Siltie Media Network

Siltie Media Network ትክክለኛ መረጃዎችን ከትክክለኛ ምንጮች ለህዝብ ማድረስ
(1)

📌 ኡስታዝ አቡሀይደር(ሳዲቅ መሀመድ) መኪናውን ተረክቧል።📌 ለድርጅቱ ማቋቋሚያ የተሰበሰበው ገንዘብም 12 ሚሊዮን 800ሺህ ብር ደርሷል።🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥Ustaaz Abu Haydar(...
15/11/2022

📌 ኡስታዝ አቡሀይደር(ሳዲቅ መሀመድ) መኪናውን ተረክቧል።
📌 ለድርጅቱ ማቋቋሚያ የተሰበሰበው ገንዘብም 12 ሚሊዮን 800ሺህ ብር ደርሷል።
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
Ustaaz Abu Haydar(Saadiiq Mohammed) konkolaataan harka isaa galeera. Qarshiin dhabbata daw'aa isaatiif walitti qabamees miliyoona 12 fi kumma 800 gaheera.

 #አው+አሽ✍️ቼክ አንታ ዲዮፕ፣ ሴንጎር፣ ኤሚ ሲዛር፣ አሊዮን፣ ኢያን ካሩ፣ ፊንች፣ ሚድልተን፣ ኢቫን ቫን ሰርቲማ፣ ጆን ክላርክ፣ ኦቤንግ፣ ጂፈርሰን፣ ቤን ጆሓና፣ ቻንስለር ዊሊያምስ...ሌሎ...
14/11/2022

#አው+አሽ

✍️ቼክ አንታ ዲዮፕ፣ ሴንጎር፣ ኤሚ ሲዛር፣ አሊዮን፣ ኢያን ካሩ፣ ፊንች፣ ሚድልተን፣ ኢቫን ቫን ሰርቲማ፣ ጆን ክላርክ፣ ኦቤንግ፣ ጂፈርሰን፣ ቤን ጆሓና፣ ቻንስለር ዊሊያምስ...ሌሎችም በርካታ መሰል ምሁራን በቅርብ ዘመን ተነስተው አካዳሚክ ትግል(Academic Struggle) በማድረግ ለዓለም አዲስ ዕይታ አበርክተዋል። እነኚህ ምሁራን ለዓለም ታሪክ አካዳሚዎች ባቀረቧቸው ተከታታይ ጥናታዊ ሥራዎቻቸው አፍሪካ ለአውሮፓ እና ለእስያ ስልጣኔና ባህል መነሻና እናት መሆኗን አውጀዋል። መጀመሪያ አከባቢ በአካዳሚክ ዘረኝነት ምክኒያት ሃሣባቸው እንደትርኪምርኪ ታይቶባቸው ነበር። ነገር ግን ያቀረቡት ጠንካራ ማስረጃ በዓለም ደረጃ በሌላ ማስረጃ ሊሻር ባለመቻሉ ቀስበቀስ አነጋጋሪ መሆን ጀመረ። ይህ የዓለምን ታሪክ ፍላጎታቸውን መሠረት አድርገው እንደገና አስተካክለው በመጻፍ ልቦለድ በማድረግ ላይ ለሚገኙ ወገኖች ራስ ምታት ሆነባቸው።

✍️ከላይ የተጠቀሱ ምሁራን አዳዲስ ማስረጃዎችን ፈልፍለው ይፋ በማውጣት ባደረጉት አካዳሚክ ትግል በርካታ ውጤቶችን አስመዝግበዋል። ከውጤቶቹም አንዱ እውነትን የሚሹ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ተመራማሪዎች ፊታቸውን ወደ አፍሪካ እንዲያዞሩ አድርገዋል።

✍️በዚህ ረገድ ፊታቸውን ወደ አፍሪካ ካዞሩ ታላላቅ ተመራማሪዎች መካከል አንዱ እወቁ የስነ-ልሳን፣ የታሪክና የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር የሆኑት ፕሮፌሰር ማርቲን ቤርናል ናቸው። ፕሮፌሰር ማርቲን ቤርናል የዓለምን ስልጣኔ ምንጭ ፍለጋ ከሮም ወደ ግሪክ ከግሪክ ወደ ጥቁር ግብጽ ከጥቁር ግብጽ ወደ አፍሪካ ቀንድ ኢትዮጵያ ሰንሰለቱን ጠብቀው እየፈለጉ መጥተው ስሩን ያገኙት ደቡብ ኢትዮጵያ አዋሽ ሸለቆ አከባቢ ነው። የአዋሽ ስልጣኔ የዓለም ስልጣኔ እናት ነው። ሴማዊ ቋንቋም ከብዙ ሺህ ዓመታት በፊት በዚሁ ደቡብ ኢትዮጵያ አከባቢ ይነገር እንደነበር ገልጸዋል። የደቡብ ኢትዮ-ሴማዊ ቋንቋ ለሰሜኑ ኢትዮ-ሴማዊ ቋንቋ አያት ነው በማለት የግዕዝ ቋንቋ ተወላጅ እንጂ ወላጅ አለመሆኑን ገልጸዋል። ይሄን ሃሣባቸውንም በዝነኛው "ብላክ አቴና" መጽሐፋቸው በካርታ አስደግፈው አብራርተዋል። በጥንቱ ዓለም ከአዋሽ የፈለቀ ስልጣኔ ወደ ተለያዩ የዓለም ክፍሎች ተሰራጭቷል።
የዋቢ መዘርዘር እና ተጨማሪ ማብራሪያ:- ቶጲያ መጽሐፍ ከገጽ 76-85

Nejashi Kedir Shamo

ብሄራዊ ጀግናችን...👌በተ.መ.ድ (UN) የኢትዮጵያ ተወካይ አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ በ2 ደቂቃ የሰጡት አስደናቂ መልስ… 🇪🇹 "እየሰማን ያለነው የሰላም መልእክት አይደለም። ተከታታይ ማስጠ...
30/10/2022

ብሄራዊ ጀግናችን...👌

በተ.መ.ድ (UN) የኢትዮጵያ ተወካይ አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ በ2 ደቂቃ የሰጡት አስደናቂ መልስ…

🇪🇹 "እየሰማን ያለነው የሰላም መልእክት አይደለም። ተከታታይ ማስጠንቀቂያዎችን ነው። ነገር ግን በርካታ የፖለቲካ ምስቅልቅሎችን ማለፍ እንደቻለች ኩሩ አፍሪካዊት ሀገር [የተባበሩት መንግሥታት] አባል ሀገራትን አንድ ነገር ማስታወስ እፈልጋለሁ።

በርካታ ችግሮቻችንን ተጋፍጠን እንዳለፍናቸው ዛሬም የገጠሙንን ችግሮች በእርግጠኝነት እንሻገራቸዋለን።

በአንዳንድ ኃያላን ሀገሮች ዐይን ፊት ልክ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት እንደሆነው [ኢትዮጵያውያን] አቅመቢስ መስለን እንታይ ይሆናል። ክቡር ሊቀመንበር አንድ ነገር ላረጋግጥልዎት እፈልጋለሁ።

የውስጣችን መንፈስ ጽኑእ ነው። የውስጣዊ መንፈሳችን ጥንካሬ ኢትዮጵያዊ ሆኖ ለመቆም ብቻ ሳይሆን ሰላማዊ ለመሆን እና ተግዳሮቶቻችንን ለመፍታት ጭምር ነው።

የ120 ሚሊዮን ሕዝባችንን ዕድል ለ200 ኤክስፐርቶች ልንተወው አንችልም። ይህንን ብዬ፤ ሁልጊዜም ቢሆን በጎ ሀሳብ ያላቸውን ተሳታፊዎች በደስታ የምንቀበል ሲሆን ሊያወግዙን እና ለሞት አሳልፈው ሊሰጡን ቀድመው የወሰኑትን ግን "የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር ይበላቸው" እላለሁ።

ስለዚህ እንደ [ኢትዮጽያ] መንግሥት ላረጋግጥላችሁ የምፈልገው ሁሉም የሰብአዊ መብት ጥሰት ላይ የተሳተፉትን ተጠያቂ እናደርጋቸዋለን። ይህንንም የምናደርገው የተወሰኑ ድርጅቶችን ወይንም ኤክስፐርቶችን ለማስደሰት ሳይሆን ለራሳችን መርኅ ስንል ነው።

ዘላቂ ሰላም መስፈን የሚችለው በሁሉም አካባቢዎች ለተሠሩ ወንጀሎች ተጠያቂነት እና ፍትህ ሲሰፍን ብቻ መሆኑን እንረዳለን። ነገር ግን ይህ በሀገሪቱ ባለቤትነት መመራት አለበት። አመሠግናለሁ ክቡር ሊቀመንበር"

🇪🇹የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ አምባሳደር ታየ አፅቀሥላሴ እድሜና ጤና ይስጦት🇪🇹

25/08/2022

ኤርትራ "ህወሓት" ኢትዮጵያ….!

ኤርትራ በተለይ ከ3 አመት ወዲህ አቅማቸውን በሰው ሀይል ፣ በቴክኖሎጂና በግብአት ካጠናከረቻቸው ተቋማቶቿ መካከል አየር ሀይሏ ተጠቃሽ ነው፡፡

አየር ሀይሏ 33 የተለያዩ ጀቶችና ወደ18 ሄሊኮፕተሮች ያሉት ሲሆን ፣ 13 አየር ማረፊያዎችም አሏት፡፡ በቅርቡ ከሩሲያ ጋር ባደረገችው ወታደራዊ ስምምነት መሠረት ከራሺያ ድሮኖችን ጨምሮ የተለያዩ ወታደራዊ መሳሪያዎችን ብሎም የስልጠና ድጋፍ አግኝታለች፡፡ የኤርትራ ወታደራዊ አየር ሀይል ያሉት ጀቶች ተዋጊና የልዩ ኦፕሬሽን ዘመናዊ ጀቶችን ያካትታሉ፡፡

ኤርትራ ካላት ከ 6 ሚሊየን በላይ የሚገመት ህዝብ ወደ 35 በመቶው ( ከ2 ሚሊየን በላይ) የሚሆነው ለግዳጅ ብቁ የሆነ ሀይል ሲሆን ከ25% በላይ (1.5 ሚሊየን በላይ) የሚሆነው ወታደራዊ ስልጠና የወሰደ በአብዛኛው ወጣት ሀይል ነው፡፡ በግንባር 175ሺህ የተሰለፈና 200ሺህ ደግሞ ተጠባባቂ ሀይል አላት፡፡

የባህር ሀይሏም ቢሆን ወደ22 የሚጠጉ ኑኩሌር መሸከም የሚችሉትን ጨምሮ ለውጊያ አገልግሎት የሚሰጡ ብሎም 18 የሚሆኑ ደግሞ ለቅኝት አገልግሎት የሚውሉ ጀልባዎችና መርከቦች ያሉት ነው፡፡

ምንም እንኳ የኤርትራ የጦር ሀይል አቅም ከአለም ሀገራት በ124ተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ቢሆንም በተለይ በሰው ሀይል ከአፍሪካ ከቀዳሚዎቹ ጥቂት ሀገራት ተርታ የሚመደብ ነው፡፡ የመረጃና ደህንነት ተቋሟም ጠንካራ የሚባል ነው፡፡

ፕሬዝደንት ኢሳያስ ከሰሞኑ ኤርትራ ላይ ተደጋጋሚ የማጥቃት ሙከራ አድርጎ ከፍተኛ ኪሳራን እያስተናገደ ያለውና የኤርትራ የምንጊዜም ባላንጣው አሸባሪው ትህነግ/ህወሓትን " ጦርነት መጀመር እንጂ መጨረስ ላይሳካለት በምዕራባውያን አጫፋሪነት ተገፋፍቶ የትግራይን ህዝብ ባያስጨርስ ይሻለዋል! >> ሲሉ ተሰምተዋል፡፡

ኤርትራ ከቀናት በፊት በሱዳን በኩል የኢትዮጵያን አየር ክልል በመጣስ ለአሸባሪው ትህነግ መሳሪያ የሚያቀብሉ 2 አውሮፕላኖችን መትታ መጣል ያልቻለችው ፥ የአየር ክልሉ የእርሷ ባለመሆኑ በኢትዮጵያ መንግሥት በኩል የሉአላዊነት ጥያቄ እንዳያስነሳ ከመስጋትና ከጊዜ ወደጊዜ እየተቀዛቀዘና እየሻከረ የመጣውን ከአራት ኪሎው ጠቅላይ ሚኒስቴር ጋር ያለውን ወዳጅነት ፈፅሞ የሚያደበዝዝ እንከል ሊፈጠር ይችላል ከሚል ስጋት ሊሆን እንደሚችል ቢታመንም ፥ ዞሮ ዞሮ ለህወሓት የሚደረግ ማንኛውም አይነት ድጋፍ የራሷን ህልውና ጭምር አደጋ ላይ የሚጥል በመሆኑ በሱዳን በኩል ያለውን ጉዳይ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በመነጋገር ያለማመንታት የቅንጅት ኦፕሬሽን መስራት ይጠበቅባታል፡፡

አሸባሪው ትህነግ ጦርነት ለመጀመር ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርግ ከሰነበተባቸው አምስት ዋና ዋና ግንባሮች መካከል ኤርትራን የሚጋብዘው የሽራሮው ግንባር አንዱ መሆኑ የሚታወስ ነው፡፡

ራይላ ኦዲንጋ በመግለጫቸው ምን አሉ ?የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር እና በወቅቱ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚደገፉት ራይላ ኦዲንጋ የምርጫ ውጤቱ ሕጋዊ ያልሆነ እና ተፈጻሚ የማይሆን ነው ብለዋል።...
16/08/2022

ራይላ ኦዲንጋ በመግለጫቸው ምን አሉ ?

የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር እና በወቅቱ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚደገፉት ራይላ ኦዲንጋ የምርጫ ውጤቱ ሕጋዊ ያልሆነ እና ተፈጻሚ የማይሆን ነው ብለዋል።

ኦዲንጋ በመግለጫቸው ፦

• ውጤቱን አልቀበልም ብለዋል።

• ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት እንደሚወስዱት ተናግረዋል።

• የኮሚሽኑን ዋና ሰብሰቢ ዋፉላ ቼቡካቲን " አምባገነን " ሲሉ በመጥራት ተችተዋቸዋል። ይፋ ያደረጉትንም ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ውጤት ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ አንቀበለውም ሲሉ ገልፀዋል።

• የኮሚሽኑ ዋና ሰብሳቢ የምርጫ ውጤቱን ይፋ ሲያደርጉ የአገሪቱን ሕገ-መንግሥት በመተላለፍ ትልቅ የሕግ ጥሰት ፈጽመዋል ብለዋል። በኮሚሽነሮች መካከል ልዩነት እያለ ዋፉላ ቼቡካቲ የምርጫ ውጤቱን ይፋ ማድረጋቸው ስህተት ነው ሲሉ ገልፀዋል።

NB. የኬንያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫን ያስፈጸመው ገለልተኛ የድንበር እና ምርጫ ኮሚሽን 7 ኮሚሽነሮች ያሉት ሲሆን ከእነዚህ መካከል 4ቱ በፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ውጤቱ አለመስማማታቸውን ትላንት መግለፃቸው ይታወሳል።

ከፍተኛ ደጋፊ ያላቸው ራይላ ኦዲንጋ የምርጫውን ውጤት አልቀበልም ማለታቸው በአገሪቱ ምርጫውን ተከትሎ ግጭት እንዲቀሰቀስ ሊያደርግ ይችላል የሚሉ ስጋቶች ከአሁኑ አይለዋል።

መረጃው ቢቢሲ የራይላን ኦዲንጋን መግለጫ ዋቢ አድርጎ ካዘጋጀው የተወሰደ ሲሆን ፎቶው ከNTV የቀጥታ ስርጭት የተወሰደ ነው።

13/08/2022
13/08/2022

ከአልጋው ማጠር ነው ወይ ከ ፍራሹ ማነስ ያልተገናኘነውI እስከዛሬ ድረስ🙄😋😋😏😏👇❤🌿🍀💚💚💚🖤

13/08/2022
Hi
12/08/2022

Hi

ምን እያላችሁ ነው???
12/08/2022

ምን እያላችሁ ነው???

ውበት ሲበዛ
12/08/2022

ውበት ሲበዛ

11/08/2022

አረ ስልጤዎች የት ናችሁ

ስልጤን የበላ ጅብ አልጮህ አለ እኮ!!

11/08/2022

ጉራጌ

የኛ

የልቤ ንግስት
11/08/2022

የልቤ ንግስት

በሬዱ
11/08/2022

በሬዱ

ከወደድኩትእምነት እና ፀናት በፍሊስጢን እናት  Media Network
10/08/2022

ከወደድኩት
እምነት እና ፀናት
በፍሊስጢን እናት

Media Network

የስልጤ ክልል ርዕሰ መዲና የሆነችው ወራቤ አመሻሽ ላይ በፎቶ📸 ላካ ከውብም በላይ ውብ የሆነች ከተማ ናት 📸📸ወራቤ📸📸 A BEAUTIFUL CITY WERABE
09/08/2022

የስልጤ ክልል ርዕሰ መዲና የሆነችው ወራቤ አመሻሽ ላይ በፎቶ📸 ላካ ከውብም በላይ ውብ የሆነች ከተማ ናት
📸📸ወራቤ📸📸

A BEAUTIFUL CITY WERABE

09/08/2022

እሱ:-በወሬ መሀል እስኪ ፎቶሽን ላኪልኝ
እሷ:-እፈራለሁ ምናልባት ፎቶዬን አይተህ ባተወደኝ
እሱ:-እኔ የውጭ ውበት ምንም አይመሰለኝም እኔ የምፈልገው የውስጥ ውበት ነው
እሷ:-ይሄ ፎቶ ላከችለት እሱ ፎቶውን ካየው ቀን ጀምሮ
ፎቶውን ባየ ቁጥር ብሎኩን እያነሳ እንደገና ብሎክ😂

09/08/2022

አምቤው በል ስልጤ

🌀✅ አስገራሚ የእንሰሳት እውነታዎች! ✅🌀1. ቀበሮ በሂወት ዘመኑ አንዴ ብቻ ነው ፍቅረኛ ሚኖረው። ምን አልባት ሚስቱ ከሞተች ቀሪ ሂወቱን ብቻውን ነው የሚያሳልፈው! ምስኪን ታማኝ!!2. የጂ...
27/07/2022

🌀✅ አስገራሚ የእንሰሳት እውነታዎች! ✅🌀

1. ቀበሮ በሂወት ዘመኑ አንዴ ብቻ ነው ፍቅረኛ ሚኖረው። ምን አልባት ሚስቱ ከሞተች ቀሪ ሂወቱን ብቻውን ነው የሚያሳልፈው! ምስኪን ታማኝ!!
2. የጂብ እድሜ ጣራ 80 ዓመት ነው!
3. አይጦች የራሳቸውን ያልሆነ ልጅ አጥብተው ያሳድጋሉ!
4. የወባ ትንኝ 47 ጥርሶች አላት!!!!
5. ፍየሎች ሴቷን ፋየል ለማማለል ሲሉ እርስበእርስ ይዋጋሉ!!!!!
6. ድመት በሂወት ዘመኗ እስከ 100 ግልገሎች መውለድ ትችላለች!!!!
7. እንደ ሰው ህልም ማየት ሚችለው አንስሳ ፈረስ ብቻ ነው!!!!
8. ዳክየ እንቁላል የምትጥለው ጧት ጧት ብቻ ነው!!!
9. የሌሊት ወፍ ጆረዋ ከተደፈነ መብረር አትችልም!!!!
10. ጊንጥ 12 አይኖች አላት!!!!
11. አዞ ምላሱን ወደውጭ ማውጣት አይችልም!!!
12. ሴት ካንጋሮ ከወንዱ ምትለየው በደረቷ ባለው ከረጢት ነው!!!
13. አይጥ ያለምግብ 14 ቀን መቆየት ትችላለች!!
14. አለም ላይ የመጀመሪያው ለማዳ እንስሳ ውሻ ነው!!
15 .የጊንጥ መርዝ ጊንጥን ሲገድል የእባብ መርዝ ግን እባብን አይገድልም!!!
16. በአንድ ጉንዳን መንጋ ውስጥ እስከ ግማሽ ሚሊየን ጉንዳኖች ሊኖሩ ይችላሉ!!!
17. ማንኛውም ስጋ በል እንስሳ በመብረቅ ተመትቶ የሞተን እንሰሳ አይበላም!!!
18. ቢራቢሮ 12, 000 አይኖች አሏት!!!
19. የመሬት ትል 5 ልቦች አሏት!!!

የትኛው ግርምት ፈጠረባቹህ?
ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል!!!!!!!!!

ምርጥ መጣጥፎች
ሼርርርር

 የከፍተኛ ትምህርት መቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ።የ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ማለፊያ ነጥብ ፦  !👉 በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር • ለተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞት ማለፊያ ነጥብ ...
14/03/2022



የከፍተኛ ትምህርት መቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ።

የ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ማለፊያ ነጥብ ፦

!

👉 በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር

• ለተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞት ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 363 ለሴት 351

• በተፈጥሮ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 351 ለሴት 339

• ለተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታ 300

• በተፈጥሮ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብ 380

🔹በመጀመሪያው ዙር የተፈተኑ እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የተፈጥሮ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 300

• ለማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 264፣ ለሴት 254

• በማህበራዊ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 254፣ ለሴት 250

• ለማህበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታዎች 250

• በማህበራዊ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ለሁለቱም ፆታ ነጥብ 280

🔹በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የማህበራዊ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 250

(የ2ኛው ዙር ተፈታኞች የመቁረጫ ነጥብ ሙሉ መረጃ ከላይ በምስሉ ተያይዟል ያንብቡ)

Address

Siltie
Arba Mintch

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Siltie Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Siltie Media Network:

Share