Addis Ababa Daily News

Addis Ababa Daily News Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Addis Ababa Daily News, Media/News Company, Addis Ababa.

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የከተማዋን አስፈጻሚ አካላት መልሶ ለማቋቋም የቀረበለትን አዋጅ በሙሉ ድምጽ አጸደቀአዲስ አበባ ፤ ህዳር 15/2016 (ኢዜአ) ፦ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤ...
25/11/2023

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የከተማዋን አስፈጻሚ አካላት መልሶ ለማቋቋም የቀረበለትን አዋጅ በሙሉ ድምጽ አጸደቀ

አዲስ አበባ ፤ ህዳር 15/2016 (ኢዜአ) ፦ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የከተማዋን አስፈጻሚ አካላት መልሶ ለማቋቋም የቀረበለትን አዋጅ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡

ምክር ቤቱ አዋጁን ያጸደቀው 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ባለበት ወቅት ነው።

በዚሁ መሰረት መልሰው የተቋቋሙት ተቋማት፡-

1- የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ

2- የስራ እና ክህሎት ቢሮ

3- የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ቢሮ

4- የፕላን እና ልማት ቢሮ

5- የመንግስት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን

6- የህብረት ስራ ኮሚሽን

7- የምግብና መድሀኒት ባለስልጣን

8- የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን

9- የሲቪል ምዝገባ እና ነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ

10- የመስሪያ ቦታዎች ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ

11- የግንባታ ፍቃድ እና ቁጥጥር ባለስልጣን ናቸው፡፡

ተቋማቱን መልሶ ማቋቋም ያስፈለገው የኑሮ ውድነቱን ለመቀነስ፤ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ እና የነዋሪውን ጥያቄ ለመመለስ ታሳቢ በማድረግ መሆኑን የከንቲባ ጽህፈት ቤት መረጃ ይጠቁማል፡፡

ትናንትና በአዲስ አበባ ከተማ በተደረገው ታላቁ ሩጫ ምንድነው የሆነው? በትናንትናው ዕለት በአዲስ አበባና ሸገር ከተሞች ታላቁ ሩጫ ላይ የተሳተፉ የስፖርት ቤተሰቦች ከ45,000 እስከ 50, ...
20/11/2023

ትናንትና በአዲስ አበባ ከተማ በተደረገው ታላቁ ሩጫ ምንድነው የሆነው?

በትናንትናው ዕለት በአዲስ አበባና ሸገር ከተሞች ታላቁ ሩጫ ላይ የተሳተፉ የስፖርት ቤተሰቦች ከ45,000 እስከ 50, 000 የሚገመት ነው።

99.9℅ ተሳታፊ ስፖርት ለጤና፣ ለህዝቦች አንድነትና አብሮነት በሚል መርህ ሩጫውን አጠቅቆ ነው ወደቤቱ የተመለሰው።

ከጠቅላላው ተሳታፊዎች 1℅ አንኳ የማይሞሉ አንዳንድ በጥላቻ ልክፍት የተመቱ ግለሰቦች ለቲክቶክ መንደር ማሞቂያ ይጠቅመናል ብለው ያሰቡትን ከፋፋይ ሀሳብ አቀርሽተዋል።

እነዚያ ይመጣሉ እያሉ የዘመሩላቸው ያረጀውንና ያፈጀውን ስርዓት ለማስመለስ የሚኳትኑ ምስኪን የስልጣን ጥመኞች በ24 ውስጥ 4ኪሎ እንገባለን ካሉ ሰነባብተዋል።

ምኞት አይከለከልም ያለው ማን ነበር?

21/11/2022

ብልፅግና ፓርቲ የፓለቲካው ዋነኛው ዓላማ ለሁሉም የምትስማማ፣ ሁሉንም ኢትዮጵያውያን የምትመስል፣ የበለፀገች፣ የብሔሮችን መብት ከግለሰብ መብቶች ጋር አጣጥማ የምታስጠብቅ፣ ጠንካራ ፌደራላዊት ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን መገንባት ነው።

ይህን ዓላማ ለማሳካት የምንከተለው መንገድ፦
👉 እስካዛሬ እንደ ሀገር ባስመዘብናቸው ድሎች ላይ መገንባት

👉 የቀድሞውን ትሩፋትና ስኬት ማስጠበቅና ማጠናከር

👉 ከቀድሞ ስህተቶች መማርና መታረም

👉 በጎውን በማስቀጠልና በማሳደግ፣ ክፉውን ማረምና አለመድገም ናቸው።

መልካም የስራ ሳምንት ይሁንልዎ!!
Addis Ababa Prosperity Party

 ;-
14/07/2022

;-

 Siidawwaan tibba kana eebbiffaman~~Siidaa Luba Guddinaa Tumsaa~Siidaa Sheek Mohammeed Rashaad Abdulle~Siidaa Dr.Hayilee...
08/07/2022


Siidawwaan tibba kana eebbiffaman~

~Siidaa Luba Guddinaa Tumsaa

~Siidaa Sheek Mohammeed Rashaad Abdulle

~Siidaa Dr.Hayilee Fidaa

~Siidaa Onesimoos Nasiib

~Siidaa Sheek Bakrii Saphaloo

26/06/2022

የህግ ማስከበር ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ለሁሉም የሚበጀው የህግ በላይነት የሰፈነባት ሃገር ስትኖረን ነው፡፡ የህግ የበላይነት እንዲሰፍን የሁላችንም ሃላፊነትና ተግበር መሆን አለበት!!
ህዝቡ በሁሉም አግባብ መንግስትን የጠየቀው ጠንካራ የህግ ማስከበር እንዲደረግና አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን ነው፡፡ ለዚህም ምላሽ መንግስት በየደረጃው ከህግ በላይ ነን የሚሉ ሃይሎችን ህግ ማስከበር በመጀመሩ ምክንያት በየቦታው ሰላም እየሆነ መጥቷል፡፡
አሁንም በዚህ የህግ ማስከበር ዘመቻ ህልውናቸው እያበቃ እንደሆነ የተረዱ ሃይሎች በጭካኔ በህዝብ ላይ ለፈፀሙት ድርጊት የእጃቸውን ያገኛሉ፡፡ በዚህ ምክንያትም ወደ ኋላ የሚመለስ የህግ ማስከበር ስራ አይኖርም፤ ይልቁንም ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
ሰዎችን በስሜት በማነሳሳት የህግ ማስከበሩን ዘመቻ ማደናቀፍ በጭራሽ አይቻልም!!

እኔ ወይም የእኔ ቡድን ብቻ ብሎ ማሰብ ለኢትዮጵያ አይሆንም !!ህብረብሄራዊነት ባለበት ጽንፈኝነት የበለጠ አደጋ ነው !! # # # # # # # # # # # # # # # # # # # # #በኢ...
19/06/2022

እኔ ወይም የእኔ ቡድን ብቻ ብሎ ማሰብ ለኢትዮጵያ አይሆንም !!
ህብረብሄራዊነት ባለበት ጽንፈኝነት የበለጠ አደጋ ነው !!
# # # # # # # # # # # # # # # # # # # # #

በኢትዮጵያ በመሰረታዊነት መቀየር (Transformed) መሆን ከሚገቡ ጉዳዮች ውስጥ አንዱ ለዘመናት የተገነባው የፖለቲካ ልምምዳችን ነው። ፖለቲካችን በጽንፍ ወይም በዋልታ-ረገጥ ዕይታዎች የተወጠረ ነው።
በፖለቲካ ልሂቃን መካከል ጫፍ ና ጫፍ ቆሞ ገመድ መጓተት ፣ እልህ መጋባትና ማኩረፍ ፣ ብጥብጥ መፍጠርና የህዝብን ሠላም ማደፍረስ ፣ያለመደማመጥ ፣ እኔ /የእኛ ቡድን ብቻ ልክ ነን ፣ ፍፁም እውነተኛ ነን ብሎ ማሰብ፣የተለየ ሀሳብ የያዘን አካል እንደ ጠላት ማየት ፣ ስለሆነም የሀሳብ ልዩነት በሀይልና አውዳሚ በሆነ መንገድ የመፍታት አባዜ ውስጥ ቆይተናል። ይህ እጅግ ኋላቀር የፖለቲካ ልምምድ ጽንፈኝነት በከፍተኛ ሁኔታ እያቆጠቆጠ እንዲመጣ መነሻ ሆኗል። በፅንፈኝነት ምክንያት ዛሬ ላይ የኢትዮጵያ ሰላም ፣አንድነትና ልማት ፈተና ውስጥ ነው።
ስለ ጽንፈኝነት (Extremism)
በርካታ መዝገበ ቃላት ሲተረጎሙ ኢ- ምክንያታዊና በብዙሃኑ ዘንድ ተቀባይነት የሌለው ርይኦተዓለም፣ ባህርይ፣ እምነትና ድርጊት እንደሆነ ያስቀምጣሉ ፡፡ አንዳንድ ምንጮች እንደሚገልጹት የጽንፈኝነት ተመሳሳይ ቃላት (ሃሳቦች) ዋልታ-ረገጥነት ፣ ዘረኝነትን፣ ሌላን ጥላቻ ፣ ያለመቻቻል፣ ኢ- ፍትሐዊነት፣ የሞራል ዝቅጠትና ልክ የለሽ ግለኝነት ናቸው፡፡
ጽንፈኝነት ዴሞክራሲያዊ አሰራርንና መንግስትን፣ የሕግ የበላይነትን፣ የግለሰቦች ነጻነትን፣ ልዩነቶችን ማክበርና ማስተናገድን፣ ችግሮችን በሕግና በውይይት መፍታትን፣ በመሬት ላይ ያለውን ማህበራዊ ስርዓት አይቀበልም፡፡
ጽንፈኝነት በሕብረተሰቡ ውስጥ ያለመረጋጋትን፣ ያለመተማመንንና ያለመተባበርን ይፈጥራል፡፡ በመሆኑም ሰላምና የልማት እንቅስቃሴ ይስተጋጎላሉ፡፡
የተባበሩት መንግስታት (2015) plan of action to prevent violent extremism በሚለው ዕቅድ/ ሰነድ እንደገለጸው ጽንፈኝነት የአንድን ቡድን ፍላጎት ለማሟላት፣ ሌለውን ወገን ለመጨቆንና ለማፈን፣ በወቅቱ ያለውን ማህበራዊና ፓለቲካዊ ስርዓት ለማናጋት፣ በአብዛኛው በሰዎችና በጾታዎች እኩልነት የማያምን አካሄድና ክስተት እንደሆነ ያመለክታል፡፡
ሰዎች ጽንፈኛ ሆነው አይወለዱም፣ በአንድ ቀንም ጽንፈኛ አይሆኑም ዘራቸው/ጎሳቸው ወይም ሃይማኖታቸውም ጽንፈኛ አያደርጋቸውም። ዕድገት፣ ኑሮ፣ ጓደኛ፣ ትምህርት፣ ሚዲያ፣ ውሎ፣ ወዘተ አስተዋጽኦ አላቸው፡፡፡
የሳልታር (2004) ጥናት እንደሚያሳየው ጽንፈኞች የሰዎችን የእኩልነት መብት አይቀበሉም፣ የተለያዩ ብሔሮች ፣ ዘሮችንና ሃይማኖቶችን ይሳደባሉ አክብሮት የላቸውም፣ ጥላቻም ያንጸባርቃሉ ፣ዛቻና ማስፈራራትን ይጠቀማሉ፡፡
ጽንፈኝነት ሰላምን ያናጋል፣ ሰዎች ደህንነት እንዳይሰማቸው ያደርጋል፣ ለአገር ልማትም እንቅፋት ነው፡፡
ጽንፈኝነት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የነበረ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ግን በብዛቱም ሆነ በዓይነቱ በአውደሚነቱና የዜጎችን ሰላም በማወክ ረገድ ከፍተኛና አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ከዕለት ተእለት እንቅስቃሴ መረዳት ይቻላል ፡፡ ጽንፈኞች የፓለቲካ ፕሮጀክታቸው መጠቀሚያ የሚያደርጉት ብሔር እና ሀይማኖትን ነው። ለዚህም ነው ዛሬ በሀገራችን በብሔር እና በሃይማኖት ስም ዘግናኝ ድርጊቶች እየተፈፀሙ ያሉት።
ለኢትዮጵያ ጽንፈኝነት በፍፁም ሊሆን አይችልም። ኢትዮጵያ በብዛሀነት ያገጠች ስትሆን ፤ጽንፍኝነት ደግሞ ከብዛሃነት ጋር እሳትና ጭድ ነው። ይህ ሁኔታ መቀየር አለበት።
የአገራችን የፖለቲካ ዕይታና ተግባር አካታች እና አሳታፊ ፣ በሀሳብ በላይነት የሚያምን ወደ መሆን መሸጋገር የግድ የሚልበት ደረጃ ላይ ነን። ፖለቲካችን ከመጠላለፍ ፣መጠፋፋትና ሴራ ወጥቶ ወደ አድስ አቅጣጫ የአስተሳሰብ ሽግግር ማድረግ አለበት። በውይይት እና ድርድር ፣ በፉክክር እና ትብብር መካከል ሚዛን መጠበቅ ያስፈልጋል። በመብትና ግዴታ በዴሞክራሲ ባህል ግንባታና የሃገር ሰላም ፀጥታ መካከል ሚዛን መጠበቅ አለብን። ህብረተሰቡ በአጠቃላይ፣ መንግስት፣ ት/ቤቶች ሚዲያ፣ የሃይማኖት ተቋማት፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራንና ለሰላምና ለአገር አንድነትና ዕድገት የቆሙ ኃይሎች በሙሉ ለጉዳዮ ትኩረት ሰጥተው ጽንፈኝነትን በጋራ መከላከል ተገቢ ነው።
ጽንፈኝነት ሄዶ ሄዶ አገር ያፈርሳል፣ ሰላም ያጠፋል ፣አዉዳሚ ነው።
የዛሬው ትውልድ ስለ ኢትዮጵያችን አንድነት ፣ ህዝቡ ሰላም ፣ ዕድገትና ብልፅግና ሲባል ጽንፈኝነትን በተባበረ ኃይል የመከላከል አገራዊ ኃላፊነት ወድቆበታል።
ኢትዮጵያ የጋራ ቤታችን ናት !!!

በG7 ስብሰባ ላይ  ኢትዮጵያ ተወድሳለች ተሞካሽታለች‼️➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ይህም ተብሏል " ኢትዮጵያን ተመልከቱ.... ! አፍሪካ በምግብ ምርት ራሷን ትችላለች። ኢትዮጵያን ተመልከቱ የስንዴ...
02/06/2022

በG7 ስብሰባ ላይ ኢትዮጵያ ተወድሳለች ተሞካሽታለች‼️
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
ይህም ተብሏል " ኢትዮጵያን ተመልከቱ.... ! አፍሪካ በምግብ ምርት ራሷን ትችላለች። ኢትዮጵያን ተመልከቱ የስንዴ ምርቷን በታላቅ እመርታ በተጨማሪ 2.6 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን አስመንጭቃዋለች። ኢትዮጵያ ከዚህ በውሃላ ስንዴ ከውጭ አታስገባም። በሚቀጥለው ጥቂት ዓመታት ኢትዮጵያ ለጎረቤቶቿ ስንዴ ኤክስፖርት የምታደርግ ሀገር እንደምትሆን እርግጠኞች ነን። የአፍሪካ ልማት ባንክ የኢትዮጵያ ግብርና እመርታ ደጋፊ በመሆኑ ኩራት ይሰማዋል።"
Akinwumi Adesina - የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት

ህንዳዊው ባለሀብት ስሙን "ለሚ ኦዳ" ብሎ  ቀየረትላንት ናሁ ቴሌቪዥን  ላይ ከፒተር ሾው ጋር ቆይታ የነበረው ህንዳዊው ባለሃብት በሞጋሳ ስርዓት "ኢትዮጵያዊ ሆኛለሁ" ያለ ሲሆን  ከዚህም የ...
30/05/2022

ህንዳዊው ባለሀብት ስሙን "ለሚ ኦዳ" ብሎ ቀየረ

ትላንት ናሁ ቴሌቪዥን ላይ ከፒተር ሾው ጋር ቆይታ የነበረው ህንዳዊው ባለሃብት በሞጋሳ ስርዓት "ኢትዮጵያዊ ሆኛለሁ" ያለ ሲሆን ከዚህም የተነሳ "ስሜ ለሚ ኦዳ ሆኗል" ብሏል።

የሐበሻ ስቲል ብረታ ብረት ድርጅት ማኔጅንግ ዳይሬክተር ኪቨን ራቫን ወይም "ለሚ ኦዳ" በድርጅታቸው በኩል ብዙ ህፃናትን እያስተማሩ እንደሆነ አብራርተዋል።

የአማራ ጨቅላ ብሄርተኝነት ደቀመዛሙርቶቹን እያወዛገበ ነዉ።===የክርስቲያን  ታደለ  የፖለቲካ አላዋቂነት  ሲገለጥ!የአብን አመራሮች እና የብልጽግና  አመራሮች በፖለቲካ ርዕዮተአለም ሆነ   ...
16/05/2022

የአማራ ጨቅላ ብሄርተኝነት ደቀመዛሙርቶቹን እያወዛገበ ነዉ።
===

የክርስቲያን ታደለ የፖለቲካ አላዋቂነት ሲገለጥ!

የአብን አመራሮች እና የብልጽግና አመራሮች በፖለቲካ ርዕዮተአለም ሆነ የሚታገሉለት አለማ እንዲሁም የፓርቲ መርሃቸው የሰማይና የምደር ያህል ልዩነት እንዳለው ይታወቃል። አብን ብሄር ተኮር ሆኖ ለአማራ ብቻ እወክላለሁ ብሎ የሚንቀሳቀስ ሲሆን በሌላ ጎኑ ደግሞ ብልጽግና ደግሞ ህብረ ብሄራዊና አካታች የሆነ ፓርቲ ነው ታዲያ እነዚህ ሁለት ፓርቲዎች ሆድ እና ጀርባ መሆናቸው እየታወቀ አቶ ክርስቲያን ታደለ የአብንን አመራሮች ከአማራ ፓርቲ ብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ጋር አላኮ የስም ማጥፋት ዘመቻ ከፍቷል ። ፍየል ወዲያ ቅዝምዝም ወዲህ እንዲሉ የየትኛውን ከየትኛው ጋር ያገናኛል ሌላው የአብን አመራሮች እንዴት እንደ አንድ ትልቅ የፖለቲካ ፓርቲ መሪ የውስጣቸውን ችግር እንደሰለጠነ ሰው በጠረጴዛ ዙሪያ በመነጋገር መፍታት እየቻሉ ወደማይመለከተው ፓርቲ ማላከኩ የሁለተናዊ ውስንነት እንደሚስተዋልባቸው ያረጋግጣል።። ክርስቲያን ታደለ የተባለ ደነዝ በአብን ውስጥ በተደጋጋሚ በሚፈጥረው የዲስፕሊን ችግር ፓርቲው የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ የተባለውን የቢጫ ካርድ አሳይቶታል። ታዲያ ይህ ሰው ችግሬ ምን ይሆን ብሎ ማስተካከል ያለብኝ ነገር ምንድነው በማለት ውስጡን ማየት ሳይችል ሌላኛውን ችግር ለመውቀስ እንዴት ይጣደፋል። እውነታው ግን ክርስቲያን/ደምለው በዋናነት በፓርቲው የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ የተሰጠው የፓርቲውን ሚስጥር በማባከን እንዲሁም በመዋለ ንዋይ በመታለል ከአማራው ጠላት ከሆነው ወያኔ ጋር መረጃዎችን በመለዋወጥ ፣ሰንዶችን በመፈራረም ላይ መሆኑን ስለተደረስበት ነው።
ሌላው ክርስቲያን እና አምሳያዎቹ ያልተረዱት ነገር ቢኖር አብን ሰማይ ዝቅ ቢል ምድር ከፍ ቢል የኢትዮጵያ ህዝቦች ብሄር በሄረሰቦች መሪ ሆኖ መንግስት መሆን አይችልም ምክንያቱም አብን ክልላዊና አማራ ብሄር ብቻ ተኮር ነው ለምን ካልን አብን አማራን ብቻ ማዕከል አድርጎ የሚንቀሳቀስ እንጂ ኢትዮጵያ ማዕከል አድርጎ የሚንቀሳቀስ ፓርቲ አይደለም አለቀ!!ስለሆነም አብን በምርጫ 100% ቢያሸንፍ እንኳ ኢትዮጵያን ሳይሆን የሚመራው አማራ ክልልን ብቻ ነው ታዲያ የአብን የፖለቲካ ድርጂት ሃላፊ ነኝ የሚለው ደምለው ይህን ሳያውቅ ነው እንዴ የአብን ከፍተኛ አመራር እንደሆነ የሚነገረው! ይገርማል ብቻ !!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በግንባታ ላይ ያለውን አዲሱን የኢቢሲ ሕንፃ ጎበኙ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በሸጎሌ የሚገኘው እና በግንባታ ላይ ያለውን አዲሱን የኢቢሲ ሕንፃ ጎብኝተዋል...
17/04/2022

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በግንባታ ላይ ያለውን አዲሱን የኢቢሲ ሕንፃ ጎበኙ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በሸጎሌ የሚገኘው እና በግንባታ ላይ ያለውን አዲሱን የኢቢሲ ሕንፃ ጎብኝተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለአሠራር ምቹ ያልሆነው የኢቢሲ የአሁኑ ሕንፃ በአዲስ እንደሚቀየር ከተቋሙ ሠራተኞች ጋር ውይይት ባደረጉት ወቅት ቃል ገብተው ነበር።

በዛሬው ዕለትም በሸጎሌ የሚገኘው አዲሱ የኢቢሲ ሕንፃ ያለበትን ሂደት ተመልክተዋል።

አዲሱ የኢቢሲ ሕንፃ ግንባታ በአጭር ጊዜ ተጠናቆ ሥራ የሚጀምር ሲሆን ሕንፃው ዘመናዊ የሬዲዮ እና የቴሌቪዥን ስቱዲዮች ይኖሩታል።

ይህም ተቋሙ በይዘት እና አቀራረብ የተሻለ ሆኖ ለመውጣት እያደረገ ያለውን ጥረት ይበልጥ እንደሚያሳድግለት ታምኖበታል።

ሕብረ-ብሄራዊነትና ወንድማማችነት ጽኑ የኢትዮጵያ አንድነት መሰረት ነው፡፡ መከባበር፤ ለጋራ ሀገራዊ ጥቅም አብሮ መቆም፤ ከልዩነት ይልቅ የጋራ እሴቶቻችንን ማጽናት ዘላቂ መፍትሄ ነው፡፡ ጽንፈ...
04/04/2022

ሕብረ-ብሄራዊነትና ወንድማማችነት ጽኑ የኢትዮጵያ አንድነት መሰረት ነው፡፡ መከባበር፤ ለጋራ ሀገራዊ ጥቅም አብሮ መቆም፤ ከልዩነት ይልቅ የጋራ እሴቶቻችንን ማጽናት ዘላቂ መፍትሄ ነው፡፡ ጽንፈኝነት የሚወክለው ብሄርም ሆነ ሃይማኖት የለውም፡፡ ለማንም ለምንም አይጠቅምም፡፡ ጸረ ህዝብ እሰከ ሆነ ድረስ ተመሳሳይ አቋም በመያዝ በጋራ ልንታገለው ይገባል፡፡

የአሜሪካ ቅዠት የሆነው የቻይና ኢኮኖሚ !! ከዛሬ 10 አመት በፊት ነበር ቻይና የጃፓንን የኢኮኖሚ ደረጃ በመንጠቅ ከአለም ሁለተኛዋ ባለግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤትነቷን የተቆናጠጠችው። የቻይና ተአ...
31/03/2022

የአሜሪካ ቅዠት የሆነው የቻይና ኢኮኖሚ !!

ከዛሬ 10 አመት በፊት ነበር ቻይና የጃፓንን የኢኮኖሚ ደረጃ በመንጠቅ ከአለም ሁለተኛዋ ባለግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤትነቷን የተቆናጠጠችው። የቻይና ተአምራዊ የኢኮኖሚ እመርታ በዚያው ግስጋሴ ይቀጥላል ብሎ የገመተ አልነበረም። አሜሪካን የሚያስጨንቅ የኢኮኖሚ ሀያልነትም በዚህ ቅርብ አመት ታሳካለች ብሎም የጠበቀ አልነበረም።

እርሷ ግን ተአምራዊ ህዝቦች ያሏት ተአምራዊ ሀገር ነበረችና ሁሉንም አልፋቸው ሄደች። አሜሪካ የቻይናን የኢኮኖሚ ግስጋሴ ለማስቆም ያላደረገችው ጥረትና ሴራ አልነበረም የቻይና ጡንቻ ግን የአሜሪካን የሴራ ምት ከምንም የማይቆጥር አለት ነበር።

ከሁለት አመት በፊት አሜሪካ የቻይናን ኢኮኖሚ ለማድቀቅ በርካታ ታሪፍና የማእቀብ አለንጋዎቿን ብታሳርፍባትም የቻይና ገላ ግን ጥይት የማይበሳው ደንዳና ነበር። አሜሪካ በቻይና ላይ በወሰደቻቸው እያንዳንዷ እርምጃዎች ተጎጂዋ ራሷ አሜሪካ ነበረች !

የኮሮና ወረርሽኝ አሜሪካን ድቅቅ አድርጎ ሲመታት ቻይና ግን ከአለም ዝቅተኛዋ የወረርሽኙ ተጠቂ ነበረች ! አሁን አሜሪካ ቻይናን ብቻዋን እንደማታስቆማት አምናለች። እናም ለጀሌዎቿ የአውሮፓ መንግስታት "ቻይናን አብረን እንመክት" ስትል ጥሪ ለማቅረብ ተገደደች። የቡድን 7 ሀገራት ቻይናን የሚገዳደር ጥምረት ለመፍጠር ቢስማሙም አሜሪካ ቻይናን ማስቆም መፎካከር ስላልቻለች ነው።

ቻይና "አንድ ቀበቶ አንድ መንገድ" ለተሰኘው ፕሮጀክቷ የመደበችው በጀት ብቻ 1.6 ትሪሊዮን ዶላር ነው። ይህ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ አለምን በንግድና ቴክኖሎጂ የሚያስተሳስር ሲሆን ይህም ምእራባዊያንን ከአለም መሪነት መንበራቸው ገልብጦ የሚጥል ነው።

በአሁኑ ሰአት የቻይናን ያክል አስፈሪ ሀይል የለም ! በኢኮኖሚ አሜሪካን አልፋ ሂዳለች። በወታደራዊው ዘርፍ ያላትን ትክክለኛ አቅም የሚያውቅ የለም ምክንያቱም ቻይና እጅግ ሚስጥራዊ ሀገር ናትና! ቻይና በአመት ለጦር በጀቷ ከ 200 ቢሊዮን ዶላር በላይ ትበጅታለች ቢባልም ጉዳዩን በቅርብ የሚያጠኑ ጠበብቶች ግን የቻይና የጦር በጀት ከ600 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚሆን ይናገራሉ። ይህም ከአሜሪካ ጋር ተቀራራቢ ማለት ነው።

ቻይና ከምእራባውያን አፍሪካን ቀምታቸዋለች ! ላቲን አሜሪካን ቀምታቸዋለች! አብዛኛው ኤዥያን ቀምታቸዋለች ! እንኳን ሌላው ቀርቶ አውሮፓ እንኳ ያለ ቻይና አይሆንላቸውም!

በ2021 በወጣው ሪፖርት ቻይና የዓለም ቁጥር አንድ ባለ-ፀጋነት ደረጃን ጨብጣለች። ቻይና አጠቃላይ ሀገራዊ ሀብቷ 120 ትሪሊየን ዶላር በማስመዝገብ አሜሪካን በልጣ የምድራችን ሀብታምነት ደረጃን መጨበጧ ይፋ ተደርጓል። የቻይና ሀብት በፈረንጆቹ 2000 7 ትሪሊየን ዶላር ነበር፡፡ በሁለት አስርት አመታት ውስጥ የ113 ትሪሊየን ዶላር እድገት ማስመዝገብ ችላለች። የአሜሪካ ሀገራዊ ጠቅላላ ሃብት 90 ትሪሊየን ዶላር በመሆን 2ኛ ደረጃ ላይ መቀመጡን " IMF " በጥናታዊ ሪፖርቱ ይፋ አድርጓል።

   ቻይና ለአሜሪካ ባለስልጣት የቪዛ አገልግሎት ላለመስጠት ወሰነች።ይህ ውሳኔ አሜሪካ ለቻይና ባለሰልጣናት ቪዛ እንደማትሰጥ ከገለፀች በኃላ በቻይና የተሰጠ ተመሳሳይ የአፀፋ ምላሽ ነው።አሜሪ...
31/03/2022



ቻይና ለአሜሪካ ባለስልጣት የቪዛ አገልግሎት ላለመስጠት ወሰነች።

ይህ ውሳኔ አሜሪካ ለቻይና ባለሰልጣናት ቪዛ እንደማትሰጥ ከገለፀች በኃላ በቻይና የተሰጠ ተመሳሳይ የአፀፋ ምላሽ ነው።

አሜሪካ ሰኞ ዕለት በሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ረገጣዎች ላይ እጃቸው አለበት ባለቻቸው የቻይና ባለስልጣናት ላይ ነው የቪዛ እገዳ ጥላ ነበር።

ሩስያ በይፋ ከአውሮፓ ምክር ቤት ጋር ተፋታች።ሩስያ ከድርጅቱ መውጣቷን ለአውሮፓ ምክር ቤት በይፋ አሳውቃለች።የሩስያ ዱማ ምክትል አፈጉባዔ ፒዮትር ቶልስቶይ ዛሬ ማክሰኞ እንዳስታወቁት ከሆነ ...
15/03/2022

ሩስያ በይፋ ከአውሮፓ ምክር ቤት ጋር ተፋታች።

ሩስያ ከድርጅቱ መውጣቷን ለአውሮፓ ምክር ቤት በይፋ አሳውቃለች።

የሩስያ ዱማ ምክትል አፈጉባዔ ፒዮትር ቶልስቶይ ዛሬ ማክሰኞ እንዳስታወቁት ከሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ደብዳቤ ለድርጅቱ ዋና ፀሃፊ ተላልፏል።

" ከአውሮፓ ምክር ቤት ጋር የሚደረገውን ውይይት ለማቋረጡ ሁሉም ሃላፊነት በNATO አባል ሀገራት ላይ ነው " ያሉት ቶልስቶይ " ይህን ሁሉ ጊዜ በሰብአዊ መብቶች ርዕስ የራሳቸውን ጂኦፖለቲካዊ ፍላጎቶች ለማሟላት እና በሀገራችን ላይ ለሚሰነዘሩ ጥቃቶች ሲጠቀሙበት ቆይተዋል " ብለዋል።

አክለውም ፤ " ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ መልኩ በተጣለው ማዕቀብና በፖለቲካዊ ጫናዎች " ምክንያት ሩስያ ዓመታዊውን ክፍያ ለአውሮፓ ም/ቤት አትከፍልም ሲሉ አሳውቀዋል።

ቶልስቶይ ሩሲያ ድርጅቱን ለቃ የምትወጣው " በራሷ ፈቃድ " እንደሆነ ገልፀው ውሳኔው ሚዛናዊ እና የታሰበት ነው ብለዋል።

   Russia has barred former and current officials, including US President Joe Biden, from returning to the country.Russi...
15/03/2022



Russia has barred former and current officials, including US President Joe Biden, from returning to the country.

Russian government bans entry into Russia

ጆ US President Joe Biden

👉 US Secretary of State Anthony Blincon

ደህንነት National Security Adviser Jack Sullivan

C CIA Director William Burns

ን White House Spokesman Jean Saki

👉 Defense Minister Leo Austin

ይ Includes former US Secretary of State Hillary Clinton.

Canadian Prime Minister Justin Trudeau has also been banned from entering Russia.

"በዐብይ ተግባር ፤ በደመቀ ጉዞ ፤ በታላቁ አደምና አዳም መንገድ በማገልገል ኢትዮጵያን ለማሻገር እንስራ!!አቶ ደመቀ መኮንንየብልፅግና  ፓርቲ ም/ ፕሬዚዳንት ክቡር
15/03/2022

"በዐብይ ተግባር ፤ በደመቀ ጉዞ ፤ በታላቁ አደምና አዳም መንገድ በማገልገል ኢትዮጵያን ለማሻገር እንስራ!!

አቶ ደመቀ መኮንን
የብልፅግና ፓርቲ ም/ ፕሬዚዳንት ክቡር

 #አሜሪካ ሩስያን አስጠነቀቀች።የአሜሪካ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ጃክ ሱሊቫን ሩስያ በNATO አባል ሀገር በሆነችው  #ፖላንድ ላይ ጥቃት ከሰነዘረች NATO ምላሽ እንደሚሰጥ አስጠንቅቀዋል...
13/03/2022

#አሜሪካ ሩስያን አስጠነቀቀች።

የአሜሪካ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ጃክ ሱሊቫን ሩስያ በNATO አባል ሀገር በሆነችው #ፖላንድ ላይ ጥቃት ከሰነዘረች NATO ምላሽ እንደሚሰጥ አስጠንቅቀዋል።

የደህንነት አማካሪው ይህን ማስጠንቀቂያ የሰጡት ዛሬ ሩስያ በፖላንድ ድንበር አቅራቢያ በሚገኝ የዩክሬን የጦር ሰፈር ላይ የአየር ድብደባ ከፈፀመች በኃላ ነው ፤ በጥቃቱ 35 ሰዎች መገደላቸው እና 134 ሰዎች መቁሰላቸው ተነግሯል።

የአሜሪካ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ጃክ ሱሊቫን ለ CBS በሰጡት ቃል በNATO ግዛት ላይ አንዳች ወታደራዊ ጥቃት ቢሰነዘር አንቀፅ 5 ወደ ትግበራ እንደሚገባና የNATO ሙሉ ኃይል ምላሽ እንደሚሰጥ አስጠንቅቀዋል።

በዛሬው ዕለት ሩስያ በፖላንድ ድንበር በሚገኝ የዩክሬን ጦር ሰፈር የፈፀመችው ጥቃት ምዕራባውያን ለዩክሬን የሚያደርጉትን ወታደራዊ ድጋፍ እንዲያቆሙ ካስጠነቀቀች ከአንድ ቀን በኃላ ነው።

ምንም እንኳን ሩስያ ምዕራባውያን " አርፋችሁ ቁጭ በሉ ዩክሬንን በወታደራዊ ትጥቅ አትደግፉ " ብትልም የአሜሪካ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ሱሊቫን ሀገራቸው አሜሪካ የዩክሬን ኃይሎችን በወታደራዊ እርዳታ መደገፏን እንደምትቀጥል ዛሬ ተናግረዋል።

በተጨማሪም አሜሪካ እና አጋሮቿ የNATO ግዛትን እያንዳንዱን ኢንች እንደሚከላከሉ ገልፀው " ሩሲያ በአጋጣሚ ወይም ሳታስበው ጥቃት ብታደርስ እራሱ NATO ምላሽ ይሰጣል " ሲሉ ሱሊቫን አስጠንቅቀዋል።

ሱሊቫን ፥ " የምለው ነገር ቢኖር ... ሩስያ በNATO ግዛት ላይ ጥቃት ብትከፍት፣ አንዲት ጥይት ብትተኩስ የNATO ጥምረት ምላሽ እንደሚሰጥ ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

NB : ፖላንድ የNATO አባል ሀገር ናት።

‹‹እስካሁን ለተገኘው ውጤት የጎረምሳው ጉልበት ብቻ ሳይሆን የሽማግሌው ጥበብ (Wisdom) ከፍተኛ ቦታ አለው፡፡ እያቀናጀን ካልሄድን አሁን ያለው ፈተና ከባድ ነው፡፡ አሁን ያለው ፈተና ትግ...
13/03/2022

‹‹እስካሁን ለተገኘው ውጤት የጎረምሳው ጉልበት ብቻ ሳይሆን የሽማግሌው ጥበብ (Wisdom) ከፍተኛ ቦታ አለው፡፡ እያቀናጀን ካልሄድን አሁን ያለው ፈተና ከባድ ነው፡፡ አሁን ያለው ፈተና ትግግዝ ይፈልጋል አሁን ያለው ፈተና ኢትዮጵያዊ መሆን ይፈልጋል፡፡
አላለቀም ሽግግሩ ፤አንዳንዴ ጎረምሶች ይሰለቻቸዋል፡፡ይታክታሉ፡፡ሽመግሌዎች እረፉ እያሉ ካልተቆጡ ችግር ነው፡፡
ወይፈኑና በሬው አብረው ሲጠመዱ ውጤታማ ይሆናሉ፡፡ ››

የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዘደንት ዶክተር አብይ አህመድ

" ስግብግብ ነጋዴዎች ሸቀጦችን ከማከማቸት እና ከመደበቅ ታቀቡ " - ጠ/ሚ ሙስጠፋ ማድቡሊየግብፅ መንግስት ከሰሞኑ በሀገሪቱ የታየውን የስንዴ ዋጋ ንረት ተከትሎ " ስግብግብ ነጋዴዎች " ሲል...
13/03/2022

" ስግብግብ ነጋዴዎች ሸቀጦችን ከማከማቸት እና ከመደበቅ ታቀቡ " - ጠ/ሚ ሙስጠፋ ማድቡሊ

የግብፅ መንግስት ከሰሞኑ በሀገሪቱ የታየውን የስንዴ ዋጋ ንረት ተከትሎ " ስግብግብ ነጋዴዎች " ሲል የጠራቸውን አካላት አስጠንቅቋል።

የግብፅ የሀገር ውስጥ ሚዲያዎች የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ከተነሳ በኋላ ግብፃውያን የዕለት ተዕለት የዳቦ እና የስንዴ ምርት ፍጆታቸውን እንዲቀንሱ የሚጠይቁ ዘመቻዎችን መክፈታቸው ተሰምቷል።

ብሉምበርግ ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበው የግብፅ መንግስት ፤ በሩስያ እና ዩክሬን ጦርነት የሚፈጠውን ተፅእኖ ለመቅረፍ የስንዴ ክምችቱን እያሳደገ እና የሀገሪቱ ዜጎችም ፍጆታቸውን ምክንያታዊ እንዲሆን ጥሪውን እያጠናከረ ነው።

የግብፁ ጠ/ሚ ሙስጠፋ ማድቡሊ ፥ " መንግስት የሀገር ውስጥ ስንዴ የመግዛት አቅሙን ወደ 5.5 ሚሊዮን ቶን ማድረሱን " ገልፀው " ዜጎች አሁንም ፍጆታቸውን ምክንያታዊ ማድረግ አለባቸው " ብለዋል።

አክለውም ፤ የመንግስት የስንዴ አቅርቦት የተረጋጋ መሆኑን እና የድጎማ ዳቦ ማቅረብ ለመቀጠል የሚያስችል በቂ አቅርቦት መኖሩን ጠቁመዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፥ ሀገራቸው በአሁን ሰዓት ተጨማሪ የስንዴ ጭነት ማስገባት እንደማያስፈልጋት ገልፀው " ስግብግብ ነጋዴዎች " ሲሉ የጠሯቸው አካላት ሸቀጦችን ከማከማቸት እና ከመደበቅ እንዲታቀቡ አስጠንቅቀዋል።

ግብፅ በዓለም ትልቋ የስንዴ አቅርቦትን ወደሀገሯ የምታስገባ ሀገር ስትሆን 80 ከመቶ የሚሆነውን አቅርቦቷን የምታስገባው ደግሞ በአሁን ሰዓት አስከፊ ጦርነት ላይ ካሉት ሩስያ እና ዩክሬን ነው።

በግብፅ እየታየ ያለው የዋጋ ንረት በተለይ ደግሞ የዳቦ ዋጋ ጭማሪ ነዋሪዎችን እያስቆጣ መሆኑን ከቀናት በፊት መዘገቡ ይታወሳል።

The first congress of the Prosperity Party elected Dr. Abiy Ahmed as the party's president.Leaders elected by councilors...
12/03/2022

The first congress of the Prosperity Party elected Dr. Abiy Ahmed as the party's president.

Leaders elected by councilors to lead the party for the coming years at a conference of the Prosperity Party
Dr. Abiy Ahmed, President of the Party with 1480 votes
Adam Farah 1330 was elected Vice President of the party.
Demeke Mekonnen was elected with 970 votes.

 የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ከምንም ጊዜ በላይ አበክሮ እንደሚሰራ የብልጽግና ፓርቲ አስታወቀአዲስ አበባ፣ መጋቢት 3፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) የዜጎችን ሰላም እና ደህንነት ለማስጠበቅ...
12/03/2022


የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ከምንም ጊዜ በላይ አበክሮ እንደሚሰራ የብልጽግና ፓርቲ አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 3፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) የዜጎችን ሰላም እና ደህንነት ለማስጠበቅ ከምንም ጊዜ በላይ አበክሮ እንደሚሰራ የብልጽግና ፓርቲ አስታወቀ።

ፓርቲው አንደኛውን ድርጅቲዊ ጉባኤው እያካሄደ ይገኛል።

የጉባኤውን ሁለተኛ ቀን ውሎ አስመልክቶ የብልጽግና ፓርቲ የህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሀላፊ ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ መግለጫ ሰጥተዋል።

የብልጽግና ፓርቲ አመራሮች፣ አባላት እና ደጋፊዎች የዜጎችን ሰላም እና ደህንነት ማስጠበቅ ቅድሚያ የሚሰጡት ስራ እንደሆነ በጉባኤው ከስምምነት መደረሱን አስታውቀዋል።

ፓርቲው ከሰላም የሚያስቀድመው ነገር አለመኖሩን ነው የተመለከተው።

የፓርቲውን አደረጃጀት፣ አመራር እና አባላት አስተሳሰብ በሚገባ በመግራት ሰላምን ማስጠበቅ የብልጽግና ፓርቲ ትልቁ ፕሮጀክት ነውም ብለዋል።

አሁን የሚፈጠረው የብልጽግና አመራር የሀገሪቱን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ ፣ የደህንነት እና ማህበራዊ ችግሮች መፍታት 24 ሰዓት የሚሠራው ስራ እንደሆነም በጉባኤው ከስምምነት ተደርሷል ብለዋል ።

የትግራይ ህዝብን በተመለከተም ጉባኤው የመከረ ሲሆን፥ በአሸባሪው ህወሓት ድርጊት ሳቢያ ህዝቡ ለችግር መዳረጉን አንስቷል ።

ብልጽግና ፓርቲ በትግራይ ህዝብ ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ ለማስቀረትና እፎይ ብሎ እንዲኖር ለማስቻል አሉ የተባሉ የሰላም አማራጮችን በሙሉ እንደሚጠቀም አስታውቀዋል።

ጉባኤው ድርቅ በተደጋጋሚ በሚከሰትባቸው ቆላማ የሀገሪቱ አካባቢዎች የዜጎችን ችግር በዘላቂነት የሚፈታ ስራ መሰራት እንደሚገባም ተመልክቷል።

የፓርቲው ጉባኤ አምስት አጀንዳዎች እንዳሉትም ዶክተር ቢቂላ ገልጸዋል።

እስካሁንም ከአጀንዳዎቹ መካከል የፓርቲውን ማዕከላዊ ኮሚቴ ሪፖርት እና የፓርቲውን የኢንስፔክሽን ዕና ስነ ምግባር ሪፖርት አድምጦ አጽድቋል ።

"Are we your slaves?" - PM Imran KahanThe West is calling on African countries and the rest of the world to condemn Russ...
07/03/2022

"Are we your slaves?" - PM Imran Kahan
The West is calling on African countries and the rest of the world to condemn Russia.
One of these countries is Pakistan.
A few days ago, Westerners demanded that Pakistan condemn Russia.
On March 1, leaders of 22 diplomatic missions, including members of the European Union, issued a joint statement urging Pakistan to support a resolution condemning Russia's "invasion of Ukraine."

, on the other hand, remained neutral.
Pakistani Prime Minister Imran Khan has strongly criticized Western envoys who have tried to pressure his country to condemn Russia's actions.

"What do you think of us? We are your slaves ... Do whatever you tell us to do," asked Imran Kahan.

"I want to ask the ambassadors of the European Union.
Have you written such a letter to India?"
He also criticized the European Union (EU) for its actions in the Kashmir conflict, in which India and Pakistan fought two wars.
"Pakistan is hurting because it supports the Western Union in Afghanistan, and it is being criticized rather than praised," he said.
"We are friends with Russia, we are friends with the United States, we are friends with China and Europe, we are not in any camp," he said.

05/03/2022
 "ፈራን"ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራንእንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድንፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድንእኛነትን ትተን እኔነትን ለመድን...።"ፈራን"ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን...
05/03/2022



"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራን
እንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድን
ፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድን
እኛነትን ትተን እኔነትን ለመድን...።
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን
በጋራ ቤታችን አጥር ድንበር ሰራን
"ናቅን"
በልዩነት ደምቀን ያልኖርን ያህል አንድም ቀን
እልህ ተናነቅን
"ናቅን"
መቻቻልን ናቅን ለፀብ አሟሟቅን
ለአመፅ ስንነሳ ለሰላም ወደቅን
አገር ስትቃጠል ከዳር ሆነን ሞቅን
©✍ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን

 The Fourth Patriarch of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, His Holiness Abune Merkorewos, has passed away.
04/03/2022


The Fourth Patriarch of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, His Holiness Abune Merkorewos, has passed away.

02/03/2022

ዛሬ የአድዋ ድል 126 ኛው በሚኒሊክ አደባባይ የተከሰተው የአዲስ አበባ ወጣቶች የሚወክል ሳይሆን ጥቂት የፓለቲካ አጀንዳ ያላቸው ግለሰቦች መሆናቸውን ተረድተናል ። የአዲስ አበባ ወጣቶች በግብረገብ የታነፁ ሀገር ወዳዶች ናቸው ።
አድዋ ድል መለት የሁላችንም አንድ የሚያደርግ አንጂ የሚያለያይ አልነበረም ስለ ዚህ የዛሬ ድርግት ግን የባንዳ ዎች ድርግት ነዉ ።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Ababa Daily News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share


Other Addis Ababa media companies

Show All