በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Butajira
  • በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት This is the official page of በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መ/ኮ/ጉ /ፅ/ቤት

የአገር መከላከያ ሚኒስቴር ለመደበኛ ሰራዊት አባልነት  ፣ ለጤና ሙተኞች ፣ ለኢንጂነሪንግ ፣  እንዲሁም በሳይበር የሙያ ዘርፎች መስፈርቱን ለሚያሟሉ ሁሉ ለመመልመል  ማስታወቂያ አውጥቷል ፡፡...
08/05/2024

የአገር መከላከያ ሚኒስቴር ለመደበኛ ሰራዊት አባልነት ፣ ለጤና ሙተኞች ፣ ለኢንጂነሪንግ ፣ እንዲሁም በሳይበር የሙያ ዘርፎች መስፈርቱን ለሚያሟሉ ሁሉ ለመመልመል ማስታወቂያ አውጥቷል ፡፡

በዚህም መሰረት አጠቃላይ እና ዝርዝር መስፈርቶቹ ከዚህ በታች እንደሚከተለው የተዘረዘረ ሲሆን መስፈርቱን የምታሟሉ ሁሉ መጥታችሁ እንድትወዳደሩ እና እንድትሳተፉ የምስራቅ መስቃን ወረዳ ሰላም እና ጸጥታ ጽ/ቤት እና ሚሊሻ ፅ/ቤት ያስታውቃል ፡፡

#አጠቃላይ #የምልመላ #መስፈርቶች
1.1. የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስት የተቀበሉ፣ በህዝቦች ሉአላዊነትና አንድነት የሚያምኑና አገራቸውን ለማገልገል ሙሉ ፍቃደኛ የሆኑ፣

1.2. ከማንኛውም የፓለቲካ ድርጅቶች ወገንተኝነት ነፃ የሆኑ፣

1.3.ከአሁን በፊት የመከላከያ፣ የፖሊስ እና የክልል ልዩ ሃይል አባል ያልነበሩ፣

1.4. አሁን ካለው ወቅታዊ የአገራችን ሁኔታ በመነሳት የጽንፈኞቹ ፋኖና ሸኔ አባልና ደጋፊ ያልሆኑ፣

1.5. በትግራይ ክልል በተደረገው ውጊያ ያልተሳተፈ፣

1.6. በወንጀል ይሁን በፍታብሄር ተከሶ የፍርድ ቤት ክርክር የሌለባቸው፣

1.7. ዜግነት ኢትዮጵያዊ፣

1.8. መሰረታዊ የውትድርና ስልጠና ወስዶ ከተመረቁ በኋላ ለ7 ዓመት ለማገልገል ውል ለመፈፀም ፍቃደኛ የሆኑ፣

1.9. በመከላከያ ሰራዊት መተዳደሪያ ደንብ መሰረት መብትና ግዴታቸውን አውቀው በተመደቡበት ቦታ ሁሉ ለማገልገል ፍቃደኛ የሆኑ፣

1.10.በተቋሙ የሚሰጣቸውን ስልጠናዎች ለመሰልጠን ፍቃደኛ የሆኑ፣ ከየትኛውም አጉል ሱሶች ከሲጋራ፣ ከጫት፣ ከሀሽሽ እና ከሌሎች ሱሶች ነፃ የሆኑ፣

1.11. በአካባቢው ማህበረሰብ የተመሰገነ ባህሪ እና ስነ-ምግባር ያላቸው፣

1.12. ከሚኖሩበት አካባቢ ከተለያዩ ወንጀሎችና ፀረ-ህዝብ ተግባር ነፃ ስለመሆናቸው ከአስተዳደር አካላትና ከፖሊስ የጽሁፍ ማስረጃ እና የቀበሌ የነዋሪነት መታወቂያ ማቅረብ የሚችሉ፣

1.13.በመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ለትምህርት ተመልምለው የሚገቡ በተማሩበት ሙያ እጥፍ ለማገልገል ፍቃደኛ የሆኑ፣

1.14.ሙሉ ጤንነት ያላቸውና ስልጠናው የሚጠይቀውን የህክምና ምርመራ ለማድረግ ፍቃደኛ የሆኑና በምርመራው ማለፍ የሚችሉ፣

1.15.ትዳር ያልመሰረቱ ልጅ ያልወለዱ፣

1.16.ዕድሜ ለወንድም ለሴትም ተመልማዮች ከ18 እስከ 24 ዓመት የሆኑ፣

II. #አካላዊ #መስፈርት

2.1.የተስተካከለ ቁመና የእግር፣ የእጅ፣ የአንገት፣ የወገብ መሰበር እና ሌሎችም ችግሮች የሌለባቸው፣

2.2.የአይን፣ የአፍንጫ፣የጆሮ፣ የጥርስ እና የከንፈር መሰንጠቅ ችግር የሌለባቸው፣

2.3. ከቲቪ፣ ከሚጥል በሽታ፣ ከስኳር፣ ከደም ግፊት፣ ከኪንታሮት እና ከእንቅርት በሽታዎች ነፃ የሆኑ፣

2.4.ቁመት ለወንድ 1.60 ለሴት 1.55 ሜትር እና ከዚያ በላይ የሆኑ፣

2.5.ክብደት ለወንድ ከ50-70 ለሴት ከ45-60 ኪ/ግራም የሆኑ፣

III. #ለመደበኛ #ሰራዊት #የአካዳሚክ #መስፈርት

· ለወንድ ተመልማዮች 8ኛ ክፍል ያጠናቀቁ እና ከዚያ በላይ የሆኑ

· ለሴት ተመልማዮች እውቅና ካለው የትምህርት ተቋም ዲፕሎማ ወይም በሌቭል ያጠናቀቁና የብቃት ማረጋገጫ(COC) ያላቸው እና ከዚያ በላይ የሆኑ የ8ኛ ክፍል የሚኒስትሪ ካርድ ማቅረብ የሚችሉ

· ሁሉም ተመልማዮች ኦርጅናል ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡

IV. #በመከላከያ #ዩኒቨርስቲ #ለኢንጂነሪንግና #ጤና #ሳይንስ #ትምህርት #የሚገቡ #ተመልማዮች #የመመልመያ #መስፈርት

· በተፈጥሮ ሳይንስ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና ወስዶ/ወስዳ በ2011፣2012 ዓ.ም እና በ2013፣በ2014 ወይም በ2015ዓ.ም የዩኒቨር

· በ2011 የትምህርት ዘመን ለተፈተኑ ለወንድም ለሴትም 140 እና ከዚያ በላይ

· በ2013 የትምህርት ዘመን በመጀመሪያ ዙር ለተፈተኑ ለወንድም ለሴትም 330 (የሲቪክስ ውጤት አይያዝም)

·በ2013 የትምህርት ዘመን በሁለተኛ ዙር ለተፈተኑ ለወንድም ለሴትም 350 እና ከዚያ በላይ

· በ2014/2015 የትምህርት ዘመን ለተፈተኑ 50% እና ከዚያ በላይ ውጤት ያላቸው

·የ10ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ለተፈጥሮ ሳይንስ በኢንግሊዘኛ፤ በሂሳብ፤ በፊዚክስና በኬሚስትሪ ከማዕከላዊ ነጥብ ከፍ ያለ (C) እና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት

V. #በመከላከያ #ዩኒቨርስቲ #ለሪሶርስ #ማኔጅመንት #ትምህርት የሚገቡ ተመልማዮች የመመልመያ #መስፈርት

· በማህበራዊ ወይም በተፈጥሮ ሳይንስ በ2011፣ 2012፣ 2013፣ 2014 እና 2015 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ያስመዘገቡ፣

·በ2011 የትምህርት ዘመን ለተፈተኑ ለወንድም ለሴትም 140 እና ከዚያ በላይ

· በ2012 የትምህርት ዘመን ለተፈተኑ ለወንዶች 330 ለሴቶች 320 እና ከዚያ በላይ

·በ2013 የትምህርት ዘመን በመጀመሪያ ዙር ለተፈተኑ ለወንድም ለሴትም 250 እና ከዚያ በላይ (የሲቪክስ ውጤት አይያዝም)

· በ2013 የትምህርት ዘመን በሁለተኛ ዙር ለተፈተኑ ለወንድም ለሴትም 300 እና ከዚያ በላይ

·በ2014 የትምህርት ዘመን ለተፈተኑ 50% እና ከዚያ በላይ ውጤት ያላቸው

·የ2015 የትምህርት ዘመን ለተፈተኑ የትምህርት ሚኒስተር የሚያውጣውን የዩንቨርሰቲ መግቢያ ነጥብ የሚያሟሉ
የ10ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ለማህበራዊ ሳይንስ በጆግራፊ እና በሂስትሪ /ታሪክ/ ከማዕከላዊ ነጥብ ከፍ ያለ (C) ከዚያ በላይ ያለው/ያላት

· በምልመላ ወቅት የ8ኛ ክፍል፣ ከ9ኛ እስከ 10ኛ እና 11ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ወይም እስከ መሰናዶ ትምህርት ድረስ ያለውን የትምህርት ድረስ ያለውን የትምህርት ውጤት /ትራንስክርቢት /ማቅረብ የሚችሉ

· በስራ ፈጠራ ወይም በልዩ ችሎታ እና ትምህርት የላቀ ውጤት ያላቸው ይበረታታሉ

·በቴክኒክና ሙያ ፕሮግራም በደረጃ 4 እና ከዚያ በላይ ያጠናቀቀና የብቃት ማረጋገጫ (COC) ማቅረብ የሚችሉ እንዲሁም የብቃት ማረጋገጫ (COC) ካገኙ በኋላ በሙያ 02 ዓመትና ከዚያ በላይ የሰሩ

·ዩኒቨርሲቲው ከሚያስተምርባቸው የትምህርት ፕሮግራሞች ውጭ በማንኛውም የትምህርት መስክ የመጀመሪያ ዲግሪ ኖሮአቸው በኢንጂነሪንግ፤ በጤና ሳይንስ፤ በሀብት አስተዳደር፤ እንዲሁም በማህበራዊ ሳይንስ ለመማር የሚፈልጉ

· በተለያዩ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በመደበኛ የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ትምህርት በመከታተል ላይ የሚገኙና የየሴሚስተሩን የትምህርት ውጤት ሪፖርት ማቅረብ የሚችሉ

· ለጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከኢንጂነሪንግ መስክ ውጭ በሳይንስና ተዛማጅ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቁና ኦፊሻል ትራንስክሪፕት ማቅረብ የሚችሉ

VI. #ለሳይበር #ሙያተኛ #የመመልመያ #መስፈርት

የትምህርት ሁኔታ

· በኮምፒዩውተር ሳይንስ፣ በኮምፒዩውተር ኢንጂነርንግ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በኮምፒዩውተር ኔትወርክና ሃርድ ዌር፣ በኢንፎርሜሽን ሲስተም በሳይበር ደህንነት በኮምፒዩውተር ኔትወርክና ሴኩሪቲ በሶፍት ዌር ኢንጂነሪግ፣ በማቲማቲክስ፣ ሳይኮሎጂ፣ በኮሚኒኬሽን ኢንጂነሪግ፣ በኤሌክትሪካል ኢንጂነሪግ፣ በኤሌክትሮኒክስ ዋርፈር የተመረቁ የመጀመሪያ ዲግሪና ከዚያ በላይ ያላቸው፡፡

- የጤንነት ሁኔታ ሙሉ ጤንነቱ በሃኪም የተረጋገጠ

- የዕጩ መኮንን ኮርስ ወስዶ ወይም ወስዳ ለመስራት ፍላጎት ያለው/ያላት

-ወደ መከላከያ ሳይበር ገብቶ /ገብታ ለመስራት ፍላጎት ያለው/ያላት

- የሳይበር ሙያ የሚጠይቀውን ሙያዊ ድስፒሊን የሚያሟላ/የምታሟላ

NB፦ ሁሉም ተመልማዮች በተራ ቁጥር 1 ከላይ የተዘረዘሩ አጠቃላይ የምልመላ መስፈርቶችን ማሟላት ይኖርባቸዋል።እንዲሁም በምዝገባ ወቅት ኦሪጅናልና ኮፒ የትምህርት ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።

የምዝገባ ቦታና ጊዜ

Ø ተመዝጋቢዎች በምስራቅ መስቃን ወረዳ ስር በሚገኙ የቀበሌ አስተዳደር ጽ/ቤቶች፣ የምስራቅ መስቃን ወረዳ ሚሊሻ ጽ/ቤት በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን የምዝገባው ጊዜ ከሚያዝያ 15/08/2016 ዓ.ም እስከ ግንቦት 09 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ይሆናል ፡፡

በሁሉም ቀበሌዎቻችን ዝርዝር የመመልመያ መስፈርቶች ተለጥፎ የሚገኙ መሆኑን እንገልፃለን።

የአገር መከላከያ ሚኒስቴር

ሚያዝያ 2016 ዓ.ም

እንሴኖ
ቴሌግራም፦ t.me/misrakmeskanworedacommunication
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/mesrakmeskan/
ኢ-ሜይል፦[email protected]
ዩትዩብ፦https://youtube.com/channel/UCH3dI7vy2ULtrlosd_GtqcQ

ህዝብ የሚያነሳቸው የልማት፣የመልካም አስተዳደር እና እንዲሁም የሰላምና ፀጥታ ጉዳዮችን ትኩረት ሰጥቶ ምላሽ መስጠት እንደሚገባ የምስራቅ መስቃን ወረዳ ምክር ቤት አስታወቀ!።።።።።።።።።።።።...
08/05/2024

ህዝብ የሚያነሳቸው የልማት፣የመልካም አስተዳደር እና እንዲሁም የሰላምና ፀጥታ ጉዳዮችን ትኩረት ሰጥቶ ምላሽ መስጠት እንደሚገባ የምስራቅ መስቃን ወረዳ ምክር ቤት አስታወቀ!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሚያዚያ 30 ፣2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት} ህዝብ የሚያነሳቸው የልማት፣የመልካም አስተዳደር እና እንዲሁም የሰላምና ፀጥታ ጉዳዮችን ትኩረት ሰጥቶ ምላሽ መስጠት እንደሚገባ የምስራቅ መስቃን ወረዳ ምክር ቤት አስታውቋል።

ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደዉ 15ኛ መደበኛ ጉባኤ የቀረቡለትን ልዩ ልዩ ሹመቶችን መርምሮ በማፅደቅ የዕለቱን መደበኛ ጉባኤ አጠናቋል።

በጉባኤዉ ከግብርና አንፃር የአርሶ አደሩ የግብዓት አቅርቦትና ስርጭትን፣ የትምህርት ስብራትን ከማሻሻል፣ ከስራ እድል ፈጠራ፣ የፅጥታ ጉዳዮችን በዘላቂነት ከመፍታት፣ የማህበረሰቡን የንፁህ መጠጥ ዉሃ ችግሮችን መቅረፍ፣ የኦዲት ግኝት ተግባራትንና ከመንግስትና ህዝብ ንብረት አጠቃቀምና አስተዳደር ተግባራትን በተመለከተ ምክር ቤቱ ቱክረት ሰጥቶ ከተወያየባቸዉ ጉዳዮች መካከል ይገኙበታል።

ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸዉ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ ጀማል አወል እንደገለፁት ከህዝብ ፍላጎት አንፃር በወረዳዉ በርካት የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች በመሰራት ላይ መሆናቸዉን ገልፅዋል።

በተለይም እንደወረዳ የዉስጥ ለዉስጥ የመንገድ ግንባታ፣ ከስራ እድል ፈጠራ አንፃር ዉዝፍ እዳዎችን የማስመለስ ስራ፣ ፅጥታን ከማስፈን፣ ልዩ ልዩ ተቋማትን ከመግንባት፣ እንዲሁም ሌሎች መሰረተ ልማቶችን በመከናወን ረገድ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት በመሰራት ላይ መሆኑን ገልፅዋል።

ከግብርና ግብዓት ጋር ተያይዞ የመጣዉ የመዳበሪያና የምርጥ ዘር ግብዓት በእቅዱ መሰረት በአግባቡ ለአርሶ አደሩ እንዲደርስ ለማስቻል በትኩረት እየተሰራ መሆኑና ከዚህ ጋር በተያያዘ ያለአግባብ የሚቀርቡ ቅሬታዎች መታረም እንዳለባቸዉ ተናግረዋል።

ከትምህርት አንፃር የተማሪዎችን ዉጤት ለማሻሻል ግብዓት መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑን ያነሱት ዋና አስተዳዳሪዉ የመፅሐፍ አቅርቦትን ለማሳካት የሀብት ማሰባሰብ ላይ በቱክረት መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል።

ከዚህ ጋር ተያይዞ የተሰሩ በርካታ ስራ ቢኖሩም ፈጥኖ ሃብት አሰባስቦ ለተማሪዎች ግብዓቶች ከማቅረብ አኳያ ጉድለቶች መኖራቸዉን አንስተዋል።

ስለሆን የትምህርት ስብራቱን ለማሻሻል የትምህርቱ ማህበረሰብ፣ ወላጆች፣ ባለሃብቶች ብሎም የሚመለከተዉ ባለድርሻ አካላት የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል።

ከጤና አንፃር የመድሃኒት አቅርቦት ችግሮችን ለመፍታት እንደወረዳ የህዝብ ፋርማሲ ለማቋቋም እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ከፅጥታ አኳያ አሁን ባለዉ ሁኔታ የተሻለ ነገር ቢኖርም ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ከክልልና ከዞን ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመሆን እየተሰራ መሆኑንና ህገ ወጥ አካላትን አስቀድሞ የመያዝ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

ከዚህ ጎን ለጎን የፖሊስ አቅምን በማጠናከር ረገድ እየተሰራ ያለ ስራ መኖሩንና ህዝቡ ከፀጥታ አጋላት ጋር በመሆን ማገዝ እንዳለበትና የሮንድ ጥበቃዎችን ማጠናከር እንዳለበት ጠቁመዋል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ አለሙ ግዛዉ እንደተናገሩት ከምክር ቤቱ የተነሱ ጥያቄዎችን መሰረታዊ ጥያቄዎችን በመለየት ከህዝብ የልማት ፍላጎት አንፃር ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባና በቀጣይ ቱክረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ ከማህበረሰቡ ጋር በመሆን መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል።

በመጨረሻም የምስራቅ መስቃን ወረዳ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሸህቾ ኢብራሂም በተጓደሉ የአመራር ቦታዎች እጩ ተሿሚዎችን ለምክር ቤቱ ያቀረቡ ሲሆን ምክር ቤቱ የቀረቡ ሹመቶችን መርምሮ ያፀደ ሲሆን በዚህም መሠረት:-

1ኛ. አቶ ወንድሙ ጀማል:- የምስራቅ መስቃን ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ፅ/ቤት ኃላፊ፣
2ኛ. አቶ መሀመድኑር ስርሞሎ:- የምስራቅ መስቃን ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ፅ/ቤት ኃላፊ፣
3ኛ. አቶ አለማየሁ ሽመክት:- የምስራቅ መስቃን ወረዳ ፋይናንስ ፅ/ቤት ኃላፊ፣
4ኛ አቶ አብድልሰመድ ሁሴን:- የምስራቅ መስቃን ወረዳ ፐ/ሰ/ልማት ፅ/ቤት ኃላፊ፣
5ኛ.ወ/ሮ ፈቲሃ በድሩ:- የምስራቅ መስቃን ወረዳ ፕላን ፅ/ቤት ኃላፊ፣
6ኛ. አቶ አብድልኸይ አህመድ:- የምስራቅ መስቃን ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት ኃላፊ፣
7ኛ. አቶ ሁሴን ተማም:- የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ኃላፊ፣
8ኛ. አቶ ያሲን ከማል:- የምስራቅ መስቃን ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት ኃላፊ አድርጎ በመሾም የእለቱ ጉባኤ ተጠናቋል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ t.me/misrakmeskanworedacommunication
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/mesrakmeskan/
ኢ-ሜይል፦[email protected]
ዩትዩብ፦https://youtube.com/channel/UCH3dI7vy2ULtrlosd_GtqcQ

በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ምክር ቤት የ2016 ዓ/ም የ3ኛ ሩብ ዓመት 4ኛ ዙር 11ኛ ዓመት 15ኛ መደበኛ ጉባኤ በማካሄድ ላይ ይገኛል!!።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ሚ...
08/05/2024

በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ምክር ቤት የ2016 ዓ/ም የ3ኛ ሩብ ዓመት 4ኛ ዙር 11ኛ ዓመት 15ኛ መደበኛ ጉባኤ በማካሄድ ላይ ይገኛል!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሚያዚያ 30 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት} በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ምክር ቤት የ2016 ዓ/ም የ3ኛ ሩብ ዓመት 4ኛ ዙር 11ኛ ዓመት 15ኛ መደበኛ ጉባኤዉን በማካሄድ ላይ ይገኛል።

መድረኩን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ አለሙ ግዛዉ ዝርዝር አጀንዳዎችን በማቅረብ አስጀምረዉታል።

በጉባኤዉ የ2ኛ ሩብ ዓመት የ4ኛ ዙር 11ኛ ዓመት 14ኛ መደበኛ ቃለ ጉባኤ መርምሮ ማፅደቅ፣ የምስራቅ መስቃን ወረዳ አስተዳደር ም/ቤት የአስፈፃሚ ተቋማት የ3ኛ ሩብ ዓመት ሪፖርት ማስገምገም፣ ሹመት መርምሮ ማፅደቅ፣ የቀጣይ የስራ አቅጣጫና መመሪያ መስጠት የሚሉ የእለቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች ናቸዉ።

ምክር ቤቱ በዛሬዉ ዉሎዉ የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን በተመለከተ አስፈፃሚ ተቋማት ለይተዉ ከመፈፅም አኳያ፣ በወረዳዉ ዉስጥ ሄድ መጣ የሚሉ የፅጥታ ጉዳዮችን በተመለከተ ፣ በየቀበሌዉ የተሰበሰቡ የህዝብና የመንግስት ሃብቶችን ፈጥኖ ወደ መንግስት ቋት የማስገባትና ገቢ ማድረግ የሚሉና ሌሎቹም ጉዳዮች አስመልክቶ በጉባኤዉ ልዩ ትኩረት የተሰጣቸዉ ነጥቦች መሆናቸዉ ተገልጿል።

በአሁን ሰዓት የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ ጀማል አወል የ9ወራት የአስፈፃሚ ተቋማት ሪፖርት ለምክር ቤቱ አባላት በማቅረብ ላይ ይገኛሉ።

በቀጣይ ዝርዝር የምክር ቤቱ ዉሎን ተከታትለን የምናደርስ ይሆናል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ t.me/misrakmeskanworedacommunication
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/mesrakmeskan/
ኢ-ሜይል፦[email protected]
ዩትዩብ፦https://youtube.com/channel/UCH3dI7vy2ULtrlosd_GtqcQ

የብልፅግና ፖርቲ በመወከል በመስቃንና ማረቆ ምርጫ ጣቢያ 2 ድጋሚ በሚደረገው ምርጫ የሚወዳደሩ ዕጩዎች ምዝገባ አደረጉ!!።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ሚያዚያ 29 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስ...
07/05/2024

የብልፅግና ፖርቲ በመወከል በመስቃንና ማረቆ ምርጫ ጣቢያ 2 ድጋሚ በሚደረገው ምርጫ የሚወዳደሩ ዕጩዎች ምዝገባ አደረጉ!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሚያዚያ 29 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት} የብልፅግና ፖርቲ በመወከል በመስቃንና ማረቆ ምርጫ ጣቢያ 2 ድጋሚ በሚደረገው ምርጫ የሚወዳደሩ ዕጩዎች ምዝገባ አደረጉ።

በ6ኛው ዙር ሀገራዊና ክልላዊ የድጋሚ ምርጫ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በመስቃንና ማረቆ የምርጫ ክልል ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ምርጫ ይካሄዳል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፅ/ቤት የዲሞክራሲ ባህል አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ነኢማ ሙኒር፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ መሰለ ጫካና የማረቆ ልዩ ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ጀማል አማሮ ፖርቲ በመወከል ለሚወዳደሩ ዕጩዎች የውክልና ድብዳቤ ሰጥተዋል።

ፖርቲው የሚወክሉት ዕጩዎችን በምርጫ ክልሉ ቆሼ ከተማ በመገኙት የዕጩነት ምዝገባ አካሄደዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፅ/ቤት የዲሞክራሲ ባህል አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ነኢማ ሙኒር በክልሉ የመስቃንና ማረቆ ምርጫ ጣቢያ 2 በድጋሚ ምርጫ እንዲደረግ ምርጫ ቦርድ በወሰነው መሰረት ሰኔ 9 ምርጫ የሚካሄድ መሆኑ አስታውሰዋል።

በመሆኑ በምርጫው ክልሉ ብልፅግና ፖርቲ አንድ የፖርላማና ሶስት የክልል ምክር ቤት ተወካይ ዕጩዎች ማቅረቡን ገልፀዋል።

ህዝብ ዲሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ ምርጫ ለመምረጥ ካርድ ወስዶ መብቱን እንዲጠቀም እንደመንግስት የቅስቀሳ ስራዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል።

ምርጫው ሰላማዊ ዲሞክራሲያዊ ነፃ ምርጫ በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያለው ሆኖ እንዲካሄድ የክልሉ መንግስትም ሆነ ፖርቲው እምነት አለው ስሉ ተናግረዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ መሰለ ጫካ ምርጫው በተቀመጠው የጊዜ ፕሮግራም መሰረት ለማካሄድ ሁለቱም መዋቅሮች በቅንጅት እየሰሩ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

በምርጫ ክልሉ 106 የምርጫ ጣቢያዎች በሁለቱ መዋቅሮች መኖራቸውን የገለፁት የዋና የመንግስት ተጠሪው ፖርቲ የሚወክሉ ዕጩዎች በማቅረብ ምዝገባ ማድረጋቸው አንስተዋል።

በአካባቢው የሚስተዋሉ የነበሩ የሰላም ችግረኞች የክልሉ መንግስት እገዛ በሁለቱም መዋቅሮች አመራርና ማህበረሰብ ጥረት ወደተሻለ ደረጃ መድረሱን የምርጫ ሂደቱን አጋዥ እንደሚሆን በመጥቀስ በቀጣይ የህዝብ ለህዝብ ትስስር ሊያጠናክሩ የሚችሉ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ አመላክተዋል።

የማረቆ ልዩ ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ጀማል አማሮ በበኩላቸው በምርጫ ክልሉ የሚደረገው ምርጫ የተሳካ እንዲሆን የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተሰርተዋል ብለዋል።

በሁለቱም መዋቅሮች አራት ምርጫ ጣቢያዎች ላይ የመራጮች ምዝገባ እየተደረገ ይገኛል መንግስት መራጮች ወደ ምርጫ ጣቢያ ሄደው የምርጫ ካርድ ወስደው ዲሞክራሲያዊ መብቶቻቸው እንዲጠቀሙ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ t.me/misrakmeskanworedacommunication
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/mesrakmeskan/
ኢ-ሜይል፦[email protected]
ዩትዩብ፦https://youtube.com/channel/UCH3dI7vy2ULtrlosd_GtqcQ

በምስራቅ መስቃን ወረዳ በሰቆጣ ቃል ኪዳን ማስፋት ምዕራፍ የታቀፈ በግብርና ፅ/ቤት የግንዛቤ መፍጠሪያ እና የትውውቅ መድረክ ተካሄደ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ሚያዚ...
07/05/2024

በምስራቅ መስቃን ወረዳ በሰቆጣ ቃል ኪዳን ማስፋት ምዕራፍ የታቀፈ በግብርና ፅ/ቤት የግንዛቤ መፍጠሪያ እና የትውውቅ መድረክ ተካሄደ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሚያዚያ 29 ; 2016ዓ.ም( የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት) በምስራቅ መስቃን ወረዳ ግብርና ፅ/ቤት በሰቆጣ ቃል ኪዳን መስፋፋት ምዕራፍ የታቀፈ የግንዛቤ መፍጠሪያ እና የ2015ዓ.ም የዕቅድ ሪፖርት አፈፃፀም በማቅረብ እና የ2016ዓ.ም እቅድ በማቅረብ የውይይት መድረክ አካሄደዋል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ፅ/ቤት ሃላፊ ዶክተር መሀመድ ሰብራላ በዕለቱ በመድረኩ በመገኘት ፕሮግራሙን አስጀምረዋል።

ሃላፊው እንደተናገሩት ሰቆጣ ቃልኪዳን ፕሮጀክት በወረዳችን ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱ ይታወቃል።

ከእነዚህም ውስጥየምግብ እና የስራዓተ ምግብ ግንዛቤ ማስጨበጥ እና የመቀጨር ችግሮችን ለመከላከል የተለያዩ የግብዓት አቅርቦት እና የስልጠና ፕሮግራሞችን በመቅረፅ ለማህበረሰቡ እያስተማረ መቆየቱን ገልፀዋል።

ፅ/ቤቱ ባደደረገው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ የሰቆጣ ቃል ኪዳን ዋና አላማውንና በወረዳው የሚያከናውናቸውን ተግባራት ለባለ ድርሻ አካላቶች ግንዛቤ ሰጥተዋል።

በዋናነት የህፃናት አእምሮና የሰውነት ቅንጨራ እንዴት እንደሚከሰትና በሰዎች ላይ ስለሚያደርሰው አደጋ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም አእምሮአዊ ችግሮች ምን ያህል አሰከፊ መሆኑንና እንዲሁም እንዴት መከላከል እንደሚቻልና ቀድሞ የማወቅና የመረዳት ስልጠናዎች በሰፊው ተሰጥተዋል።

ለዚህም ዋና መፍትሄ የአመጋገብ ስርዓት ማዘመን ለሁለንተናዊ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን እና መቀንጨርን የመከላከል ዋነኛ መንገድ መሆኑ ተገልጿል ።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ የግብርና ፅ/ቤት ም/ኃላፊና የመሬት አስተዳደር ኃላፊ አቶ ሀሰን ረዲ እንደገለፁት የሰዎች አዕምሮ በስርዓተ ምግብ ያለመበልጸግ ችግሮች በማህበረሰቡ የሚዳደርሰው ችግር በጣም አስከፊ መሆኑን ገልጸው፤ ከእንግዲህ ሁሉም ምግቡ ከጓሮው አምርቶ የመጠቀምና ከምግብ እጥረት ከሚመጣው የመቀንጨር ችግር ሊላቀቅ እንደሚገባም አስታውቀዋል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ የግብርና ፅ/ቤት ም/ሃላፊ እና የኤክስቴንሽን ዘርፍ ሃላፊ አቶ ዋሲሁን ዘርጋው በበኩላቸው የተመጣጠነ ምግብ ለማግኘት ሩቅ መሄድ ሳያስፈልግ አካባቢያችን ከሚገኙ አትክልት፣ፍራፍሬ፣ጥራጥሬና የእንስሳት ተዋጽኦ ማግኘት እንደሚቻልም አስታውቀዋል።

በተመሳሳይ መልኩ የጋራ ርብርብና ቅንጅታዊ አሰራር ለጋራ አዕምሮዓዊም ይሁን ቁሳዊ ለውጥ ወሳኝ መሆኑን አዎንታዊ እንድምታ እንደሚኖረው ተናግረዋል።

በመድረኩ ተገኝተው የግንዛቤ ስልጠና ከወስዱት ባለሞያዎች የተለያዩ ሀሳብና አስተያየት እንዲሁም ጥያቄዎችን አንስተው ተወያይተዋል።

በመጨረሻም ይህ የተጀመረው የሰቆጣ መድረክ እስከ ታች ወርዶ በተግባር እንደሚሰራበትም ተገልጿል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ t.me/misrakmeskanworedacommunication
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/mesrakmeskan/
ኢ-ሜይል፦[email protected]
ዩትዩብ፦https://youtube.com/channel/UCH3dI7vy2ULtrlosd_GtqcQ

06/05/2024

Thanks for being a top engager and making it on to my weekly engagement list! Meshetifea Jmal Teiera, Laila Love, Ebrahim Arsenal's Coffee, Hailu Worsa, የመስቃን ድምፅ, Eman Sheref, ቃለና ቃሉ, Abdo Ahmed, Be Rational, Shurala Sani Abedi, Abdilaziz Mifta, Hassen Redi Sulyeman, ሸምሱ ኸይር ሰማን, Fedilu Shafi, ሂዳያ ሂዳያ, Abdrehim Adem Ebrahim, Ane Man, Mule Darunga, Getachew Abayneh, Abdu Shafi, ኢብራሂም ነኝ ከኢንሴኖ, ፈራገዘኘ ሚድያ, Yetmwork Nigussie, Shemsed Shems, Aisha Alisha, ሙህዲን.አህመድ. ሀቢብ, Abdi Shemsu, Gag Fay, አልሃምዱሊላህ አላኩሊሃል, Abdks Yeabo Abdi Nesru, Getahun Tesfaye Terefe, Hairu Kedir, Sabir Shifa, Shemsu Oumer, Zeynu Kasim Dedu, Shakir Ahmed Ke Meskan, Samera Samera, Shifa Mohammed Mohammed, Birhanu Esatu, እንም በደን, ፈረአገዘኛ የገጉ, Shehicho Ahmed, Tigistu Endeshaw Wedajo, Mohamedsani Kedire, Faruke Sebre Ahmed, Abule Genzbahew Abule Genzbahew, Asnake Tarekegn, Desalegn Lemma, Hussan Hulgeicho, Hassen Shafi

ታግታ የተወሰደችው የ2 ዓመት ከ8 ወር ሕጻን በ3 ቀናት ውስጥ ተገኘች!!።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ሚያዚያ 28 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ...
06/05/2024

ታግታ የተወሰደችው የ2 ዓመት ከ8 ወር ሕጻን በ3 ቀናት ውስጥ ተገኘች!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሚያዚያ 28 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት} ታግታ የተወሰደችው የ2 ዓመት ከ8 ወር ሕጻን በ3 ቀናት ውስጥ ተገኘች!!
ታግታ የተወሰደችውን የ2 ዓመት ከ8 ወር ሕጻን የአዲስ አበባ ፖሊስ ከብሔራዊ መረጃ አገልግሎት ጋር ባደረጉት የተቀናጀ ጠንካራ ክትትል በሦስት ቀናት ውስጥ መገኘቷን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።

የ2 ዓመት ከ8 ወር ዕድሜ ያላት አቢጊያ ዳንኤል የተባለችው ሕጻን የታገተችው በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ሳርቤት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ተወስዳ እንደሆነ ተገልጿል።

ቸርነት ጥላሁን የተባለው ተጠርጣሪ ከቤተሰቡ ጋር በነበረው ቅርበት ሕፃን አቢጊያን በተለያዩ ቦታዎች እየወሰደ በማዝናናት እንደ ቤተሰቡ አባል ያጫውታት እንደነበረ ተጠቅሷል።

በተጨማሪም ተጠርጣሪው ከአምስት ወር በላይ ከቤተሰቡ ጋር በትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪነት የነበረው ቅርርብ ወንጀሉን በቀላሉ ለመፈፀም ምቹ ሁኔታን እንደፈጠረለት ተጠቁሟል።

ግለሰቡ ሚያዝያ 25 ቀን 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ስዓት ተኩል ገደማ ወደ ህፃኗ ወላጆች መኖሪያ ቤት በመሄድና "እናቷ አምጣት ብላኛለች "ብሎ ለቤት ሰራተኛዋ ከነገረ በሗላ ሕጻን አቢጊያ ዳንኤልን ወስዶ በማገት ገንዘብ እንዲሰጠው ከወላጆቿ ጋር ሲደራደር መቆየቱ ተገልጿል።

ተጠርጣሪው 150 ሺህ የአሜሪካን ዶላር እንዲሰጠው በመጠየቅ ገንዘቡን ማግኘት ካልቻለ ሕፃኗን በሕይወት እንደማያገኟት ሲዝት እንደነበረ የህፃን አቢጊያ ወላጅ እናት ተናግራለች።

የአዲስ አበባ ፖሊስ፤ ሕፃኗን ለማስመለስና ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ለማዋል ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመቀናጀት ቀንና ሌሊት ክትትል ሲያደርግ መቆየቱ ተመላክቷል።

በተደረገው ክትትልም በዛባ ዕለት በልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ዓለም ሰላም ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተጠርጣሪው ተከራይቶ በሚኖርበት መኖሪያ ቤት ውስጥ ለሦስት ቀናት ያህል ታግታ የቆየችው ሕጻን መገኘቷን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

ሕጻናት ልጆች ለመሰል ወንጀል ተጋላጭ እንዳይሆኑ እንዲጠብቁ አደራ የተሰጣቸው ግለሰቦችም ሆኑ ሞግዚቶችና ወላጆች ነገሮችን በጥርጣሬ በማጤን የማረጋገጥ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።


ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ t.me/misrakmeskanworedacommunication
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/mesrakmeskan/
ኢ-ሜይል፦[email protected]
ዩትዩብ፦https://youtube.com/channel/UCH3dI7vy2ULtrlosd_GtqcQ

የምስራቅ መስቃን ወረዳ አስተዳደር የ2016 ዓ/ም የአስፈጻሚ ተቋሟት የ9ወር እቅድ አፈጻጸም ገመገመ!!።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ሚያዚያ 28 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ...
06/05/2024

የምስራቅ መስቃን ወረዳ አስተዳደር የ2016 ዓ/ም የአስፈጻሚ ተቋሟት የ9ወር እቅድ አፈጻጸም ገመገመ!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሚያዚያ 28 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት} የምስራቅ መስቃን ወረዳ አስተዳደር የ2016 ዓ/ም የአስፈጻሚ ተቋማት የ9ወር እቅድ አፈጻጸም ገምግሟል።

በመድረኩም የወረዳው አስፈፃሚ ሴክተር መስሪያ ቤት አመራሮች የተገኙ ሲሆኑ የ9ወር የስራ አፈጻጸም ዝርዝር ተግባራቶችን አስመልክቶ ሪፖርት ለቤቱ አቅርበዋል።

በዚህም በ2016 ዓ/ም በ9 ወር በተከናወኑ አበይት ተግባራትን አስመልክቶ የታዩ ጠንካራ አፈፃፅሞችንና ለወደፊት ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን በመገምገም የጋራ መግባባት መፋጠር መቻሉና በቀጣይ ቱክረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ ሰፋ ያለ ዉይይት እንደተደረገም ተገልጿል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አወል በመድረኩ እንደተናገሩት ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥን ከማሻሻል ፣ ብልሹ አሰራሮችን ከመከላከል፣ ማህበረሰቡ የሚያነሷቸዉን ልዩ ልዩ የልማት ስራዎችን በመለየትና ተግባራትን በቅንጅት በማከናወን ረገድ የሚጠበቅባቸዉን ማከናወን እንዳለባቸዉ ተናግረዋል።

ከዚህ አንፃር በተቋማት የታዩ መልካም ውጤቶችን በማስቀጠልና በሚስተዋሉ ጉድለቶች ላይ አፋጣኝ እርምትን በመውሰድ እንዲሁም የተሻለ ተቋማዊ አሰራሮችን በመከተል በቀጣይ የተሻለ ዉጤት ማስመዝገብ እንደሚገባም አመላክተዋል።

ከዕቅድ አንፃር በወረዳው ባለፉት 9 ወራት በተከናወኑ ተግባራቶች የታዩ የምልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ብሎም ልማትን ለማፋጠን የተሰሩ ስራዎች አበረታች መሆናቸዉና በግብርና፣ በትምህርት፣ ከስራ እድል ፈጠራ እንዲሁም በሌሎችም ተቋማት የተጀመሩ ጠንካራ ስራዎችን ተጠናክረዉ መቀጠል እንዳለባቸዉና የተለዩ ጉድለቶች ከማረም አኳያ ከአመራሩ ጠንካራ ስራ እንደሚጠበቅም ተገልጿል።

በመጨረሻም ከአፈፃፅም አንፃር በዕቅድ ተይዘዉ ያልተከናወኑ ተግባረቶችን፣ ከህዝብ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በመለየት ትኩረት ሰጥቶ መስራትና ያሉ ጉድለቶች ላይ የክትትልና የቁጥጥር ስራዎችን በማጠናከር መስራት እንደሚገባ የቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ የነበረዉ መድረክ ተጠናቋል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ t.me/misrakmeskanworedacommunication
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/mesrakmeskan/
ኢ-ሜይል፦[email protected]
ዩትዩብ፦https://youtube.com/channel/UCH3dI7vy2ULtrlosd_GtqcQ

የምስራቅ መስቃን ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት በትላንትናው እለት ውይይት አካሂዷል።ሚያዝያ 27፣2016 ዓ.ም (የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ) የምስራቅ መስቃን ...
06/05/2024

የምስራቅ መስቃን ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት በትላንትናው እለት ውይይት አካሂዷል።

ሚያዝያ 27፣2016 ዓ.ም (የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ) የምስራቅ መስቃን ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት በቀበሌ ደረጃ ለተዋቀሩ የእስልምና ጉዳይ ኮሚቴዎች እውቅና መስጠቱን ገለፀ።

የእስልምና ጉዳይ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሁሴን ሸይቾ በመድረኩ በመገኘት ለወረዳው እስልምና ምክር ቤት አባላት መልክታቸውን አስተላልፈዋል። ኡስታዝ ሁሴን ሸይቾ እንዳሉት ሙስሊሙ ማህበረሰብ በአንድነት በዚህ መድረክ በመገኘቱ እና የሙስሊሙን አንድነት ለማጠናከር በጣም አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ የእስልምና ጉዳይ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሸረፋ ባዲ እንደገለፁት የሙስሊሙ ማህበረሰብ ከመከፋፈል ወደ አንድ ለማምጣት የዚህ ምክር ቤት አባላት በሚገባ መስራት እንዳለበት አሳውቀዋል።

በአጠቃላይ ቀጣይ ለሚታሰቡ እቅዶች ስኬታማነትና ተቋሙ ለሁሉም የወረዳ ሙስሊም ማህበረሰብ ለማገልገል ይረዳ ዘንድ የቀበሌያት የእስልምና ጉዳይ ምክር ቤት በመቋቋምና እውቅና በማስጠት ስብሰባው ተጠናቋል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ሊግና ወጣቶች ሊግ ፅ/ቤት ከወረዳዉ ሴቶችና ህፃናት እንዲሁም ወጣቶች ፅ/ቤት ጋር በጋራ በመሆን የትንሳኤ በዓልን ምክኒያት በማድረግ ለአቅመ ደካ...
04/05/2024

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ሊግና ወጣቶች ሊግ ፅ/ቤት ከወረዳዉ ሴቶችና ህፃናት እንዲሁም ወጣቶች ፅ/ቤት ጋር በጋራ በመሆን የትንሳኤ በዓልን ምክኒያት በማድረግ ለአቅመ ደካሞች፣ ህፃናትና አረጋዊያን ልዩ ልዩ ድጋፎችን አደረገ!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሚያዚያ 26 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት} የምስራቅ መስቃን ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ሊግና ወጣቶች ሊግ ፅ/ቤት ከወረዳዉ ሴቶችና ህፃናት እንዲሁም ወጣቶች ፅ/ቤት ጋር በጋራ በመሆን የትንሳኤ በዓልን ምክኒያት በማድረግ ለአቅመ ደካሞች፣ ህፃናት እንዲሁም አረጋዊያን የዘይት፣ የዶሮ ፣ የዱቄትና መሰል የበዓል ስጦታዎችን ድጋፍ አድርጓል።

ድጋፉ የተደረገው ከወረዳው ከተለያዩ ቀበሌያት ለተዉጣጡ በተለያዩ ማህበራዊ ችግር ዉስጥ የሚገኙ አቅመ ደካሞች፣ ተጋላጭ ህጻናትና አረጋዊያን ሲሆኑ በዓሉን ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተደስተው ለማክበር የሚያስችላቸዉን ከ 45, 000 ብር በላይ የሚያወጣ እንደሆነም ተገልጿል።

በስጦታ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አወል እንደገለፁት ድጋፍ የተደረገላቸዉ አካላት በዓሉን በሰላም፣ በአብሮነት እንዲያከብሩ ብሎም የብቸኝነት ስሜት እንዳያሰማቸዉና ከጎናቸዉ መሆናችንን ጨምር ለማሳየት እንደሆነ ተናግረዋል።

በተጨማሪም በድጋፉ መደሰታቸዉንና የዚህን ዓይነት በጎ ተግባር በዓላትን ምክንያት በማድረግ ብቻ ሳይሆን የሁልጊዜ ተግባራችን መሆን እንዳለበትና በተለያዩ አጋጣሚዎች ያቅማችንን በማድረግ በጎ ተግባራትን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል።

የመስራቅ መስቃን ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ የሴቶች ሊግ ፅ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ለምራ ኑሪ በበኩላቸዉ እንደተናገሩት የተደረገው ድጋፍ በቂ ሆኖ ሳይሆን የመረዳዳት የአብሮነት እንዲሁም የበጎነት ተምሣሌት በመሆኑ አቅም ለሌላቸው የማህበረሰባችን ክፍሎች ድጋፍ በማድረግ የበኩላችን ለመወጣት እንደሆነ ገልፅዋል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ወጣቶች ሊግ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ሀቢብ አህመዲን አቅም ለሌላቸውና ለችግር የተጋለጡ የህብረተሰባችን ክፍሎች ድጋፍ ማድረግ ወንድማማችነትና እህትማማችነት ለማጎልበት እንደሚረዳ ገልፀዋል።

በመጨረሻም ድጋፍ የተደረገላቸዉ አካላት በስጦታዉ መደሰታቸዉንና ይህን ድጋፍ ላስተባበሩ አካላት፣ የወረዳዉ አስተዳደር ለሌሎች የሚመለከታቸዉ አካላት ምስጋናቸዉን አቅርበዋል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ t.me/misrakmeskanworedacommunication
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/mesrakmeskan/
ኢ-ሜይል፦[email protected]
ዩትዩብ፦https://youtube.com/channel/UCH3dI7vy2ULtrlosd_GtqcQ

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ2016 ዓ/ም የስቅለትና የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!! ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ሚያዚያ 25 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን...
03/05/2024

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ2016 ዓ/ም የስቅለትና የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሚያዚያ 25 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት} ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ2016 ዓ/ም የስቅለትና የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ:- የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ ጀማል አወል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ ጀማል አወል የስቅለትና የትንሳኤ በዓልን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳቹሁ መልእክት አስተላልፈዋል።

ዋና አስተዳዳሪዉ በመልዕክታቸዉ:- የትንሳኤ በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በብዙ ሃይማኖታዊ ትዉፊት በድምቀት ከሚከበሩ ዓበይት በዓላት አንድ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ህዝበ ክርስቲያኑ ለሁለት ወራት ያክል በፆም፣ በፀሎት እንዲሁም ሌሎች ሃይማኖታዊ ስርዓቱ የሚፈቅደዉን በጎ ተግባራት ሲያከናዉን መቆየቱንና ለሃገር ሰላምና አንድነት ብሎም መረዳዳት ህዝበ ክርስቲያኑ ሲያከናዉን የነበረዉን መልካም ተግባራት ከበዓሉ በኃላም አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

በዓሉ የፍቅር፣ የይቅርታ በዓል በመሆኑ ህዝበ ክርስቲያኑ በዓሉን ሲያከብር የተቸገሩትን በመርዳት፣ አቅመ ደካሞችን በመጠየቅና በመተሳሰብ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል።

ከበዓሉ ጎን ለጎን ህዝበ ክርስቲያኑ ከዚህ በፊት ሲያደርግ እንደነበረዉ በልማቱ እንዲሁም ሰላምን፣ አንድነትን ከማስጠበቅ አኳያ ንቁ ተሳታፊ በመሆን ተግባሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አስተላልፈዋል።

በመጨረሻም የተከበሩ ዋና አስተዳዳሪዉ ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለስቅለትና ለእየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት ያላቸዉን መልካም ምኞት ገልፀዉ በዓሉ የሰላም ፣ የደስታና የመተሳሰብ እንዲሆን ተመኝተዋል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ t.me/misrakmeskanworedacommunication
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/mesrakmeskan/
ኢ-ሜይል፦[email protected]
ዩትዩብ፦https://youtube.com/channel/UCH3dI7vy2ULtrlosd_GtqcQ

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አወል እንዲሁም የወረዳዉ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሸህቾ ኢብራሂም በወረዳዉ እየተከናወኑ የሚገኙ የመንገድ ልማት ስራዎችን አስመልክቶ የመስ...
02/05/2024

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አወል እንዲሁም የወረዳዉ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሸህቾ ኢብራሂም በወረዳዉ እየተከናወኑ የሚገኙ የመንገድ ልማት ስራዎችን አስመልክቶ የመስክ ምልከታ አደረጉ!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሚያዚያ 24 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት} የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አወል እንዲሁም የወረዳዉ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሸህቾ ኢብራሂም በወረዳዉ እየተከናወኑ የሚገኙ የመንገድ ልማት ስራዎችን አስመልክቶ የመስክ ምልከታ አደረጉ።

በበጀት አመቱ በካፒታል በጀት ለማከናወን ከተያዙ የልማት ስራዎች ዉስጥ ከይመር ዋጮ1ኛ እስከ ዶበና ባቲ የሚዘልቀዉ ከ 8 ኪሎ ሜትር በላይ የውስጥ ለውስጥ መንገድ ስራ አንዱ ሲሆን በዛሬዉ እለት ዋና አስተዳዳሪዉን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የመንገድ ልማት ስራዉ ያለበትን ደረጃ በተመለከተ የመስክ ምልከታ አድርገዋል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አወል እንደተናገሩት የመንገድ ልማት ስራዉ ሲጠናቀቅ ለአከባቢዉ ማህበረሰብ ትልቅ ጥቅም የሚሰጥ መሆኑንና በፊት የዉስጥ ለዉስጥ መንገድ ባለመኖሩ ሲደርስ የነበረዉን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን መቅረፍ የሚችል የልማት ስራ መሆኑን ተናግረዋል።

ከዚህ ጋራ ተያይዞ በክረምት ወቅት በጭቃ ምክንያት ማህበረሰቡ ላይ የሚደርሰዉን እንግልት ጭምር በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንስም ዋና አስተዳዳሪዉ አክለዉ ገልፀዋል።

የወረዳዉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሸህቾ ኢብራሂም በበኩላቸዉ እንደወረዳ የማህበረሰቡን የመንገድ ጥያቄዎች ለመቅረፍ ከሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመሆን በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዉ በቀጣይም ህዝቡን ባሳተፈ መልኩ መስል የልማት ስራዎችን ተጠናክረዉ እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ በድሩ ጉደታ እንደገለፁት መንገዱ 4 ቀበሌዎችን ማለትም ይመር ዋጮ1ኛ፣ ይመርዋጮ 2ተኛ ፣ የኢሌ ቀበሌ እና ዶበና ባቲ ቀበሌዎችን የሚያገናኝ ወሳኝ የውስጥ ለውስጥ መንገድ መሆኑን ገልፀዋል።

የመንገድ ልማት ስራዉ 50% በወረዳዉ አስተዳደርና በአከባቢዉ ማህበረሰብ የሚሸፈን ሲሆን 50% ደግሞ በክልሉ በጀት የሚሸፈን መሆኑም ተገልጻል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ t.me/misrakmeskanworedacommunication
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/mesrakmeskan/
ኢ-ሜይል፦[email protected]
ዩትዩብ፦https://youtube.com/channel/UCH3dI7vy2ULtrlosd_GtqcQ

የትንሳኤ በዓል  በሠላም እንዲከበር  ፖሊስ አስፈላጊዉን ዝግጅት ማድረጉን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ሳጅን አዲሱ ጊማሮ ገለፁ !!።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ሚያዚያ 24 ፣ 2...
02/05/2024

የትንሳኤ በዓል በሠላም እንዲከበር ፖሊስ አስፈላጊዉን ዝግጅት ማድረጉን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ሳጅን አዲሱ ጊማሮ ገለፁ !!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሚያዚያ 24 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት} የትንሳኤ በዓል በሠላም እንዲከበር ፖሊስ አስፈላጊዉን ዝግጅት ማድረጉን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ሳጅን አዲሱ ጊማሮ ገልፀዋል።

በዓሉ ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም ተከብሮ እንዲዉል አጭር የፀጥታ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ተግባር መገባቱንም ሳጅን አዲሱ ተናግረዋል።

በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት የሚከበረው የ2016 ዓ.ም የስቅለትና የትንሳኤ በዓል ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም ተከብሮ እንዲዉል ፖሊስ ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር በመሆን የቅድመ ጥንቃቄ ስራዎች መሰራታቸዉና በየቀጠናዉ የፅጥታ አካላት ስምሪት እንደተሰጠም ተገልጿል።

ህዝበ ክርስቲያኑ ለሁለት ወራት ያህል በጾም ፀሎት መቆዩቱ ተከትሎ በዓሉን በድምቀት አክብሮ ለመዋል ለሸመታ ወደ ገበያ ሲያቀና የወንጀል ሰለባ ላለመሆን ተገቢዉ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት ጠቁመዋል።

ከዚህ ጋር ተያይዞ በበዓሉ ግርግር ሀሰተኛ የብር ኖት ዝዉዉሮች፣ የእሳት አደጋዎች ሊኖር ስለሚችል ህብረተሰቡ የተለመደዉን ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበትም ተናግረዋል።

በመጨረሻም ሳጅን አዲሱ ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለስቅለትና ለእየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት ያላቸዉን መልካም ምኞት ገልፀዉ በዓሉ የሰላም፣የደስታና የመተሳሰብ እንዲሆን ተመኝተዋል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ t.me/misrakmeskanworedacommunication
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/mesrakmeskan/
ኢ-ሜይል፦[email protected]
ዩትዩብ፦https://youtube.com/channel/UCH3dI7vy2ULtrlosd_GtqcQ

ለአርሶ አደሩ የምርጥ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ ግብዓቶችን ለማቅረብ ዝግጅት መጠናቀቁን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ግብርና ፅ/ቤት ገለፀ!!።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ሚያዚያ 24 ፣ 2016 ...
02/05/2024

ለአርሶ አደሩ የምርጥ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ ግብዓቶችን ለማቅረብ ዝግጅት መጠናቀቁን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ግብርና ፅ/ቤት ገለፀ!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሚያዚያ 24 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት} ለአርሶ አደሩ የምርጥ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ ግብዓቶችን ለማቅረብ ዝግጅት ማጠናቀቁን የምስራቅ መስቃን ወረዳ ግብርና ፅ/ቤት ገልጿል።

የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የግብዓት አቅርቦት ዋነኛ ጉዳይ መሆኑ ይታወቃል። ስለሆነም በወረዳ ደረጃ ግብዓቶችን ለአርሶ አደሩ ለማቅረብ ከዚህ በፊት የተለያዩ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸዉንና አሁን ላይ ስርጭት ለማካሄድ ዝግጅት መጠናቀቁ ተገልጿል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ፅ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር መሃመድ ሰብራላ እንደተናገሩት ግብዓት ለአርሶ አደሩ በበቂ ሁኔታ መዘጋጀቱን ጠቅሰዉ ስርጭቱ በተሳካ ሁኔታ ለአርሶ አደሩ ተደራሽ እንዲሆን አመራሩ እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች ላይ ጠንከር ያለ ስራ መሰራት እንዳለበት ገልፀዋል።

አርሶ አደሩ የበልግ ስራዉን አስመልክቶ የማሳ ዝግጅትና መሰል ስራዎች ላይ ተግባሩን አጠናክሮ እንዲቀጥልና በቀረበዉ ምርጥ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ በመጠቀም በወቅቱ ዘር እንዲዘራ የፅ/ቤቱ ሃላፊዉ ጥሪ አስተላልፈዋል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ t.me/misrakmeskanworedacommunication
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/mesrakmeskan/
ኢ-ሜይል፦[email protected]
ዩትዩብ፦https://youtube.com/channel/UCH3dI7vy2ULtrlosd_GtqcQ

1 ሺህ 180 ኢትዮጵያውያን ከሳውዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ!!።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ሚያዚያ 23 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤ...
01/05/2024

1 ሺህ 180 ኢትዮጵያውያን ከሳውዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሚያዚያ 23 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት} 1 ሺህ 180 ኢትዮጵያውያን ከሳውዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ።

በሶስት ዙር በረራ በተከናወነ በሳውዲ አረቢያ በችግር ውስጥ የነበሩ ዜጎችን የመመለስ ስራ 1 ሺህ 180 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው መመለስ ተችሏል።

በዛሬው እለት ወደ ሀገር ከተመለሱት 1 ሺህ 180 ዜጎች ውስጥ 1 ሺህ 98 ወንዶች፣ 79 ሴቶች እና 3 ጨቅላ ህፃናት ሲሆኑ ከተመላሾች መካከል 228 የሚሆኑት እድሜያቸው ከአስራ ስምንት አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች መሆናቸው ተጠቅሷል።

ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ከቤተሰብ ጋር የመቀላቀል ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

ከሚያዚያ 04 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ በሚገኘው ዜጎችን ወደ ሀገር የመመለስ ስራ ከ13 ሺህ 900 በላይ ኢትዮጵያውያንን መመለስ መቻሉም ተጠቁሟል።


ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ t.me/misrakmeskanworedacommunication
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/mesrakmeskan/
ኢ-ሜይል፦[email protected]
ዩትዩብ፦https://youtube.com/channel/UCH3dI7vy2ULtrlosd_GtqcQ

ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ብሎም ሠራተኛው የስራ ላይ ዋስትና እንዲያገኝ በማህበር መደራጀት ጥቅሙ የጎላ መሆኑን የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ገለፅ!!።።።።።።።...
01/05/2024

ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ብሎም ሠራተኛው የስራ ላይ ዋስትና እንዲያገኝ በማህበር መደራጀት ጥቅሙ የጎላ መሆኑን የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ገለፅ!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሚያዚያ 23 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት} ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ብሎም ሠራተኛው የስራ ላይ ዋስትና እንዲያገኝ በማህበር መደራጀት ጥቅሙ የጎላ መሆኑን የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ገለፅ።

በዕለቱ በዞኑ ውስጥ በቡታጅራ ከተማ አምስተኛ የሠራተኞች ማህበር በአፍራን የቆሎ ማምረቻ አክሲዮን ማህበር መስርቷል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ አቶ አህመዲን ደድገባ እንደገለፁት ሠራተኛው ግዴታውንና መብቱን አውቆ ስራ ላይ እንዲገኝና በራሱ ጥቅም ላይ ለሚያነሳቸው የደሞዝ ጭማሪ የትርፍ ሰዓት ክፍያ እና የመሳሰሉ መብቶች ሊያስከብርና ሊጠይቅ የሚችልበት ቀላሉ መንገድ በማህበር መደራጀት መሆኑን ጠቁመዋል።

በአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1157/2011 መሰረት ማንኛውም ሰራተኛ ከ12 በላይ ሆኖ በግል ድርጅት ውስጥ ተቀጥረው ሲሰሩ ሰራተኞችም በሚሰሩበት ድርጅት ውስጥ የራሳቸው ማህበር መመስረት እንደሚችሉ ጠቁመዋል።

ከዛም ባሻገር ሰራተኞች በስራ ላይ ጉዳት ቢደርስባቸው በማህበሩ አማካኝነት ተገቢውን የጤና ኢንሹራንስ ወይም የጤና ህክምና ማግኘት እንዲችሉም አይነተኛ መፍትሔ መሆኑንም አቶ አህመዲን ተናግረዋል።

ዞኑ ከግማሽ ዓመት በኃላ ዘጠኝ ማህበራት ለማቋቋም አቅዶ እየተንቀሳቀሰ ሲገኝ እስከ አሁን አምስት ማቋቋሙንና ቀሪዎቹን በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ አጠናቀው እንደሚሰሩም ኃላፊው ጠቁሟል።

ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን የመንግሥት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ t.me/misrakmeskanworedacommunication
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/mesrakmeskan/
ኢ-ሜይል፦[email protected]
ዩትዩብ፦https://youtube.com/channel/UCH3dI7vy2ULtrlosd_GtqcQ

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ገመገመ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ሚያዚያ 22 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽ...
30/04/2024

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ገመገመ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሚያዚያ 22 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት} የምስራቅ ጉራጌ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ከየወረዳዎች እና ከየከተማ አስተዳደሩ ከተዉጣጡ የማኔጅመንት አባላትና ባለድርሸ አካላት ጋር የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈፃፀም በእንሴኖ ከተማ ገምግሟል።

የግምገማ መድረኩ ዋና አላማ ያለፈዉን ዘጠኝ ወራት አፋፃፅም ምን እንደሚመስል ለመገምገም እንዲሁም ያሉ ጉድለቶችን በመለየት ከፊታችን ባሉት ወራቶች ተግባራትን አጠናክሮ ለማስቀጠልና ግብረ መልሶችን መሰረት በማድረግ ሰፋ ያለ ዉይይቶችን ለማድረግ እንደሆነ ተገልጻል።

የመምሪያው ኃላፊዋ ወ/ሮ ቤተልሄም ታደሰ እንደተናገሩት በተቋሙ በ9 ወራት ታቅደው የተሠሩ ተግባራት ላይ የነበሩ ጠንካራና ደካማ ጎኖች ተለይተው በጥልቀት መገምገማቸውን ጠቁመዋል ።

እንደ ኃላፊዋ ገለጻ የንግድ ህግን ከማስከበር፣ ህገ ወጥ የነዳጅ ዝዉዉርን ከመቆጣጠር፣ ግዜ ያለፈባቸዉን ምርቶች በግብረ ሃይል ከማስወገድ፣ የንግድ ስርዓቱን ከማዘመን ብሎም ህገ ወጥ ነጋዴዎችን ወደ ህጋዊ የንግድ ስርዓት ከማስገባት አኳያ በጥንካሬ የተከናወኑ ተግባራት መሆናቸዉን ተናግረዋል።

ዋጋ ከማረጋጋት ጋር ተያይዞ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት አበረታች ቢሆኑም ነገር ግን የሰንበት ገበያን በስፋት ከማቋቋም ጋር ተያይዞ ጉድለቶች መኖራቸዉንና በቀጣይ በትኩረት በመስራት የፋብሪካ ምሮቶችን ጭምር ለተጠቃሚ ለማቅረብ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

በተጨማሪም ህግ ከማስከበር ጋር በተያያዘ የሚከናወኑ ተግባራቶች የአንድ ወቅት ተግባር መሆን እንደሌለበትና የክትትልና የቁጥጥር ስራዎች ተጠናክረዉ መቀጠል እንዳለባቸዉ ኃላፊዋ አክለዉ ገልጸዋል።

በመጨረሻም ወ/ሮ ቤተልሄም ከእቅድ አፈፃፀም አንፃር በጥንካሬ የተከናወኑ ተግባራቶች በማስቀጠል በጉድለት የታዩ ተግባራት ላይ ትኩረት በመስጠት በቀጣይ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።



ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ t.me/misrakmeskanworedacommunication
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/mesrakmeskan/
ኢ-ሜይል፦[email protected]
ዩትዩብ፦https://youtube.com/channel/UCH3dI7vy2ULtrlosd_GtqcQ

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ገቢዎች መምሪያ ከምስራቅ መስቃን ወረዳና ከኢንሴኖ ከተማ አስተዳደር ጋር በጋራ በመሆን ለ ደረጃ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋዮች በሂሳብ መዝገብ አያያዝ ዙሪያ ስልጠና እየ...
30/04/2024

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ገቢዎች መምሪያ ከምስራቅ መስቃን ወረዳና ከኢንሴኖ ከተማ አስተዳደር ጋር በጋራ በመሆን ለ ደረጃ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋዮች በሂሳብ መዝገብ አያያዝ ዙሪያ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሚያዚያ 22 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት} የምስራቅ ጉራጌ ዞን ገቢዎች መምሪያ ከምስራቅ መስቃን ወረዳና ከኢንሴኖ ከተማ አስተዳደር ጋር በጋራ በመሆን ለ ደረጃ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋዮች በሂሳብ መዝገብ አያያዝ ዙሪያ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።

መድረኩ በዋናነት የንግድ ማህበረሰብ ተገቢ የሆነ የመዝገብ አያያዝ ስልትን በመከተል ዉጤታማ የገቢ እና ወጪ ስርዓትን እንዲከተል ለማስቻልና ነጋዴዉ ከግብር ስወራ ጋር ተያይዞ ያሉ ጉድለቶችን ለማረምና ሰፊ ግንዛቤዎችን ለመስጠት ያለመ እንደሆነ ተገልጻል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ t.me/misrakmeskanworedacommunication
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/mesrakmeskan/
ኢ-ሜይል፦[email protected]
ዩትዩብ፦https://youtube.com/channel/UCH3dI7vy2ULtrlosd_GtqcQ

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን በዞኑ ለስድስት ወራት የሚቆይ የአካባቢ ብክለት መከላከል ንቅናቄ ፕሮግራም አስጀመሩ!!።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ሚያዚያ 21 ፣ ...
29/04/2024

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን በዞኑ ለስድስት ወራት የሚቆይ የአካባቢ ብክለት መከላከል ንቅናቄ ፕሮግራም አስጀመሩ!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሚያዚያ 21 ፣ 2016 ዓ,ም {የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት} የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን በዞኑ ለስድስት ወራት የሚቆይ የአካባቢ ብክለት መከላከል ንቅናቄ ፕሮግራም አስጀመሩ።

"ብክለት ይብቃ ውበት ይንቃ"! በሚል መሪ ሃሳብ የተጀመረው ንቅናቄ ለተከታታይ ስድስት ወራት የፕላስቲክ ፣ የአየር፣ የውሀ፣ ወንዞችን የማጽዳት፣ የአፈርና የድምፅ ብክለትን የመከላከል ስራዎች እንደሚከናወን ተጠቁሟል።

የንቅናቄው ስራው ውጤት በማምጣት በማህበረሰቡ ጤና ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ እንዲኖረው የከተማና የወረዳ መዋቅሮች በትኩረት እንዲመሩ አቅጣጫ ተቀምጧል።

መድረኩ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን ጨምሮ የዞን የካቢኔ አባላት፣ የወረዳ አስተዳዳሪዎች፣ የከተማ ከንቲባዎች፣ የየወረዳውና ከተማ አስተዳደር የደንና አካባቢ ጥበቃ እንዲሁም የፖርቲ ፅ/ቤት ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የዘገበው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ t.me/misrakmeskanworedacommunication
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/mesrakmeskan/
ኢ-ሜይል፦[email protected]
ዩትዩብ፦https://youtube.com/channel/UCH3dI7vy2ULtrlosd_GtqcQ

Address

Ensseno
Butajira

Telephone

+251924705963

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት:

Videos

Share