ሰማያዊ ደስታ/Heavenly Joy

ሰማያዊ ደስታ/Heavenly Joy Spiritual/Social/Promotive/Educative

ወገኔ ተጠንቀቅ!የዛሬ አምስት ዓመት በ2018 ውጫውያን አቆጣጠር ነበር፣ ኢየሱስ ክርስቶስ መጥቷል በማለት በእንግሊዝ ለንደን ሕዝብ   ወደ ሰማይ እያሸቀበ ምጻቱን የጠበቀው፡፡ በማቴዎስ 24፡...
23/09/2023

ወገኔ ተጠንቀቅ!
የዛሬ አምስት ዓመት በ2018 ውጫውያን አቆጣጠር ነበር፣ ኢየሱስ ክርስቶስ መጥቷል በማለት በእንግሊዝ ለንደን ሕዝብ ወደ ሰማይ እያሸቀበ ምጻቱን የጠበቀው፡፡ በማቴዎስ 24፡ 24-27 ድረስ፣ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲህ አለ፡ "²⁴ ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት ይነሣሉና፥ ቢቻላቸውስ የተመረጡትን እንኳ እስኪያስቱ ድረስ ታላላቅ ምልክትና ድንቅ ያሳያሉ። ²⁵ እነሆ፥ አስቀድሜ ነገርኋችሁ። ²⁶ እንግዲህ፦ እነሆ፥ በበረሀ ነው ቢሉአችሁ፥ አትውጡ፤ እነሆ፥ በእልፍኝ ነው ቢሉአችሁ፥ አትመኑ፤ ²⁷ መብረቅ ከምሥራቅ ወጥቶ እስከ ምዕራብ እንደሚታይ፥ የሰው ልጅ መምጣት እንዲሁ ይሆናልና፤"
መልካም ሰንበተ ቅዳሜ!
የፎቶ ምንጭ፡ ከፋይል

Beware my friends!
It was five years ago in 2018, when the people of London, England waited for the second coming of Jesus Christ,and assumed as He had come. In Matthew 24: 24-27, the Lord Jesus Christ said: "For false Christs and false prophets will arise, and if they can, they will show great signs and wonders until they deceive even the elect., if they say to you that it is by me, do not believe it.

Happy Saturday!

Photo source: From file

ወገኔ ተጠንቀቅ!የዛሬ አምስት ዓመት በ2018 ውጫውያን አቆጣጠር ነበር፣ ኢየሱስ ክርስቶስ መጥቷል በማለት በእንግሊዝ ለንደን ሕዝብ   ወደ ሰማይ እያሸቀበ ምጻቱን የጠበቀው፡፡ በማቴዎስ 24፡...
23/09/2023

ወገኔ ተጠንቀቅ!

የዛሬ አምስት ዓመት በ2018 ውጫውያን አቆጣጠር ነበር፣ ኢየሱስ ክርስቶስ መጥቷል በማለት በእንግሊዝ ለንደን ሕዝብ ወደ ሰማይ እያሸቀበ ምጻቱን የጠበቀው፡፡ በማቴዎስ 24፡ 24-27 ድረስ፣ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲህ አለ፡ "²⁴ ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት ይነሣሉና፥ ቢቻላቸውስ የተመረጡትን እንኳ እስኪያስቱ ድረስ ታላላቅ ምልክትና ድንቅ ያሳያሉ። ²⁵ እነሆ፥ አስቀድሜ ነገርኋችሁ። ²⁶ እንግዲህ፦ እነሆ፥ በበረሀ ነው ቢሉአችሁ፥ አትውጡ፤ እነሆ፥ በእልፍኝ ነው ቢሉአችሁ፥ አትመኑ፤ ²⁷ መብረቅ ከምሥራቅ ወጥቶ እስከ ምዕራብ እንደሚታይ፥ የሰው ልጅ መምጣት እንዲሁ ይሆናልና፤"

መልካም ሰንበተ ቅዳሜ!
የፎቶ ምንጭ፡ ከፋይል

Be careful my friend!

It was five years ago in 2018, when the people of London, England waited for the second coming of Jesus Christ,and assumed as He had come. In Matthew 24: 24-27, the Lord Jesus Christ said: "For false Christs and false prophets will arise, and if they can, they will show great signs and wonders until they deceive even the elect., if they say to you that it is by me, do not believe it.

Happy Saturday!

Photo source: From file

እግዚአብሔር ይመስገን!የዶ/ር በየነ አበራ የአእምሮው እጢ ህኪምና በህንድ አገር ልምድ ባላቸው ሀኪሞች በሰላም ተጠናቋል፡፡ በፀሎትና በሚያስፈልገው ሁሉ የተባበራችሁ እግዚአብሔርን አመስግኑ!
22/09/2023

እግዚአብሔር ይመስገን!

የዶ/ር በየነ አበራ የአእምሮው እጢ ህኪምና በህንድ አገር ልምድ ባላቸው ሀኪሞች በሰላም ተጠናቋል፡፡ በፀሎትና በሚያስፈልገው ሁሉ የተባበራችሁ እግዚአብሔርን አመስግኑ!

12/09/2023

*የኢትዮጵያ ዩኒየን ወንጌል ክፍል መልዕክት*

እንኳን ለ2016 ዓ/ም በሰለም አደረሳችሁ አደረሰን! አዲሱ ዓመት የፍቅር፣ ሰላምና በሁሉም ዘርፍ ለፈጣሪ ክብርና ለሰው ጥቅም የምንሰረበት ዘመን ይሁንልን!
“አቤቱ፥ ዝናህን ሰምቼ ፈራሁ፤ አቤቱ፥ *በዓመታት መካከል ሥራህን ፈጽም* ፤ በዓመታት መካከል ትታወቅ፤ በመዓት ጊዜ ምሕረትን አስብ።” ዕንባቆም 3፥2፡፡ እያለ የዩኒየኑ ወንጌል ክፍል መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡ በጌታችን በክርስቶስ ኢየሱስ ደም የተዋጃችሁ ውድ ወንድሞቼና እህቶቼ፣ የዩኒየኑ ወንጌል ሥራ እቅድ፣ በግንቦት 12/2015 ዓ/ም በደቡብ ምዕረብ ፊልድ አንሾ አጥቢያ በነበረው መንፈሳዊ ስብሰባ፣ ከባለፈው ሰኔ 01/2015 ዓ/ም እስከ ያካቲት 02/2016 ዓ/ም ድረስ ማለትም ጳጉሜን ሳይጨምር በ240 ቀናት የሚከናወን ወንጌል ሥራ በኢትዮጵያ ዩኒየን ፕሬዝደንት ፓ/ር ሌንጫ ተክሌ አማካይነት ጥቅስ ተነቦ በፀሎት መከፈቱ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም የዩኒየኑ ወንጌል ክፍሉም በሰኔ ወር " *ስለ ወንጌል"* በሚል መርህ (“በወንጌልም ማኅበረተኛ እሆን ዘንድ ስለ ወንጌል ሁሉን አደርጋለሁ።” 1ኛ ቆሮንቶስ 9፥23) በፀሎትና በገንዘብ ድጋፍ በወንጌል ሥራ፣ በሐምሌና ነሐሴ ወራትም በተለያዩ ተግባራት በ90 ቀናት ውስጥ ስለተሰተፋችሁ ፈጣሪ ይባርካችሁ ይላችኀል፡፡ አሁን ደግሞ "ወንጌሉ ምስክር እንዲሆን መስካሪዎች መሆን" በሚል መርህ (ማቴ.24:14) ከነሐሴ 25/2015 ዓ/ም ጀምሮ በወንጌሉ ዘርፍ ትምህተ ጉባዔ (ሴሜናር) እየሰጠ መሆኑን አስታውሶ፣ ከመስከረም 01/2016 ዓ/ም እስከ ያካቲት 02/ 2016 ዓ/ም ድረስ " ለ150 ቀናት *ክርስቶስ ለሞተለት ነፍስ እሰራለሁ* " በሚል መርህ መላው የቤተክርስቲያን አበላት የሚሠተፉበትን የወንጌል እቅድ ማቀዱን ስገልጽ በታለቅ አክብሮትና ደስታ ነው፡፡ ስለዚህ በፊልድ መሪዎች ብሎም በሁሉም ፊልዶች ስር በሚገኙ አብያተ-ክርስቲያናት መሪዎች አማካይነት በሚደረሰው ወንጌል ሥራ እቅድ እንዲትሳተፉ ዘንድ ጥሪውን በታላቅ አክብሮትና ትህትና አቅርቧል፡፡

" *ወደ ዓለም ሁሉ እሄዳለሁ፤ የምስራች ነጋሪ ነኝ!"

ወ/ም ደነበ በቀለ
የኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ወንጌል ክፍል አስተባባሪ🙏

*Ethiopian Union Missionary Department Message*

Happy New Year 2016!
May the new year be a time of love, peace and in all areas we strive for the glory of the Creator and the benefit of humanity!

“Lord, I was afraid when I heard your fame; Lord, *perform your work between the years*;
Be known among the years. Think of mercy at the time of death.”
Habakkuk 3:2. In this Biblical verse, the Union Missionary Department expresses its good wishes for all. My dear brothers and sisters who
redeemed by the blood of our Lord Christ Jesus, as you know, the union gospel work plan geared in South West Field Ansho local church on May 12/2015 A.D. during the spiritual meeting held in union wise. The work that will be done since last June 01/2015 A.D. and will be continued till February 02/2016 A.D. for 240 days without including leap year opened by the Ethiopian Union President by Pr. Lencha Tekle in reading a verse and praying for the successfulness of the activities. Therefore, the Union Missionary Department would like to express deep heartful thanks for those who participated in gospel activities in all sides since the month of June unto the end of the last August within the 90 days. Now the seminar is being given in the field of the gospel works with the principle of "Being witnesses; Gospel to be a witness" (Matthew 24:14) starting from August 25/2015 AD. Finally, the Missionary Department would like to request all churches members, who are found under the fields, in order to participate 150 days missionary activities in following the guidance of respective leaders.

Happy New Year!

"*I will go to all the world; I am a bearer of good news!"

Mrs. Denbe Bekele

International Missionary Society [Seventh Day Adventist] Church Reform Movement -Ethiopian Union Missionary leader

Report: IMSEM🙏

12/09/2023

"አዲሱ ዓመት ማለትም 2016 ዓ/ም፣ በግል ህይወታችን መድኃኒታችንን የሱስን ይበልጥ በቅርበት የሚንከተልበትና እዉነተኛዉን ቅድስና የሚንለማመድበት ዘመን እንድሆንልን ምኞቴና ፀሎቴ ነዉ፡፡" ብለዋል ለምዕመናኑ ፓ/ር ሌንጫ ተክሌ (በጳጉሜ 04/2015 ዓ/ም ሰንበት ከተነበበው " *ወጣቶችና ቅድስና* " ከሚል ጽሑፍ የተወሰደ)፡፡ በተጨማሪም ከጳጉሜ 02-05/2015 ዓ/ም በሀዋሳ ታቦር ክፍለ ከተማ በተደረገው መንፈሳዊ ወንጌል ስርጭት ወቅት፣ ለሀገራችን ሰለምና መረጋጋት፣ በተለያዩ ስልጣን ደረጃ ያሉ የሀገር መሪዎች በማስተዋል ሀገሪቱን እንዲመሩ እግዚአብሔር ጥበብ እንድሰጣቸው ፀልየዋል፡፡

መልካም አዲስ ዓመት!
“በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ፥ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል።” መዝሙር 65፥11፡፡

ፓስተር ሌንጫ ተክሌ
ኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አዲቬንቲስት] ቼርች ሪፎርም ሙቭመንት የአፍሪካን ድቭዥን ኮሚቴ አማካሪና የኢትዮጵያ ዩኒየን ፕሬዝደንት🙏

"It is my wish and prayer that the new year, 2016 AD, should be a time in our personal lives where we follow our Savior Jesus Christ more closely and experience true holiness." said to the devotees, Pr. Lencha Tekle (taken from the article "*Youth and Holiness*" which was read on Leap year Saturday 04/2015 AD).
In addition, during the spiritual gospel distribution in Hawassa Tabor Sub-district from Pagume 02-05/2015, he prayed that God would give wisdom for country leaders to lead the country wisely and prayed for the peace and stability of our country.

Happy New Year!
"By your kindness you make the year abundant, and the wilderness is filled with fat."
Psalm 65:11.

Pastor Lencha Tekle

International Missionary Society [Seventh Day Adventist] Church Reform Movement African Division Committee Advisor and Ethiopian Union President🙏
ዘገበው፡ የIMSEM ነው

በአዲስ (2016) ዓመት በመጀመሪያ ቀን መልካም በመስራት እንጀምር! ለዶ/ር በየነ አበራ ውጪ ሄዶ እንዲታከም እንድረስለት! እርሱን መርዳት በወልድ ጊዜ ብዙ እናቶችን መርዳት መሆኑን ካወቅን...
12/09/2023

በአዲስ (2016) ዓመት በመጀመሪያ ቀን መልካም በመስራት እንጀምር! ለዶ/ር በየነ አበራ ውጪ ሄዶ እንዲታከም እንድረስለት! እርሱን መርዳት በወልድ ጊዜ ብዙ እናቶችን መርዳት መሆኑን ካወቅን፣ በአገር ውስጥና በውጭ ያላችሁ ውድ ወንድም እህቶች በፀሎትና ከታች ባሉት አማራጮች የገንዘብ ድጋፍ እናድርግ!

“ታምሜ ጠይቃችሁኛልና፥ ታስሬ ወደ እኔ መጥታችኋልና።”
— ማቴዎስ 25፥36፡፡
መልካም አዲስ ዓመት እንደገና!

Let's start the New Year (2016) by doing good on the first day! Let's reach to Dr. Beyene Abera to go outside and be treated! If we know that helping him means helping many mothers during childbirth! Dear brothers and sisters who live in the country and abroad, let's support him in prayer and financially through the options below!

"Because you asked me when I was sick, and you came to me in prison."Matt.25:36.

12/09/2023

አዲሱ 2016 ዓመት የፍቅር፣የሰላም በመንፈሳዊነት የማደግና ከሥጋዊ ደዌ የመለቀቅ ዓመት ይሁንልን!

“አምላክህ እግዚአብሔር የሚጐበኛት አገር ናት፤ ከዓመቱ መጀመሪያ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ የአምላክህ የእግዚአብሔር ዓይን ሁልጊዜ በእርስዋ ላይ ነው።”
— ዘዳግም 11፥12፡፡
መልካም አድስ ዓመት!!

Let 2016 be a year of love, peace, spiritual growth and release from physical illness!

“A land which the LORD thy God careth for: the eyes of the LORD thy God are always upon it, from the beginning of the year even unto the end of the year.”
— Deuteronomy 11፥12 (KJV)


Happy New Year!!

✿✿አስደሳች ዜና!✿✿“በአንዳንዶችም ዘንድ ልማድ እንደ ሆነው፥ መሰብሰባችንን አንተው እርስ በርሳችን እንመካከር እንጂ፤ ይልቁንም ቀኑ ሲቀርብ እያያችሁ አብልጣችሁ ይህን አድርጉ።”  — ዕብራ...
11/01/2023

✿✿አስደሳች ዜና!✿✿

“በአንዳንዶችም ዘንድ ልማድ እንደ ሆነው፥ መሰብሰባችንን አንተው እርስ በርሳችን እንመካከር እንጂ፤ ይልቁንም ቀኑ ሲቀርብ እያያችሁ አብልጣችሁ ይህን አድርጉ።”
— ዕብራውያን 10፥25፡፡
እነሆ ታላቅ መንፈሳዊ የበረከት ስብሰባ ከያከቲት 01/2015 ዓ/ም - 04/06/2015 ዓ/ም ድረስ በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን-ደቡብ ፊልድ በጃርሶ አጥቢያ ተዘጋጅቷል፡፡ በመሆኑም የበረከቱ ተከፋዮች ትሆኑ ዘንድ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል፡፡ የመርሃ ግብሩን ዝርዝር ሀሳብ በቀጣይ እናሳውቃለን፡፡

ወደ ዓለም እሄዳለሁ፤ የምስራች ነጋሪ ነኝ!

ዘገበው: የIMS Ethiopia Media ነው፡፡

02/12/2022

✿አስደሳች ማስታወቂያ!✿
እነሆ ኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን፡
1ኛ. የወንጌል አገልጋዮች ትምህርተ-ጉባዔ (ሴሜናር) ከተህሳስ 10 እስከ 13/2015 ዓ/ም በሆሳዕና ፊልድ በሮማ ቤ/ክ ይደረጋል፡፡
2ኛ. ከተህሳስ 13/2015 ዓ/ም ማታ ጀምሮ እስከ 15/2015 ዓ/ም ማታ ድረስ አገር አቀፍ ህዝባዊ ስብሰባ እላይ በተጠቀሰው ቦታ ይካሄዳል፡፡
3ኛ. ከዛሬ ጀምሮ ማለትም ከ23/03/2015 ዓ/ም -01/04/2015 ዓ/ም ድረስ የሚጠና ድንቅ የፀሎት ሳምንት በሰማያዊ ደስታ/Heavenly Joy/ ዋትስ አፕና ቴሌግራም ገጾች ተለቋል፡፡ አውርዳችሁ ተጠቀሙበት፤ መረጃውን ለሌሎችም አካፍሉ፡፡

ዘገበው፡ የIMS Ethiopia Media ነው፡፡

✿አስደሳች ዜና!✿እነሆ ከጥር 30/2015ዓ.ም እስከ ያካቲት 04/2015 ዓ.ም ድረስ ታላቅ መንፈሳዊ አገር አቀፍ ስብሰባ፣ በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ሪፎርም...
05/11/2022

✿አስደሳች ዜና!✿
እነሆ ከጥር 30/2015ዓ.ም እስከ ያካቲት 04/2015 ዓ.ም ድረስ ታላቅ መንፈሳዊ አገር አቀፍ ስብሰባ፣ በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን ደቡብ ምዕራብ ፊልድ ስለሚካሄድ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል፡፡ የመርሃ ግብሩን ዝርዝር ሀሳብ እስከምናስታውቃችሁ ጊዜ ድረስ መልካም ቆየይታ፡፡
መልካም ዕለተ ቅዳሜ ሰንበት!

በሰማያዊ ደስታ፣ አለ ሁለንተናዊ እርካታ!

ዘገበው: የIMS Ethiopia Media ነው፡፡

✿✿ አስደሳች ዜና!✿✿እነሆ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የእህታችን ዘማሪት ምርታየሁ መኮሮ  #1 አልባም በአውዲዮ/Audio/ ነገ በቤ/ክርስቲያኒቷዋ ከአምልኮ በኀላ ተማርቆ፣ በ"ሰማያዊ ደስታ/...
21/10/2022

✿✿ አስደሳች ዜና!✿✿
እነሆ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የእህታችን ዘማሪት ምርታየሁ መኮሮ #1 አልባም በአውዲዮ/Audio/ ነገ በቤ/ክርስቲያኒቷዋ ከአምልኮ በኀላ ተማርቆ፣ በ"ሰማያዊ ደስታ/Heavenly Joy" በዋትስ አፕ/What's app እና በቴሌግራም ቻናል/Telegram channel ነገ ከሰዓት በኀላ ለአድማጮች ይለቀቃል፡፡ ይህን አገልግሎት በፀሎትና በገንዘብ የደገፋችሁትን ምዕመናንን እንዲሁም ዘመድ አዝማድ በሙሉ የሰማይና የምድር ፈጣሪ አምላክ ይባርካችሁ!

“እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው፤ የእስራኤል አምላክ እርሱ ኃይልን ብርታትንም ለሕዝቡ ይሰጣል፤ እግዚአብሔርም ይመስገን።”
— መዝሙር 68፥35፡፡

መልካም ሰንበት ለቤ/ክ አበላት በሙሉ! ሰላም ለአገራችን ይሁን!

ማሳሰቢያ:-በጉሩፑ አድ እንዲያደርጋችሁ የሚትፈልጉ በውስጥ መስመር መጠየቅ ትችላላችሁ::

ምንጭ:- የIMS Ethiopia Media ነው፡፡

15/10/2022

ውድ "የሰማያዊ ደስታ" ገጽ ተከታይ ኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ሪፎርም ሙቭመንት አበላት በሙሉ! በ17ኛው ሰ/ት ወይም መጽሐፍ ቅዱስ ጥናት መመሪያ ከዩኒየን የቀረበውን ማስተካከያ ከዋትአፕና ከቴሌግራም አገኙ፤ ለሌሎችም አካፍሉ፡፡ በሰዓት እጥረት ስለተፈጠረው ቴክንካል ግድፈቱ ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡ የዩኒየኑ ማተሚያ ክፍል፡፡

ምንጭ፡ የIMS Ethiopia Media ነው፡፡

አስደሳች ዜናእነሆ ከመስከረም 19 እስከ 21/2015 ዓ/ም ድረስ በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይት [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን ሲዳማ ፊልድ በዌዴ...
25/09/2022

አስደሳች ዜና

እነሆ ከመስከረም 19 እስከ 21/2015 ዓ/ም ድረስ በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይት [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን ሲዳማ ፊልድ በዌዴሳ ቤ/ክ መንፈሳዊ ስብሰባ ይካሄዳል፡፡ በመሆኑም የበረከቱ ተከፋዮች እንድትሆኑ ጥሪ ተደርጎላችሃል፡፡ በዕለቱም ለሕዝብ ከሚቀርበው ትምህርት በተጨማሪ ለቤ/ክ መሪዎች ሴሜናር ይሰጣል፡፡

ከዩኒየን ተጋባዥ እንግዶች:
1.ፓ/ር ልባሙ ጃለታ
2. ፓ/ር ደረጄ ጉደታና
3. ወ/ም ደነበ በቀለ ሲሆኑ የፊልዱ ወንጌላውያን፣ አስደሳች ዜና

እነሆ ከመስከረም 19 እስከ 21/2015 ዓ/ም ድረስ በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይት [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን ሲዳማ ፊልድ በዌዴሳ ቤ/ክ መንፈሳዊ ስብሰባ ይካሄዳል፡፡ በመሆኑም የበረከቱ ተከፋዮች እንድትሆኑ ጥሪ ተደርጎላችሃል፡፡ በዕለቱም ለሕዝብ ከሚቀርበው ትምህርት በተጨማሪ ለቤ/ክ መሪዎች ሴሜናር ይሰጣል፡፡

ከዩኒየን ተጋባዥ እንግዶች:
1.ፓ/ር ልባሙ ጃለታ
2. ፓ/ር ደረጄ ጉደታና
3. ወ/ም ደነበ በቀለ ሲሆኑ የፊልዱ ወንጌላውያንና በመዝሙር የፊልዱ ኳየርና የግል መዘምራ ያገለግላሉ፡፡

ወደ ዓለም እሄዳለሁ፤ የምስራች ነጋሪ ነኝ!

ዘገበው:- የአይ ኤም ኤስ ማልቲ ሚዲያ ነው፡፡

እንኳን ለ2015 ዓ/ም በሰላም አደረሳችሁ! ዓመቱ የሰላም፣ የፍቅርና በሁሉም ዘርፍ ፍሬ የማፍራት ዓመት እንዲሆን እንመኛለን::“ቢሰሙ ቢያገለግሉትም፥ ዕድሜአቸውን በልማት፥ ዘመናቸውንም በተድ...
09/09/2022

እንኳን ለ2015 ዓ/ም በሰላም አደረሳችሁ! ዓመቱ የሰላም፣ የፍቅርና በሁሉም ዘርፍ ፍሬ የማፍራት ዓመት እንዲሆን እንመኛለን::
“ቢሰሙ ቢያገለግሉትም፥ ዕድሜአቸውን በልማት፥ ዘመናቸውንም በተድላ ይፈጽማሉ።”
— ኢዮብ 36፥11፡፡

መልካም አዲስ ዓመት!
በሰማያዊ ደስታ፣ አለ ለነፍስ እርካታ!

Coming soon! በሥራው ላይ እጅ በመጨመር የበረከት ተከፋይ ለመሆን የሚትፈልጉ የዘማሪዋን የባንክ ደብተር ቁጥር ለማገኘት inbox አርጉልኝ ወይም በፖስተሩ ላይ ባሉት ስልክ ቁጥሮች ደው...
08/09/2022

Coming soon!
በሥራው ላይ እጅ በመጨመር የበረከት ተከፋይ ለመሆን የሚትፈልጉ የዘማሪዋን የባንክ ደብተር ቁጥር ለማገኘት inbox አርጉልኝ ወይም በፖስተሩ ላይ ባሉት ስልክ ቁጥሮች ደውላችሁ ማገኛት ትችላላችሁ::

❖❖ ማስታወቂያ❖❖“ዘመኑ ቀርቦአልና የሚያነበው፥ የትንቢቱን ቃል የሚሰሙትና በውስጡ የተጻፈውን የሚጠብቁት ብፁዓን ናቸው።”— ራእይ 1፥3፡፡በጳጉሜ ወር የሚነበብ የጾምና የፀሎት ንባብ፣ በኢን...
26/08/2022

❖❖ ማስታወቂያ❖❖

“ዘመኑ ቀርቦአልና የሚያነበው፥ የትንቢቱን ቃል የሚሰሙትና በውስጡ የተጻፈውን የሚጠብቁት ብፁዓን ናቸው።”— ራእይ 1፥3፡፡

በጳጉሜ ወር የሚነበብ የጾምና የፀሎት ንባብ፣ በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን ስለተዘገጃ፣ ከሰማያዊ ደስታ/Heavenly Joy ዋትስ አፕና ቴሌግራም ፔጅ እንዲሁም ከIMS Ethiopia Youth ቴሌግራም ፔጅ አውርዳችሁ እንድትጠቀሙና ለሌሎችም እንድታካፍሉ ዘንድ ቤ/ክ-ቷዋ ታሳስባለች፡፡ መልከም ዕለተ ሰንበት!

ዘገበው፡ የIMS Ethiopia Media (IEM) ነው፡፡

✿✿ኤልሸዳዩ አምላክ ይመስገን!✿✿“እናንተ የበሬና የአህያ እግር እየነዳችሁ በውኃ ሁሉ አጠገብ የምትዘሩ ብፁዓን ናችሁ።”  — ኢሳይያስ 32፥20፡፡በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ኤስ ዲ ኤ...
23/08/2022

✿✿ኤልሸዳዩ አምላክ ይመስገን!✿✿

“እናንተ የበሬና የአህያ እግር እየነዳችሁ በውኃ ሁሉ አጠገብ የምትዘሩ ብፁዓን ናችሁ።”
— ኢሳይያስ 32፥20፡፡

በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ኤስ ዲ ኤ] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን ምዕራብ ወለጋ ፊልድ በከለቾ አጥቢያ ቤ/ክን ከሰኔ 11 እስከ 14, 2014 ዓ/ም ድረስ የተደረገው መንፈሳዊ ስብሰባ በሰላም ተጠናቋል። በስብሰባው ላይ የኢትዮጵያ ዩኒየን ፕሬዝደንት ፓ/ር ሌንጫ ተክሌና የፊልዱ ፕሬዝደንት እ/ር ተሸመ መኮንን፣ ሌሎች ኮሚቴ አበላትና ወንጌላዊያን ተገኝተዋል፡፡

በዕለቱም እግዚአብሔር በተለያዩ አርእስት ሕዝቡን ስበርክና ስያነቃቃ ነበር፡፡ ሰንበት ዕለት ከአምልኮ በኀላ በተደረገው ጥሪ አንድ ቤተሰብ የወቅቱን እውነት ተቀብለዋል። በንስኃ የተመለሰ አንድ የቤተሰብ አባወራም ነበረ። ስለ አስደናቂ ሥራው እግዚአብሔር ይመስገን።🍇🍓

ዘገበው፡ የዩኒየኑን IMS Ethiopia Media እንደዘገበው፡፡

ድሉ የእግዚአብሔር ነው!በእግዚአብሔር ዕርዳታ ተከታተይ ለአራት ቀናት በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን በሲዳማ ፊልድ ...
16/08/2022

ድሉ የእግዚአብሔር ነው!

በእግዚአብሔር ዕርዳታ ተከታተይ ለአራት ቀናት በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን በሲዳማ ፊልድ በድክቻ ከተማ ስደረግ የቆየው ክሩሰይድ በሰላም ተጠናቋል፡፡ በጨቤ ከተማ ለማድረግ የታሰበው ክሩሰይድ የከሸፈ ብመስለውም፣ በጨቤ ከተማም ለጥናት ፍላጎት ያላቸውን ነፍሳት በማገኛት፣ የጠላት እቅድ በዜሮ ተባዝቷል፡፡ ሰይጣን ሞኝ ነው፤ አጠፋለሁ ብሎ የፈጣሪን ሥራ ከበፊቱ ይልቅ እንድበዛ ያደርጋል፡፡

በቆይተውም፡ በዘመን መጨረሻ ክስታቶች ዙሪያ፣ ዘመን ስለማይሽራው መጽሐፍ ቅዱስ፣ የዳንኤልና የራዕይ ቅዱሳት መጽሐፍት ትንቢት ጥናት፣ ስለ ጤና ትምህርት (የደም ግፍት መንስዔ፣ ውጤቱና መፍትሔ፣ ስለ ግልና አከባቢ ንጽህና አጠባበቅ፣ አስካሪ መጠጦችና ጎጂ ምግቦች) እና ለአበላት በተለያዩ አርእስት (የዓይን ምስክሮች፣ እግዚአብሔር ልብን ያውቃል፣ ጥልቅ ልባዊ የሆነ መለወጥ) እና በመሳሰሉት ሴሜናራዊ የሆነ በረከት ፈሷል፡፡ በተጨማሪ ለአካባቢው፣ ለአገራችንና ለዓለም ሰላም ሁኔታና ለታመሙ ፀሎት ተደርጓል፡፡

በመጨረሻም የኢትዮጵያ ዩኒየን ም/ፕሬዝደንት ፓ/ር ብርሃኑ ኤርሞሎ በክሩሰይዱ ያገላገሉ ፓ/ር ልባሙ ጃለታን (ዓለም አቀፍ ሠራተኛ)፣ ወ/ም ደነበ በቀለን (የዩኒየኑ ሚሽናሪ መሪ)፣ የሲዳማ ፊልድ ኮሚቴዎችን፣ በመዝሙር ያገለገሉ የፊልዱን መዘምራን፣ ዘማሪ ደሞዜ ጉዬ፣ ዘማሪ አገኘሁ ጎቴ፣ የጨፌ ቀበሌ የመንግሥት አመራሮችንና የጨፌ ቤ/ክ አበላትን አመስግነዋል፡፡ የዩኒየኑ ሚሽናሪ መሪም አክለውም ለፕሮግራሙ መሰካት ምክንያት የሆኑት ሁሉ አመስግነው በተለይም ባጄቱን የመደቡ በፊልዱ ውስጥ ያሉ በመንግሥትና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች የሚሠሩ ሠራተኞችን አመስግነዋል፡፡ እንደነዚህ ወገኖች በኢትዮጵያ ዩንየን ሥር የሚትገኙ በመንግሥት ሆነ በግል ድርጅቶች የሚትሠሩ ሰራተኞች የእግዚአብሔርን ሥራ ከበፊቱ ይልቅ እንድትደግፉ ዘንድ በጌታ ፍቅር እጠይቃችኀለሁ ብለዋል ሚሽናሪው፡፡

ይህ ለእግዚአብሔር የሥራ ጊዜ ነው፤ ሕግን ሸሩት (መዝሙር 119:126):: 1ቆሮን.15:58::

ወደ ዓለም ሁሉ እሄዳለሁ፣ የምስራች ነጋሪ ነኝ!

ዘገበው: የIMS Ethiopia Media ነው፡፡

የተለየ በረከት ጊዜ ነበረን!ዛሬ ከ3:00-6:00 ለምዕመናን "ለክርስቶስ ሕያው ምስክሮች" የሚል የጥናት ርዕስ በፓ/ር ልባሙ ጃለታ፣ ከምሽቱ 11:30-12:30 "እግዚአብሔርን መስማትና መገ...
12/08/2022

የተለየ በረከት ጊዜ ነበረን!

ዛሬ ከ3:00-6:00 ለምዕመናን "ለክርስቶስ ሕያው ምስክሮች" የሚል የጥናት ርዕስ በፓ/ር ልባሙ ጃለታ፣ ከምሽቱ 11:30-12:30 "እግዚአብሔርን መስማትና መገዛት" በሚል ዙሪያ ፓ/ር ብርሃኑ ኤርሞሎ እናም ከ12:45-2:50 "የአልኮል መጠጥ ጎጅነትና መንግስተ ሰማይ ምንድር ናት እናም የት ነው ያለችው?" በሚለው ርዕስ በፓ/ር ልባሙ ጃለታ ጥናት ቀርቧል፡፡ መዝሙር: በዘማሪ ሰሎሞን አብርሃም፣ በዘማሪ ደሞዜ ጉዬ፣ በዘማሪ አገኘው ጎቴ፣ በዘማሪ ደነበ በቀለና በሲዳማ ፊልድ መዘምራን ቀርቧል፡፡

መልካም ሰንበት!
ወደ ዓለም እሄዳለሁ፤ የምስራች ነጋሪ ነኝ!

ዘገበው:የIMS Ethiopia Media ነው፡፡

በድክቻ ከተማ በረከቱ እንደቀጠለ ነው!በሲዳማ  ፊልድ ድክቻ ከተማ በረከቱ እንደቀጠለ ነው:: ዛሬ ከ3:00 እስከ 7:30 ለምዕመናን በመነቃቃትና ተሐድሶ ዙሪያ ሴሜናራዊ ጉበዔ በቤ/ክ የተደረ...
11/08/2022

በድክቻ ከተማ በረከቱ እንደቀጠለ ነው!

በሲዳማ ፊልድ ድክቻ ከተማ በረከቱ እንደቀጠለ ነው:: ዛሬ ከ3:00 እስከ 7:30 ለምዕመናን በመነቃቃትና ተሐድሶ ዙሪያ ሴሜናራዊ ጉበዔ በቤ/ክ የተደረገ ሲሆን፣ ከ10:30 እስከ ማታ 3:00 ድረስ ደግሞ ጽድቅ በሃይማኖት ትምህርትና በሞራል ውድቀት ዙሪያ፣ በዳንኤል ምዕራፍ 7 እና ተጨማሪ ክለሰ በፍጻሜው ዘመን ክህስተቶችና እግዚአብሔርን ባለመታዘዝ በሚመጡ መቅሰፍት ዙሪያ ጥናት ቀርቯል፡፡

እግዚአብሔር ድንቅ አምላክ ነው፡፡ ሥራውን ማን ሊገታ ይችላል!

ምንጭ: IMS Ethiopia Media ነው፡፡

በድክቻ ከተማ የወንጌል በረከት ስዘንብ ውሏል!ትላንትና በጨቤ ከተማ የወንጌል በረከት እንዳይዘንብ ብከለከልም ቅሉ በአሮሬሳ ወረዳ በድክቻ ከተማ ዛሬ ስለ፡ ዘመን የማይሽረው መጽሐፍ ቅዱስ፣ ዳ...
10/08/2022

በድክቻ ከተማ የወንጌል በረከት ስዘንብ ውሏል!

ትላንትና በጨቤ ከተማ የወንጌል በረከት እንዳይዘንብ ብከለከልም ቅሉ በአሮሬሳ ወረዳ በድክቻ ከተማ ዛሬ ስለ፡ ዘመን የማይሽረው መጽሐፍ ቅዱስ፣ ዳንኤል ምዕራፍ ሁለት፣ አዳኛችን ኢየሱስ ዳግም ምጻትና መጨረሻ ዘመን ክስህተቶች፣ ንጽህና አጠባበቅና በመሳሰሉት እግዚአብሔር ሕዝቡን ስባርክ ውሏል፡፡
እግዚአብሔር መልካም ነው ሁል ጊዜ፡፡ አሰራሩ ልዩ ነው፡፡ መልካም አዳር!

ዘገበው: የIMS Ethiopia Media ነው፡፡

በሲዳማ ፊልድ ጨቤ ከተማ ክሩሰይድ ሰይጣን ለምን ተቆጣ!በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስ] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን በሲዳማ ፊልድ በጨቤ ከተማ ለማ...
09/08/2022

በሲዳማ ፊልድ ጨቤ ከተማ ክሩሰይድ ሰይጣን ለምን ተቆጣ!

በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስ] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን በሲዳማ ፊልድ በጨቤ ከተማ ለማድረግ ባቀደችው ክሩሰይድ ሰይጣን ተቆጥቷል፡፡ ሰሞኑን የወረዳው ፍትህና ጸጥታ ብፈቅድላቸውም ቅሉ ከዛሬ ጧት ጀምሮ ይህ ዜና እስከተጠነቀራበት ጊዜ ድረስ በወረዳ ውስጥ ባሉት የሌሎች ሃይማኖት መሪዎች፣ የሃይማኖት እኩልነትን ጥሰው ክሩሰይዱ አይካሄድም ብለው ማመልከቻ ሲያስገቡ የፈቀደው አካልም በፍራቻ ቃሉን በማጠፍ ቤተ ክርስቲያንቷን አታድርጊ ብሎአታል፡፡ በጉዳዩም የፊልዱ ወንጌላዊያን፣ ኮሚቴ አበላትና ከዩኒየን ፓ/ር ብርሃኑ ኤርሞሎ (የዩኒየኑ ም/ፕሬዝደንት)፣ ፓ/ር ልባሙ ጃለታ (በኢትዮጵያ ዩኒየን ፈቃድ ሠራተኛ) እና ወ/ም ደነበ በቀለ (ሚሽናሪ መሪ) ጨምሮ አቤቱታ ለማቅረብ ወደ ወረዳ አስተዳዳሪ ብሄዱም፣ ቢሮው ዝግ በመሆኑ ወደ ቤት ተመልሰዋል፡፡ በጉዳዩ ላይ በውይይት ላይ ናቸው:: ቀጣዩ ዜና ከአፍታ በኀላ ይዘን እንመለሳለን፡፡

ተቀላቀሉና ተባረኩበት!
09/08/2022

ተቀላቀሉና ተባረኩበት!

03/08/2022

የእግዚአብሔር ሰላም

✿✿ መልካም ዜና ✿✿ማቴዎስ 24"¹⁴ ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፥ በዚያን ጊዜም መጨረሻው ይመጣል።¹⁵ እንግዲህ በነቢዩ በዳንኤል የተባለው...
31/07/2022

✿✿ መልካም ዜና ✿✿
ማቴዎስ 24
"¹⁴ ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፥ በዚያን ጊዜም መጨረሻው ይመጣል።¹⁵ እንግዲህ በነቢዩ በዳንኤል የተባለውን የጥፋትን ርኩሰት በተቀደሰችው ስፍራ ቆሞ ስታዩ፥ አንባቢው ያስተውል፥"

በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት፣ ሲዳማ ፊልድ ጨቤ ከተማ ከነሐሴ 3-7/2014 ዓ/ም ድረስ ታላቅ መንፈሳዊ ክሩሰይድ ይደረጋል፡፡

✿ዋና ተናጋሪዎች፡
ፓ/ር ልባሙ ጃለታ (በኢትዮ ዩኒንየን በፈቃድ ሥራ የሚያግዙ) እና ፓ/ር ብርሃኑ ኤርሞሎ (የኢትዮ ዩኒየን ም/ፕሬዝደንትና የሆሳዕና ፊልድ ፕሬዝደንት)

✿መዘምራን፡
ዘ/ሪ ደሞዜ ጉዬ፣ ዘማሪ አገኘሁ ጎቴና የስደማ ፊልድ መዘምራን

✿አስተባባሪዎች፡
ወ/ም ደነበ በቀለ (ዩኒየን ሚሽናሪ ዘርፍ መሪ)፣ ወ/ም አደነ ያየ (የኢትዮ ዩኒየን ወጣቶችንና መልካሙ ሳምራዊ ዘርፍ መሪ)፣ የሲዳማ ፊልድ ወንጌላውያንና ኮሚቴ አበላት

✿የትምህርቱ አርእስት፡
❖የዳንኤልና የዮሐንስ ራዕይ ቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት
❖ፀጋና ህግ
❖የፍጻሜ ዘመን ክህስተቶች
❖የእውነተኛዪቱ የእግዚአብሔር ቤ/ክ ባህርያት
❖ለአገራችን ሰላም መፀለይ

✿ ትምህርት የሚቀርብበት አጋዥ መሰሪያ፡
❖መጽሐፍ ቅዱስ፣ በራሪ ወረቀቶች፣ ፕሮጀክተር፣ ባይነር፣ ከሙዚቃ ዕቃዎች ክቦርድና ጊታር

✿ ቦታ፡ የጨቤ ከተማ መዘጋጀ የፈቀደው ቦታ ይሆናል

✿ሰዓት፡ ከጧት::2:30-6:00 ቤት ለቤት ምስክርነት ጊዜ
❖ከ6:00-7:30 የምሳ ሰዓት
❖ከ7:30-10:30 የዝግጅት ጊዜ
❖ከ10:30-1:00 የክሩሰይዱ ጊዜ
❖ከ1:00 በኀላ የዕረፍት ጊዜ

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይበርካት፤ ሰላምም ያድርጋት!

ምንጭ፡ የIMS Ethiopia Media ነው፡፡

የጾታ ቅይይር ማድረግ መሰልጠን ነው ወይስ መሰይጠን? Is being trans-genderred- civilization or satanization?በ19ኛው ምዕተ ዓመት መጨረሻዎች፣ ወንዶች እንደ ...
27/07/2022

የጾታ ቅይይር ማድረግ መሰልጠን ነው ወይስ መሰይጠን? Is being trans-genderred- civilization or satanization?
በ19ኛው ምዕተ ዓመት መጨረሻዎች፣ ወንዶች እንደ ሴቶች አርግዘው መውለድ አለባቸው የሚል ጽንሰ-ሀሰብ ተጀምሮ፣ ከ20ኛው ምዕተ ዓመት ጀምሮ እስከ አሁን በዓለማችን በተለያዩ ክፍሎች ጾታ ቅይይር እየተደገ ልጅም እየተወለደ ይገኛል፡፡ ይህ ተግባር መሰልጠን ነው ወይስ መይሰይጠን ነው ትላላችሁ? በፈጣሪ ቃልማ:“እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው።” — ዘፍጥረት 1፥27:: ይላል፡፡

- -ማስታወቂያ--ኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት መመሪያ ዋጋ መጨመሩን አስታወቀ፡፡ ከዚህ በፊት...
22/07/2022

- -ማስታወቂያ--
ኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት መመሪያ ዋጋ መጨመሩን አስታወቀ፡፡

ከዚህ በፊት በቅናሽ ዋጋ ለምዕመናኑ ሲቀርብ የነበረው በየስድስት ወር አንዴ ታትሞ የሚወጣው የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት መመሪያ (ሰንበት ትምህርት) ከማተሚያ ቤት ወረቀትና ቀለም ዋጋ ግሽበት የተነሳ፣ አሁን ለህዝቡ የቀረበው"እርዳታ ከቤተ መቅደሱ" የሚለው የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት መመሪያ (ሰ.ትምህርት) ከበፊቱ የአንዱ ዋጋ ወደ ኢትዮ.ብር 50 ከፍ ማለቱን የዩኒየኑ ፕሬዝደንት ፓ/ር ሌንጫ ተክሌ አስታውቀዋል፡፡ ከዚህ በፊት አንዱ በቅናሽ ዋጋ ከሚታተመው፣ የአሁኑ ከሰኔ 25/2014 ዓ.ም እስከ ታህሳስ 22/2015 ዓ.ም ለተከታታይ ስድስት ወር የሚጠነው የአንዱ ወጪ በ67 ኢትዮ.ብር ስለታታመ፣ እላፊውን ብር ዩኒየኑ ለአበላት ድጎማ አድርጓል ብለዋል ፕሬዝደንቱ፡፡

❖የጥናት መመሪያውን ያዘገጁት: አንቶኒዮ ዳይፍራንካ ሲሆኑ
❖ አማርኛና ኦሮምኛ የተረጓመው፣ ያሰተማውና ያከፋፈለው፡ ኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ዩኒየን ነው፡፡

“ዘመኑ ቀርቦአልና የሚያነበው፥ የትንቢቱን ቃል የሚሰሙትና በውስጡ የተጻፈውን የሚጠብቁት ብፁዓን ናቸው።” — ራእይ 1፥3፡፡
ወደ ዓለም ሁሉ እሄዳለሁ፤ የምስራች ነጋሪ ነኝ!

የዘገበው ምንጭ፡ የIMS Ethiopia Media ነው፡፡

የዩኒየኑ ቦርድ የግማሽ ዓመት ሥራ አፈጻጸም ገመገመ፡፡ባሰለፍነው ወር ነበር የኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት የኢትዮጵያን ዩኒየን ቦርድ...
20/07/2022

የዩኒየኑ ቦርድ የግማሽ ዓመት ሥራ አፈጻጸም ገመገመ፡፡

ባሰለፍነው ወር ነበር የኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት የኢትዮጵያን ዩኒየን ቦርድ የግማሽ ዓመት ሥራ አፈጻጸም የገመገመው፡፡ የዩኒየኑ 5ኛው ዙር ምርጫ በህዳር 30/03/2014 ዓ.ም መደረጉ የሚታወስ ሲሆን ቦርዱ በካሄደው 2ኛ ዙር መደበኛ ስብሰባ ላይ: በወንጌል ሥራ ዘርፍ፣ በዩኒየን ግንባታ ዙርያ፣ በፊልዶች ሥራ አፈጻጸምና በሌሎች ጉዳዮችም ተወያይቷል፡፡
1ኛ.የውጭውን (Outreach) ወንጌል ዘርፍ በተመለከተ፣ በክሩሳይዶች የተወሰነ እንቅስቃሴ መደረጉን ገምግሞ ይህ በበቂ ሁኔታ መሠራት እንዳለበት አስቀምጧል፡፡ በወንጌል ሠራተኞች ረገድም አዳዲስ ነፍሳት ወደ ጌታ በመመለሳቸው ፈጣሪን አመስግኖ፣ የሚጠበቀው ያልህ አለመሥራቱን ያወሰው ቦርድ፣ ለዚህም ችግር መንስኤ በአገራችን የተከሰተውን የዋጋ ግሽበት ሊሆን ይችላል የሚለውን በግንዛቤ ውስጥ በማስገባት፣ከሐምሌ ወር ጀምሮ እስከ 3ኛ መደበኛ ጉባዔ ድረስ ለትራንስፖርት ድጋፍ የሚሆን ገንዘብ (Transport Allowance) ለሠራተኞች እንድሰጥ ወስኗል፤ በዚህ የሚቻላቸውን ያህል ለነፍሳት ዳህንነት እየሠሩ፣ ከቀጣይ ስብሰባ በኀላ ግን ተወካዮች ባስቀመጡት መሠረት የደሞዝ መሸሻያ እንደሚያደርግ ገልጿል፡፡ ከዚህም ጋር በመያያዝ የሠራተኛ እጥረት ባለበት ፊልድ ሁለት ቋሚና ሶስት ፈቃድ ሠራተኞችን ቀጥሯል፡፡
2ኛ. የዩኒየኑን ባለሶስት ክፍሎችና አጥር ግንባታ በተመለከተ፣ ቦርዱ በሰጣቸው ስልጣን መሠራት ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ 90% ከመቶ በመስራታቸው እጅግ አመስግኖ፣ ለዚህም ሥራ ድጋፍ የሚሆን ገንዘብ ከሚመለከታቸው ምንጮች በሚገባ መሰበሰብ እንደለበት ጠቁሟል፡፡
3ኛ. የዩኒየኑ ገ/ያዥ ወ/ም አበበ ሎምባሞ በመታመሙ ምክንያት በጊዜያዊነት የእርሱ ረዳት ሆኖ እንድሠራ እ/ር ሳሙኤል ኑኔን ወስኗል፡፡
4ኛ. ቤተሰብ በኤደን ገነት በፈጣሪ የተቋቋመ ተቋም በመሆኑ፣ የጋብቻ ቅዱስነት ለመጠበቅ ከመተጫጨት እስከ ጋብቻና በተያያዥ ጉዳዮች ጥንዶች መከተል ያለባቸውን ደንብ በቀጣይ ጉባዔ በህኑና ምስክሩ መሠረት ለመጽደቅ አቅጣጫ ይዟል፡፡ ለዚህም ተግባር ንድፈ-ሀሳቦችን ለቦርድ እንድያቀርቡ፡ 1ኛ ፓ/ር ሌንጫ ተክሌ (የዩኒየኑ ፕሬዝደንት)፣ 2ኛ.ፓ/ር ብርሃኑ ኤርሞሎ (የዩኒየኑ ም/ፕሬዝደንት) እና 3ኛ.ፓ/ር ፀጋዬ ኦቦላን (የዩኒየኑ ፀሐፍ) ቦርዱ መርጧቸዋል፡፡ እነርሱም ከዩኒየኑ ቤትና ቤተሰብ ክፍል ጋር በመሆን ይሠራሉ ተብሏል፡፡
5ኛ. ቦርዱም ስብሰባውን ቀን እያደረገ ከቀኑ አስር ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት የዩኒየኑ ዋና ቢሮ ባለበት አከባቢ፣ በሴንትራል ጊዜያዊ ሚሽን ፊልድ በሳሪስ ቤ/ክ አዘጋጅነት የታቀደውን ክሩሴይድ አካሂዷል፡፡

ወደ ዓለም ሁሉ እሄዳለሁ፤ የምስራች ነጋሪ ነኝ!

ምንጭ፡ የIMS Ethiopia Media ነው፡፡

የተሸለ አገልግሎት ለመስጠት፣ አስተያየትዎን እንፈልጋለን! We need your genuine recommendation to serve you better!በሰማያዊ ደስታ፣ አለ ሁለተናዊ እርካታ!
18/07/2022

የተሸለ አገልግሎት ለመስጠት፣ አስተያየትዎን እንፈልጋለን! We need your genuine recommendation to serve you better!
በሰማያዊ ደስታ፣ አለ ሁለተናዊ እርካታ!

ዓለም አቀፋዊ የተወካዮች ስብሰባ ጊዜ ተገለጸ፡፡መዝሙር 133¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¹ ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፥ እነሆ፥ መልካም ነው፥ እነሆም፥ ያማረ ነው። ² ከራስ እስከ ጢም እንደሚፈስስ፥ እስ...
15/07/2022

ዓለም አቀፋዊ የተወካዮች ስብሰባ ጊዜ ተገለጸ፡፡
መዝሙር 133
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፥ እነሆ፥ መልካም ነው፥ እነሆም፥ ያማረ ነው። ² ከራስ እስከ ጢም እንደሚፈስስ፥ እስከ አሮን ጢም፥ በልብሱ መደረቢያ እንደሚወርድ ሽቱ ነው። ³ በጽዮን ተራሮች እንደሚወርድ እንደ አርሞንዔም ጠል ነው፤ በዚያ እግዚአብሔር በረከቱን ሕይወትንም እስከ ዘላለም አዝዞአልና።

የኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ጄኔራል ኮንፍራንስ የተወካዮች ስብሰባ ከ04/11/2015 ዓ.ም እስከ 23/11/2015 ዓ/ም ወይም እአአ ከጁለይ/ሐምሌ 11-30/2023 በደቡብ አሜሪካ፣ ፔሩ እንደሚካሄድ ተገለጸ፡፡ የሕዝብ ስብሰባ ደግሞ ከ26/11/2015 ዓ.ም እስከ 30/11/2015 ዓ.ም ወይም እአአ ከአጎስት/ነሐሴ 2-5/2023 ይካሔዳል፡፡

ለዚህም ከየአገራት የተመረጡ ተወካዮች አስፈላጊውን ቅድመ-ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባቸው የጄኔራል ኮንፍራንስ ፕሬዝደንት ፓ/ር ትዝቭታን ፔትኮቭ ገልጾዋሉ፡፡ የምዝገባ ቅጽ ከሐምሌ 25/2014 ወይም እአአ ከኦጎስት 1/2022 በኀላ በድርጅቱ ድህረ-ገድ sda.1844.org እንደሚለቀቅም ነው ፕሬዝዳንቱ የገለጹት፡፡ ታዲያ ከቤ/ክ አበላት ምን ይጠበቃል? መልሱ ግልጽ ነው፡ ለቀጣይ አምስት ዓመት ቤ/ክ-ቷን የሚመሩት እግዚአብሔር እንድመርጣቸው መጸለይ ነው፡፡

ወደ ዓለም እሄዳለሁ፤ የምስራች ነጋሪ ነኝ!

ምንጭ፡ የIMS Ethiopia Media ነው፡፡

እግዚአብሔር ይመስገን!በፀሎትና በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው፣ የኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን ሆሳዕና ፊልድ በባምቦ አጥ...
12/07/2022

እግዚአብሔር ይመስገን!

በፀሎትና በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው፣ የኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን ሆሳዕና ፊልድ በባምቦ አጥቢያ ቤ/ክ አዘጋጅነት ከ29/10/14 እስከ 02/11/14 ዓ.ም የተደረገው ስብሰባ በሰላም ተጠናቀቀ፡፡ በስብሰባው የተገኙ: የኢትዮጵያ ዩኒየን ፕሬዝዳንት ፓ/ር ሌንጫ ተክሌና የዩኒየኑ ፀሐፊ ፓ/ር ፀጋዬ ኦቦላ በቃል ያገለገሉን ሲሆኑ፣ የወሼባ ድስትሪክ/ጣቢያ/፣ የሆሳዕናና የሰሜን ሆሳዕና አብያተ-ክርስቲያናት መዘምራን፣ ዘማሪ ፓ/ር ዘላለም አዲሱ(የደቡብ ፊልድ ፕሬዝደንት)፣ ዘማሪት አልማዝ ገብሬና ሌሎች የዩኒየኑ ሚሽናሪ መሪ ወ/ም ደነበ በቀለ፣ ፓ/ር ፍቅሬ አኑሎ (በፈቃድ በሆሳዕና ፊልድ የሚያገለግሉ)፣ የሆሳዕና ፊልድ ም/መሪና የፕሬዝዳንቱ ተወካይ ወ/ዊ አዲሴ ሀብቴ፣ የፊልዱ የቀድሞ ፕሬዝዳንት አቶ መለሰ አቡራና የሰሜን ሚሽን ፊልድ ፕሬዝደንት ወ/ዊ ተሰማ ገ/መድህን ተገኝተው አገለግለዋል፡፡ በዕለቱ የተደረጉ ዋና ዋና ተግባራት:
1ኛ. ለሕዝብ ሴሜናራዊ የሆነ ትምህርት በተለያዩ አርእስት ቀርቧል፣
2ኛ. በአቡነ/ጌጃ ከተማ ለተከታታይ አራት ቀናት ክሩሳይድ ተደርጓል፤ የትንብተ ዳንኤልና የዮሐንስ ራዕይ መጽሐፍት ጥናት በከፊል ተጠንቷል፤ በቁጥር 420 የሚሆን "የአዳኛችን የኢየሱስ ዳግም መምጣት ምልክቶች" የሚል በራሪ ወረቀት ተሰራጭቷል፣
3ኛ. 4 ወንዶችና 7 ሴቶች በድምሩ 11 ነፍሳት በፓ/ር ፍቅሬ አኑሎ ተጠምቀው፣ በዩኒየኑ ፕሬዝደንት በፓ/ር ሌንጫ ተክሌ የማደፋፈሪያ ጥቅስ ለእያንዳንዳቸው ተሰጥቶ አቀባበል በማድረግ በቤ/ክ ተጨምረዋል፡፡
4ኛ. ለሁለት ቤተሰብና አንድ ነፍስ ወደ ጌታ ለመመለስ ቃል ገብተዋል፡፡ ሁላችሁንም ጌታ በፀጋው ጨምሮ ይጎበኛችሁ!
“ስለ በጎ ፈቃዱ መፈለግንም ማድረግንም በእናንተ የሚሠራ እግዚአብሔር ነውና።”— ፊልጵስዩስ 2፥13፡፡
ወደ አለም ሀሉ እሄዳለሁ፤ የምስራች ነጋሪ ነኝ!

ዘገባው: የIMS Ethiopia Media ነው፡፡

06/07/2022

የፓ/ር ልባሙ ጃለታ እናት ባለፈው ሰንበት (ቅዳሜ) ከሰዓት አርፈው ትላንትና በ27/10/2014 ዓ/ም ም.ወለጋ በመንዲ የግብዓተ መሬት ሥነ-ሥርዓት ተፈጽሟል፡፡ ለፓ/ር ልባሙና ለቤተ-ሰቦቻቸው፣ የቤ/ክርስቲያን አበላት በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን!
“እርሱ በመከራችን ሁሉ ያጽናናናል፥ ስለዚህም እኛ ራሳችን በእግዚአብሔር በምንጽናናበት መጽናናት በመከራ ሁሉ ያሉትን ማጽናናት እንችላለን።” 2ኛ ቆሮ 1፥4፡፡ ደውላችሁ ለመጽናናት የሚትፈልጉ በ0911373991 መገናኘት ትችላላችሁ!
ምንጭ፡-IMS Ethiopia Media

ኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን፣ ባለሶስት ክፍል ቤትንና የግቢውን አጥር ግንባታ በ200,000 ሺህ ብር አከባቢ ወጪ ...
30/06/2022

ኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን፣ ባለሶስት ክፍል ቤትንና የግቢውን አጥር ግንባታ በ200,000 ሺህ ብር አከባቢ ወጪ አድርጎ እስከዚህ ደረጃ አድርሷል፡፡ ወጪውም የሚሸፈነው በምዕመናኑ፣ በዩኒየኑና በለጋሽ ግለሰቦች ድጋፍ ነው ተብሏል፡፡ ታዲያ እርስዎ ለፈጣሪ ሥራ ምን ያህሉን አበረከቱ? አሁኑኑ ፈጥነው ከበረከቱ ይካፈሉ፡፡ የቤ/ክርስቲያንቷዋን የባንክ ደብተር ቁጥር ከፈለጉ በውስጥ መስመር ያናግሩን!
“... የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል፥ እኛም ባሪያዎቹ ተነሥተን እንሠራለን፤....።”— ነሀምያ 2፥20፡፡

ልክ እንደና ነህምያ ዘመን፣ የእግዚአብሔር ቤት ሥራ እንዳይሠራ ከውስጥና ከውጪ ጠላቶች ብዙ ናቸው፡፡ በፀሎት፣ በሀሳብና በገንዘብ በመርዳት ፋንታ በትችትና በሞኝነት ወሬ የመቅደሱ ገንቢዎችን ጉልበት የሚያደክሙ ጥቂቶች አይደሉም፡፡ በእነዚህ ሳንሸበር፣ በቀኝ እጃችን የወንጌል እወጃችንን፣ በግራ እጃችን መቅደሱን እየገነበን እንበርታ!

ወደ ዓለም እሄዳለሁ፣ የምስራች ነጋሪ ነኝ!

የዘገበው ምንጭ፡ IMS Ethiopia Media ነው

በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን ሆሳዕና ፊልድ በባምቦ አጥቢያ ከ29/10/2014 ዓ/ም - 02/11/2014 ዓ/ም ድ...
26/06/2022

በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን ሆሳዕና ፊልድ በባምቦ አጥቢያ ከ29/10/2014 ዓ/ም - 02/11/2014 ዓ/ም ድረስ አገር አቀፍ መንፈሳዊ ስብሰባና በአቡና ከተማ ክሩሰይድ በዳንኤልና በራዕይ መጽሐፍትና በፍጻሜው ዘመን ክህስተቶች ዙሪያ ልዩ ጥናት ተዘጋጅቷል፡፡ በዕለቱ ፓ/ር ሌንጫ ተክሌ (የዩኒየኑ ፕሬዝደንት)፣ ፓ/ር ፀጋዬ ኦቦላ (የዩኒየኑ ፀሐፊ) ፣ ፓ/ር ልባሙ ጀለታ (በኢትዮ ዩኒየን ፈቃድ ሠራተኛ) እና ሌሎችም ለአገልግሎት ታድመዋል፡፡ ከመንፈሳዊ በረከት እንድትካፈሉ ቤ/ክርስቲያንቷዋ ጥሪ አድርጋሃለች!
“ዘመኑ ቀርቦአልና የሚያነበው፥ የትንቢቱን ቃል የሚሰሙትና በውስጡ የተጻፈውን የሚጠብቁት ብፁዓን ናቸው።” ራእይ 1፥3፡፡

የፎቶው ምንጭ፡ በሲዳማ ፊልድ በቅርብ ጊዜ ከተደረገው ክሩሳይድ የተወሰደ፡፡

21/06/2022

In this page, weekly live program coming soon! Please hurry up to be its member!

በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን፣ በሰሪስ ቤ/ክና በአዲሱ ጊዜያዊ  ሴንቴራል ሚሽን ፊልድ ትብብር የተዘጋጀው "የዳንኤ...
15/06/2022

በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን፣ በሰሪስ ቤ/ክና በአዲሱ ጊዜያዊ ሴንቴራል ሚሽን ፊልድ ትብብር የተዘጋጀው "የዳንኤልና የራዕይ መጽሐፍት ትንቢት ጥናት"የአደባባይ ስብከት (ክሩሰይድ) በአዲስ አበባ ከተማ ከትላንትና 11:00 ጀምሮ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 11 ጋርመንት አከባቢ በዚህ መልኩ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ የክሩሰይዱ ተናጋሪዎች: ፓ/ር ሌንጫ ተክሌ (የዩኒየኑ ፕሬዝደንት)፣ ፓ/ር ልባሙ ጀለታ(በኢትዮጵያ በፈቃድ ሥራ የሚያግዙ) እና ሌሎችም ፓ/ር ብርሃኑ ኤርሞሎ፣ፓ/ር ፀጋዬ ኦቦላ፣ ዘማሪ ፓ/ር ዘላለም አዲሱ፣ ዘማሪት ምርታየሁ መኮሮና የየፊልድ መሪዎችን ጨምሮ ይገኙበታል፡፡
“ዘመኑ ቀርቦአልና የሚያነበው፥ የትንቢቱን ቃል የሚሰሙትና በውስጡ የተጻፈውን የሚጠብቁት ብፁዓን ናቸው።” ራእይ 1፥3፡፡

13/06/2022

ነገ ማለትም ከ07/10/2014 ዓ/ም ጀምሮ እስከ 10/10/2014 ድረስ የኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ [ሰቬንዝ ዴይ አድቬንቲስት] ቸርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን ቦርድ ኮሚቴ 5ኛ ዙር ምርጫ ከተደረገበት ጊዜ ጀምሮ የተከናወኑ ሥራዎችን በተወካዮች ጉባዔ ይገመግማል፡፡ በግምገመውም መሠረት የተለያዩ ውሳኔዎችን ያስተላልፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በተጨማሪ በመዲነዋ አዲስ አበባ ከተማ፣ በጊዜያዊ ሴንትራል ሚሽን ፊልድ አዘጋጅነት በተዘጋጀው ክሩሴይድ ከምሽቱ 11:00 ጀምሮ ቦርዱ ይሰተፋል፡፡ በክሩሴይዱም ከዩኒየን መሪዎች በተጨማሪ የዓለም አቀፍ ሠራተኛ የሆኑ ፓ/ር ልባሙ ጀለታ ተገባዥ ተናጋሪ መሆናቸውንም ከዩኒየን ዋና ቢሮ ያገኛነው መረጃ ያሰያል፡፡

ወደ ዓለም እሄዳለሁ፣ የምስራች ነጋሪ ነኝ!

በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ (ሰቬንዝ ዴይ አድቬንትስት) ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን በሆሳዕና ፊልድ ሰሜን ሆሳዕና ቤ/ክ ለአንድ ሳምንት (ከ23/08/2014ዓ/ም እስከ ...
17/05/2022

በኢንተርናሽናል ሚሽናሪ ሶሳይቲ (ሰቬንዝ ዴይ አድቬንትስት) ቼርች ኦፍ ሪፎርም ሙቭመንት ኢትዮጵያ ዩኒየን በሆሳዕና ፊልድ ሰሜን ሆሳዕና ቤ/ክ ለአንድ ሳምንት (ከ23/08/2014ዓ/ም እስከ 28/08/2014 ዓ/ም ሲካሄድ የነበረው የመጀመሪያ ዙር የወንጌል ሠራተኞች "የዳንኤልና የራዕይ መጽሐፍት ትንቢት ጥናት" እና "መሠረታዊ የኮምፒውተር" ስልጠና በሰላም ተጠናቋል፡፡ የትንቢት ጥናት አሰልጣኞች ፓ/ር ሌንጫ ተክሌ (የዩኒየኑ ፕሬዝደንት)፣ ፓ/ር ልባሙ ጀለታ (በኢትዮ.በፈቃድ የሚያገለግሉ) ሲሆኑ በኮምፒተር እ/ር ተስፋዬ ኢያሱና እህታችን ታደለች ሰለሞን ነበሩ፡፡ በስጣናውም መጨራሻ የተለያዩ ምክርና አስተያየት ተደርጎ፣ ለሠልጣኞች በዩኒየኑ ጽ/ቤትና በወንጌል ሥራ ዘርፍ ትብብር የተዘጋጀ የምስክር ወረቀት በፓ/ር ሌንጫ ተክሌ፣ በፓ/ር ልባሙ ጀለታና ፓ/ር ፀጋዬ ኦቦላ ተበረክቶላቸዋል፡፡

ወደ ዓለም ሁሉ እሄዳለሁ፣ የምስራች ነጋሪ ነኝ!

የዘገበው ምንጭ: ከዩኒየን ጽ/ቤት ነው፡፡

Address

Hossana

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሰማያዊ ደስታ/Heavenly Joy posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ሰማያዊ ደስታ/Heavenly Joy:

Videos

Share

Category