Yeneta tube የኔታ ቲዩብ

Yeneta tube የኔታ  ቲዩብ Your premier source for engaging discussions and thought-provoking content on social issues. contact us +12404687690

የኢንፊኒክስ ስማርት ቲቪ X5 ዲዛይን እጅግ ቀጭን ሆኖ መሰራቱ ከቤቶት እና ከቢሮዎት ዲዛይን ጋር በምንም አይነት አቀማመጥ አብሮ ከመሄዱም ባሻገር ከየትም አንግል ቴሌቭዥን ለመመልከት አመቺ ...
11/22/2024

የኢንፊኒክስ ስማርት ቲቪ X5 ዲዛይን እጅግ ቀጭን ሆኖ መሰራቱ ከቤቶት እና ከቢሮዎት ዲዛይን ጋር በምንም አይነት አቀማመጥ አብሮ ከመሄዱም ባሻገር ከየትም አንግል ቴሌቭዥን ለመመልከት አመቺ ያደርገዋል፡፡



|

የዶክተሩን ነፍስ ያጠፋው የፖሊስ አባሉ የ10 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈረደበትየዶ/ር እስራኤል ጥላሁን ተሽከርካሪን ለማስቆም በተኮሰው ጥይት ግድያ የፈፀመው ኮንስታብል ማክቤል ሮባ በ10 ዓመት ...
11/22/2024

የዶክተሩን ነፍስ ያጠፋው የፖሊስ አባሉ የ10 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈረደበት

የዶ/ር እስራኤል ጥላሁን ተሽከርካሪን ለማስቆም በተኮሰው ጥይት ግድያ የፈፀመው ኮንስታብል ማክቤል ሮባ በ10 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ

ባለፈው ዓመት ዶ/ር እስራኤል ጥላሁን ሲያሽከረክር የነበረውን ተሽከርካሪ ለማስቆም በተኮሰው ጥይት ግድያ የፈጸመው ኮንስታብል ማክቤል ሮባ በ10 አመት ጽኑ እስራት ተቀጥቷል፡፡

ወንጀለኛው ህዳር 3 ቀን 2016 ሌሊት በግምት 11:20 ቦሌ ክፍለከተማ ወረዳ አራት በተለምዶ ፋሲካ መኪና መሸጫ አካባቢ በመደበኛ የወንጀል መከላከል ስራ ላይ እንደነበር የክስ መዝገቡ ያስረዳል፡፡

ፍርደኛው ሟችን በወቅቱ በፍጥነት ሲያሽከረክር ከነበረበት ለማስቆም ምልክት ሲያሳየው እልታዘዝ ማለቱን ተከትሎ ተሽከርካሪውን ለማስቆም የተኮሰው ጥይት ተሽከርካሪዋን አልፎ ዶ/ር እስራኤል ጥላሁንን የቀኝ ደረቱን በመምታት ህይወቱ ሊያልፍ ችሏል፡፡

በመሆኑም ሰው ለመግደል አስቦ ቢተኩስ በከባድ ግድያ ሊመሰረትበት የነበረው ክስ በወንጀል ህጉ 540 ተራ የሰው ግድያ ክስ ተመስርቶበት በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ የከባድ ግድያ እና ውንብድና ጉዳይ ችሎት ጉዳዩ ሲታይ ቆይቷል፡፡

የተላለፈበትን የጥፋተኝነት ውሳኔ ተከትሎ ዛሬ ችሎቱ በልዩነት ሀሳብ በአብላጫ ድምጽ ነው የተወሰነው፡፡

በውሳኔ መዝገቡ የሰፈረው የልዩነት ሀሳብ ወንጀለኛው ሊከላከል የሚገባው በቀላል ግድያ እንጂ በተራ ግድያ መሆን የለበትም የሚል ነው፡፡

ይህ የልዩነት ሀሳብ የተንጸባረቀበት የወንጀል ህጉ 541 ቀላል ግድያ ደግሞ ቅጣቱ ከአምስት ዓመት ያልበለጠ ነው፡፡

ከዚያ በላይ የሚያስቀጣው ተራ የሰው ግድያ 540 አብላጫ ድምጽ አግኝቷል በችሎት ዳኞች፡፡

ከዚህ በመነሳት ፍርድ ቤቱ በተመሰረተበት ተራ የሰው ግድያ ወንጀል ወንጀለኛውን ያስተምራል ሌሎችን ያስጠነቅቃል በማለት በአስር አመት ጽኑ እስራት ቀጥቶታል።
EBC

ፖሊስ በመርካቶ አዲስ አበባ የገበያ ማዕከል  በኮንትሮባንድ የገቡ የሞባይል ስልኮችን ያዝኩኝ አለየአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ፖሊስ ባደረገው የክትትልና የጥናት ተግባር በርካታ የኮንትሮባንድ ዕቃዎ...
11/22/2024

ፖሊስ በመርካቶ አዲስ አበባ የገበያ ማዕከል በኮንትሮባንድ የገቡ የሞባይል ስልኮችን ያዝኩኝ አለ

የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ፖሊስ ባደረገው የክትትልና የጥናት ተግባር በርካታ የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን መያዙን አስታውቋል፡፡

የፖሊስ መምሪያው የወንጀልና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ዲቪዥን ኃላፊ የሆኑት ዋና ኢንስፔክተር ተስፋዬ ለማ እንደገለፁት ህዳር 12 ቀን 2017 ዓ/ም በክ/ከተማው ወረዳ 8 ልዩ ቦታው አዲስ አበባ የገበያ ማዕከል ውስጥ በሚገኝ የንዋየ ቅዱሳትና ሞባይል ቀፎ መሸጫ ሱቅ ላይ በተደረገ ፍተሻ በርካታ የሞባይል ቀፎዎችን ከነ ቻርጀሮቻቸው መያዙን ገልፀዋል፡፡ በፍተሻውም 301 የስማርት ስልክ ቀፎዎች፣ 61 ኖርማል በተን ሞባይል ስልክ ቀፎዎች እንዲሁም 29 የሞባይል ቻርጅሮች ይገኙበታል ብለዋል፡፡

የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ የተያዘበት አንደኛው ሱቅም የንዋየ ቅዱሳት መሸጫ ቢሆንም ከውስጡ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች የሚከማቹበት መሆኑንም ማረጋገጥ እንደተቻለ የገለፁት ኃላፊው ከተሰጣቸው የንግድ ፈቃድ ውጪ በንዋየ ቅዱሳት መሸጫ ሱቅ ስም የሀገርን ኢኮኖሚ በእጅጉ የሚጎዳ ተግባር ለመፈፀም የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችም ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ኃላፊው በመልዕክታቸው አስታውቀው መሰል ህገ-ወጥ ተግባራትን ለመቆጣጠር የፀጥታ አካላት የሚያከናውኑትን ሥራ ህብረተሰቡ መረጃ በመስጠት እንዲተባበር መልዕክት ተላልፏል፡፡

(ዘገባ፡- ረ/ኢንስፔክተር ዳዊት እርገጤ - አ/አ ፖሊስ)

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአፍሪካ ስማርት ከተሞች ኢንቨስትመንት ፎረም ሽልማት አገኘ።ይህ የአፍሪካ ስማርት ከተሞች ኢንቨስትሜንት ፎረም ሽልማት ሊሰጥ የቻለበት ዋነኛ ምክንያት በኮርደር...
11/22/2024

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአፍሪካ ስማርት ከተሞች ኢንቨስትመንት ፎረም ሽልማት አገኘ።

ይህ የአፍሪካ ስማርት ከተሞች ኢንቨስትሜንት ፎረም ሽልማት ሊሰጥ የቻለበት ዋነኛ ምክንያት በኮርደር ልማት ከተማይቱን ለነዋሪዎቿ እና ለእንግዶቿ ምቹና ተስማሚ ለማድረግ በአጭር ጊዜ የተገኘውን አመርቂና ውጤታማ ተግባር መሰረት በማድረግ እና በአረንጓዴ አሻራ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ እየተተገበረ ያለውን ተምሳሌታዊ ተግባር በማስመልከት ነው ተብሏል::

በተጨማሪም "ሰው ተኮር ስማርት ከተሞች ለትውልድ ግንባታ" በሚል ሀሳብ በከተማይቱ ተግባራዊ በመደረጉ እና ዘመናዊና ምቹ ከተማን ለመፍጠር የእግረኛ መሄጃ እና የሞተር አልባ ተሽከርካሪዎች መንገድ ደረጃውን በጠበቀ መንገድ መገንባታቸውን መሰረት በማድረግ መሆኑም በሽልማት ስነ-ስርዓቱ ላይ ተገልፇል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከተማዋን ለማዘመንና ስማርት በማድረግ ውብ፣ ፅዱና ለኑሮ ምቹ ብሎም የአፍሪካዊያን ኩራትና የአለም የዲፕሎማቲክና የኮንፍራንስ እንዲሁም የቱሪዝም ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማጉላት በኮሪደር ልማት በተሰራው አኩሪ ስራ መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤን በመወከል ኬንያ ናይሮብ ሽልማቱን የተቀበሉት አቶ መኮንን ያኢ ያስታወቁ ሲሆን ሽልማቱ ለበለጠ ስራ የሚያነሳሳ በመሆኑ ይህንን ሽልማት ላዘጋጁ አካላት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ህዝብ ስም ምስጋና አቅርበዋል።

እንግሊዝ ኔታንያሁን ለዓለም አቀፉ ወንጀለኞች ፍርድ ቤት አሳልፋ ልትሰጥ እንደምትችል ገለጸችየእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ወደ እንግሊዝ ከተጓዙ ለዓለም አቀፉ ወንጀለኞች ፍር...
11/22/2024

እንግሊዝ ኔታንያሁን ለዓለም አቀፉ ወንጀለኞች ፍርድ ቤት አሳልፋ ልትሰጥ እንደምትችል ገለጸች

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ወደ እንግሊዝ ከተጓዙ ለዓለም አቀፉ ወንጀለኞች ፍርድ ቤት (አይሲሲ) አሳልፋ ልትሰጥ እንደምትችል አስታወቀች።

የጠቅላይ ሚኒስትር ኪዬር ስታርመር መንግስት በሄግ የሚገኘውን የዓለም አቀፍ ወንጀለኞች ፍርድ ቤትን እርምጃ እንደሚደግፍ አስታውቋል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል አቀባይ “የዓለም አቀፉ ወንጀለኞች ፍርድ ቤትን ገለልተኝነት እናከብራለን” በማለት በተዘዋዋሪ ከተቋሙ ጋር እንደሚተባበር መግለጹን ዘ ደይሊ ቴሌግራፍ ዘግቧል።

ሆኖም ወግ አጥባቂው የእንግሊዝ ፓርቲ በሌበሮቹ የሚመራው መንግስት ውሳኔን ተቃውሟል። “ አይ.ሲ.ሲ በዴሞክራሲያዊ መንገድ በተመረጡት የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትርና የቀድሞ መከላከያ ሚኒስትር ላይ የእስር ትዕዛዝ ማውጣቱ አሳሳቢና ተንኳሽ” ውሳኔ ሲሉ የወግ አጥባቂው ትይዩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዳሜ ፕሪቲፓቴል ተቃውመዋል።

ፍርድ ቤቱ ትናንት በጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ፣ በቀድሞው እስራኤል መከላከያ ሚኒስትር ዮዋቭ ጋላንት እና በሃማሱ ወታደራዊ አመራር መሀመድ ደይፍ ላይ የጦር ወንጀል ፈፅመዋል በሚል የዕስር እዝ ማውጣቱ ይታወቃል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጋዛ እያካሄዱ ባለው ጦርነት ሰዎችን በማስራብና በሰባዓዊ መብት ጥሰት ወንጀል ከሶ ነው የዕስር ትዕዛዝ ያወጣባቸው።

እንግሊዝን ጨምሮ 123 አባል አገራት የዓለም የጦር ወንጀለኞች ፍርድ ቤትን ውሳኔ የማስፈፀም ኃላፊነት እንዳለባቸው የተቋሙ ህግ ያስገድዳል።

የፍርድ ቤቱን እርምጃ አሜሪካ እና እስራኤል በፅኑ አውግዘውታለ።

11/22/2024

"የ 20 ሚልዮን ብር ሽልማት"

11/22/2024

ቦሌ የሚገኘው ግዙፍ ህንፃ ባለቤት ነኝ ህንፃውን ተዘረፍኩ የሚሉት ይህ ሰው ሰሚ እንዴት አጡ ? እውነታውስ ምንድን ነው ?

አቶ በላይነህ ክንዴ ለጎንደር ከተማ አሥተዳደር በኤሌክትሪክ ኃይል የሚንቀሳቀሱ አውቶብሶችን አስረከቡየከተማ አውቶብሶቹ በበላይነህ ክንዴ ቢዝነስ ግሩፕ የተገጣጠሙ ሲሆን 126 ሚሊየን ብር ወጪ...
11/22/2024

አቶ በላይነህ ክንዴ ለጎንደር ከተማ አሥተዳደር በኤሌክትሪክ ኃይል የሚንቀሳቀሱ አውቶብሶችን አስረከቡ

የከተማ አውቶብሶቹ በበላይነህ ክንዴ ቢዝነስ ግሩፕ የተገጣጠሙ ሲሆን 126 ሚሊየን ብር ወጪ እንደተደረገባቸው እንዲሁም ነዳጅ እና ዘይት የማይጠቀሙ እንደሆኑም ተገልጿል፡፡

ከተማዋን ለማዘመን በሚደረገው ጥረት ውስጥ የዘመኑ ቴክኖሎጂን መጠቀም የቱሪስት ተመራጭነቷን የሚያሳድግ ነውም ተብሏል።

ባለሃብት በላይነህ ክንዴ በተገኙበት በዛሬው እለት የኤሌትሪክ አውቶብሶችን ርክክብ ተደርጓል።
ባለሃብቱ በላይነህ ክንዴ በርክክቡ ወቅት አውቶብሶቹ ለከተማዋ ቱሪዝም እድገትና ለነዋሪዎችም የተስማሙ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ድርጅታቸው ከጎንደር ከተማ ልማት ጋር አብሮ እንደሚሰራና የልማት ክፍተቶችን እንደሚሞላም አንስተዋል፡፡

የ20 ሚልየን ብር ድጋፍ ተደረገላቸውየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ ተከስቶ በነበረው የእሳት አደጋ ሱቅ የተቃጠለባቸው ነጋዴዎችን በጊዜያዊነት መልሶ ለማቋቋም የ20 ...
11/22/2024

የ20 ሚልየን ብር ድጋፍ ተደረገላቸው

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ ተከስቶ በነበረው የእሳት አደጋ ሱቅ የተቃጠለባቸው ነጋዴዎችን በጊዜያዊነት መልሶ ለማቋቋም የ20 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ዛሬ ህዳር 13/2017 ዓ.ም አድርጓል::

በድጋፍ መርሃ ግብሩ ወቅት ንግግር ያደረጉት ከንቲባ አዳነች አቤቤ አካባቢው ደረጃውን በጠበቀ መልኩ መልሶ እስኪገነባ ሱቅ ለተቃጠለባቸው ነጋዴዎች የመስሪያ ቦታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ እንዲጠናቀቅ ከተደረገው የ20 ሚሊዮን ብር ድጋፍ በተጨማሪ የአይነት እና የቴክኒክ ድጋፎችን እናደርጋለን ብለዋል::

በአካባቢው ያለውን ጥግጊትና መጨናነቅ በዘላቂነት በመቅረፍ፣ የተሽከርካሪ መንገድን በማካተት እንዲሁም ለአደጋ ተጋላጭ በማያደርጋቸው መልኩ በዘላቂነት በአክሲዮን ተደራጅተው ደረጃውን የጠበቀ የገበያ ማዕከል መገንባት እንዲችሉ የከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ ከንቲባ አዳነች ጨምረው ገልጸዋል::

ድጋፉን የተቀበሉት የአካባቢው ነጋዴ ተወካዮች በበኩላቸው የከተማ አስተዳደሩ አደጋው ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ ላደረገው ድጋፍ እና ክትትል አመስግነው ድጋፉ በፍጥነት ወደ ስራ እንዲገቡ የሚያደርጋቸው መሆኑን ተናግረዋል::(ከንቲባ ፅ/ቤት)

11/22/2024

የሞቱት አሕዮች ጭንቅላት ተቀያይሮ ቢገጠምም…

በቅድስት ቤተ ክርስቲያችን ትልቅ ስራ ከሰሩና ትልቅ ተጋድሎ ካላቸው ቅዱሳን አባቶች አንዱ ቅዱስ ቶማስ ዘመራስ ነው፡፡ መራስ የትውልድ ሀገሩ ናትና በዚያው ይጠራል፡፡ ዲዮቅልጥያኖስና መክስሚያኖስ በክርስቲያኖች ላይ መከራ ባጸኑበት ዘመን ለ22 ዓመታት የተጋደለው ይህ ድንቅ ሰማዕትና ሐዋርያ ገና በወጣትነቱ መንኖ ገዳም የኖረ፣ በጾም፣ በጸሎት፣ በሰጊድ፣ ቀንና ሌሊትም በመትጋት ለድኆችና ለምስኪኖችም በመራራት ተጠምዶ የኖረ ነበር፡፡

በጨካኞቹ ነገስታት ዘመንም ለጣኦት እንዲሰግድ የደረሰበትን መከራ ታግሶ በክርስቶስ ፍቅር በመጽናቱ በ22 ዓመታት የመከራ ጊዜው ጨለማ ውስጥ ጥለውት አካሉን እየቆራረጡ ለጣዖታቸው ያጥኑ ስለነበር 2 እግሮቹ፣ 2 እጆቹ፣ 2 ጀሮዎቹ፣ አፍንጫውና ፪ ዐይኖቹ አልነበሩም፡፡ የተጣለበትን ስፍራ የምታውቅ አንዲት ሴትም በስውር እየገባች ትመግበው ነበር፡፡

እኛ በዘመናችን ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ፍቅር የትኛውን አካላችን እንድንሰዋ አልጠተየቅንም፤ ወይም በረሀብ አልተቀጣንም፡፡ ይልቁንም በነጻነት የምናመልክበት እድል እነዚህ ቅዱሳን አባቶቻችን መከራውን ታግሰው ባቆዩልን እምነት መጽናትና ቤተ ክርስቲያናችንን በተሰጠን ስጋዊና መንፈሳዊ ሃብት ማገዝ ብቻ ነው የሚጠበቅብን፡፡

የቤተክርስቲያን የመከራ ዘመን አልፎ ንጉስ ቆስጠንጢኖስ ስልጣን ከተረከበ በኋላ በኒቂያ ጉባኤ አርዮስን ለማውገዝ ከተሰበሰቡት 318 ሊቃውንት አንዱ ቅዱስ ቶማስ ዘመራስ ነበር፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ስጋዊ አካሉ የጎደለውን ቅዱስ ሰማዕት በቅርጫት አድርገው በአሕዮች ጭነው ለቀናት ተጉዘው ነበር ወደ ኒቂያ የወሰዱት፡፡ በመንገድ ላይ ሳሉም ካደሩበት ቦታ የአርዮስ ተከታዮች የአሕዮቹን ራስ ቆርጠው ገድለዋቸው ሔዱ፡፡

ምንም እንኳን ሁለት አይኖቹ ቢጠፉም መንፈሳዊ ምጥቀቱ ከፍ ያለ ነበርና በሌሊት ገስግሰው ሊጓዙ ሲነሱ የአሕዮቹን ሁኔታ ደቀ መዛሙርቱ ሲነግሩት ቀድሞ አውቆት ነበርና ጭንቅላታቸውን ከአካላቸው ጋር እንዲገጥሙት አዘዛቸው፡፡ ከዚያም ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክት አሕዮቹ እደገና ነፍስ ዘርተው ተነስተው መንገዳቸውን ቀጥለዋል፡፡ አስገራሚው ነገር በጨለማው ምክንያት አንዱን ከአንዱ መለየት ስላልቻሉ የነጩን አሕያ ጭንቅላት ለጥቁሩ፣ የጥቁሩንም ለነጩ እንደገጠሙላቸው ጠዋት በብርሃን አዩት፡፡

ቅዱስ ቶማስ ዘመራስም አርዮስን አውግዞ ወደ ሀገሩ ስብከቱ ተመልሶ ጸሎተ ሃይማኖት የተባለውን ጸሎት ለሕዝቡ አስተምሯል፡፡ በተጨማሪም ለ40 ዓመታት በጵጵስና አገልግሎ አልፏል፡፡ ቅዱሳን አባቶች በትልቅ መስዋዕትነት ራሳቸውን አሳልፈው ሰጥተው ያቆዩዋትን እምነት ለመጠበቅ እጃችንን እንድንዘረጋ መጠየቅ በራሱ ከበረከታቸው መካፈል ነውና ገዳማትን እንርዳ፡፡

ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

የፖሊስ አባልን ሆን ብሎ በመግጨት በአሰቃቂ ሁኔታ የግድያ ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ የ20 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣየወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው በድሬዳዋ ከተማ ወረዳ ልዩ ቦታው ገነት መናፈሻ ...
11/21/2024

የፖሊስ አባልን ሆን ብሎ በመግጨት በአሰቃቂ ሁኔታ የግድያ ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ የ20 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ

የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው በድሬዳዋ ከተማ ወረዳ ልዩ ቦታው ገነት መናፈሻ ኬላ እየተባለ በሚጠራው ስፍራ ህዳር 18 ቀን 2015 ዓ.ም በግምት ከለሊቱ 9:00 ሰዓት ላይ ነው።

መደበኛ ስራውን በማከናወን ላይ የነበረን የፖሊስ አባልን ተከሳሽ በተሽከርካሪ ሆን ብሎ በመግጨት በአሰቃቂ ሁኔታ የግድያ ወንጀል መፈፀሙን ተገልጿል ።ተከሳሽ ሙክታር አብዱል ቃድር አህመድ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3. 19171 በሆነ ኤፍ ኤስ አር ተሽከርካሪ ህገ ወጥ ኮንትሮባንድ እቃዎችን ጭኖ ከድሬዳዋ ወደ ሀረር አቅጣጫ በከፍተኛ ፍጥነት እየተጓዘ ሳለ ገነት መናፈሻ ፍተሻ ኬላ ላይ ሲደርስ በወቅቱ መደበኛ ፖሊሳዊ ስራውን በማከናወን ላይ የነበረ አባል ተሽከርካሪው ቆሞ መፈተሽ እንዳለበት በእጅ የያዘውን ባትሪ አብርቶ በማወዛወዝ ምልክት ያሳየዋል።

በሰአቱም ተሽከርካሪውን በማሽከርከር ላይ የነበረው ተከሳሽ ፍጥነቱን በመቀነስ ቀኙን ይዞ የቆመ በማስመሰል ለፍተሻ ወደ ተሽከርካሪው እየተጠጋ የነበረውን የፖሊስ አባል በድንገት ፍጥነት ጨምሮ ሙሉ በሙሉ የሰውነት ክፍሉን በመግጨት በአሰቃቂ ሁኔታ የግድያ ወንጀል ፈፅሞ ሊሰወር ችሏል ።

ድርጊቱ መፈፀሙ እንደተሰማ የምርመራ ቡድን በማደራጀት በስፍራው የሰው እና የሰነድ ማስረጃዎች በማሰባሰብ እና ተከሳሽ ግለሰብን አድኖ ለመያዝ ከድሬዳዋ ፖሊስ የወንጀለኞች ክትትልና እስረኛ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ጋር ቅንጅታዊ ስራ ሲሰራ ቆይቷል። ተከሳሽ ተሰውሮ ከነበረበት ቦታ ጉዳዩ ተረስቷል በሚል ከ 2 ዓመት በኋላ ህዳር 9 ቀን 2017 ዓ.ም ሶስት ኪሎ እየተባለ በሚጠራው ስፍራ መታየቱን ተከትሎ ህብረተሰቡ ለፖሊሰ ባደረሰው ጥቆማ በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን ገልጸዋል ።

በዚህም በፖሊስ ተጣርቶ አቃቤ ህግ የመሰረተውን የክስ መዝገብ የተመለከተው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 4ኛ ወንጀል ችሎት የወንጀሉን ክብደት በመረዳት ተከሳሽ በሌለበት መዝገቡን ሲከታተል መቆየቱ ተገልጿል ።በዚህም መሰረት ነሀሴ 12 ቀን 2016 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ሙክታር አብዱልቃድርን አህመድን ጥፋተኛ ሆኖ በመግኘቱ በ20 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ የተወሰነበት ሲሆን ተከሳሹ ህዳር 9 ቀን 2017 ዓ.ም በፖሊስ ቁጥጥር ስር በመዋሉ በሌለበት የተወሰነውን የቅጣት ውሳኔ እንዲፈጽም ወደ ማረሚያ መላኩንየድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የሚዲያ እና ገጽታ ግንባታ ዲቪዥን ሀላፊ ኢንስፔክተር ዳግም ተፈራ ተናግረዋል

11/21/2024

“በጎዳናህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላዕክትን ስላንተ ያዝዛቸዋል በእጃቸውም ይደግፉሃል፡፡” ይላል ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት፡፡ ይልቁንም የመላእክት ሁሉ አለቃቸው የሚሆን ቅዱስ ሚካኤል ከእግዚአብሔር ተልኮ በርካቶችን ሲጠብቅ በቅዱስ መጽሐፍ ተመልክተናል፡፡ በየዓመቱ በህዳር በ12 ቀን በዓለ ሲመቱ የሚከበረው ቅዱስ ሚካኤል የዋህ፣ ርህሩህ፣ አዛኝ፣ ለወዳጆቹ ቅርብ፣ የሰው ሁሉ ልጆችን ጠላት በእሳት ሰይፍ መትቶ የጣለው በክንፎቹ ረድኤት የሚጠብቀንም ነው፡፡ “በሰማይ ብርቱ ሰልፍ ሆነ ሚካኤልና መላአክቱም ዘንዶውን ተዋጉት ዘንዶውም አልቻላቸውም። ከዚያም በኃላ በስማይ ቦታ አልተገኘለትም” ተብሎ በራዕይ 12÷7 እንደተጻፈ ዲያብሎስ በትዕቢቱ ከወደቀ በኋላ የመላዕክት ሁሉ አለቃ የሆነው ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡

አምላካቻን እግዚአብሔር ወደር የማይገኝለት ኃያል፣ የሚመስለው የሌለ ብርቱ፣ ዘመን የማይቆጠርለት ዘለዓለማዊ ነው፡፡ መላዕክቱን መንፈስ የሚላኩትን የእሳት ነበልባል የሚያደርጋቸው ተብሎ እንደተጻፈ የኃይሉ መገለጫ ከሆኑት አንዱ ናቸው ቅዱሳን መላዕክት፡፡ ይልቁንም የስሙ ትርጓሜ “ማን እንደ አምላክ ማለት የሆነው ታላቁ አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በርካታ ድንቅ ስራ ሰርቷል፡፡ በበዓለ ሲመቱም በየዓመቱ ከሕዳር 12 እስከ የአእላፍ መላእ በዓል እስከሚከበርበት ሕዳር 13 ለሰው ልጆች ሁሉ ከአምላካችን ምሕረት ይለምናል፡፡ ስፍር ቁጥር የሌላቸው ነፍሳትንም ከሲዖል ያወጣል፡፡

ሕዳር 12 እስራኤላውያንን ከግብጽ ባርነት መርቶ ያወጣበትም ቀን ነው፡፡ 430 ዘመን በባርነት ከቆዩባት ምድረ ግብጽ በሙሴ መሪነት ሲጓዙ፣ ግርማ ሌሊቱን በብርሃን አምድ፣ የቀኑን ሐሩር ደግሞ በደመና ጋርዶ ወደ ተስፋይቱ ምድር ያገባቸው እርሱ ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ ከሙሴ በኋላ እስራኤልን የመራው ነቢዩ ኢያሱም ኢያሪኮን ለመያዝ ሲሰናዳ የመላእክት ሁሉ አለቃቸው የሚሆን የከበረ ገናና መልአክ ቅዱስ ሚካኤል የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ ይዞ ተገለጸለት፡፡ እርሱም በምድር ላይ በግንባሩ ተደፍቶ ሰገደለት፡፡ ወደ እርሱ ቀርቦም “አንተ ከእኛ ወገን ነህ ወይስ ከጠላቶቻችን?” ሲል ጠየቀው፡፡ እርሱም “አይደለሁም ነገር ግን የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁንም ወደ አንተ መጥቻአለው አለው፡፡ ኢያሱ 5÷13፡፡ የኢያሪኮ ግምብን አፍርሶም ድልን አጎናጽፎታል፡፡

ለሚጠሩት ሰዎች ሁሉ ቅርብ የሆነው ቅዱስ ሚካኤል ዛሬም በዙሪያችን ከቦ ይጠብቀናል፣ ያድነንማል፡፡ ነብዩ ቅዱስ ዳንኤልም “በዚያም ዘመን ለሕዝብ ልጆች የሚቆመው ታለቁ አለቃ ሚካኤል ይነሳል።” እንዲል ሁሌም ጥበቃው ከኛ ጋር ነው፡፡ ከእግዚአብሔር በተሰጠው ቃል ኪዳን ልጆቹን ለመርዳት ቸል አይልም፡፡ ይልቁንም በዱር በገደል ጤዛ ልሰው፣ ድንጋይ ተንተርሰው፣ ዳዋ ለብሰው የሚኖሩትን ገዳማዊያን ዘወትር ይጠብቃቸዋል ጸሎታቸውንም ያሳርጋል፡፡ የእግዚአብሔር ሰራዊት አለቃ ሆኖ ወደ እነርሱ ይመጣል፡፡ ለእነዚህ ገዳማዊያንና ለገዳማቸው እገዛ በማድረግ የመልአኩ ጥበቃና የጸሎታቸው በረከት ተካፋይ እንሁን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:-ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

🌻🌻 ታላቅ የምስራች በቅርቡ ለምትጋቡ ሙሽሮች 🎈TOMI🎈TOMI🎈TOMI ፎቶ እና ቪዲዮ  🎈በአይነቱ ለየት ያለ የሠርግ ቀን ጥቅሎችን በ40,000ብር, በ45,000ብር በ50,000ብር እና በ6...
11/21/2024

🌻🌻 ታላቅ የምስራች በቅርቡ ለምትጋቡ ሙሽሮች 🎈TOMI🎈TOMI🎈TOMI ፎቶ እና ቪዲዮ 🎈በአይነቱ ለየት ያለ የሠርግ ቀን ጥቅሎችን በ40,000ብር, በ45,000ብር በ50,000ብር እና በ65,000ብር አቅርቦላቹሀል!!🌻🌻🎈🎈
☎️☎️ 📞 TOMI ፎቶ እና ቪዲዮ
0926455964
🌻🌻 የሠርግ ቀን 🎈🎈🌻🌻 platinum package🌻🌻🎈
🔴በ4 Camera
🔴 Drone footage
🔴 Ronin gimbal
🔴Ameran light
🔴Triller video
🔴Full Edited video
🔴 Color Grading
🔴2 .30*90 laminate album
🔴1 50*80 laminate board
🔴 1 ቬሎ
🔴 ሱፍ
🔴All soft copy free
🔴🔴Total price 65,000birr
🌻🌻 የሠርግ ቀን 🌻🌻 Golden package🌻🌻

🔴 በ4 Camera
🔴Ronin gimbal
🔴 Ameran light
🔴Triller video
🔴Full Edited video
🔴Color Grading
🔴1 30*90 laminated album
🔴1 50*80 laminate board
🔴 1 ቬሎ
🔴 1 ሱፍ
🔴All soft copy free
🔴Total price 55,000
🌻🌻 የሠርግ ቀን🌻🌻 sliver package
🔴በ3 camera
🔴Ronin gimbal
🔴 Ameran light
🔴 Triller video
🔴Full Edited video
🔴Color Grading

🔴1 ቬሎ
🔴 1 ሱፍ
🔴All soft copy free
🔴🔴Total price 45,000birr

🌻🌻 የሠርግቀን🌻🌻 Bronze package
🔴በ2 camera
🔴Ronin gimbal
🔴Ameran light
🔴 Triller video
🔴 Full Edited video
🔴 Color Grading

🔴1 ቬሎ
🔴 1 ሱፍ
🔴 All soft copy free
🔴🔴 Total price 40,000birr
የሰርግ ቀን ፎቶ እና ቪዲዮኦትን አለም የደረሰበትን የቴክኖሎጂ ጥግ በመጠቀም እናሳምርሎታለን!!!
አድራሻ 22 አክሱም ሆቴል አለፍ ብሎ ትጋት የገበያ ማዕከል 2ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁ F1- 03
🎈TOMI 🎈TOMI 🎈TOMI🎈

አንጋፋው ድምጻዊ  ነዋይ ደበበ
11/21/2024

አንጋፋው ድምጻዊ ነዋይ ደበበ

11/21/2024

#የእግዚአብሔር ሰራዊት አለቃ ሆኜ ወዳንተ መጥቻለሁ

“በጎዳናህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላዕክትን ስላንተ ያዝዛቸዋል በእጃቸውም ይደግፉሃል፡፡” ይላል ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት፡፡ ይልቁንም የመላእክት ሁሉ አለቃቸው የሚሆን ቅዱስ ሚካኤል ከእግዚአብሔር ተልኮ በርካቶችን ሲጠብቅ በቅዱስ መጽሐፍ ተመልክተናል፡፡ በየዓመቱ በህዳር በ12 ቀን በዓለ ሲመቱ የሚከበረው ቅዱስ ሚካኤል የዋህ፣ ርህሩህ፣ አዛኝ፣ ለወዳጆቹ ቅርብ፣ የሰው ሁሉ ልጆችን ጠላት በእሳት ሰይፍ መትቶ የጣለው በክንፎቹ ረድኤት የሚጠብቀንም ነው፡፡ “በሰማይ ብርቱ ሰልፍ ሆነ ሚካኤልና መላአክቱም ዘንዶውን ተዋጉት ዘንዶውም አልቻላቸውም። ከዚያም በኃላ በስማይ ቦታ አልተገኘለትም” ተብሎ በራዕይ 12÷7 እንደተጻፈ ዲያብሎስ በትዕቢቱ ከወደቀ በኋላ የመላዕክት ሁሉ አለቃ የሆነው ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡

አምላካቻን እግዚአብሔር ወደር የማይገኝለት ኃያል፣ የሚመስለው የሌለ ብርቱ፣ ዘመን የማይቆጠርለት ዘለዓለማዊ ነው፡፡ መላዕክቱን መንፈስ የሚላኩትን የእሳት ነበልባል የሚያደርጋቸው ተብሎ እንደተጻፈ የኃይሉ መገለጫ ከሆኑት አንዱ ናቸው ቅዱሳን መላዕክት፡፡ ይልቁንም የስሙ ትርጓሜ “ማን እንደ አምላክ ማለት የሆነው ታላቁ አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በርካታ ድንቅ ስራ ሰርቷል፡፡ በበዓለ ሲመቱም በየዓመቱ ከሕዳር 12 እስከ የአእላፍ መላእ በዓል እስከሚከበርበት ሕዳር 13 ለሰው ልጆች ሁሉ ከአምላካችን ምሕረት ይለምናል፡፡ ስፍር ቁጥር የሌላቸው ነፍሳትንም ከሲዖል ያወጣል፡፡

ሕዳር 12 እስራኤላውያንን ከግብጽ ባርነት መርቶ ያወጣበትም ቀን ነው፡፡ 430 ዘመን በባርነት ከቆዩባት ምድረ ግብጽ በሙሴ መሪነት ሲጓዙ፣ ግርማ ሌሊቱን በብርሃን አምድ፣ የቀኑን ሐሩር ደግሞ በደመና ጋርዶ ወደ ተስፋይቱ ምድር ያገባቸው እርሱ ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ ከሙሴ በኋላ እስራኤልን የመራው ነቢዩ ኢያሱም ኢያሪኮን ለመያዝ ሲሰናዳ የመላእክት ሁሉ አለቃቸው የሚሆን የከበረ ገናና መልአክ ቅዱስ ሚካኤል የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ ይዞ ተገለጸለት፡፡ እርሱም በምድር ላይ በግንባሩ ተደፍቶ ሰገደለት፡፡ ወደ እርሱ ቀርቦም “አንተ ከእኛ ወገን ነህ ወይስ ከጠላቶቻችን?” ሲል ጠየቀው፡፡ እርሱም “አይደለሁም ነገር ግን የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁንም ወደ አንተ መጥቻአለው አለው፡፡ ኢያሱ 5÷13፡፡ የኢያሪኮ ግምብን አፍርሶም ድልን አጎናጽፎታል፡፡

ለሚጠሩት ሰዎች ሁሉ ቅርብ የሆነው ቅዱስ ሚካኤል ዛሬም በዙሪያችን ከቦ ይጠብቀናል፣ ያድነንማል፡፡ ነብዩ ቅዱስ ዳንኤልም “በዚያም ዘመን ለሕዝብ ልጆች የሚቆመው ታለቁ አለቃ ሚካኤል ይነሳል።” እንዲል ሁሌም ጥበቃው ከኛ ጋር ነው፡፡ ከእግዚአብሔር በተሰጠው ቃል ኪዳን ልጆቹን ለመርዳት ቸል አይልም፡፡ ይልቁንም በዱር በገደል ጤዛ ልሰው፣ ድንጋይ ተንተርሰው፣ ዳዋ ለብሰው የሚኖሩትን ገዳማዊያን ዘወትር ይጠብቃቸዋል ጸሎታቸውንም ያሳርጋል፡፡ የእግዚአብሔር ሰራዊት አለቃ ሆኖ ወደ እነርሱ ይመጣል፡፡ ለእነዚህ ገዳማዊያንና ለገዳማቸው እገዛ በማድረግ የመልአኩ ጥበቃና የጸሎታቸው በረከት ተካፋይ እንሁን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:-ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

የማሊ ጦር የሀገሪቱን ጠቅላይ ሚኒስትርን እና መንግስት ከስልጣን አባረረ የማሊ ወታደራዊ አስተዳደር የሀገሪቱን ሲቪል ጠቅላይ ሚኒስትር እና መንግስትን ከስራ ማሰናበቱን ያስታወቀ ሲሆን ጠቅላይ...
11/21/2024

የማሊ ጦር የሀገሪቱን ጠቅላይ ሚኒስትርን እና መንግስት ከስልጣን አባረረ

የማሊ ወታደራዊ አስተዳደር የሀገሪቱን ሲቪል ጠቅላይ ሚኒስትር እና መንግስትን ከስራ ማሰናበቱን ያስታወቀ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ቾጌል ኮካላ ማይጋ በወታደራዊ ገዥዎቹ ላይ ያልተለመደ ትችት ካቀረቡ ከቀናት በኋላ የተወሰደ እርምጃ ነው።

በጄኔራል አሲሚ ጎይታ የተሰጠውን ውሳኔ እና የፕሬዚዳንቱ ዋና ፀሀፊ አልፎሴኒ ዲአዋራ በመንግስታዊው የቴሌቪዥን ጣቢያ ላይ ቀርበው "የጠቅላይ ሚኒስትሩ እና የመንግስት አባላት ተግባር ተቋርጧል" ሲሉ መግለጫውን አንብበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ማይጋ ባለፈው ቅዳሜ የሀገሪቱን ወታደራዊ መሪዎች የሽግግር ጊዜ የሚባለውን ጊዜ እንዲያበቃ እንዲወያዩ ጠይቀዋል።

ይህ ንግግራ በገዢው ወታደራዊው አገዛዝ ላይ ያልተለመደ ትችት ተደርጎ ተወስዷል። የማሊ ወታደራዊ አገዛዝ በመጋቢት 26, 2024 ያበቃል ተብሎ ነበር። ነገር ግን ላልተወሰነ ጊዜ የተራዘመ ሲሆን ይህ በአንድ ወገን በመንግስት ውስጥ ከፍተኛ ክርክር አስነስቷል።ማይጋ ይህንን ንግግር ያደረጉት የፖለቲካ እንቅስቃሴያቸው ደጋፊዎች በተገኙበት መድረክ ላይ ነበር።

እ.ኤ.አ. በ2020 እና በ2021 በተከታታይ ከተደረጉ መፈንቅለ መንግስት በኃላ ሀገሪቱ በወታደራዊ አገዛዝ ስትመራ ቆይታለች። በሰኔ 2022 የወታደራዊ አስተዳደር ምርጫን ለማካሄድ እና ስልጣንን በመጋቢት 2024 መጨረሻ ለሲቪሎች ለማስረከብ ቃል ገብቷል። ነገር ግን ይህንን ቃሉን በማጠፍ ስልጣኑን ለሲቪል አገዛዝ የሚያስረክብበትን ወቅት ላልተወሰነ ጊዜ አራዝሟል። ከ 2012 ጀምሮ ማሊ በበርካታ የታጠቁ ቡድኖች ጥቃቶች እንዲሁም በሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል ውስጥ ከሚገኙ ተገንጣይ ኃይሎች ጋር በተፈጠረው ግጭት በፖለቲካ እና በፀጥታ ቀውስ ውስጥ ገብታለች።

ማሊ ከወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት በኃላ ከምዕራቡ ዓለም ጋር ያላት ግንኙነት በመሻከሩ ፊቷን ወደ ሩሲያ ማዝወራ ይታወሳል። በተያዘው ዓመት በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ማሊ በተፈጸመ አደገኛ የሽብር ጥቃት የዩክሬይን ተሳትፎ ነበረበት በሚል ባማኮ ከዩክሬን ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷን ማቋረጧም አይዘነጋም።

የማሊ ጦር በሰሜናዊ የሀገሪቱ ክፍል በቲንዛኦዌተን በተቀሰቀሰው ግጭት ከፍተኛ የወታደሮች ሞት ኪሳራ እንደደረሰበት አሳውቋል። ከሩሲያ ጋር ግንኙነት ያለው የዋግነር ቡድን የማሊን ጦር የሚደግፍ ሲሆን በቡድኑ ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ደርሷል የጦር አዛዡ ህልፈትም እርግጥ መሆኑ መነገሩ ይታወሳል።

በስምኦን ደረጄ
ዳጉ ጆርናል

በትግራይ ክልል የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ የማቋቋም ሥራ በይፋ ተጀመረየቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም ዛሬ በይፋ በተጀመረው ስራ፣ በትግራይ ክልል የቀድሞ ተዋጊዎችን ወደ ተሃድሶ ማዕከላት ማ...
11/21/2024

በትግራይ ክልል የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ የማቋቋም ሥራ በይፋ ተጀመረ

የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም ዛሬ በይፋ በተጀመረው ስራ፣ በትግራይ ክልል የቀድሞ ተዋጊዎችን ወደ ተሃድሶ ማዕከላት ማስገባት መጀመሩን የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
በዚሁ መሰረት የመጀመሪያው ዙር የነፍስ ወከፍ እና የቡድን ጦር መሳሪያዎች ርክክብም የአፍሪካ ህብረት፣የመንግስታቱ ድርጅትና የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች በተገኙበት ተከናውኗል።በመቐሌ፣ እዳጋ ሀሙስ እና ዓድዋ የመጀመሪያ ዙር ተዋጊዎች ስልጠና የሚወስዱባቸው ማዕከላት መዘጋጀታቸውን የብሔራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን ማስታወቁ ይታወሳል።

የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ከሰባት ክልሎች ከ371 ሺህ በላይ የቀድሞ ተዋጊዎችን ትጥቅ በማስፈታት ወደ ማዕከላት ለማስገባት የመለየት ሥራ መጠናቀቁን ገልጿል፡፡
በዛሬው ዕለትም በመጀመሪያው ምዕራፍ በትግራይ 75 ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ የማቋቋም ሥራ በይፋ መጀመሩን ኮሚሽኑ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አስታውቋል፡፡
በሁለት ዓመታት ውስጥ በሚከናወነው የቀድሞ ተዋጊዎችን ትጥቅ የማስፈታትና ወደ ማህበረሰቡ የመቀላቀል ሥራ ከ760 ሚሊየን ዶላር በላይ በጀት መያዙ ተጠቁሟል፡፡

የእግዚአብሔር ሰራዊት አለቃ ሆኜ ወዳንተ መጥቻለሁ“በጎዳናህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላዕክትን ስላንተ ያዝዛቸዋል በእጃቸውም ይደግፉሃል፡፡” ይላል ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት፡፡ ይልቁንም የመላእክ...
11/21/2024

የእግዚአብሔር ሰራዊት አለቃ ሆኜ ወዳንተ መጥቻለሁ

“በጎዳናህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላዕክትን ስላንተ ያዝዛቸዋል በእጃቸውም ይደግፉሃል፡፡” ይላል ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት፡፡ ይልቁንም የመላእክት ሁሉ አለቃቸው የሚሆን ቅዱስ ሚካኤል ከእግዚአብሔር ተልኮ በርካቶችን ሲጠብቅ በቅዱስ መጽሐፍ ተመልክተናል፡፡ በየዓመቱ በህዳር በ12 ቀን በዓለ ሲመቱ የሚከበረው ቅዱስ ሚካኤል የዋህ፣ ርህሩህ፣ አዛኝ፣ ለወዳጆቹ ቅርብ፣ የሰው ሁሉ ልጆችን ጠላት በእሳት ሰይፍ መትቶ የጣለው በክንፎቹ ረድኤት የሚጠብቀንም ነው፡፡ “በሰማይ ብርቱ ሰልፍ ሆነ ሚካኤልና መላአክቱም ዘንዶውን ተዋጉት ዘንዶውም አልቻላቸውም። ከዚያም በኃላ በስማይ ቦታ አልተገኘለትም” ተብሎ በራዕይ 12÷7 እንደተጻፈ ዲያብሎስ በትዕቢቱ ከወደቀ በኋላ የመላዕክት ሁሉ አለቃ የሆነው ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡

አምላካቻን እግዚአብሔር ወደር የማይገኝለት ኃያል፣ የሚመስለው የሌለ ብርቱ፣ ዘመን የማይቆጠርለት ዘለዓለማዊ ነው፡፡ መላዕክቱን መንፈስ የሚላኩትን የእሳት ነበልባል የሚያደርጋቸው ተብሎ እንደተጻፈ የኃይሉ መገለጫ ከሆኑት አንዱ ናቸው ቅዱሳን መላዕክት፡፡ ይልቁንም የስሙ ትርጓሜ “ማን እንደ አምላክ ማለት የሆነው ታላቁ አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በርካታ ድንቅ ስራ ሰርቷል፡፡ በበዓለ ሲመቱም በየዓመቱ ከሕዳር 12 እስከ የአእላፍ መላእ በዓል እስከሚከበርበት ሕዳር 13 ለሰው ልጆች ሁሉ ከአምላካችን ምሕረት ይለምናል፡፡ ስፍር ቁጥር የሌላቸው ነፍሳትንም ከሲዖል ያወጣል፡፡

ሕዳር 12 እስራኤላውያንን ከግብጽ ባርነት መርቶ ያወጣበትም ቀን ነው፡፡ 430 ዘመን በባርነት ከቆዩባት ምድረ ግብጽ በሙሴ መሪነት ሲጓዙ፣ ግርማ ሌሊቱን በብርሃን አምድ፣ የቀኑን ሐሩር ደግሞ በደመና ጋርዶ ወደ ተስፋይቱ ምድር ያገባቸው እርሱ ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ ከሙሴ በኋላ እስራኤልን የመራው ነቢዩ ኢያሱም ኢያሪኮን ለመያዝ ሲሰናዳ የመላእክት ሁሉ አለቃቸው የሚሆን የከበረ ገናና መልአክ ቅዱስ ሚካኤል የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ ይዞ ተገለጸለት፡፡ እርሱም በምድር ላይ በግንባሩ ተደፍቶ ሰገደለት፡፡ ወደ እርሱ ቀርቦም “አንተ ከእኛ ወገን ነህ ወይስ ከጠላቶቻችን?” ሲል ጠየቀው፡፡ እርሱም “አይደለሁም ነገር ግን የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁንም ወደ አንተ መጥቻአለው አለው፡፡ ኢያሱ 5÷13፡፡ የኢያሪኮ ግምብን አፍርሶም ድልን አጎናጽፎታል፡፡

ለሚጠሩት ሰዎች ሁሉ ቅርብ የሆነው ቅዱስ ሚካኤል ዛሬም በዙሪያችን ከቦ ይጠብቀናል፣ ያድነንማል፡፡ ነብዩ ቅዱስ ዳንኤልም “በዚያም ዘመን ለሕዝብ ልጆች የሚቆመው ታለቁ አለቃ ሚካኤል ይነሳል።” እንዲል ሁሌም ጥበቃው ከኛ ጋር ነው፡፡ ከእግዚአብሔር በተሰጠው ቃል ኪዳን ልጆቹን ለመርዳት ቸል አይልም፡፡ ይልቁንም በዱር በገደል ጤዛ ልሰው፣ ድንጋይ ተንተርሰው፣ ዳዋ ለብሰው የሚኖሩትን ገዳማዊያን ዘወትር ይጠብቃቸዋል ጸሎታቸውንም ያሳርጋል፡፡ የእግዚአብሔር ሰራዊት አለቃ ሆኖ ወደ እነርሱ ይመጣል፡፡ ለእነዚህ ገዳማዊያንና ለገዳማቸው እገዛ በማድረግ የመልአኩ ጥበቃና የጸሎታቸው በረከት ተካፋይ እንሁን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:-ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

Address

Seattle, WA

Telephone

+12149974245

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yeneta tube የኔታ ቲዩብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Yeneta tube የኔታ ቲዩብ:

Videos

Share

Nearby media companies


Other Seattle media companies

Show All