አጋዥ ትምህርት በመስጠት ላይ በአጽንኦት እንዲሳተፉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።

ወ/ሮ እቴነሽ አክለውም ወጣቶች ከበጎ ተግባራት ጎን ለጎን በማህበራዊ ሚዲያ በሚሰራጩ የሀሰት ትርክቶች ሳይወሰዱ የአከባቢውን ሰላም ለማስጠበቅ መስራት እንዳለባቸው ገልጸዋል።

መርሃ ግብሩን ያስጀመሩት የሀድያ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ ዶ/ር በፈቃዱ ገ/ሀና በክረምት በወጣቶች የሚሰራው በጎ አድራጎት ስራ ሁሉን ያሳተፈና ቅንጅታዊ እንዲሆን አመራሩ ተቀናጅቶ መምራት እንዳለበትም አሳስበዋል።

የወጣቶች ስብዕና ግንባታ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት አለበት ያሉት ዶ/ር በፈቃዱ በመልካም ስብዕና የተካኑ ወጣቶች የፀና ሰላም እንዲኖር የጎላ ሚና እንደሚኖራቸው አስገንዝበዋል።

የሀዲያ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ተሻላ ደሳለኝ በዞኑ ከ540 ሺህ በላይ ወጣቶች በተለያዩ በጎ ፈቃድ አገለግሎት ዘርፎች እንደሚሳተፉ ተናግረዋል።

አቶ ተሻለ አያይዘውም በክረምት ወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳታፊ እንደሚሆን ጠቁመው በክረምት በጎ ፈቃድ መርሀ ግብሩ የመጠናከሪያ ትምህርት፣ደም ልገሳ፣ የአቅመ ደካሞች ቤት እድሳት፣የመንገድና ጥገና፣ ችግኝ ተከላ፣የከተማ ጽዳትና ሌሎችም ተግባራት እንደሚከናወንም አስረድተዋል።

የሀዲያ ዞን ሴቶችና ህፃናት መምሪያ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ዓለምፀሐይ ተሰማ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከማህበረሰብ ለማህበረሰብ የሚደረገው እንቅስቃሴ በተቀናጀ መንገድ መመራት እንዳለበትም አሳስበዋል ፡፡

ታሪኩ ሞላ

በሀድያ ዞን በ6 ወረዳዎች ያልተከተቡና ክትባቱን  ጀምረው  ያቋረጡ  ህፃናትን   የማሰከተብ ዘመቻ በጎምቦራ ወረዳ  ተጀመረ።የሀድያ ዞን ጤና መምሪያ የመድኃኒት  አቅርቦት  ስርጭት ሀላፊ አ...
27/06/2024

በሀድያ ዞን በ6 ወረዳዎች ያልተከተቡና ክትባቱን ጀምረው ያቋረጡ ህፃናትን የማሰከተብ ዘመቻ በጎምቦራ ወረዳ ተጀመረ።

የሀድያ ዞን ጤና መምሪያ የመድኃኒት አቅርቦት ስርጭት ሀላፊ አቶ ሚሻሞ ዋሞሌ በጎምቦራ ወረደ በሀብቾ ክትባት ባስጀመሩበት ወቅት ክትባቱ በዞኑ ከሚሰጥባቸው 5 ወረዳዎችና 1 የከተማ አሰተዳደር አንዱ የጎምቦረ ወረደ መሆኑን ጠቁመው፣በወረደውም ከሰኔ ለ10 ተከታታይ ቀናት በዘመቻ መልክ ቤት ለቤት በመግባት አንደሚሰጥም ተናግረው ፣የክትባት ዘመቻው እንድሳከም ድጋፍና ክትትል እንደማይለይም አሰረድተዋል።
በክትባት ዘመቻው ወቅት ሁሉም ባለሙያዎችና ባለድርሻዎች የተከተቡትንና ያልተከተቡትን እንዲሁም ክትባት ጀምረው ያልጨረሱትን በመለያት ተገቢውን አገልግሎትን በሀላፊነት መስጠት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል ።
የጎምቦራ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አማኑኤል አዳነ፤ ክትባቱን በወረዳው በሚገኙ 27 ቀበሌያት ለመስጠት ከባለሙየዎች ሥልጠና አንስቶ የሚያስፈልገውን ቅድመ ዝግጅት እንደተጠናቀቀ ገልጸው ፣የክትባት ዘመቻው ቤት ለቤት ያልተከተቡትንና ያቋረጡት መረጀ በማጠናቀር እንደሚሰጥም ተናግረዋል።

ኃላፊው አክለውም ከክትባት ጎን ለጎን ፣ የፌስቱላና የማህፀን ችግር ያለባቸውን እናቶች መርዳትና ሌሎችም የጤና አገልግቶች እንደሚሰጥም ተናግረዋል።

የሀብቾ ጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያ ወ/ሮ ቦጋለች ቸርነት በበኩላቸው የቤት ለቤት ክትባት ለመስጠት አሰፈላጊ መድኃኒትና የህክምና ቁሳቁሶች ዝግጅት ተደርጎ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

ከተማ ጨቅላ ህፃን ሲያስከትቡ የነበሩ ወ/ሮ ፀጋይነሽ ከበደም ህፃናትን በወቅቱ ማስከተብ ከበሽታዎች እንደሚከላከል አወቀው እያስከተቡ መሆናቸውን ነግረውናል።
ደለለኝ ጋሻሁን

ህብረተሰቡ ከሀሰተኛ መረጃዎች ይጠንቀቅ- የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት  ሆሳዕና -ሰኔ 20/ 2016 (ሀድያ ቴሌቪዥን) ከሶማሌላንድ ጋር የተደረገውን የመግባቢያ ስምምነት አስመልክቶ በዲጂታ...
27/06/2024

ህብረተሰቡ ከሀሰተኛ መረጃዎች ይጠንቀቅ- የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት

ሆሳዕና -ሰኔ 20/ 2016 (ሀድያ ቴሌቪዥን) ከሶማሌላንድ ጋር የተደረገውን የመግባቢያ ስምምነት አስመልክቶ በዲጂታል ሚዲያው ላይ እየተሰራጩ ያሉ ሀሰተኛ መረጃዎችን ህብረተሰቡ እንዲጠነቀቅ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት አሳሰበ።

ከሶማሌላንድ ጋር የተደረገውን የመግባቢያ ስምምነት አስመልክቶ በዲጂታል ሚዲያው ላይ እየተሰራጩ ያሉ ሀሰተኛ መረጃዎችን ህብረተሰቡ እንዲጠነቀቅ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት አሳስቧል፡፡

አካባቢያዊ፣ ክልላዊ እና ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮችን የሚመለከቱ ይፋዊ ግንኙነቶች በፅህፈት ቤቱ ይፋዊ የዲጂታል አማራጮች ብቻ እንደሚሰራጩ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት አስታውቋል።

የፅህፈት ቤቱን ሎጎ አላግባብ በመጠቀም የውሸት መረጃዎችን ከሚያሰራጩ አካላት ማህበረሰቡ እራሱን እንዲጠብቅም የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት አሳስቧል ሲል FBC ዘግቧል።

የፓሪስ 2024 ኦሎምፒክ ችቦ ሽኝት መርሃ ግብር  በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል  በሆሳዕና ከተማ ተካሄደ፡፡አንድነትን መተሳሰርን ፍቅርን እና አብሮነትን እንዲገነባ በማለም የተጀመረው "ኢትዮጵያ...
26/06/2024

የፓሪስ 2024 ኦሎምፒክ ችቦ ሽኝት መርሃ ግብር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ተካሄደ፡፡

አንድነትን መተሳሰርን ፍቅርን እና አብሮነትን እንዲገነባ በማለም የተጀመረው "ኢትዮጵያ ትወዳደር ተወዳድራም ታሸንፍ" በሚል መሪ ሃሳብ በትግራይ ክልል ጅማሮውን ያደረገው የ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ የችቦ ቅብብል ንቅናቄ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የነበረውን ቆይታ አጠናቆ ዛሬ በሆሳዕና ከተማ አሸኛኘት ተደርጎለታል::

በሽኝት መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የክልሉ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘሪሁን እሸቱ እንደተናገሩት፤ ኦሎምፒክ በዓለም ካሉ ስፖርት ውድድሮች ላቅ ያለ መሆኑን ጠቁመው ስፖርት በሕብረተሰቡ ውስጥ የማህበራዊ ግንኙነት ኃይል እንደመሆኑ ችቦው በሀገሪቱ አንድነትን እና አብሮነትን እንደሚያጎልብት ተናግረዋል::
በመርሃ ግብሩ ንግግር ያደርጉት የክልሉ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ መዘረዲን ሁሴን በበኩላቸው፤ ኦሎምፒክ ከስፖርት ውድድርነቱ ባሻገር የተራራቁትን በማቀራረብ፣ የተጣሉትን በማሳታረቅ፣ በስፖርት ውድድሩ አሸናፊ ለሆኑት እውቅና በመስጠት ፍቅርን እንደሚያጎለብት ተናግረው ኢትዮጵያም በፓሪስ ኦሎምፒክ ተሳታፊ እንደመሆኗ በሀገር ውስጥ መተሳሰር እንዲጎለብት የችቦ ቅብብሎሽ ንቅናቄ ሚናው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል::

በመርሃ ግብሩ የማስ ስፖርትን ጨምሮ የሩጫ ውድድር በክልሉ አትሌቶች መሃከል የተደረገ ሲሆን በወንዶች የሶስት ሺ ሜትር በቀለ ተክሉ እና አብዱል መናን ከጉራጌ ዞን አንደኛ እና ሁለተኛ ሆነው ሲያጠናቅቁ ደረጀ ሲሳይ ከሀድያ ዞን ሶስተኛ ሆኖ ፈፅሟል:: በሴቶች የሶስት ሺ ሜትር ውድድር ሎምባሜ ደሳለኝ እመቤት ደሳለኝ እና ፅዮን ኤርቲሮ ከሀድያ ዞን ከአንድ አስከ ሶስት በመውጣት ማሸነፍ ችለዋል::

በመጨረሻም የፓሪስ 2024 ኦሎምፒክ ችቦ ተለኩሶ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር አስረክቧል::

በመኸር ወቅት ከ9 ሺህ 214 ሄክታር መሬት በላይ በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች ለመሸፈን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የአመካ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ገለጸ። ሆሳዕና-18/10/2016 (ሀድያ ቴሌቪ...
25/06/2024

በመኸር ወቅት ከ9 ሺህ 214 ሄክታር መሬት በላይ በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች ለመሸፈን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የአመካ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ገለጸ።

ሆሳዕና-18/10/2016 (ሀድያ ቴሌቪዥን) የአመካ ወረዳ የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ግዛው ኑኔ ለሀድያ ቴሌቪዥን በሰጡት አስተያያት በ2016 እና በ2017 ዓ/ም የምርት ዘመን በአዝርእትና ሆርቲካልቸር የሰብል ዓይነቶች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በመኸር ወቅት በሁለቱም የሰብል ዓይነቶች ከ9ሺ214 ሄክታር መሬት በላይ ለመሸፈን ዕቅድ አቅዶ ወደ ሥራ መግባት እንደተቻለ የገለጹት ኃላፊው ፤ ከታቀደውም ውስጥ በአንደኛው ዙር እርሻ ከ3 ሺህ 500 ሄክታር በላይ መሬት መታረስ እንደቻለ አብራርተዋል።

ፎርቆሴን ጨምሮ ታችኛው የወረዳ አከባቢዎች በሜካናይዝድ የእርሻ ቴክኖሎጂ እየታረሰ እንደሚገኝ የገለጹት የአመካ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ግዛው ኑኔ በትራክተር ለማረስ የማይመቹ አከባቢዎች ባህላዊ የእርሻ ዘዴዎችን በመጠቀም እየታረሰ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የዓመቱ የእርሻ ዝግጅት ጥሩ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፤አሁን በወረዳ ውስጥ ያለው የአፈር ማዳበሪያ በቂ አለመሆኑን እና የበልግ ዕቅዱንም ጭምር በዓመቱ ከታቀደው ዕቅድ 36% ብቻ ወደ አከባቢው መግባቱን ጠቁመው ይህም በበለግ ወቅት የገባ መሆኑንና ለመኸር ወቅት የገባ የአፈር ማዳበሪያ እንደሌለ ጠቁመዋል።

እንደ አምና የአፈር ማዳበሪያ እጥረት እንዳይፈጠር ከዞንና ከክልል ጋር በሚያደርጉት ተግባቦት አንጻር እጥረት እንደማይኖር እየተነገረ ነው ያሉት አቶ ግዛው ኑኔ ፤ በወረዳ ደረጃ ለአርሶአደሮች መጥቶ ካልደረሰ ስጋት መሆኑ እንዳልቀረም አስረድተዋል።

ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የምርጥ ዘር አቅርቦት አንዱ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ፤ ከአከባቢው አግሮ ኢኮሎጂ ጋር የሚስማሙ ምርጥ የስንዴ ዘር 300 ኩንታል እንዲሁም ምርጥ የጤፍ ዘር 50 ኩንታል ለማስገባት ዝግጅት እንደተደረገም ተናግረዋል።

ከአቅርቦት አንጻር ከአምና የተሻለ እንቅስቃሴ መኖሩን የገለጹት ኃላፊው ፤ ከዞንም ሆነ ከክልል እየተሰጠ ያለው ተስፋ ጥሩ በመሆኑ አርሶ አደሮች ያለምንም ስጋት የማሳ ዝግጅታቸውን አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በማቴዎስ መኔዶ

ሀዲያ ስፖርት በሀዲያ ቲቪ ዛሬ ምሽት 2:00 ሰዓት የሀዲያ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ከኢንስትራክተር ሙሉነህ ማሞ ጋር በመተባበር ላለፉት 12 ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው ስልጠና አጠ...
24/06/2024

ሀዲያ ስፖርት

በሀዲያ ቲቪ

ዛሬ ምሽት 2:00 ሰዓት

የሀዲያ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ከኢንስትራክተር ሙሉነህ ማሞ ጋር በመተባበር ላለፉት 12 ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው ስልጠና አጠናቋል ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ክለቦች ሻምፒዮን የመጨረሻው ውድድር ሰኔ 24 እንደሚካሄድ ይታወቃል ። ሀዲያ ዞን የቦክስ ቡድን ዝግጅቱን በተጠናከረ መልኩ እየሰራ ይገኛል።

ከሆሳዕና ከተማና አከባቢው የተወጣጡ የቀድሞ እና አሁን ላይ በተለያዩ ክለቦች እየተጫወቱ የሚገኙ ተጨዋች ተሰብስበው የመሰረቱ ኳስ_ቡድን በትላንትናው እለት በአቢዬ ኤርሳሞ መታሰቢያ ስታዲየም ከወልቂጤ ከተማ ጤና ቡድን ጋር የወዳጅነት ጨዋታ በማድረግ 6 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል ።

ሀዲያ ሆሳዕና ከሁለት ተከታታይ ሳምንታት ሽንፈት በኃላ ድሬዳዋ ከተማን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል ። በጨዋታው ከ27ኛው ሳምንት የአምስት ተጨዋቾች ቅያሪ አድርጎ የገባው የአሰልጣኝ ግርማ ታደሰ(መንቾ) ቡድን ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ ማድረግም ችሏል ።

ሀዲያ ስፖርት በዛሬው ፕሮግራሙ ከላይ ባተነሱ ጉዳዮች ላይ ያዘጋጀውን ፕሮግራም ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ እንድትከታተሉ ግብዣችን ነው !



በሳምንት አንድ ቀን
በየሳምንቱ ሰኞ ምሽት 2.00 ላይ ይጠብቁን !

Satellite Ethiosat; NSS-12
Frequency: 11105
Symbol Rate: 45000
Polarization ; H

[ታሪኩ አበራ]

Ka maaraqqi hagayyi Abuulli baxina harshisaancho ammani afisimmina quux moo'oo manninne sheeqqarama baxamoolli ihukkisa ...
24/06/2024

Ka maaraqqi hagayyi Abuulli baxina harshisaancho ammani afisimmina quux moo'oo manninne sheeqqarama baxamoolli ihukkisa Hadiyyi zoo'n won gassaanchi Anniyyi Abb Maatiwoos wocakko'o.

Ka maaraqqi hagayyi abuullina 160 k*m hanaan ihoo harshisaancho abuullaanina afisimmina qoodamaa baxamukkuuyyi yoo'isa kurakkam hadiyyi zoo'n Abuulli shoqqi la'm beyyi awwonsaanchi Yohannis Abb Tashaal kabad afeebe'e 113 k*mii hanaan ihoo harshisaancho woradduwwina afisamukkisam caakkisakko'ookko.

Abuulli shoqqi la'm beyyi awwonsaanchi kurakko'isanne harshisaanchii midaadinne sire'i gudishshi qeddi bee'isa kurakka'a abuullaan ammani sire'e aa'amoo'isinam asso higisakko'ookko.
Abb Tashaal edakkahim mat mat hegeegguwwanne harshisaancho afishshina issakkam maratonne moo'amookki fongoga ifisimmina quux moo'oo baxxanchuwwinne qoxxamaa baxamoolli ihukkisam caakkisakko'ookko.

Abb Tashaal caakkisakko'isanne Zoonoomannem 149 heektaar uulla annanni annanni wix sire'inne ifisimmina qoodamukkan ihaa kabe 127 k*m uulli gudukkisam caakkisakko'ookko.

Harshisaancho afisimmina baxakkam woradduwwi lambe'ii mat lee'm worad ihaa woraxxi won gassaanchi Damis Abb Taaddal woraxxisoomannem Higukki hiinchonne harshisaanchi afisimmi qeddi hee'ukkisa kurakka'a ka maaraqqisanne mah qeddim bee'eka abuullaanina afishshina qoxxamaa baxamoolli ihukkisam kurakko'ookko.

Hadiyyi zoo'n won gassaanchi Anniyyi Abb Maatiwoos Harshisaanchi abuullaan gudisukki uulli qaxoominne moo'amaa afoo'isinaa afishshi maratonne moo'amookki gamo hoo'lanchina Hundem quux moo'oo manninnem sheeqqaramaa baxamoolli ihukkisam caakkisakko'ookko.

Abb Maatiwoos edakkahim Woradduwwannem harshisaanchi abuullaa'n anganne afookki marat gamiinse musuusimmi muccur ihoo'isina quux moo'oo baxxanchuwwi qoxxamaa baximmi hasisoo'isa kurakkaa eekka issobee'i woraxxi awwonsaanonne mixxeelluwwanne hasisoo murato massamoohan ihukkisam kurakko'ookko.

Won gassanchimi ka maaraqqi hagayyi abuullina gudukki uulluwwa annanni annanni woradduwwanne abuullaa'n bax marato daadeesha issakko'isim la'aamookko.

Taariiku molla

ንፁህ የመጠጥ ውኃ በማጣታቸው ምክንያት ለችግር እየተዳረጉ መሆናቸውን  በአመካ ወረዳ የጊዳሻ ቀበሌ ነዋሪዎች ተናገሩ። ሆሳዕና፣ ሰኔ 17፣2016 ዓ/ም (ሀድያ ቴሌቪዥን) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ...
24/06/2024

ንፁህ የመጠጥ ውኃ በማጣታቸው ምክንያት ለችግር እየተዳረጉ መሆናቸውን በአመካ ወረዳ የጊዳሻ ቀበሌ ነዋሪዎች ተናገሩ።

ሆሳዕና፣ ሰኔ 17፣2016 ዓ/ም (ሀድያ ቴሌቪዥን) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀድያ ዞን በአመካ ወረዳ ንፁህ የመጠጥ ውሃ በማጣታቸው ምክንያት ለችግር እየተዳረጉ መሆናቸውን የጊዳሻ ቀበሌ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ለሀድያ ቴሌቪዥን አስተያየታቸውን ከሰጡ የቀበሌው ነዋሪዎች መካከል አቶ ደሱ በቀለ ፣ አቶ ዘውዴ አቡዋ እንዲሁም አቶ ብርሃኑ በቀለን ጨምሮ ሌሎችም መንግስት የህብረተሰብ ተጠቃሚነትን መሰረት በማድረግ ንፁህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ያስገነባ ቢሆንም የጄኔሬተር ነዳጅ ወጪ ባለመቻላቸው ምክንያት የንፁህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት እንዳላገኙ ተናግረዋል።

ከዚህም የተነሳ ህብረተሰቡ ንፁህ የመጠጥ ውኃ ለማግኘት ሩቅ ቦታ የሚሄዱ ከመሆናቸውም ባሻገር ንፁህ የመጠጥ ውሃ በማጣታቸው ምክንያት ንፁህ ያልሆነ ውሃ በመጠጣት ለችግር እየተዳረጉ መሆናቸውን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

ነዋሪዎቹ ለሚመለከታቸው ክፍሎች በተደጋጋሚ ጥያቄ ያቀረቡ ቢሆንም ምላሽ እንዳልተሰጠ የገለጹት የጊዳሻ ቀበሌ ነዋሪዎች ፤ የተገነባው የውሃ ፕሮጀክት ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጥ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ያለውን ችግር በአፋጣኝ እንዲፈቱም ጠይቀዋል።

የአመካ ወረዳ ውሃ፣ መስኖ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ጽ/ቤት ኃላፊ ተከተል ጋሼ በበኩላቸው ፤ በወረዳ ያለው ንፁህ የመጠጥ ውሃ ተደራሽነት ዝቅተኛ እንደሆነና 24.15% ብቻ መሆኑን በመግለጽ በዘመናዊ መንገድ በብዙ በጀት ተገንብቶ አገልግሎት ካልሰጡ የውኃ ፕሮጀክት አንዱ የጊዳሻ ውኃ ፕሮጀክት ነው ብለዋል።

ፕሮጀክቱ በነዳጅ የሚሰራ መሆኑን ያነሱት ሀላፊው፤ የነዳጅ ዋጋ ከመጨመሩ ጋር ተያይዞ ህብረተሰቡ የነዳጅ ፍጆታ ወጪ ሊሸፍን ባለመቻሉ የውሃ ፕሮጀክቱ አገልግሎት ሊሰጥ አልቻለም ብለዋል ።

ይህንን ችግር ለመቅረፍ ከኤሌክትሪክ መስመር ጋር ለማገናኘት ጥናቶች እየተደረጉ እንደሚገኙ የገለጹት ኃላፊው፤ ጉዳዩን የወረዳው የውኃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ጽ/ቤት ለብቻ የሚፈታ ጉዳይ አለመሆኑንና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የህብረተሰቡን ንፁህ የመጠጥ ውሃ ችግር በቅርብ ጊዜ እንደሚፈታ ተናግረዋል።

በማቴዎስ መኔዶ

Hawaassi Yunversiite'i istaadiyoomanne issamukkuuyyi yookki 28 Saanti Itophphe'i primeer liiganne exxamukki Hadiyya Hosa...
21/06/2024

Hawaassi Yunversiite'i istaadiyoomanne issamukkuuyyi yookki 28 Saanti Itophphe'i primeer liiganne exxamukki Hadiyya Hosaanii Diredaawwi gaalchi lellonne Hadiyya Hosaan 3:1 ihaakko mishinne Diredaawwi gaalcha kaa'ukko.

Hadiyya Hosaa'n goola aagganneme guzumo'inne aphphisamukki xulbe'e Baqqal Girma'a 2 daqiiqanne, Wuubisheet Qaala'aab 65' Haafitayye Sammar 88 daqiiqanne xigisameena xanamaakko.

Ahimmad Makki Diredaawwa kaa'anchi gatisoobee'i mat goola 96 daqiiqanne xigiseena xanaakko.

Lelloomannem Teewdiroos Taaffas e'lookki xulbe'e amajjinne danaam lello moo'ishshinnee ee'isame goolina ihoo xulbe'em gudisaa uwweena xanaakko.

Ka kaachcha awwonaahim Hadiyya Hosaan mulli lelli issameebe'e 38 tako'inne 9 gabala amadaa siidamookko.

Beeddeena afukki Itophphe'i primeer liiqqi lellonneme awwonookki ammanenne Hadiyya Hosaan 29 saantanne Itophphe'i Madiininnee 30 saantanne Itophphe'i Bunna'inne exxoohan ihookko.

Fiitaamo Desta

ሀዲያ ሆሳዕና በውድድር ዓመቱ ስምንተኛውን ድል ተቀዳጀ!በ28ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕርሜየር ሊግ ሀዲያ ሆሳዕናን ከድሬደዋ ከተማ ባገናኘው ጨዋታ ነብሮቹ በ27ኛው ሳምንት በወላይታ ዲቻ ከተሸ...
21/06/2024

ሀዲያ ሆሳዕና በውድድር ዓመቱ ስምንተኛውን ድል ተቀዳጀ!

በ28ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕርሜየር ሊግ ሀዲያ ሆሳዕናን ከድሬደዋ ከተማ ባገናኘው ጨዋታ ነብሮቹ በ27ኛው ሳምንት በወላይታ ዲቻ ከተሸንፉበት ጨዋታ የአምስት ተጨዋች ለውጥ አድርገው ወደ ሜዳ ሲገቡ በአንፃሩ ድሬዎች በ27ኛው ሳምንት ጊዮርጊስን ካሸንፉበት ጨዋታ የአራት ተጨዋች ለውጥ አድርገው ወደ ሜዳ ገብተዋል::

በመጀመሪያው አጋማሽ ጨዋታው በተጀመረበት የመጀመሪያ ደቂቃ ባለፉት ሳምንታት ጥሩ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የተመለከትነው የሀዲያ ሆሳዕና የአማካይ ስፍራ ተጨዋች ቴዎድሮስ ታፈሰ ከግራ መስመር የቆመ ኳስ ወደ ግብ አሻምቶ ግርማ በቀለ በግምባሩ ኳሷን ከመረብ አዋህዶ ነብሮቹ መሪ ማድረግ ችሏል::

ከግቧ መቆጠር በኃላ ድሬዎች ኳስን መሰረት አድርገው ለማጥቃት ቢሞክሩም ጥሩ የጎል ዕድል መፍጥር ተስኗቸዋል:: በአንፃሩ ነብሮቹ ከግቡ መቆጠር በኃላ በተመስገን ብርሃኑ፣በደስታ ዋሚሾ እና በቴዎድሮስ ታፈሰ ወደ ግብ የተቃረበ እንቅስቃሴ ቢያደርጉም ተጨማሪ ግብ ሳያገኙ የመጀመሪያው አጋማሽ ተጠናቆ ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል::

በሁለተኛው አጋማሽ ድሬዎች ነጥብ ይዘው ለመውጣት ለማጥቃት ሙከራዎችን ያደረጉ ሲሆን በተለይም በ54ኛው ደቂቃ ካርሎስ ዳምጠው የቆመ ኳስ አክርሮ ወደ ግብ ቢመታም ወጣቱ ግብ ጠባቂ ያሬድ በቀለ ከግብነት ኳሷን ታድጕል::

በአንፃሩ ነብሮቹ በሁለተኛ አጋማሽ ውጤቱን አስጠብቀው ለመውጣት በመልሶ ማጥቃት የመረጡ ሲሆን በ65ኛው ደቂቃ ከቆመ ኳስ ተጨራርፎ ወጣቱ ተስፈኛው ቃልአብ ውብሸት በእርጋት ኳስን ከመረብ አዋህዶ ነብሮቹን በሁለት የግብ ልዩነት መምራት ችለዋል::

ሀዲያ ሆሳዕና ጨዋታውን በሁለት ግብ መምራት ከጀመረ በኃላ በውድድር ዓመቱ የመጨዋት ዕድል ያለገኙ ተጨዋቾች ወደ ሜዳ በመግባት ጥሩ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ በ88ኛው ደቂቃ ተቀይሮ ወደ ሜዳ የገባው ሰመረ ሃፍታይ የድሬዎችን ተከላካይ ተጠቅሞ ነብሮቹ ሶስት ለ ዜሮ መምራት ችለዋል:: ድሬዎች በመጨረሻ ደቂቃ ግብ ቢያስቆጥሩም ነብሮቹ ጨዋታውን ሶስት ለአንድ በሆነ ውጤት አሸንፈዋል::

ውጤቱን ተከትሎ ሀዲያ ሆሳዕና በ38 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጡ ድሬዎች በ40 ነጥብ 8ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል::

የግብርና ግብዓቶችን በወቅቱ ለአርሶ አደሮች ተደራሽ በማድረግ የተቀናጀ የመኸር ወቅት ግብርና በታቀደው ልክ ለማሳካት በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ የሀድያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዎስ አኒዮ...
21/06/2024

የግብርና ግብዓቶችን በወቅቱ ለአርሶ አደሮች ተደራሽ በማድረግ የተቀናጀ የመኸር ወቅት ግብርና በታቀደው ልክ ለማሳካት በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ የሀድያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዎስ አኒዮ ተናገሩ።

ሆሳዕና-14/10/2016 (ሀድያ ቴሌቪዥን) የሀድያ ዞን ግብርና መምሪያ በመኸር እርሻ ከ149 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለማልማት አቅዶ እየሰራ ይገኛል።

የሀድያ ዞን ግብርና መምሪያ የመኸር የተቀናጀ የግብርና ልማት ሥራዎች የንቅናቄ መድረክ በሆሳዕና ከተማ አካሄዷል።

የሀድያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዮስ አኒዮ በዞኑ የግብርና ግብዓቶችን በወቅቱ ለአርሶ አደሮች ተደራሽ በማድረግ የተቀናጀ የመኸር ወቅት ግብርና በታቀደው ልክ ለማሳካት በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ ተናግረዋል ።

የማዳበሪያ እጥረት ለመቅረፍ ቅድሚያ ለሚዘሩ ዘሮች በዞኑ ያለውን ማዳበሪያ ተደራሽ ማድረግ እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል።

ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ዞኑ ምቹ የአየር ሁኔታና ምህዳር ያለው መሆኑን የገለፁት አቶ ማቲዎስ አኒዮ በመኸር ወቅት የታቀደውን እቅድ ለማሳካት ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የሀድያ ዞን ግብርና መምሪያ አቶ ተሻለ ዮሐንስ የመኸር እርሻ፣ የአትክልትና ስራስር ሰብሎች ፣ የአረንጓዴ አሻራ፣ የሌማት ትሩፋት ፣ የቡናና ቅመማቅመም ምርት እና የእንሰት ምርት ማሳደግ ላይ በመኸር ወቅት ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

በዚህም በመኸር እርሻ ከ149 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ነው ያነሱት።

በራስ አቅም ራስን በመቻል ተረጂነትን ለማስቀረት በአርሶ አደሮች ላይ የአመለካከት ለውጥ በማምጣት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።

የሀድያ ዞን ህብረት ሥራ ማህበር መምሪያ ኃላፊ አቶ ታደለ ኢቴቦ ክልሉ ከ166 ሺህ በላይ ማዳበሪያ ለዞኑ መላኩን ገልፀው፤ ከ113 ሺህ በላይ ማዳበሪያ ለህብረት ሥራ ማህበራት ተደራሽ መደረጉን አንስተዋል።

ፋሲል ወንድሙ

Hadiyyi zoo'n abuulli awwonsi 2016 H.D hagayyi aga'n abuullina 149.8 kaak*m heekitaar uullii hanaan annanni annanni hurb...
21/06/2024

Hadiyyi zoo'n abuulli awwonsi 2016 H.D hagayyi aga'n abuullina 149.8 kaak*m heekitaar uullii hanaan annanni annanni hurbaatinne ifiisimmina qoodaa 7.78 kaak*miinse hanaan ihookki kuntaal atoota siideena baxoolli ihukkisa Hadiyyi zoo'n abuulli awwonsi la'isaakko.

Awwonsoomim hagayyi aga'n abuullanne,duubbi kaashshanne,shaano'i fiishsho'i kaashshanne,leemaaxxi fafoomanne,bunannee shaahe'i enjannee wees kaashsha haraassimminne zoonoomannem hundem abuulli atootinne 2016/17 H.D atooxxi misha li'isimmina xiniinsi uwwama baxamoo'isim caakkaakko.

Hadiyyi zoo'n abuulli awwonsi hagayyi aga'n hunda edaakko abuulli lichchi baxonne hundem sheeqqaro'uwwinnee quux moo'ookki baxxanchinne atoorachchi issamaakko.

Fiitaamo Dasta

በመገባደድ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ28ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ ሲቀጥል በተከታታይ ሳምንታት ሽንፈት የገጠመው ሀድያ ሆሳዕና በተከታታይ ሳምንታት ድል ካደረገው ድሬደዋ ከተማ ...
21/06/2024

በመገባደድ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ28ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ ሲቀጥል በተከታታይ ሳምንታት ሽንፈት የገጠመው ሀድያ ሆሳዕና በተከታታይ ሳምንታት ድል ካደረገው ድሬደዋ ከተማ ጋር የሚገናኙ ይሆናል::

በፕሪሚየር ሊጉ ጠንካራ የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ካላቸው ክለቦች መሃከል ተጠቃሽ የሆነው ሀድያ ሆሳዕና በተከታታይ ሁለት ሳምንት በሐዋሳ ከተማ እና በወላይታ ዲቻ ሁለት ለአንድ በሆነ ውጤት መሸነፉ አይዘነጋም::

በጊዜያዊው አሰልጣኝ ግርማ ታደሰ (መንቾ) ሚመሩት ነብሮቹ ባለፉት ሰባት ሳምንታት አራት ሽንፈት አስተናግደው በሁለቱ አቻ ተለያይተው ከአንድ ጨዋታ ብቻ ሶስት ነጥብ በማግኘት ምንም እንኳን የመውረድ ስጋት ባይኖርባቸውም የውጤት ቀውስ ውስጥ ይገኛሉ::

በአንፃሩ የምስራቁ ተወካይ የሆነው ድሬደዋ ከተማ ከአሰልጣኝ አስራት አባተ ጋር ተለያይቶ በጊዜያዊው አሰልጣኝ ኮማንደር ሽመልስ አበበ መመራት ከጀመረ ወዲህ በሊጉ ብርቱ ተፎካካሪ መሆን የቻለ ሲሆን በኢትዮጵያ መድን አምስት ለምንም በ25ኛ ሳምንት ከተረታ በኃላ በ26ኛ ሳምንት ወልቂጤ ከተማን እና በ27ኛው ሳምንት የአምና የሊጉ ባለክብር የሆነውን ቅዱስ ጊዮርጊስን በመርታት ለሁለት ተከታታይ ሳምንታት ባለድል በመሆን ጥሩ ግስጋሴ ላይ ይገኛል::

ሁለቱም ክለቦች የመውረድም ይሁን የሻምፒዮንነት ቦታ ማግኘት የማይችሉ ቢሆንም እንኳን ከጨዋታው ሚያገኙት ሶስት ነጥብ በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ ላይ የተሻለ ቦታ ለመያዝ አለፍ ሲልም ለሁለቱም ጊዜያዊ አሰልጣኞች ስለ ቀጣይ ዓመት ኮንትራት መራዘም እና መፍረስ ላይ ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሎ ይገመታል::

ድሬደዋ ከተማ በሊጉ ካደረጋቸው 27 ጨዋታዎች አስራ አንዱን በማሸነፍ በሰባቱ አቻ በመለያየት በ9 ጨዋታ በመሸነፍ በ40 ነጥብ 8ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ሀድያ ሆሳዕና ከ27 ጨዋታዎች ሰባት ጨዋታ በማሸነፍ በ14 ጨዋታዎች አቻ በመለያየት በ6 ጨዋታዎች በመሸነፍ በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ ላይ 11ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል::

በድሬደዋ እና በሀድያ ሆሳዕና መሃከል እስከ ዛሬ ስምንት ጨዋታዎች የተገናኙ ሲሆን ሶስት ሶስት በመሸናነፍ በሁለቱ አቻ ተለያይተዋል:: ዛሬ ሚያደርጉት ጨዋታ በታሪካቸው ለዘጠነኛ ጊዜ ሲሆን ጨዋታው በሐዋሳ ዩንቨርስቲ ስታዲዮም ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ላይ ይካሄዳል::

በናሆም ዩሐንሰ

Shaano'i bojja kaasimmi hurbaatoomina awwaaxximmiinsem higaa buchchi agamoobee'isina hara'moohan ihukkisa Hadiyyi zoo'n ...
21/06/2024

Shaano'i bojja kaasimmi hurbaatoomina awwaaxximmiinsem higaa buchchi agamoobee'isina hara'moohan ihukkisa Hadiyyi zoo'n la'm beyyi gassaanchi Dr. Bafiqaadu W/Hanna wocakko'o.

2016 H.D Shaano'i bojji kaasimmi marat leemmo'i woraxxi Hayse'i ga'nanne Hadiyyi zoo'n shiqqeen adi'l bax awwonsaan annanni annanni woradduwwiinsi siidamamukki gassaanii quux moo'ookki baxxanchuwwi siidamamukki beyyonne asheessiisakko'i
Hadiyyi zoo'n biltsiginna'i shoqqi awwonsaanchii hara'maanchi adi'l weeshamaanchi Abb. Saamu'eel Baanxuur, meera gaaga'isimminaa minaadaba awwaaxxaan issimmina shaano'i bojji shiqqeen awwaad yoo'isam wocakko'ookko.

Shaano'i bojji hegeegonne muccur hafachcha qooccimmiinse biiren meera gaaga'isiminam shiqqeen beyyi yoohan ihukkisam caakkisakko'ookko.

Balloomannem asheeramukki shaano'i bojji kaasimmi baxoomam zoo'nisanne hundem woradduwwinam haraarisa afisimmina qoodakka'a baxakkamulli ihukkisa hadiyyi zoo'n abuulli awwonsi la'm beyyi awwonsaachi Abba. Tashaal Yoohaannis la'isakko'ookko.

የሀድያ ዞን ግብርና መምሪያ የመኸር የተቀናጀ የግብርና ልማት ሥራዎች የንቅናቄ መድረክ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሆሳዕና ከተማ እያካሄደ ነው።ሆሳዕና -14/10/2016 (ሀዲያ ቴሌቪዥን)...
21/06/2024

የሀድያ ዞን ግብርና መምሪያ የመኸር የተቀናጀ የግብርና ልማት ሥራዎች የንቅናቄ መድረክ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሆሳዕና ከተማ እያካሄደ ነው።

ሆሳዕና -14/10/2016 (ሀዲያ ቴሌቪዥን) የመኸር እርሻ፣ የአትክልትና ስራስር፣ ሰብሎች ፣ የአረንጓዴ አሻራ፣ የሌማት ትሩፋት ፣ የቡናና ቅመማ ቅመም ምርት እና የእንሰት ምርት ማሳደግ ላይ በመኸር ወቅት ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተጠቁሟል።

በወረዳ ደረጃ ትኩረት ተሰጥቶ በሚሰራባቸው የመኸር ወቅት ጥምር ግብርና ላይ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ አቅጣጫ የሚሰጥ የውይይት መድረክ መሆኑ ተጠቁሟል ።

የፍራፍሬ ልማት ለቤተሰብ፣ ለማህበረሰብና ለሀገር የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን በውይይቱ ተገልጿል።

በሌማት ትሩፋት የተጀመረው 30 40 30 የሙዝ ምርት ለማሳደግ በሁሉም አከባቢዎች ተደራሽነቱን ለማስፋፋት በዕቅድ እየተሰራ መሆኑም ተገልጿል ።

ፋሲል ወንድሙ

በሀድያ ዞን በሌሞ ወረዳ በሃይሴ ቀበሌ የአረንጓዴ አሻራ  የችግኝ ተከላ መራሃ ግብር  ማስጀመሪያ በፎቶ
21/06/2024

በሀድያ ዞን በሌሞ ወረዳ በሃይሴ ቀበሌ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መራሃ ግብር ማስጀመሪያ በፎቶ

በሀድያ ዞን በሌሞ ወረዳ በሃይሴ ቀበሌ የአረንጓዴ አሻራ  የችግኝ ተከላ መራሃ ግብር  ማስጀመሪያ ና የመህር እርሻ ማስጀመሪያ ፕሮግራም  ማስጀመሪያ  ተካሄዷል።በመራሃ ግብሩ ላይ የሀድያ ዞን...
21/06/2024

በሀድያ ዞን በሌሞ ወረዳ በሃይሴ ቀበሌ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መራሃ ግብር ማስጀመሪያ ና የመህር እርሻ ማስጀመሪያ ፕሮግራም ማስጀመሪያ ተካሄዷል።

በመራሃ ግብሩ ላይ የሀድያ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ ዶ/ር በፍቃዱ ወ/ሃና ፣የሀድያ ዞን ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ሳሙኤል ባንጡራ ፣የዞን መምሪያ ኃላፊዎች ፥የወረዳ አስተዳዳሪዎችና አስተባሪዎች፣የግብርና ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተገኝተዋ።

በዕለቱም የምርጥ ዝርያ የአቮካዶ ችግኝ ተከላም ተካሄዷል።

በክልሉ መንገዶች ባለ ስልጣን ሆሳዕና ዲስትሪክት የኩናፋ ፉገጃ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት  በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነበሀድ...
20/06/2024

በክልሉ መንገዶች ባለ ስልጣን ሆሳዕና ዲስትሪክት የኩናፋ ፉገጃ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ

በሀድያ ዞን በአመካ ወረዳ ግንባታው ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው የጠጠር መንገድ ፕሮጀክት የህብረተሰቡን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስርን እንደሚያጠናክርም ተገልጿል ።

ከ2 ሺህ 5 መቶ ሄክታር  በላይ ማሳ በዝንጅብል ተክል መሸፈን መቻሉን በሀድያ ዞን የምዕራብ ሶሮ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።ከዘርፉ 623 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅም ተ...
20/06/2024

ከ2 ሺህ 5 መቶ ሄክታር በላይ ማሳ በዝንጅብል ተክል መሸፈን መቻሉን በሀድያ ዞን የምዕራብ ሶሮ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

ከዘርፉ 623 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅም ተጠቁሟል።

በሀድያ ዞን የምዕራብ ሶሮ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ቡናና ቅመማ ቅመም ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ጩፋሞ ሎምበሶ ለሀድያ ቴሌቪዥን እንደገለጹት በወረዳው በቡናና ቅመማ ቅመም ምርት በማሳደግ አርሶ አደሮችን የዘርፉ ተጠቃሚ ለማድረግ የግብዓትና ሙያዊ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አንስተው፤ በወረዳው ለዝንጅብል ምርት አመቺ በሆኑ 12 ቀበሌያት 2ሺህ 509 ሄክታር ማሳ መሸፈኑን ገልጸል።

በዚህም 6 መቶ 23 ሺህ 760 ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅም ጠቅሰው ዘርፉ ለአርሶ አደሮች ካለው ተጠቃሚነት አንጻር የማሳ ሽፋን ለመጨመርና የገበያ ትስስር ለመፍጠር እየተሠራ መሆኑን አቶ ጬፋሞ አንስተዋል።

በወረዳው በቸቾ ቀበሌ በዘርፉ ከተሰማሩ አርሶ አደሮች መካከል አቶ ተመስገን አረጋ፣ አየለ ለጫሞና ታገሰ ሱጌቦ እንደተናገሩት፤ ዝንጅብል የማምረት ተግባር በአነስተኛ ማሳ ብዙ ገቢ የሚገኝበት በመሆኑ ከዚህ በፊት በባለሙያ ምክር መሰረት በመሥራት ያገኙት ምርት በኑሯቸው ለውጥ እንዲመጣ አስተዋጽኦ በማድረጉ በአሁኑ ወቅት በማስፋፋት እንክብካቤ እያደረጉ መሆኑን ተናግረው በቀጣይም የገበያ ትስስር እንዲፈጠርላቸው አርሶአ ደሮቹ ጠይቀዋል።

በአድማሱ ወልዴ

20/06/2024
በሀድያ ዞን ጊቤ ወረዳ በዳንጋ ቀበሌ ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበት የተሰራው የሀንዶሼ አነስተኛ መስኖ ፕሮጀክት ተመረቀ።ከ26 ነጥብ 1 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበት የተገነበ...
20/06/2024

በሀድያ ዞን ጊቤ ወረዳ በዳንጋ ቀበሌ ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበት የተሰራው የሀንዶሼ አነስተኛ መስኖ ፕሮጀክት ተመረቀ።

ከ26 ነጥብ 1 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበት የተገነበው የሀንዶሻ አነስተኛ መስኖ የመስኖ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል።

ፕሮጀክቱ ከ65 ሄ/ር በላይ መሬት የሚያለማ ሲሆን 300 አባወራዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግም ተስፋ ተጥሎበታል።

በምረቃ መርሐ ግብሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ ዋና የመንግስት ተጠሪ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ፣ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አንተነህ ፍቃዱ፣የክላስተር አስተባባሪዎች እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

በሃዲያ ዞን ሶሮ ወረዳ ከ27 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተገነባዉ የአጃቾ አነስተኛ መስኖ ኘሮጀክት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በአቶ እንዳሻው ጣሰው ተመርቆ አገልግሎት መስጠት...
19/06/2024

በሃዲያ ዞን ሶሮ ወረዳ ከ27 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተገነባዉ የአጃቾ አነስተኛ መስኖ ኘሮጀክት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በአቶ እንዳሻው ጣሰው ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

ኘሮጀክቱ ከ750 በላይ የቤተሰብ አባላት ን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተጠቁሟል።

40 k*m minaadaba awwaaxxaan issoo qanqqichchi waagabaxxi muccur aggi wo'i pirojekti masae'amaakko Danaam gassi xa'michch...
19/06/2024

40 k*m minaadaba awwaaxxaan issoo qanqqichchi waagabaxxi muccur aggi wo'i pirojekti masae'amaakko
Danaam gassi xa'michchi ihaa dasaa hee'ukki qanqichikii waagabaxxi muccur aggi wo'i pirojekt 1 xibbinnee 22 kaak*m birinne baxamaa maase'amaakko.

ka maas seeranne siidammaa atoorassinummi qanqqichikii waagabaxxi minaadab wocamukkisanne qeeraa'l ammannuwwina muccur aggi wo'i bee'imminne wo'i hasanina qeeraa'l googo taake'imminne muccur ihubee'i wo'o awwaaxximminne annanni annanni kolbammi wo'i waaroo jabbuwwina biir ihamaa hee'amukkisa kuramaakko.

Kaballa maasse'amaa awwaado uwwimma asheeru qanqqichchi waagabaxxi wo'i pirojekt kannii illageen afam hee'ukki badallato gatiseena xanoohan ihukkisanne liiramamukkisa minaadab eddamaa woccamaakko.

Muccur aggi wo'i pirojektoomim 40 k*mi minaadabina awwaado uwwima xanoo pirojekt ihukkisam kuramaakko.

Adaana Bayyana

40 ሺህ ነዋሪዎችን ንጹህ የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ የሚያደርገው የቀንቅቾ ዋገበታ የውሃ  ፕሮጀክት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።በ122 ሚሊዮን ብር ተገንብቶ አገልግሎት መስጠት የጀመረው ፕሮ...
19/06/2024

40 ሺህ ነዋሪዎችን ንጹህ የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ የሚያደርገው የቀንቅቾ ዋገበታ የውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

በ122 ሚሊዮን ብር ተገንብቶ አገልግሎት መስጠት የጀመረው ፕሮጀክቱ በንፁህ የመጥጥ ውሃ እጦት ምክንያት ይደርስ የነበረውን ችግር የሚፈታ ነው።

በምረቃ ሥነሥርዓት አግኝተን ያነጋገርናቸው የዱና ወረዳ የቀንቅቾና የዋገበታ ነዋሪዎች እንደተናገሩት፤ ለረዥም ዓመታት ንፁህ የመጠጥ ውሃ እጦት ምክንያት ውሃ ፍለጋ ርቀት በመሄድ ንፁህ ያልሆነ ውሃ በመጠቀም ለተለያዩ ውሃ ወለድ በሽታ ሲጋለጡ እንደነበር ተናግረዋል።

በምረቃ መርሐ ግብሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ፣ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አንተነህ ፍቃዱ እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

አዳነ በየነ

በዱና ወረዳ ከ40 ሺህ በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ የታመነበት የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ ተጠናቆ ነገ  እንደሚመረቅ የሀድያ ዞን ውሃ፣ መስኖ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ...
18/06/2024

በዱና ወረዳ ከ40 ሺህ በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ የታመነበት የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ ተጠናቆ ነገ እንደሚመረቅ የሀድያ ዞን ውሃ፣ መስኖ፣ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ አስታወቀ።

ፕሮጀክቱ ከ122 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገበት ታውቋል።

የሀድያ ዞን ውሃና ማዕድን ኢነርጂ መምሪያ ኃላፊ አቶ መለሠ ሀይሌ እንደገለፁት ቀንቅቾ ንፁህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ ለ40 ሺህ ነዋሪዎች ንጹህ የመጠጥ ውሃ ለማቅረብ እንደሚያስችል ገልጸው፤ አሁን ላይ ያለውን 43 በመቶ የውሃ ሽፋን ከፍ ለማድረግ እንደሚሠራ ገልጸዋል።

ፕሮጀክቱ የክልል፣ የዞንና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮችና ሌሎች እንግዶች በተገኙበት ይመረቃል ተብሎ ይጠበቃል።

አዳነ በየነ

2016 H.D. 6.32 kaak*m fiishsho'o Gudishshina qoodaa 6.4 kaak*mii hanaan ihaakko annanni annanni fishsho'o kaashshina gud...
18/06/2024

2016 H.D. 6.32 kaak*m fiishsho'o Gudishshina qoodaa 6.4 kaak*mii hanaan ihaakko annanni annanni fishsho'o kaashshina gudisukkisa Gibe'i Woraxxi Abuulli kitaaphphi Min la'isukko.

Gibe'i woraxxi won Gassaanchi abb.Lintise Beetaale adi'l dissukki ogora awwoonimminne higukki soor hiinchuwwanne kaasamukki fishsho'i hafachchi amaxxanne e'lokki awwaado eebukkisa wocimminne;woradoom ka ammanenne mulli woradduwwina higisa uwweena xano fishsho'o gudisukkisa caakkisaakko'ookko.

Abb. Betaalle woradoomanne; bu'n atootanne xiniinsi uwwamaa baxamoo'isa wocaakka'a; ka gudukki fishsho'o hundem minaadabim mateeyyanne ihaa gudukki beeyyi aa'aa kasoo'isina asso higisakko'ookko.

Gibe'i woraxxi la'm beyyi gassaanchii abuulli k/mi'n awwonsaanchi abb. Shifar Dani'eel woradoomanne ka maaragenne 6.4 kaak*m fishsho'i gudukkisa caakkisimminne kanii illageen kaasamukki fiishsho'oom 95 ang amadukkisame la'isakko'ookko.

Woradoomanne annanni annanni hurbaatoominaa hafachchi amaxxa dabaseena xanoo fishsho'o kaasimminne minaadaphphi hurbaaxxi lubbatooma xassimminam xiniinsa uwwamaa baxamoolli ihukkisame wocakko'ookko.

Woradoo'm abuulli kitaaphphi mi'n la'm beyyi awwoonsaanchi abb.Abab Dajane,SLMS pirojektti awwonsaanchi abb.Abaati Hiriggii Buchchihii wo'o abooyyimmu sho'qi awwonsaanchi abb.Dabar Abrihaamee sawwite uwwamukkisanne 20 fishsho'o gudishshi beyyonne dut hagar fiishsho'o gudukkisa wociminne minaadabim ka fishsho'o haramamchchinne ga'qi quuxi issaa baximmi hasisookko yamaakko.

Fiitaamo Dasta

ከመደበኛ ሥልጠና ጎን ለጎን በሀገር ውስጥና በውጪ ሀገር በሥራ ለሚሠማሩ ዜጎች አጫጭር ስልጠናዎች እየተሰጠ እንደሚገኝ የሆሳዕና ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ገለጸ። የሆሳዕና ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን ...
18/06/2024

ከመደበኛ ሥልጠና ጎን ለጎን በሀገር ውስጥና በውጪ ሀገር በሥራ ለሚሠማሩ ዜጎች አጫጭር ስልጠናዎች እየተሰጠ እንደሚገኝ የሆሳዕና ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ገለጸ።

የሆሳዕና ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ አወል ሸንጎ እንደገለፁት ኮሌጁ በሁለት ዓለማዎች ትኩረት አድርጎ እየሠራ መሆኑን ገልጸው ፤ የመጀመሪያው መደበኛና አጫጭር ስልጠናዎችን በመስጠት በተለያዩ የሙያ መስኮች ላይ ዜጎችን አሰልጥኖ የሙያ ባለቤት ማድረግ መሆኑን እና በሁለተኛ ደረጃ ለአካባቢ ህብረተሰብ ጠቃሚ የሆኑ ቴክኖሎጅዎችን በመቅዳት ፣ በማለመድ ፣ በመፍጠር ለኢንተርፕራይዞች የማሸጋገር ሥራ መሥራት ነው ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ በመደበኛ በ16 የስልጠና መስኮች ላይ ከ4 ሺህ በላይ የሚሆኑ ሠልጣኞችን ተቀብሎ ስልጠና እየሰጠ እንደሚገኝ የገለጹት አቶ አወል ሸንጎ ስልጠናውን ከሌሎች የአካዳሚ ዘርፎች የተለየ የሚያደርገው በንድፈ ሀሳብ 30% እንዲሁም በተግባር 70% የሚሰለጥኑ መሆኑ ነው ብለዋል።

ኮሌጁ መደበኛ ስልጠና ከመስጠት ጎን ለጎን አጫጭር ስልጠናዎችን በሁለት ዓላማዎች ላይ እየሰጠ እንደሚገኝ የተናገሩት ዋና ዲኑ ፤ የመጀመሪያ በሀገር ውስጥ የተለያዩ ስልጠነዎችን ወስዶ ተደራጅተው የሥራ ዕድል እንዲያገኙ የሚያስችል ስሆን በሁለተኛው ደረጃ ለሥራ ስምሪት ወደ ውጪ ሀገር የሚሄዱ ዜጎች ማሰልጠን ነው ብለዋል።

ለዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር በሀገር ደረጀ 77 ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በሥራና ክህሎት ሚኒስትር ተመርጠው ሥልጠና በመስጠት ላይ እንደሚገኝ የገለጹት አቶ አወል ከእነዚህም ውስጥ የሆሳዕና ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አንዱ መሆኑንና የሚሰጠው ስልጠና በዜጎች ላይ የሚደርሱ ችግሮችን በማስቀረት ሂደት ላይ አውንታዊ ጠቀሜታ ያለ መሆኑንም አብራርተዋል።

የኮሌጁ አካዳሚክ ምክትል ዲን አቶ ድሌቦ አባተ በበኩላቸው ፦በክህሎት ሚኒስቴር በኩል በተመቻቸው መንገድ ኮሌጁ በሥራ ስምሪት ወደ ውጪ ሀገር የሚሄዱ ዜጎችን እያሰለጠነ እንደሚገኝና ይህም ዜጎች ስልጠና ወስዶ የሙያ ባለቤት ሆኖ የሙያ ሰርተፊኬት እንዲያገኙ የሚያስችል ከመሆኑም በላይ የተሻላ ክፍያ እንዲያገኙ የሚያስችል እንደሆነም አቶ ድሌቦ አብራርተዋል።

በበጀት ዓመቱ በአሁኑ ሰዓት ሁለተኛ ዙር ስልጠና እየተሰጣ እንደሚገኝ እና በመጀመሪያ ዙር 715 ሠልጠኞችን አሰልጥኖ ማውጣቱን የተናገሩት አቶ ድሌቦ አባተ በሁለተኛ ዙር 375 ገደማ ሠልጠኞች ስልጠና እየወሰዱ እንደሚገኝ እና ለሦስተኛ ዙር ደግሞ ሠልጣኞች እየተመዘገቡ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

ስልጠና እየወሰደ ከሚገኙት ውስጥ 90% ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል ነው ያሉት አቶ ድሌቦ የውጪ ሀገር የሥራ ስምሪት ስልጠና የሚውሰደው ጊዜ 21 ቀን መሆኑንና ዜጎች በህገ ወጥ ደላላዎች ሳይታለሉ ተገቢ ስልጠና ወስዶ በህጋዊ መንገድ እንዲሄዱ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በኮሌጁ ስልጠና በመስጠት ላይ ከተገኙ የሆቴል ማኔጀመንት መምህራን ውስጥ መምህርት ቅድስት ወ/ሰነበት እና መምህር ኢዮብ ሀምሶ በበኩላቸው ፤ በምግብ ዝግጅት ፣ በቤት አያያዝ እና በሌሎችም የተለያዩ ስልጠናዎችን እየሰጡ እንደሚገኝ በመግለጽ ስልጠናው ጠቃሚና አስፈላጊ ነው በማለት ተናግሯል።

በማቴዎስ መኔዶ

ሀዲያ ስፖርት በሀዲያ ቲቪ ዛሬ ምሽት 👉የሆሳዕና ከተማ ነዋሪ ሆኖ በልጅነቱ ጎፈር ሜዳ ላይ ኳስ ያልተጫወተ ፣ እሩጫ ያሮጠ ፣ ሳይክል ያልነዳ ፣ አልያም ሞተር ያልተለማመድ ልጅ ይኖራል ብሎ ...
17/06/2024

ሀዲያ ስፖርት

በሀዲያ ቲቪ

ዛሬ ምሽት

👉የሆሳዕና ከተማ ነዋሪ ሆኖ በልጅነቱ ጎፈር ሜዳ ላይ ኳስ ያልተጫወተ ፣ እሩጫ ያሮጠ ፣ ሳይክል ያልነዳ ፣ አልያም ሞተር ያልተለማመድ ልጅ ይኖራል ብሎ መገመት አዳጋች ነው ።

👉ሀዲያ ስፖርት በዛሬው ፕሮግራሙ የብዙ የሆሳዕና ልጆች ትዕዝታ ያለበትና የበርካታ ስፖርተኞች መፍለቂያ የሆነችው ተገኝቶ የሜዳውን አሁናዊ ሁኔታ ፣ ሰለሜዳውና መሰል ጉዳዮች ከተለያዩ የቀድሞ ስፖርተኞችና የስፖርት ቤተሰቡ ጋር ቆይታ አድርጓል !

👉ሀዲያ ሆሳዕና በ27ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በወላይታ ዲቻ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ተሸንፏል ። ነብሮቹ ካለፉት ሰባት ተከታታይ ጨዋታዎች በአራቱ ሽንፈት ያስተናገዱበት ምክንያት ምንድነው ?



በሳምንት አንድ ቀን
በየሳምንቱ ሰኞ ምሽት 2:00 ላይ ይጠብቁን !

Satellite Ethiosat; NSS-12
Frequency: 11105
Symbol Rate: 45000
Polarization ; H

[ታሪኩ አበራ]

Address

Hossana
Hossana

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hadiya.TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hadiya.TV:

Videos

Share

Category



You may also like