Mahir Endris

Mahir Endris Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Mahir Endris, Digital creator, .

25/04/2024

ሁለንተናዊ ብልጽግና ማለት ምን ማለት ነዉ?

ብልጽግና ምሉዕ የሆነ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊ፣ የሀገር ደህንነትና ውጭ ግንኙነት ልህቀት ውጤት ነው፡፡ ከፖለቲካው አንጻር ብልጽግና መካከለኛና አካታች የፖለቲካ እይታን ይከተላል፡፡

ከዚህ አንጻር ሲታይ ብልጽግና በቀኝና በግራ ዋልታዎች መካከል ሚዛን በመበጠበቅ በመደመር እሳቤ የተቃኘ የተረጋጋ የፖለቲካ ሀይሎች አሰላለፍና መስተጋብር የሰፈነበት ምህዳር የበለጸገ ፖለቲካ ማሳያ ነው፡፡ ሁሉም ማንነቶችና ፍላጎቶች እውቅናና ክብር አግኝተው የሚደመጡበት፣ ህግና ስርዓት የሰፈነበት አውድ ነው።
ቅቡልነት የተጎናፀፈ ሀገረ መንግሥት የተረጋገጠበት ነው። ፍትህና ርትህ እውን የሆነበት፤ የኢትዮጵያ ህዝቦች ሉዓላዊ የስልጣን ባለቤትነት የሰፈነበት ነው፡፡

በሌላ በኩል ሁለንተናዊ ብልፅግና የብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚ እውን የሆነበት ነው፡፡ ሁለንተናዊ የግብርናና ኢንዱስትሪ ልማትና ዕድገት የተሰናሰለበት ነው፡፡ ገቢ ምርቶች በብዛትና በጥራት የተተኩበት፣ የኤክስፖርት ምርቶችም በዚያው ልክ በብዛትና በጥራት የተመረቱበትና የውጭ ምንዛሬን ማሳደግ የተቻለበት፣ ለሰፊ የተማረ የሰው ኃይል ዘላቂና አስተማማኝ የስራ ዕድል መፍጠር የተቻለበት ነው፡፡

ብልጽግና ፓርቲ የኢኮኖሚ ሽግግርን ለማፋጠን የግብርናና ኢንዱስትሪ ዘርፉን ትስስር የሚያጠናክርና ሀገራችንን በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ቀዳሚ ማዕከል እንድትሆን የሚያስችሉ ስራዎችን በስፋት እየሰራ የሚገኘውም ከዚሁ እሳቤ በመነሳት ነው፡፡

25/04/2024

ሀገራዊ ገዥ ትርክት ማጠናከርና የኢትዮጵያን ብልፅግና ማረጋገጥ የሁላችንም ሃላፊነት ነው!!

በኢትዮጵያ የህዝብን አንድነት የሚያጠናክር አሰባሳቢ ትርክት መገንባት ላይ በአግባቡ ባለመሰራቱ ዜጎች በተለያዩ ጊዜያት ዋጋ ሲከፍሉ ቆይተዋል። ልዩነቶችን ቁጭ ብሎ ተነጋግሮ መፍታት አለመቻል ዜጎችን ለሞት፣ ለመፈናቀልና ለንብረት ውድመት ሲዳርጋቸው ይስተዋላል።

በመሆኑም ብዝሃነትን ማዕከል ያደረገ አሳባሳቢ ትርክት መገንባት የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልፅግና ማረጋገጥ ወሳኝ ሚና ያለው በመሆኑ የተቃርኖ ገጽታዎችን በማከም፣ ልዩነትን በማጥበብና ስብራትን በመጠገን ሀገርን በሚያጸና አሰባሳቢ ትርክቶች ላይ አተኩረን በመሥራት የሀገራችን ብልፅግና ማረጋገጥ ይገባል ።

ኢትዮጵያ ውስጥ የተፈጠሩና እየተፈጠሩ ያሉ ችግሮች ዋነኛው መነሻቸውና አባባሽ ጉዳይ ነጠላ ትርክት መሆኑንና አንድ አገር የሚጸናው በአገሪቱ በተገነባው የጋራ ትርክት መሆኑን በመረዳት ሁሉም ኢትዮጵያውያን በተለይም ወጣቱ ትውልድ የተናጠል ትርክት ሰለባ እንዳይሆን ወላጆችና ማሕበረሰቡ ፣ የሃይማኖት ተቋማት ብዝሃነትን ማዕከል ባደረገ መልኩ ለአሰባሳቢ ትርክት ቅድሚያ በመስጠት የሚያግባባንን አሰባሳቢ የጋራ ትርክት ማጉላት ይጠበቅባቸዋል ።

የመደመር ትውልድ በአንድነትና በጋራ ለአንድ አላማ በመቆም ሀገራችንን በወንድማማችነት እና እህትማማነት መንፈስ በመቃኘት የኢትዮጵያን ብልፅግና ማረጋገጥ ቀዳሚ ተግባራችን ነው!!

መልካም ቀን ተመኘን!
-ብልፅግና

25/04/2024
24/04/2024
24/04/2024
24/04/2024

ብልጸግና አሰባሳቢ ትርክትን በመቅረፅ የበለጸገች ኢትዮጵያ ይገነባል!

ሀገራችን ኢትዮጵያን የአሁኑንና የመጪውን ትውልድ ጥቅምና ፍላጎት የሚያስከብር አስተማማኝ መሰረት ዛሬ ላይ በመገንባት ሰላም፣ ዴሞክራሲ፣ ኅብረ ብሔራዊ አንድነት፣ የዜጎች ክብር፣ ፍትሕ እና የጋራ ብልጽግና የተረጋገጠባት ሀገር መሆን ይኖርባታል።

ሀገራችን ኢትዮጵያ የጥንታዊ ስልጣኔና የቀደመ ሀገረ-መንግስት ባለቤት ብትሆንም አሰባሳቢ የሆነ ሀገራዊ ትርክት መገንባት ባለመቻሏ ትርክቶቿ በስርዓታት ፖለቲካ ፍላጎት ላይ ብቻ የተንጠለጠሉ ሆነው በመቆየታቸው ስርዓታት በወጡ እና በወረዱ ቁጥር የሚገለባበጡ ነጠላ ትርክቶች ገዥ እየሆኑባት የሀገረ-መንግስት ግንባታ ተግባሯን ያለ ተቃርኖ ለማስቀጠል አልታደለችም። በአንፃሩ የአሜሪካን፣ የቻይናን የፈረንሳይን ሀገራዊ ገዥ ትርክቶች የሚነግሩን ስርዓቶች ቢቀያየሩም ገዥ ሀገራዊ ትርክታቸው መሰረቱ ሀገረ-መንግስቱ ላይ በመገንባቱ በየወቅቱ የሚነሱ ፖለቲካዊ ፍላጎቶች አይለዋወጥም።

ሀገራት ህዝባቸውን ከየት እንደተነሱና ወዴት እንደሚደርሱ በአሰባሳቢ ገዥ ትርክት በመገንባት ከአስተዳደራዊ ወሰናቸው አልፈው በዓለም ላይ የበላይነታቸውን ቅቡልነት አረጋግጠዋል።
የዓለማችን ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የሚዘውሩት የትርክት የበላይነት በያዙ ሀገራት እና ተቋማት ፍላጎት ነው። እነዚህ ሀገራትም ይሁኑ ተቋማት የትርክታቸውን የበላይነት ለማስጠበቅ ሁሉንም ዓይነት ሀይል የማስጠበቂያ አማራጮችን ይጠቀማሉ።

ትርክት ቻይናን ከወደቀችበት አንስቶ የዓለም ተፆዕኖ ፈጣሪ ሀገር አድርጎ ከፊት አስቀምጧታል። ትርክት ሶሪያ ከዓለም ቀደምት ሀገርነት ወደ ፍርስራሽነት ቀይሩታል። ትርክት ኢትዮጵያን ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲነገር የሚኖረውን በቅኝ-ገዥዎች ቅኝ ያለመገዛት ታሪክ እንዲትሰራ አስችሏታል።

ትርክት በህዝብ ውስጥ ለጋራ ዓላማና ራዕይ በአብሮነት በማነሳሳትን በአርበኝነት እንዲፈፅሙ የሚያንቀሳቅስ ታላቅ ሀይል መሆኑን በመረዳት ብልጽግና ፓርቲ በተራራቀ ዋልታ የሚገኙትን የሀገራችን ትርክቶች ወደ አሰባሳቢ ገዥ ትርክት ለማምጣት በህብረ-ብሄራዊ አንድነትና ወንድማማችነት ላይ የተመሰረት ብሄራዊ አርበኝነት የሀገራችን ገዥ ትርክት እንዲሆን እየሰራ ይገኛል።

ብልፅግና በህብረ-ብሄራዊ አንድነትና ወንድማማችነት ላይ የተመሰረተው ብሄራዊ አርበኝነት የሀገራችንን ያልፈውን የጉዞ ምዕራፍ ፣ የዛሬን ነባራዊ ሁኔታ እና የነገን መዳራሻ የምንመለከትበት የጋር አሰባሳቢ ሀገራዊ ፕሮጀክት ነው ብሎ ያምናል።

በህብረ-ብሄራዊ አንድነትና ወንድማማችነት ላይ የተመሰረተው ብሄራዊ አርበኝነት ገዥ ትርክት የትላንቱን ኢትዮጵያ ህዝቦች ታሪክ መሰረት አድርጎ የዛሬውን አስተሳስሮ ነገን ማመልከት የሚችል የህዝባችንን ዋና ዋና የጋራ እሴቶችን፣ ፍላጎቶችንና ግቦችን የሚያሳካና የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ያደርጋል።

ፓርቲያችን ህዝባችን የጋራ ታሪክ ያለው፣ ብዙ ትላንቶችን በጋራ የተሻገረ አሁን ስንቅ ልናደርጋቸው የሚገቡ አያሌ ታሪኮችን እንዳሉት ያምናል።

በዚሁ አግባብ ብልፅግና በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ አማካይነት ነባር የተፈጥሮ ሀብቶችን በማልማት፣ ታሪካዊ እሴቶችን አውጥቶ በማበልፅግ እና በማህበራዊ ካፒታላችንን በመጠቀምና በእነዚህ ላይ እሴቶችን በመጨመር ለነገ ብልጽግናችን በሚሆን መንገድ ማልማት በሰፊው ቀጥሏል።

ከትላንት የተሻለ ሀገራችንንና ህዝቡቿን የሚጠቅም ታሪክ እንድሰራ፣ የትውልዶችን ድካም በማረም ለትወልድ የበለፅገች ሀገር ለማስረከብ እንትጋ። ስለዚህ ትርክታችን ያለፈውን ብቻ ሳይሆን የዛሬን ዕድል እና የገነን ተስፋ ታሳቢ ያደረገ መሆን አለበት።

23/04/2024

በፈጠራ ስራ የዳበረ ትውልድ ለሁለንተናዊ እድገትና ብልፅግና ወሳኝ ነው!!

ለወጣቶች ስራ እድል መፍጠር የሀገሪቷን ኢኮኖሚ ለማሳደግ ፋይዳው የጎላ ነው። ሰሪ ኃይል በተበራከተ ቁጥር ኢኮኖሚው ይነቃቃል። ስራ እድል ፈጠራ የወጣቱን ስራ አጥነት መቀነስ ብቻ አይደለም አላማው፣ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ድርሻን መወጣት መቻልም ጭምር ነው።

ወጣቶች ስራ ከመጀመራቸው በፊት የስራ ላይ ልምምድ እንድኖራቸው በማድረግ ስራ የመፍጠር አድሱ ልምምድ ለምርታማነት እጅግ አጋዥ ነው። በክ/ከተማችንም የዚህ የስራ ላይ ልምምድ በመስጠት ወጣቶችን ወደ ስራ ለማስገባት እየተሰራ ነው። ይህ ተግባር በአንድ በኩል የወጣቶቹን የስራ ክህሎት በማሳደግ በሚሰማሩበት ቦታ ምርታማ እንዲሆኑ ያግዛል፤ በሌላ በኩል ደግሞ የግል አምራች ተቋማት ልምድ ያለው አምራች ሀይል በማገኘት ለማሰልጠን የሚፈጁትን ጊዜ ምርት ወደ ማምረት ያስገባሉ። ለማሰልጠን የሚወጣ ገንዘብ ይቀንሳሉ። ምርታማነት መጨመሩ ደግሞ እንደ ሀገር የምናልመውን ኢኮኖሚያዊ ብልፅግና ያመጣል።

ወጣትነት ስራ እንዲፈጠርለት ብቻ ቁጭ ብሎ ስራ እድል የሚጠብቅበት እድሜ አይደለም። ስራ ፈጣሪ በመሆን ለራስ፣ ለወገን ለሀገር መጥቀም መቻል አለበት። ለዚህም ስራ ፈጣሪ ወጣቶችን በማበረታታት በማገዝና በመደገፍ ፈጠራን ለማበረታታት እየተሰራ ያለው ስራ ጠቃሚ ነው።

የስራ እድል ለዜጎች መፍጠር ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለው በመሆኑ በተያዘበት አግባብ አጠናክሮ መቀጠል ያስፈልጋል። ዜጎችም ከመንግስት ብቻ የስራ እድል እንዲፈጥር ከመጠበቅ ወጥተው ስራ በራሳቸው የመፍጠር ልምምድ ሊኖራቸው ይገባል።

የወጣቶችን ተጠቃሚነት እያረጋገጥን የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የምንሰራውን መልካም ጅማሮ አጠናክሮ መቀጠል ይገባል። ወጣቶች ከስራ ጠባቂነት ተላቀው ስራ ፈጣሪ በመሆን የድርሻቸውን መወጣት ይኖርባቸዋል። የወጣቶቻችንን አቅም ተጠቅመን የበለፀገች ኢትዮጵያን እንገነባለን!

መልካም ቀን ይሁንለዎ!
prosperity party-ብልፅግና

23/04/2024

በሀገራችን ኢትዮጵያ ህብረ ብሄራዊ አንድነት መገንባት አማራጭ የሌለው ብቸኛ መንገድ ነው!

የህብረ ብሄራዊነት ዋነኛ መገለጫዎች ከሆኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል የብሄር፣ የቋንቋ፣ የኃይማኖት እና የመሳሰሉት ብዝሃነት ግንባር ቀደም ተጠቃሾች ናቸው፡፡

ዘላቂ ሰላምና ሁለንተናዊ ብልፅግና የተላበሰች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ ይቻል ዘንድ በሀገራችን እነዚህን ተፈጥሮአዊ ልዩነቶችን ተቀብሎ ማስተናገድና ህብረ ብሄራዊ አንድነት መገንባት አማራጭ የሌለው ብቸኛ መንገድ መሆኑን ብልጽግና ፓርቲ ያምናል።

ብዝሃነት ሁሉንም ማንነቶች በእኩልና በአግባቡ ያቀፈ ህብረ ብሄራዊ አንድነት ሲሆን ብዙ ሆነን እንደ አንድ፣ አንድ ሆነንም እንደ ብዙ የምንሆንበት፤ ለጋራ ግብና አላማ የምንደመርበት የኢትዮጵያ ነባራዊ ሀቅ ነው፡፡

ከህብረ ብሄራዊ አንድነት እሴቶች መካከል "በህብረት ሆነን እንበለፅጋለን፤ በልፅገንም በህብረት እንኖራለን" የሚለው መሪ ሀሳብ ሲሆን አድሎንና አግላይነትን የሚያርሙ ናቸው፡፡

23/04/2024

ሀገር በትብብር ይገነባል!

የመተባበር አስኳል ደግሞ ወንድማማችነትን ማጠናከር፣አብሮነትን ማጎልበት፣ አንዱ ለሌላው ማሰብ ፣ እኔ ብቻ ከሚሉት የፀልማት ጉዞ በመወጣት አንድነትን ዘብ መቆም፣ እርስ በእርስ መተዛዘን፣ በሰዎች መካከል መከባበርና መተሳሰብን አብዝተን መሻትን ይጠይቃል።

ከምንም በላይ በገፍ ሰላማችን እንዲበዛ ፍቅርን እንስበክ፣ መዋደድን በተግባር መኖር እንጀምር!!

22/04/2024

የዴሞክራሲ ባህል የሚዳብረው ምን ሲሆን ነው?

በወንድማማችነትና ዴሞክራሲ መካከል ያለው ቁርኝት ምንድነዉ?

መሪ ሰነዳችን የሆነው የመደመር መጽሀፍ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲን ለመትከልና ለማጽናት በሚደረገው ጥረት ካጋጠሙ ተግዳሮቶች መካከል በሀገራችን የወንድማማችነት እሴትና የሲቪክ ባህል ደካማ መሆናቸውን እንደ ትላልቅ ሳንካዎች ይጠቅሳቸዋል።

ኢትዮጵያዊያን ከመጣንበት የብሄረ-መንግስት ምስረታና ሀገረ-መንግስት ግንባታው ስብስብነት የተነሳ ከተናጠል ቡድናዊ እውነቶቻችን ተሻግረን የወል እውነት መገንባት ስላልቻልን ከተወለድንበት ብሄርና ጎጥ፣ የምንከተለውን ሀይማኖትና እምነት፣ ከምናራምደው የፖለቲካ አመለካከት የተነሳ እርስ በርሳችን ስንገፋፋ፣ ስንናቆር፣ ብሎም ወደ ለየለት የእርስ በርስ ጦርነት አዙሪት ዉስጥ ስንማቅቅ የኖርንበት አንዱና ዋነኛው ምክንያት ይሄው ነው፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ ደካማ የወንድማማችነት እሴት የህዝበኝነት (Populism) ሰለባ የሆኑ የፖለቲካ ሀይሎች እንዲፈጠሩ ስለሚያደርግ እሱም ዞሮ ዞሮ ዴሞክራሲን ያደናቅፋል፡፡ የሲቪክ ባህል ደካማነትም ለዴሞክራሲያችን መቀጨጭ የራሱን አስተዋጽኦ አበርክቶአል፡፡

ከዚህ ባህል ደካማነት የተነሳ ዜጎች የኔብለዉ ከሚያምኑት ነጠላ ቡድናዊ አጃንዳዎች (የብሄር፣ የሀይማኖት ወዘተ) ተሻግረዉ ሀገራዊ አሰባሳቢ አጀንዳዎች ላይ አነጣጥረው መደገፍ፣ መቃወምና መምረጥ አልቻሉም፡፡ የመደመር ዴሞክራሲ አነዚህን የዴሞክራሲ ጋሬጣዎችን ምንነት፣ ምንጮቻቸውንና የአደናቃፊነት ደረጃቸውን በወጉ ለይቶ እየሰራባቸው ይገኛል፡፡

የመደመር ዴሞክራሲ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲ ነው፡፡ የመደመር ዴሞክራሲ ለኢትዮጵያዊ የዴሞራሲ እጦት ኢትዮጵያዊ መፍትሄ የሚያፈላልግ ነው፡፡ ግቡም የማኅበረሰብና የሲቪክ መብቶችንና ጥቅሞች ወጥነትና ዘላቂነት ባለው አግባብ ማረጋገጥ ነው፡፡

ከሁሉ በላይ ደግሞ ወንድማማችነት፣ ነፃነትና እኩልነት ቁልፍ የዴሞክራሲ ባህል እሴቶች (ምሰሶዎች) ስለሆኑ በቤተሰብ፣ ማህበረሰብ፣ ፖለቲካ ፓርቲዎችና መሰል ተቋማት ደረጃ ማበብ እንዲችሉ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን አስተዋጽኦ ወጥነትና ዘላቂነት ባለው አግባብ እንዲወጡ መደረግ አለበት።

መልካም የስራ ሳምንት ይሁንላችሁ።
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅቤት

22/04/2024

የፓርቲያችን ብልፅግና ዋነኛ ዓላማ ህብረ ብሔራዊነቱ የተጠበቀ አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ መገንባት ነው።

ፓርቲያችን ህብረ ብሔራዊነት በሁሉን አቀፍነት፣ በብዝኃ ልሳንነት እና በአሳታፊነት ሊገለጽ ይገባል ብሎ ያምናል።

ህብረ ብሔራዊ፣ አንድነት ታሪካዊና ነባራዊ በደሎች ከማድበስበስ ይልቅ ታርመው እንዲሄዱ፣ ይህም ለቁርሾ ሳይሆን ወዳጅነትን ለማጠናከር እንዲውል የሚያደርግ አካሄድ ነው።

ህብረ ብሔራዊ አንድነት፣ የሚከፋፍሉ እና የሚያጣሉ ትርክቶችን ከማጉላት ይልቅ የሚያቀራርቡና የሚያስተሣሥሩንን እውነታዎች በማጉላት፣ ከትናንት ጠቃሚ ትምህርቶችን በመውሰድ እንዲሁም ዛሬና ነገ ላይ በማተኮር እህታዊ/ወንድማዊ ህብረትን በዜጎች መካከል ማጠናከርን ይመርጣል።

ህብረ ብሔራዊ አንድነት ብዙ ሆነን አንድ፣ አንድ ሆነንም ብዙ የምንሆንበት፣ ለጋራ ግብና ዓላማ የምንደመርበት ቀመር ነው። በብዝኃነታችን ደምቀን፣ በአንድነታችን በርትተን ወደፊት የምንራመድበት የውበትና የጥንካሬያችን ምንጭ ነው።

ፍትህ ከሰፈነ፣ ሰብአዊ ክብር ከጎለበተ እና ብልጽግና ከመጣ እንደ ሀገር የመቀጠል ተስፋችን ይለመልማል። ሆኖም ግን ኅብረ ብሔራዊ አብሮነት እነዚህ ምሦሶዎች ከተሳኩ በኋላ የሚመጣ ብቻ ሳይሆን ለዓላማዎች ስኬትም ዓይነተኛ ድርሻ የሚወጣ አስቻይ አቅም በመሆኑ ፓርቲያችን “በህብረት ሆነን እንበለጽጋለን፤ በልጽገንም በህብረት እንኖራለን” በሚል መርሕ ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማረጋገጥ በከፍተኛ ትኩረት ይሠራል።

መልካም ቀን ይሁንልዎ!!

https://www.facebook.com/kolfeprosperityparty?mibextid=ZbWKwL

22/04/2024

ህብረ ብሄራዊ አንድነታችን ለሚገጥሙን የውስጥና የውጪ ፈተናዎች ሁሉ የመፍትሄ መንገድ ነው!!

የሀገራችን ህዝብ አንድነቱን በማጠናከር ከውስጥም ከውጪም አብሮ ሲሰራ ማንኛውንም ችግር መሻገር እንደሚችል በአንድነታችን የተመዘገቡት ስኬቶች እና ትልቅ ድሎችን ማስመዝገብ መቻሉ ማሳያዎች ናቸው።

ኢትዮጵያን ለማፍረስ የሚፈልጉ አካላት አላማቸው ሊሳካ የሚችለው የኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት ሲዳከም ብቻ እንደሆነ ይረዳሉ። ለዚህም ህዝብ እንዲከፋፈል የሚያደርጓቸውን የሀሰት አጀንዳዎችን በማሰራጨት ሰላም ለማደፍረስ ይጥራሉ።

ሀገራዊ አንድነታችን ህብረብሄራዊነት ብዝሃነትን ያረጋገጠ ሀገራዊ አንድነት ጠንካራ ስርዓት የገነባች እና ዘላቂ ልማትን ያረጋገጠች ሀገር ለመፍጠር ትልቅ ሚና ይጫወታል።

የኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት ሲጠናከርና በውስጡ መረጋጋት ሲሰፍን ኢትዮጵያ ታላቅ ሀገር መሆን እንደምትችል ከለውጡ በኋላ የተገኙ ውጤቶች ትልቅ ማሳያ ናቸው።

ብልፅግና ፓርቲ ኢትዮጵያን ለሁሉም የምትመች፣ ህብረ ብሔራዊነት እና ወንድማማችነት የምታስተናግድ ሀገር እንድትሆን ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል።

የሚያጋጥሙንን ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች እና ተግዳሮቶችን በመቅረፍ በዘላቂነት ለመፍታት አንድነትን ማጠናከር እንደ ህዝብና እንደ ሀገር ሰላምና መረጋጋትን እና ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማስፈን ትልቅ ሚና ይጫወታል። ስለሆነም በአንድ በኩል የሚገጥሙንን ፈተናዎች በመመከት፣ በሌላ በኩል ሀገሪቱን ለትውልድ የማሻገር ኃላፊነት ለመወጣት ሁሉም ብሄር ብሄረሰቦች አንድነታችንን በማጠናከር ጠንካራ ሀገረ መንግስት መፍጠር እና መገንባት የሁላችንም ድረሻ ሊሆን ይገባል።

በህብረ ብሄራዊነት የደመቀች ሀገር ሰላም ፍትህ ዲሞክራሲ የተረጋገጠባት ሀገር ለመገንባት በሚደረገው ሁሉን አቀፍ ተግባር በህብረት መስራት ይጠበቅብናል!

19/04/2024

የመደመር ትውልድ ልዩነትን የሚያከብርና አንድነትን የሚያጠናክር ነው!!

የመደመር ትውልድ ጥላቻን በፍቅር፣ ቂምን በይቅርታ፣ ግጭትን በውይይት የሚተካ ትውልድ ነው።

የመደመር ትውልድ ልዩነትን የሚያከብርና አንድነትን የሚያጠናክር ፤ ጽንፈኝነትን የሚጸየፍ ትውልድ ነው።

የመተማመን ክበቡ በብሄርና በመንደር ሳይታጠር ኢትዮጵያዊነትን በአርበኝነት መንፈስ የሚያፀና ነው።

በመሆኑም ከራስ ወዳድነት የፀዳ፣ ለሌሎች የሚራራ፣ ሀላፊነት የሚሸከም ፣ እውነተኛና የሌላው ህመም የሚያመው ትውልድ መቅረጽ የጋራ ሀላፊነት ሊሆን ይገባል።

በመደመር ትውልድ ተሠናስለን ተከባብረንና ተባብረን ለጋራ ግብ ቋሚ ተሰላፊ በመሆን ኢትዮጵያን እናበለጽጋለን።

19/04/2024
18/04/2024

ቁልፍ የፖለቲካ ስብራታችንን ከመጠገን አንጻር የብሔራዊነት ትርክት ፋይዳ ምንድነው?

እኛ ኢትዮጵያዊያን የወል ብሔረ መንግስት (Nation) በመመስረት አሰባሳቢ ሀገረ መንግስት (State) መገንባት ከጀመርንበት ጊዜ አንስቶ በርካታ ዘላቂ ወረቶች በጋራ ያካበትን ህዝቦች ነን፡፡

በጋራ ያካበትናቸው ወረቶች እንደተጠበቁ ሆነው እስካሁንም ያልተሻገርናቸው የፅንፍ አስተሳሰቦች አሉ፡፡ እነዚህ የጽንፍ አስተሳሰቦች በአንድ አመራር ትውልድ የተፈጠሩ ሳይሆን ከብሔረ- መንግስታችን ምስረታ እና ከሀገረ - መንግስታችን ግንባታ ጀምሮ የነበሩና እስካሁንም ድረስ ከእኛ ጋር ያሉ ናቸው፡፡ ዳሩ ግን እነዚህ ዋልታ ረገጥ አስተሳሰቦችና ከእነሱ የሚመነጩ ድርጊቶች የየራሳቸው ምንጮች ያላቸው ናቸው፡፡

ምንጮቻቸውም ፓርቲያችን በተለያዩ ጊዜያት በትላልቅ ሰነዶቹ ጭምር በግልፅ እንዳስቀመጣቸው ፍፁማዊ አንድነትና ፍፁማዊ ልዩነት የሚሰኙ የተቃርኖ ትርክቶች ናቸው፡፡ በብልፅግና እምነት ደግሞ ፍጹማዊ አንድነትም ሆነ ፍጹማዊ ልዩነት ሀገራችን ኢትዮጵያን የማይመስሉ ብቻ ሳይሆን የማይመጥኑም መሆናቸው ነው፡፡

እነዚህ የህዝቦች አንድነትና የሀገር ቀጣይነት ላይ ከፍተኛ አደጋ የደቀኑ ትርክቶችና ፅንፈኛ አስተሳሰቦችን ተሻግረን ሁሉም ህዝቦችና ዜጎች እኩል የሆኑበት ከተማና ሀገር እውን ለማድረግ ሁሉም ዜጋ ሃላፊነት አለበት።

የብሄራዊነት ትርክት በአንድ በኩል ሀገራችን ኢትዮጵያ ከመጣችባቸው አባጣ ጎርባጣ የሀገር ምስረታና ሀገረ መንግስት ግንባታ የሚነሱ የተቃርኖ ትርክቶችን ከስር መሰረታቸው በመግራት ሀይል ለማሰባሰብ ያግዛል፤ በሌላ በኩል ደግሞ በአርበኝነት መንፈስ የተቃኘ አንድነት፣ ወንድማማችነትና አብሮነት በመትከል የጠነከረችና ሰላማዊት የሆነች ሃገር እውን ለማድረግ ያስችለናል፡፡

ይሄን ማድረግ በመቻላችን በሃገራችን ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን፣ እኩልነት እንዲረጋገጥ፣ ወንድማማችነት እንዲያብብ፣ የዴሞክራሲ ባህል እንዲዳብርና ሁለንተናዊ ብልጽግና እውን እንዲሆን ያስችላል፡፡

17/04/2024

ስለ ሰላም እንዘምራለን፤ ደግሞም እንሰራለን!

የዴሞክራሲ ምህዳሩን በማስፋት ሲንከባለሉ የመጡ እና በየጊዜው ቅርፃቸውን የሚቀያይሩ ሳንግባባ ያደርንባቸውን አገራዊ ጉዳዮች ጭምር ህዝባችንን በማሳተፍ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ እልባት በመስጠት አገራዊ አንደነታችንን በማይናወጥ መሰረት ላይ ለመገንባት ከለውጡ ጀምሮ የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ።

በእሳት ተፈትኖ ነጥሮ እየወጣ ያለው የለውጡ መሪ መንግስታችን እና ፓርቲያችን "ኢትዮጵያ አበቃላት" ያስባለውን ከውጭም ከውስጥም የተደቀነባትን ምናልባትም በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ውስብስብ ፈተና ህዝቡን ከጎኑ አሰልፎ እንደ ጉም ከመግፈፉ በተጨማሪ የቆመለትን ኢትዮጵያን የማበልፀግ ዓላማ ለአፍታም ሳይገታ አጠናክሮ አስቀጥሏል።

በሌላ በኩል ደግሞ የኢትዮጵያን መለወጥ የማይመኙ፣ በልፅጋ ማየት የማይፈልጉ የውስጥና የውጭ ፀረ-ሰላም ሀይሎች ፍላጎታቸው የሚሳካው እርስ በእርስ ስንጣላ እንጅ ስንፋቀር ባለመሆኑ 24 ሰዓት በታዛቢነት ከዳር ሆነው የሚመለከቱትን የጦርነት ፊሽካ መንፋታቸውንና ከእሳት ላይ ቤንዚን ማርከፍከፋቸውን አላቆሙም።

ኢትዮጵያዊያን የጦርነትን እና የግጭትን አስከፊነት በየጊዜው የህይወት መስዋዕትነት እና የንብረት ውድመት ውድ ዋጋ እያስከፈለን እያለፍንበት ያለ የአስከፊ ታሪካችን ገፅታ ጭምር እንጂ ከርቀት የምንሰማው ጉዳይ አይደለም።

የግጭት አትራፊዎች ያልተቋረጠ የገቢ ምንጭ በሬ ወለደ የሚሉ የሀሰት ወሬዎች በመሆናቸው ሳያረጋግጡና ሳያመዛዝኑ የሚያዳምጡ ግለሰቦችን ወደ እኩይ መረባቸው ለማስገባት ጠዋት ማታ ያሰራጫሉ።

ከሀሰተኛ መረጃዎች ራስን መጠበቅ እንዲሁም በዘመኑ የሚዲያ አማራጮች ውሸታቸውን ማጋለጥም ከእያንዳንዳችን ይጠበቃል።

የአገር ዋልታ የሆነው መከላከያ ሰራዊታችን እና ሌላውም የፀጥታ ሀይላችን አስተማማኝ ሰላማችንን ለማረጋገጥ ለሚወስዳቸው አጥፊዎችን ወደ ህግ የማቅረብና ህግን የማስከበር እርምጃዎች እንደተለመደው ደጀንነታችንና ድጋፋችንን ማጠናከርም ይገባል።

የግጭት አትራፊዎች ስለሰላም ማውራትን፣ ስለሰላም ነገሮችን በትዕግስት ማለፍን እንዲሁም የሀይማኖት አባቶችን የሰላም ምክር እንደ ሞኝነት ቢቆጥሩትም የኢትዮጵያን አስተማማኝ ሰላም ለማረጋገጥ እንዲሁም ሁለንተናዊ ብልፅግናዋን እውን ለማድረግ ቆርጠን በመነሳታችን ዛሬም ሆነ ነገ ስለ ሰላም እንዘምራለን፤ ደግሞም እንሰራለን!

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mahir Endris posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share