Basket News Network BNN

Basket News Network BNN Basket News Network is a media which serves the community by informing News happen in every where!!

  በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በባስኬቶ ዞን የተወለደች ባለ ስጦታ እንስት ነች። አሁን በሀገራችን የስፖርት ኢንዳስትሪ ዉስጥ በጠረጰዛ ተኒስ በሀገር ደረጃ ተጽዕኖ እየፈጠሩ ካሉ ሴት ስፖርተኞች ...
04/02/2024

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በባስኬቶ ዞን የተወለደች ባለ ስጦታ እንስት ነች። አሁን በሀገራችን የስፖርት ኢንዳስትሪ ዉስጥ በጠረጰዛ ተኒስ በሀገር ደረጃ ተጽዕኖ እየፈጠሩ ካሉ ሴት ስፖርተኞች አንዷ ስትሆን በዛሬዉ ዕለት ማለትም በቀን 26/05/2016 ዓ.ም በአድስ አበባ በተደረገዉ የክለቦች ዉድድር ንግድ ባንክን በመወከል ተወዳድራ የአሸናፍዎች አሸናፍ በመሆን ዉድድሩን ከማጠናቀቅም በላይ የኮከብ ተጨዋች ሆና በመመረጧ ደስ ብሎናል እንኳን ደስ ያለሽ!!!

"High class ከሆኑ ሰዎች ጋር መዋል በጣም ደስ ይላል፣ ዛሬ ከምርጥ ሰዎች ጋር ምሳ በልቼ ከፍ ከፍ ያሉ ነገር አወራን ረጅም አመት እንድኖር መመኘት ጀመርኩ፣ ባለፈው ከብሄርተኛ ጋር ቡ...
24/01/2024

"High class ከሆኑ ሰዎች ጋር መዋል በጣም ደስ ይላል፣ ዛሬ ከምርጥ ሰዎች ጋር ምሳ በልቼ ከፍ ከፍ ያሉ ነገር አወራን ረጅም አመት እንድኖር መመኘት ጀመርኩ፣

ባለፈው ከብሄርተኛ ጋር ቡና ጠጥቼ ጥላቻ ብቻ አውርቶኝ መንገድ ላይ ሰው ሳገኝ የሚገድለኝ ነበር የሚመስለኝ። ከሚጠቅማችሁ ሰዎች ጋር ብቻ ዋሉ!!''

ከይስሐቅ አዱኛ የግሉ ገጽ ላይ የተወሰደ

የጌዴኦ ብሔር የዘመን መለወጫ ''ዳራሮ'' በዓል በዞኑ ገደብ ከተማ እየተከበረ ይገኛል። እንኳን አደረሳችሁ!!
23/01/2024

የጌዴኦ ብሔር የዘመን መለወጫ ''ዳራሮ'' በዓል በዞኑ ገደብ ከተማ እየተከበረ ይገኛል።

እንኳን አደረሳችሁ!!

ጥምቀት በዉብቷ ባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ!እንኳን አደረሳችሁ/አደረሰን  #2016ዓ.ም
20/01/2024

ጥምቀት በዉብቷ ባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ!

እንኳን አደረሳችሁ/አደረሰን #2016ዓ.ም

አባታችን ረጅም ዕድሜ ከጤና ጋር ይስጥልን!!የበዓሉ ድምቀት!
15/01/2024

አባታችን ረጅም ዕድሜ ከጤና ጋር ይስጥልን!!

የበዓሉ ድምቀት!

ነፍስህ በአፀደ ገነት ትረፍ አንተ መልካም ሰዉ😢
15/01/2024

ነፍስህ በአፀደ ገነት ትረፍ አንተ መልካም ሰዉ😢

እንኳን ለባስኬት ብሔረሰብ የምስጋና በዓል ሾልኣ ካሻ በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ/አደረሰን!!
12/01/2024

እንኳን ለባስኬት ብሔረሰብ የምስጋና በዓል ሾልኣ ካሻ በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ/አደረሰን!!

የባሏ ህይወት እንዲቀጥል አንዱ ኩላሊት ለባሏ ሰታ በአንዱ ኩላሊት የምትኖር ሚስት 👰👰መርሐዊት ገ/መድህን ትባላለች ባለቤቷ ፀጋዬ ገብሩ ሁለት ኩላሊቶቹ እንደማይሰሩ በዶክተሮች ይነገራዋልሚስት...
09/01/2024

የባሏ ህይወት እንዲቀጥል አንዱ ኩላሊት ለባሏ ሰታ በአንዱ ኩላሊት የምትኖር ሚስት 👰👰

መርሐዊት ገ/መድህን ትባላለች ባለቤቷ ፀጋዬ ገብሩ ሁለት ኩላሊቶቹ እንደማይሰሩ በዶክተሮች ይነገራዋል

ሚስትም ይህን ስትሰማ ያለምንም ማንገራገር ለዶክተሮቹ የኔ የሚሆን ከሆነ የኔን መስጠት እችላለው ትላለች

ሲመረመሩ የእሷ ኩላሊት ለባሏ እንዲመሆን ይነገራታል

እሷም በፍቅር ና በፍላጎት ይህው አንዱን ኩላሊቷን ሰታው እሷም ባለቤቷም በፍቅር ና በጤና አንድ ላይ እየኖሩ ይገኛል💑

ፍቺ ና ክህደት በበዛበት በዚች ዓለም እንደዚህ አይነት ለባሏ ህይወትን የምትሰጠ ሚስት ማግኘት ይከብዳል::

እረጅም እድሜ ከጤና ጋር ይስጥልን 🙏🙏

ለመላው የክርስትና እምነትን ተከታዮች ፣ የገፃችን ተከታዮች እንኳን ለዓለም መድሀኒት ለሆነው ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ/አደረሰን!!Happy Chris...
07/01/2024

ለመላው የክርስትና እምነትን ተከታዮች ፣ የገፃችን ተከታዮች እንኳን ለዓለም መድሀኒት ለሆነው ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ/አደረሰን!!

Happy Christmas🌲🌲

 #ዲላ ኢትዮጵያ ከሶማሌ ላንድ ጋር የባሕር በር ለማግኘት የተፈራረመችው ሥምምነት አስመልክተው ህዝቡ በዲላ ከተማ አደባባይ ወጥቶ ደስታቸውን ገልጸዋል።
01/01/2024

#ዲላ ኢትዮጵያ ከሶማሌ ላንድ ጋር የባሕር በር ለማግኘት የተፈራረመችው ሥምምነት አስመልክተው ህዝቡ በዲላ ከተማ አደባባይ ወጥቶ ደስታቸውን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ከሶማሌ ላንድ ጋር የባሕር በር ለማግኘት የተፈራረመችው ሥምምነት አስመልክተው ህዝቡ በወላይታ ሶዶ ከተማ አደባባይ ወጥቶ ደስታቸውን ገልጸዋል።
01/01/2024

ኢትዮጵያ ከሶማሌ ላንድ ጋር የባሕር በር ለማግኘት የተፈራረመችው ሥምምነት አስመልክተው ህዝቡ በወላይታ ሶዶ ከተማ አደባባይ ወጥቶ ደስታቸውን ገልጸዋል።

You did it my hero!!
01/01/2024

You did it my hero!!

ቅኗ እህታችን ለታካሚዉ ልጃችን አለባቸው ተስፋዬ በንግድ ባንክ አካውንታቸው 10,000 ሺ ብር ገቢ አድርጋለች ተባረክልን ለሎች ደጋግ ወንድምና እህቶች የሚትችሉትን ታደርጉ ዘንድ ተማጽኖችን ...
31/12/2023

ቅኗ እህታችን ለታካሚዉ ልጃችን አለባቸው ተስፋዬ በንግድ ባንክ አካውንታቸው 10,000 ሺ ብር ገቢ አድርጋለች ተባረክልን ለሎች ደጋግ ወንድምና እህቶች የሚትችሉትን ታደርጉ ዘንድ ተማጽኖችን ጽኑ ነዉ።

ዉድ የfb ተጠቃሚዎች በገንዘብ እንኳ መረዳት ባንችልም share በማድረግ መርዳት ለሚችሉ ወገኖች እናድርስ።

በወጣ ይተካ ብለናል🙏🙏

 😢ይህ ከታች በፎቶግራፍ የምታየው ህፃን  #አለባቸው ተስፋዬ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በባስኬቶ ዞን የዶኮ ጨሬ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆን በግንባሩ ላይ ባልታሰበ ሁኔታ በተፈጠረው ከባድ ቁስል በተለያ...
31/12/2023

😢

ይህ ከታች በፎቶግራፍ የምታየው ህፃን #አለባቸው ተስፋዬ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በባስኬቶ ዞን የዶኮ ጨሬ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆን በግንባሩ ላይ ባልታሰበ ሁኔታ በተፈጠረው ከባድ ቁስል በተለያዩ ከፍተኛ ሆስፒታሎች ቢያሳክሙም በሽታው እየተባባሰ አሁን ላይ ወደ አዲስ አበባ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሪፈር በመታዘዙ ቤተሰቦቹ በሕክምና ገንዘባቸውን እና ንብረታቸውን ጨርሰው አሁን ላይ በእግዚአብሔር ስም ልጄን እንድትረዱልኝ ስል የእርዳታ ጥሪያቸውን አቅርበዋል ።

በውጭም ሆነ በሀገር ውስጥም ያላችሁ ቅን ኢትዮጵያዊያን በርካቶች በእናንተ እርዳታና ድጋፍ ታክመው፣ ተረድተው የተሻሉ እንዳሉ ሁሉ ይህን ልጅ አቅማችሁ በፈቀደው ልክ በመደገፍ እንድትታደጉልኝ ስል እማጸናለሁ ለመርዳት ለምትፈልጉ:-
1ኛ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቁጥር 1000596625553(ተስፋዬ ገታቸዉ ፃኖ)
2ኛ. በስልክ 0920369310/0949778637.
3ኛ. Share በማድረግ ለሎች እንዲደርስላቸው እናድርግ እና በፀሎታቸው እንድታስቡ
50 ሎሚ ለአንድ ሰዉ ሸክም ለ50 ሰዉ ገጥ ነዉና ።

  Music is lodging!Misker Mindaye &Tilaye Abayneh♥
29/12/2023

Music is lodging!

Misker Mindaye &Tilaye Abayneh♥

መርቁልኝ እስት አባታችንን🙏🙏me፦ live long!
27/12/2023

መርቁልኝ እስት አባታችንን🙏🙏

me፦ live long!

  ለሾልኣ ካሻ በዓላችን በሰላም አደረሳችሁ!!
25/12/2023

ለሾልኣ ካሻ በዓላችን በሰላም አደረሳችሁ!!

           👉Oneሾልኣ በዓመት አንድ ጊዜ የሚከበር ባህላዊ እሴት ሲሆን ካሻ ደግሞ በጾስታ ውስጥ የሚከበር የጎሳው የአምልኮ ስርዓት ነው። ምርት በባስኬት ብሔረሰብ ሲደርስ የሾልኣ ካሽ...
24/12/2023

👉One
ሾልኣ በዓመት አንድ ጊዜ የሚከበር ባህላዊ እሴት ሲሆን ካሻ ደግሞ በጾስታ ውስጥ የሚከበር የጎሳው የአምልኮ ስርዓት ነው። ምርት በባስኬት ብሔረሰብ ሲደርስ የሾልኣ ካሽ ሥኔ-ስርዓት ሳይፈጸም አይቀመስም። በመሆኑም የጎሳ መሪው ካቲ፣ ዳና እና ጉዳ ከሁሉም ጎሳ አባላት የሚያመጡላቸውን የምርት ጫፍ ‘ቡሃ’ ካቲው በራሱ ምርት ላይ ጨምሮ ‘ሾልኣ’ ያዘጋጃል። ‘ቡሃ’ በጎሳ አባላት የሚቀርብ የጎሳ አባላት የእህል ስጦታ ነው። የሚሰጠውም ለጎሳው መሪ ለካቲ ነው። ይህም ለሾልኣ ከበራ የሚዘጋጅ ግብዓት ይሆናል።

#ሾልኣ የሚያዘጋጁት በካቲው ቤት ሲሆን የጎሳው አባላት ወጣቶች በዝግጅቱ ላይ ይሳተፋሉ። ሴቶች መካከል ደግሞ የወር አበባ ያላዩ ልጃገረድ ሴቶች የሚዘጋጁ ሲሆን በወንዶችም በኩል ጎረምሳዎች ተሳታፊ ናቸው።

#ሾልኣ’ የጎሳው አጠቃላይ ምርት ተሰብስቦ ለ‘ካሻ’ የሚሰናዳበት ሂዴት ነው። ይህን ሾልኣ ካቲው በራሱ ቤት አቅራቢያ ሲያዘጋጅ የጎሳው መሪዎች አንዱ የሆነው ጉዳ የበዓሉን ዝግጅት ብቅል በምርቃት ስነስርዓት ያስጀምራል። ይህ የመጀመሪያውን ምርቃት የሚሰጠው ጉዳ ለበዓሉ ዝግጅት በተለይ ለሾልኣ ድግስ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ዕለት ነው። ሾልኣ ድግስ ዝግጅት ልክ በፌስቲቫል ሂዴት ስር የሚካተት ነው። በሾልኣ ድግስ ላይ ባህላዊ ሙዚቃዎችን ይጫወታሉ። የተለያዩ ምግቦች ቀርበው ለምስጋናው #ካሻ’ ስርኣት ይሰናዳሉ።
ሾልኣ ድግስ ተደግሶ በጾስታ ውስጥ ምስጋናው ስርዓት ካሻ ለካቲ በጾይታን አማካኘነት በጉዳ እንድሁም በዳናዎች ብቻ መስዋዕት ቀርቦ ለአምላክ ጾሳ በጾስታ ደን ውስጥ ምስጋና ከቀረበ በኋላ ድግሱ ሾላኣ ምግብና መጠጥ
ከምስጋናው ካሻ በኋላ የበዓሉ ከበራ ይከናወናል።

በመሆኑም አብረው የሚሄዱ የምስጋና ስርዓቱ ጅምር እና የከበራው ቀን ሁኔቶች ናቸው። ሁለቱም አይነጣጠሉም። ሾልኣ ሳይኖር ካሻ የለም። ሾልኣ በዓመት አንድ ጊዜ ምርት ሲደርስ በካቲው ቤት ብቻ ይከበራል። ካሻ በጾስታ ውስጥ ይከናወናል። ሾልኣ ድግስ በመሆኑ በካቲው ደጅ ላይ የደስታ ስርዓት ይሆናል። በሾልኣ ከበራ ቀን ካሻን የጎሳዎች መሪ ብቻ የሆኑት ካቲ፤ጉዳ እና ዳና በጎሳው የጋራ ጾስታ ውስጥ ያከናውናሉ።

#ካሻ በሌሎች ቀኖች በግለሰብ ኮራ ጾስታ ደኖች ውስጥ ለተለያዩ ዝግጅቶችም ሊያከናውኑ ይችላሉ። ልዩነቱ ቡሃ ቀርቦ ሾልኣ ተጠምቆ የሚደረገው ካሻ በጎሳ መሪዎች ብቻ ሲሆን በዓመት ደማቅ ከበራ ይሆናል።
ከዚህ በተጨማሪ የስያስፈልግ ጊዜ (ሰው ሲታመም፤ ሌሎች ምርቶች በቤተሰብ ደረጃ የሚቀመሱ ሲደርሱ)፤ ሰው ሲሞት፤ህልም ሲታይ የሚከበሩ የካሻ ዓይነቶች (Occasional rituals ) የስያስፈልግ ጊዜ ካሻዎች አሉ። ነገር ግን እነዚህ በቤተሰብ ደረጃ ሊያልቁ ይችላሉ። የሾልኣ ካሻ ስርዓት ደረጃ ግን አይስተካከሉም።

▶ቀጣይ በለሎች ተያያዥ ጉዳዮች እስክንገናኝ ሰላም ቆዩልን።

▶ የምስጋና በዓል ለሆነው ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ!!

ጥቂት ስለ ጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በኮንታ ዞንና በዳውሮ ዞን መካከል የሚገኝ እና በዕምቅ የተፈጥሮ ሀብት የታደለ ነ...
21/12/2023

ጥቂት ስለ ጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ

የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በኮንታ ዞንና በዳውሮ ዞን መካከል የሚገኝ እና በዕምቅ የተፈጥሮ ሀብት የታደለ ነው፡፡

ብሔራዊ ፓርኩ በ1997 ዓ.ም በኮንታና በዳውሮ ህዝቦችና አስተዳደር አካላት ጥያቄና ተሳትፎ መሰረት በብሄራዊ ፓርክ ደረጃ የተቋቋመ ሲሆን÷ ፓርኩ የሚያካልለው የቆዳ ስፋት 1 ሺህ 410 ካሬ ኪሎ ሜትር ስኩዌር ነው፡፡

ፓርኩ በመካከለኛው ኦሞ ሸለቆ ውስጥም የሚገኝ እና ከአዲስ አበባ በ475 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል።

ፓርኩ የግዙፉ የአፍሪካ ዝሆን መኖሪያም ሲሆን በውስጡ ከ800 በላይ የሚሆኑ ዝሆንና ከ5 ሺህ በላይ ጎሽ የሚገኙበት መሆኑ ፓርኩን ልዩ ያደርገዋል፡፡

በተጨማሪም 40 ትላልቅና መካከለኛ አጥቢ እንዲሁም 18 ትናንሽ አጥቢ የዱር እንስሳት ዝሪያዎች ይገኛሉ።

በጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ እንደ አጥቢዎቹ ሁሉ የበርካታ የአዕዋፋት ዝርያዎች መኖሪያም ጭምር ነው፡፡

እስካሁን በተጠናው ውስን ጥናት ብቻ 137 የአዕዋፍ ዝርያዎች የተለዩ ሲሆን÷ ከእነዚህም ውስጥ 6ቱ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ናቸው፡፡

ፓርኩ በብዙ መልኩ የተፈጥሮ ሀብቱ የተጠበቀ ፓርክ ነው ያስባለው የእጽዋት ስብጥሩና ደኑ ነው፡፡

እንዲሁም 106 እንጨታማ የእጽዋት ዝሪያዎች የሚገኝበት ሲሆን÷ ከእነዚህ ውስጥ ስድስቱ የእጽዋት ዝርያዎች በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ናቸው፡፡

በተጨማሪም በውስጡ ከሚገኙ የዱር ዕፅዋት ዝሪያዎች መካከል ዝንጅብል፣ ቡና፣ ኮረሪማ፣ እንሰት፣ እጣንና የጌሾ ዝርያዎች ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡

በፓርኩ ውስጥ ባሄ፣ ቡሎ፣ ሺታ፣ ቆቃ፣ ከሪቤላና ጮፎሬ የተሰኙ ስድስት አስደናቂና የጎብኚን ቀልብ የሚስቡ ሐይቆች አሉ።

በብሔራዊ ፓርክ ውስጥ ከሚገኙ ሐይቆች በአንዱ ብርቅዬ ወርቃማ የዓሳ ዝርያ የተገኘ ሲሆን÷ በዓለም ሊቃውንት እውቅና አግኝቶ በሳይንሳዊ ስሙ ጋራ ጨበራ በመባልም ይጠራል፡፡

ሌላኛው ከብሔራዊ ፓርኩ ገፀበረከቶች መካከል ለአብነት ፏፏቴዎች፣ ፍልውሃዎችና የማዕድን ውሃዎች የሚጠቀሱ መሆናቸውን የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

ብሔራዊ ፓርኩ በአሁኑ ሰዓት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነት የተጀመረውና ከ2 ቀናት በኋላ የሚመረቀው የገበታ ለሀገር ኮይሻ ፕሮጀክት አካል የሆነው የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ ክላስተር "የዝሆን ዳና ሎጅ" ፕሮጀክትን ይዟል።

ፕሮጀክቱ ቱሪስቶች ብዙም ሳይጉላሉና ሳይለፉ በቀላሉ ጎብኝተው እንዲመለሱ ምቹ ሁኔታ ከመፍጠሩም ባለፈ ፓርኩን በተገቢው ሁኔታ ለማስተዳደርና የዱር እንስሳትን በቅርበት ለመከታተልና ለመጠበቅ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል ነው የተባለው፡፡

ይህ ብሄራዊ ፓርክ በኮንታ እና በዳውሮ ህዝብ ፍላጎት እንደተቋቋመ ሁሉ በጥበቃ ሂደትም ህዝቡ ከፍተኛ ዋጋ በመክፈል ብሄራዊ ፓርኩን ከተለያዩ ጥፋቶች በመታደግ መልካም ዝና እንዲኖረው አድርገውታል።

ለመጀመሪያ ጊዜ በ2015 ዓ.ም በላስካ ኮ/ኢ/ኮሌጅ ደረጃ የተከበረዉ    ክብረ በዓል በኮሌጃችን    ት/ት  ክፍል በ2016 ዓ.ም እንድከፈት እንደ ዋነኛ መስፈርት ለምመለከተዉ ፍቃድ ሰጭ ...
19/12/2023

ለመጀመሪያ ጊዜ በ2015 ዓ.ም በላስካ ኮ/ኢ/ኮሌጅ ደረጃ የተከበረዉ ክብረ በዓል በኮሌጃችን ት/ት ክፍል በ2016 ዓ.ም እንድከፈት እንደ ዋነኛ መስፈርት ለምመለከተዉ ፍቃድ ሰጭ አካል ልያቀርብ መሆኑን ኮሌጁ አሳወቀ፡፡

ኮሌጁም በቅጥር ጊቢ ዉስጥ 2ኛዉን ክብረ በዓል ከባላባቶች፣ ከዞኑ እና ከከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች፣ ምሁራንና ታዋቅ ግለሰቦች ጋር በጋራ #ቅዳሜ 13/04/2016 ዓ.ም ለማክበር ቅድሜ ዝግጅቶቱን ማጠናቀቁን ኮሌጁ እያሳወቀ

#እንኳን ለዓመታዊ የምስጋና በዓል ዋዜማ አደረሳችሁ በማለት ኮሌጁ መልካም ምኞቱን እየገለጸ #ከሰኞ ታህሳስ 8/2016 ዓ.ም ጀምሮ በወጣዉ ማስታወቂያ መሰረት ሰልጣኞች ምዝገባ በመመዝገብ የሙያ ባለቤት እንድትሆኑ ጭምር ኮሌጁ ያሳስባል፡፡

#የ2015 ዓ.ም ክብረ በዓል የፎቶ ማስታወሻ

ላስካ ኮ/ኢ/ኮሌጅ
ታህሳስ 2016 ዓ.ም

የባስኬቶ ዞን አስተዳደር ከፋን ኢትዮጵያ ትሬዲንግ ጋር በመተባበር "ሾልአ_ካሻ" በዓልን ምክንያት በማድረግ 8 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ ልካሄድ ነው።ላስካ ታ...
18/12/2023

የባስኬቶ ዞን አስተዳደር ከፋን ኢትዮጵያ ትሬዲንግ ጋር በመተባበር "ሾልአ_ካሻ" በዓልን ምክንያት በማድረግ 8 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ ልካሄድ ነው።

ላስካ ታህሳስ 8/2016 ዓ.ም (ባስኬቶ ዞን ኮሙኒኬሽን) የባስኬቶ ዞን አስተዳደር ከፋን ኢትዮጵያ ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ጋር በመተባበር የባስኬት ብሔረሰብ ምስጋና በዓል ለሆነው "ሾልአ_ካሻ" በዓልን ምክንያት በማድረግ 8 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ ይካሄዳል።

የፋን_ኢትዮጵያ መስራችና ስራአስኪያጅ አትሌት ወ/ሪት ፋንቱ ሜግሶ በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ ተገኝተው ከባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳደሪ ኢንጂነር ፍሬው ፍሻለው ጋር ውይይት አድርገዋል።

የባስኬቶ ዞን አስተዳደሪ ኢንጂነር ፍሬው ወደ አከባቢያችን ለመምጣት የመንገዱ ችግር አሳሳቢ ብሆንም ይህ የህዝቡ ችግር የእኔ ችግር ነው ብለው ብዙ ያልተዘመረለትና ያልተዘፈነለት አከባቢን ለማስተዋወቅ እስከዚህ ድረስ በመምጣታቸው በዞኑ መንግስትና ህዝብ ስም ምስጋና አቅርበዋል።

የፋን ኢትዮጵያ መስራችና ስራአስኪያጅ አትሌት ወ/ሪት ፋንቱ ሜግሶ የእኛ ዋና ዓላማችን ብዙ ያልተዘመረላቸውና ያልተዘፈነላቸው አከባቢዎችን የማስተዋወቅ በመሆኑ እስከዚህ ድረስ በመምጣቴ ልዩ ደስታ ይሰማኛል ብለዋል።

አትሌት ወሪት ፋንቱ የፋን ኢትዮጵያ መስራችና ስራአስኪያጅ የእኛ ዋና ዓላማ "ትንሽ ጥላቻ ትልቁን ፍቅር አያጠፋም፣ ለኢትዮጵያ ለውጥ አብረን እንሩጥ" በሚል በተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞች የተደረገና በባስኬቶ ዞን የባስኬት ብሔረሰብ የምስጋና በዓል የሆነው "ሾልኣ ካሻ" ምክንያት በማድረግ ለዓለም ህዝብ ለማስተዋወቅ የታለመ መሆኑን ገልጸዋል።

በዕለቱ ለሚደረገው 8 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫና ለባስኬት ብሔረሰብ የምስጋና በዓል "ሾልኣ ካሻ" ድምቀት የሚሆኑ ትሸርቶች ከ10,000 በላይ የተዘጋጀ ስሆን የአንዱ ዋጋ 350 ብር መሆኑ ታውቋል።

የጎዳና ላይ ሩጫና ለባስኬት ብሔረሰብ የምስጋና በዓል "ሾልኣ ካሻ" በዓልን ለዓለም ህዝብ ለማስተዋወቅ በዕለቱ ከ12 በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ ሚድያዎች ይገኛሉ።

በመጨረሻም የባስኬቶ ዞን አስተዳደር ከፋን ኢትዮጵያ መስራችና ስራአስኪያጅ አትሌት ወ/ሪት ፋንቱ ሜግሶ ጋር ከፋን ኢትዮጵያ ትሬዲንግ በመተባበር "ሾልአ_ካሻ" በዓልን ምክንያት በማድረግ 8 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በጋራ ለማስኬድ የተዘጋጀ የውል ሰነድ ተፈራርመዋል።

እንኳን የባስኬት ብሔረሰብ የምስጋና በዓል ለሆነው "ለሾልአ ካሻ" ዋዜማ አደረሳችሁ አደረሰን!!

 #ገመዳ፦ "በውጭ ሀገር እንደምናውቀው አትሌቶች ቅንጡ Super Car የሚባሉትን መኪናዎች ነው የሚያሽከረክሩት ቀነኒስ?" #ቀነኒሳ፦ "እውነት ለመናገር በሀገራችን አለኝ ብለህ ዘመናዊና ቅን...
18/12/2023

#ገመዳ፦ "በውጭ ሀገር እንደምናውቀው አትሌቶች ቅንጡ Super Car የሚባሉትን መኪናዎች ነው የሚያሽከረክሩት ቀነኒስ?"

#ቀነኒሳ፦ "እውነት ለመናገር በሀገራችን አለኝ ብለህ ዘመናዊና ቅንጡ መኪና ይዘህ ለመውጣት ህሊናህ አይፈቅድም። ምክኒያቱም ከቤትህ ወጥተህ እስክትመለስ በየመንገዱ ተቸግሮ ማደሪያና የሚበላው አጥቶ የሚለምንህ አለ።"

"በዚህ ሁሉ ውስጥ አንተ አለኝ ብለህ በዚህ ህዝብ ላይ ልታይ ልታይ ማለት ምን ያደርጋል? አንድ አባባል አለ ድሀ በበዛባት ሀገር ሀብታምም ደሀ ነው። በየመንገዱ የምታየው ሁሉ እናትህ፣ አባትህ እህትህ እና ወንድምህ ነው።"

"ታዲያ ማን ላይ ነው ይህን የምታደርገው??"

የሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀAMN-ታህሳስ 07/2016 ዓ.ም በ17ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተጠባቂ የነበረው እና ሊቨርፑልን ከማንቸስተር ዩናይትድን ያገናኘው የሳ...
17/12/2023

የሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ

AMN-ታህሳስ 07/2016 ዓ.ም

በ17ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተጠባቂ የነበረው እና ሊቨርፑልን ከማንቸስተር ዩናይትድን ያገናኘው የሳምንቱ ጨዋታ ያለምንም ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቅቋል።

አንፊልድ ላይ ማንቸስተር ዩናይትድን ያስተናገደው ሊቨርፑል ነጥብ ተጋርቶ ወጥቷል።

ውጤቱን ተከትሎ ሊቨርፑል ባደረጋቸው 17 ጨዋታዎች 38 ነጥብ በመሰብሰብ በሊጉ 2ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ፤ 28 ነጥብ የሰበሰበው ማንቸስተር ዩናይትድ 7ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን አርሰናል በ39 ነጥብ መምራት ችሏል።

12 ቻይናውያን የጋብቻ ስነስርዓት እያከናወኑ ነው今天,12位中國人在友​​誼廣場舉行婚禮   | በአዲስ አበባ ወዳጅነት አደባባይ 12 ቻይናውያን የጋብቻ ስነስርዓት እያከናወኑ ነው። መልካም ጋብቻ !...
15/12/2023

12 ቻይናውያን የጋብቻ ስነስርዓት እያከናወኑ ነው
今天,12位中國人在友​​誼廣場舉行婚禮

| በአዲስ አበባ ወዳጅነት አደባባይ 12 ቻይናውያን የጋብቻ ስነስርዓት እያከናወኑ ነው።

መልካም ጋብቻ !

ኢትዮጵያችን በዉጭ ዜጎች ተመራጭነቷ እየጨመረ ነዉ!!

 #ብንሄድ ይሻለናል ለሚሉ ሰዎች መሄጃ  ማሽን መጥቷል --------------------------------------------------------------------እነሆ የኔዘርላንድ ሳይንቲስ...
13/12/2023

#ብንሄድ ይሻለናል ለሚሉ ሰዎች መሄጃ ማሽን መጥቷል
--------------------------------------------------------------------
እነሆ የኔዘርላንድ ሳይንቲስቶች ለአለም ህዝብ ጌጥ
ብለው ያለ ስቃይ የሚገድል ቴክኖሎጂ አበርክተዋል።
በ3D Printing እና AI መሳሪያ ሲሆን ይህ መሳሪያ ራሱን ለማጥፋት የሚፈልግ ሰው ያለምንም ስቃይ ከ1 ደቂቃ ባነሰ ሰከንዶች ፀጥ የሚያደርግ መሰሪያ በጣም ምቹና ተመራጭ መሳሪያ እንደሆነ ዩሮኒውስ ዘግቧል ። ይህ #ሰርኮ የሚል ስያሜ የተሰጠው የራስን መግደያ መሳሪያ በአሁን ሰአት ራስን ማጥፋት በማይከለክሉ ሀገራት ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን። ባለፈው አንድ አመት በጀርመን ብቻ (ብንሄድ ይሻላል) ብለው ተመዝግበው ከፍለው በዚህ መሳሪያ ራሳቸውን ያጠፉ ሰዎች ብዛት 1,300 መሆኑ ተገልጿል

የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ የነበረዉ  ታዬ ደንደአ በህግ ቁጥጥር ሥር ዋለ*******************(ኢ ፕ ድ) የፀጥታና ደኀንነት የጋራ ግብረ ኃይል ለኢፕድ በላከዉ መግለጫ እንዳስታወቀዉ፤ ...
12/12/2023

የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ የነበረዉ ታዬ ደንደአ በህግ ቁጥጥር ሥር ዋለ
*******************
(ኢ ፕ ድ)

የፀጥታና ደኀንነት የጋራ ግብረ ኃይል ለኢፕድ በላከዉ መግለጫ እንዳስታወቀዉ፤ በህግ ቁጥጥር ስር የዋለዉ የሰላም ሚንስትር ዴኤታ የነበረዉ ታየ ደንደአ፥ ከለውጡ በፊት የኦነግ አባል የነበረና በእስር ቤት የቆየ ሲሆን፤ የለውጡ መንግስት ባደረገለት ምህረት ከማረሚያ ቤት ተለቆ በተሰጠዉ እድል በተለያዪ የክልልና የፌደራል መንግስት የሀላፊነት ቦታዎች ላይ ሲሰራ ነበር ብሏል።

ይሁን እንጂ ታዬ ደንደአ ከህዝብና ከመንግስት የተሰጠዉን ሀላፊነት በተለይም ደግሞ የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ ሆኖ ሰላምን ለማስፈን መሥራት ሲገባዉ፤ በተቃራኒዉ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከሚንቀሳቀሱ ፀረሰላም ኃይሎች ጋር በመተሳሰር ለጥፋት ተልዕኮ በህቡዕ ሲሰራ ተደርሶበታል ብሏል መግለጫዉ።

መግለጫዉ አያይዞም በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች በንፁሃን ዜጎች ላይ ሲፈፀሙ በነበሩ የሽብር ተግባራት በተለይም ደግሞ ከእገታ ጋር በተያያዘ እጁ እንደአለበት የተደረሰበት መሆኑን አስታዉቋል።

ይህንን እኩይ ዓላማ ሲያሪምድ የነበረዉ ተጠርጣሪ ታየ ደንደአ፤ በመንግስት ቁጥጥር ስር ሊዉል እንደሚችል ሲገምት ታጋይ ለመምሰል በራሱና በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገጾች አፍራሽና ፀረ ሰላም ፅሁፎችን፣ ንግግሮችንና መግላጫዎችን በማን አለብኝነት ሲያስተላልፍና ሲሰጥ ቢቆይም ከተጠያቂነት ማምለጥ ባለመቻሉ በጋራ ግብረ ኃይሉ በቁጥጥር ስር መዋሉን መግለጫዉ አመልክቷል።

በተጨማሪ የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መግለጫ እንደገለፀዉ፥ ታዬ ደንደአ መንግስታዊ ኃላፊነቱን ተቀብሎ እየሰራ በነበረበት ወቅት መንግስታዊና የፓርቲ መዋቅሩን በሴራ ለመናድ በህቡእ እንቅስቃሴ ሲያደርግ መቆየቱን በመረዳት ያላሰለሰ ጥናትና ክትትል ሲደረግበት ነበር ብሏል፡፡

በተደረገው ክትትልም ታየ ደንደአ ከኦነግ ሸኔ አመራሮችና በሽብር ወንጀል ከተጠረጠሩ ጽንፈኛ ኃይሎች ጋር ትስስር በመፍጠር መንግስትን በአመጽ፣ በሽብርና፣ በትጥቅ ትግል ለመጣል ሲያሴር እንደ ተደረሰበት መግለጫዉ ጠቁሟል፡፡

ተጠርጣሪዉ ታዬ ደንደአ በህግ ቁጥጥር ሥር በዋለበት ወቅትም በመኖሪያ ቤቱ ዉስጥ በተደረገ ፍተሻ፤ ግለሰቡ በህቡዕ ለሚያደርገዉ ፀረ-ሰላም እንቅስቃሴ ሲገለገልባቸዉ የነበሩ የተለያዩ 9 ሞባይሎች፣ 4 ላፕቶፖች፣ 3 አይፖዶች፣ በርካታ ፍላሾች፣ 4 የተለያዩ ተሸከርካሪ ሰሌዳዎችና ልዩ ልዩ የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች፣ ክላሽንኮቭ ጠመንጃና ሽጉጦች ከመሰል ጥይቶች ጋር እንዲሁም የኦነግ ሸኔ አርማዎችና በተለያዩ ግለሰቦች ስም የተዘጋጁ የኦነግ ሸኔ መታወቂያዎች፣ ሰነዶችና ማስታወሻዎች እንደተገኙ ግብረ-ኃይሉ በላከው መግለጫ አረጋግጧል፡፡

ከዚህም ባሻገር በብርበራ ወቅት በመኖሪያ ቤት ውስጥ በሶስት መታወቂያዎች የሚጠቀም አንድ የኦነግ ሸኔ አባል ተደብቆ መገኘቱንና በቁጥጥር ሥር መዋሉንም መግለጫዉ ጨምሮ ገልጿል።

ታየ ደንደአ በተመደበበት ከፍተኛ የመንግስት ስልጣን ላይ ሆነ በተደጋጋሚ መንግስትን ገዳይና ጨፍጫፊ እያለ ሲወቅስ የሚደመጥ ቢሆንም፤ በተግባር ግን ከሽብርተኞች፣ ጽንፈኛችና ነፍሰ ገዳዮች ጋር የጥፋት ትስስር የነበረው ራሱ መሆኑ በተደረገ ክትትል መረጋገጡን የጋራ ግብረ ኃይሉ መግለጫ ጠቁሟል።

በመጨረሻም በመንግስትና በፖርቲ መዋቅር ዉስጥ ሆነዉ በተመሳሳይ እኩይ ዓላማ በተሰማሩ አካላት ላይ በጥናት የተመሰረተ ጥብቅ ክትትል የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል እያደረገባቸዉ እንደሚገኝና እንደአስፈላጊነቱ የሚወሰዱ ህጋዊ እርምጃዎችን

በወንዝ ዳርቻ ፎቶ እየተነሱ የነበሩ የወላይታ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተንሸራተው ወንዝ ውስጥ ገብተው ህይወታቸው አለፈቅዳሜ ህዳር 29 ቀን 2016 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ ሁምቦ እየተባለ በሚ...
10/12/2023

በወንዝ ዳርቻ ፎቶ እየተነሱ የነበሩ የወላይታ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተንሸራተው ወንዝ ውስጥ ገብተው ህይወታቸው አለፈ

ቅዳሜ ህዳር 29 ቀን 2016 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ ሁምቦ እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በሚገኝ ወንዝ ዉስጥ ሁለት የወላይታ ዩኒቨርስቲ የ3 ኛ ዓመት ተማሪዎች በወንዙ ዳርቻ ፎቶግራፍ በመነሳት ላይ ሳሉ ተንሸራተዉ ወደወንዙ በመግባታቸዉ የሁለቱም ተማሪዎች ህይወት አልፏአል።

የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ለአዲስ አበባ ከተማ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በጠየቀዉ ድጋፍ መሰረት የኮሚሽኑ ጠላቂ ዋናተኞች የወጣቶቹን አስከሬን ዛሬ ህዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም አዉጥተዉ ማስረከባቸውን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት ባለሞያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለፋስት መረጃ ነግሯል።

ተማሪዎዎችና ወጣቶች ፎቶ ግራፍ ለመነሳትና ለመዝናናት በሚል ወንዝ አካባቢ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ መሰል አደጋዎች የሚያጋጥሙ በመሆኑ ወንዝ አካባቢና የመዋኛ ስፍራዎች አካባቢ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ ኮሚሽን መ/ቤቱ አሳስበዋል።

Address

Sikela
Arba Mintch

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Basket News Network BNN posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share