የኛ ሰው ከደቡብ አፍሪካ

የኛ ሰው ከደቡብ አፍሪካ ትኩስ መረጃዎችን ለማግኝት like and share ያድርጉ ።

ብልፅግና እንደ ቀልድ ስድስት ዓመት ሞላው። ምድሪቱ በደም አበላ ከጨቀየች እነሆ አምስት የአኬልዳማ ዓመታት! ድርጅቱ እስከ አንገቱ በደም ተነክሮ ፈታ ዘና ብሎ እንደ ትላንቱ በውብ የቃላት ጋ...
01/01/2025

ብልፅግና እንደ ቀልድ ስድስት ዓመት ሞላው። ምድሪቱ በደም አበላ ከጨቀየች እነሆ አምስት የአኬልዳማ ዓመታት!
ድርጅቱ እስከ አንገቱ በደም ተነክሮ ፈታ ዘና ብሎ እንደ ትላንቱ በውብ የቃላት ጋጋታ እና ዲኮር ታጅቦ አምስተኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አክብረዋል። በዓሉን ትተን ብልፅግና በኢኮኖሚ ደረጃ ባይኖርም በድርጅት ደረጃስ አለ ወይ ብለን እንጠይቅ....

ብልፅግና የምር አባል አለው..? ርዕዮተ-ዓለም አለው..? ሀሳብስ አለው..? ለሀሳቡ እና ርዕዮተ-ዓለሙ የሚታገል..የሚሰዋ አመራርስ አፍርቷል..? ውግንናውስ ለማነው..?

ድርጅቱ በኦሮሚያ ብቻ 5 ሚሊየን አባለት አሉኝ ይላል። እኔ ግን በፊት አንድ አባል ነበረው...አሁን ግን ምንም የለውም እላለሁ። ያ ብቸኛው ለማስመሳል ሳይሆን የምሩን ለሕዝብ ተጠቃሚነት የቆመ፣ የውስጠ ድርጅት ትግል እንዲኖር የጣረ፣ ብቻውን ብዙ ሆዳሞችን ሲታገል የቆየው የኩዩው ጥቁር አለት ዛሬ ከርቸሌ ነው።

አሁን ድርጅት ውስጥ ሀሳብ የለም። የውስጠ ድርጅት ትግል የለም። የዓላማ አንድነት የለም። ዓላማ እራሱ የለም። ጠንካራ ድርጅታዊ አደረጃጀት የለም። ስጋ መቁረጥ እንጂ የስራ ቁርጠኝነት የለም። ከሆድ ውጭ ሌላ የጋራ አጀንዳ የለም። በውሸት ሪፖርት ይሸላለማሉ። ውሸትነቱን እያወቁ በውሸትነቱ ይረካሉ። የጠራ መስመር..የጠራ አይዲዮሎጂ...ብሎ ነገር የለም። የአይዲዮሎጂን መስመር ሳይሆን የሆድን መስመር ይዞ ይነጉዳሉ...ልክ እንደዛ ሳሩን ብቻ እያየ እንደሚሄደው በሬ...ይህ ደግሞ በሬውን ብቻ ከገደል አፋፍ አያደርስም...ሙሉውን የሆድ ለስራ ስብስብን ከነ ድርጅቱ ገደል ልጨምር ይችላል...

13/12/2024

ኢትዮጲያን የባህር በር ባለቤት ያደረጋት ፈጣሪ ይመስገን እንጂ ሌላ ምን ሊባል ይችላል! ፈጣሪ ምን ይሳነዋል?

እንኳን ደስ አላችሁ ወዘተ በሚል ደናቁርት ደጋፊዎቻቸውን በባዶ ያስጨፈሩበት ስምምነት ውሃ በላው።

ብር  አምጡ ብሏል  ማለት ነው አለቃቸው።የጉራጌ ንብረት  በእሳትና  በኮሪደር  ልማት ስም  ከ90% በላይ አፍርሶ  ደሃ  ካደረገ  በኃላ አሁን  ጅብ ከሄደ ውሻ  ጮኸ  አይነት  የስካር ሀ...
08/12/2024

ብር አምጡ ብሏል ማለት ነው አለቃቸው።የጉራጌ ንብረት በእሳትና በኮሪደር ልማት ስም ከ90% በላይ አፍርሶ ደሃ ካደረገ በኃላ አሁን ጅብ ከሄደ ውሻ ጮኸ አይነት የስካር ሀንጎበር ነው።

የወልቂጤ ነገር… The same old s**t!አንድ አመት ሙሉ ስራቸው እርስ በርስ መሿሿም የሆኑ አመራሮች ሁኔታ ግርም ይላል። የወልቂጤ ከተማን ድንበር አስከብሩ ሲባሉ እነሱ "የሕልም ጉልበ...
13/11/2024

የወልቂጤ ነገር… The same old s**t!

አንድ አመት ሙሉ ስራቸው እርስ በርስ መሿሿም የሆኑ አመራሮች ሁኔታ ግርም ይላል። የወልቂጤ ከተማን ድንበር አስከብሩ ሲባሉ እነሱ "የሕልም ጉልበት ..." ምናምን እያሉ ይዝጋሉ። ህዝቡ አዲስ ነገር እንዲጠብቅ አዳዲስ ተሿሚዎች እያመጡ በተሰለቸ ስልጠና ወስብሰባ ህዝቡን ይጠምዱታል።

እውነታው ግን ልዩ ወረዳው ግማሹን ወልቂጤ ከተማ በሕልም ሳይሆን በእውን ጉልበት እያስተዳደረ ነው። ግብር እየሰበሰበ ነው። መሬት እየቸበቸበ ነው። ፖሊስና ትራፊክ አሰማርቷል። ወጣቶችን ለጥቃት እያደራጀ ነው።

ሌላም ጉድ አለ እንጂ። ልዩ ወረዳው በይፋ ዛሬም የወልቂጤ ከተማ ምክትል ከንቲባ ነው። ግማሹን ከተማ በጉልበት፣ ግማሹን ከተማ ደግሞ በህግ እያስተዳደረ ነው። ታዲያ ወልቂጤ የማናት እንበል ጎበዝ??? ምን ዓይነት መርገምት የሆነ አመራር ነው የያዘን?? በጉልበት የያዙትን ቦታ ማስለቀቅ ቢያቅታችሁ እንዴት በህጋዊ መንገድ በራሳችሁ አንገት ላይ ገመድ ትጠመጥማላችሁ? ወይስ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል ነው?

ከአምናው የተሻላችሁ ለመሆን ከአምናው የተሻለ ነገር መስራት ይጠበቅባችኋል። አምና ችግር ያመጣ መንገድ ዘንድሮ መፍትሄ አይሆንም። 75% ጉራጌ በሆነበት ልዩ ወረዳ አንድ የካቢኔ ቦታ ለጉራጌ ሳይሰጡ እናንተ ያው በተለመደው የውድቀት መንገድ በመጓዝ በምክትል ከንቲባነት ቁጭ ታደርጓቸዋላችሁ? ምን አይነት ቸርነት ነው ባካችሁ?i

አንድ የተለየ እርምጃ ሳትወስዱ የተለየ ውጤት ትጠብቃላችሁ? The same old s**t!

ወልቂጤ ትንኮሳ አለ ፤ቆሴ ወረራ ተፈፅሞብናል ፤ የመደራደር አቅማቸው አነስተኛ ነው።ወኔ የላቸው ፣ የታሰሩት የጉራጌ ልጆች እንኳን ማስፈታት አልቻሉም ። የአመራር መድረክ ላይ ጉራጌን በሚመጥ...
12/11/2024

ወልቂጤ ትንኮሳ አለ ፤ቆሴ ወረራ ተፈፅሞብናል ፤ የመደራደር አቅማቸው አነስተኛ ነው።

ወኔ የላቸው ፣ የታሰሩት የጉራጌ ልጆች እንኳን ማስፈታት አልቻሉም ። የአመራር መድረክ ላይ ጉራጌን በሚመጥን መልኩ አያወሩ ፤አይሞግቱ ዝም ብለው ተወካይ ።
እነሱ የስልጣን ዘመናቸውን ለማስረዘም ወጣት ጡረተኞች በመቀለብ ተጠምደዋል ። ከማህበራዊ ሚዲያ ውጪ ከማስጮህ ውጪ እዚህ ግባ የሚባል ለማህበረሰቡ የሚጠቅም የሚጨበጥ ፤ የሚዳሰስ ስራ አልሰሩም።ዝምብሎ ፉከራና ሽለላ ለጉራጌ የሚጠቅመው አንዳች ነገር የለም ።

ሊበሏት ያሰቧትን አሞራ ጅግራ ነሽ ይሏታል።
02/11/2024

ሊበሏት ያሰቧትን አሞራ ጅግራ ነሽ ይሏታል።

👉ስንታየሁ ወ/ሚካኤል📞  "ሄሎ ተመስገን  በቅርቡ በክልሉ ባሉ ከተሞች  የኮሪደር ልማት ስለምናስጀምር ወልቂጤ  ላይ  ደግሞ  ሰላም  አይደለም የሚል ሰበብ ብንፈጥር ምን ይመስሀል "👉ተመስገ...
02/11/2024

👉ስንታየሁ ወ/ሚካኤል📞 "ሄሎ ተመስገን በቅርቡ በክልሉ ባሉ ከተሞች የኮሪደር ልማት ስለምናስጀምር ወልቂጤ ላይ ደግሞ ሰላም አይደለም የሚል ሰበብ ብንፈጥር ምን ይመስሀል "

👉ተመስገን ካሳ📞 " ወልቂጤ አሁን አንፃራዊ ሰላም አለ ምን ይሻላል "

👉ስንታየሁ ወ/ሚካኤል📞 " ሌላውን ለእኔ ተወው አንተ ብቻ ለክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ወልቂጤና ሰላም በሚመለከት የሆነ ነገር እንዲያስተላልፉ አድርግ ተሜ"

👉ተመስገን ካሳ📞 "እሺ ስንቴ ግን ለምን ፈልገኸው ነው "

👉ስንታየሁ ወ/ሚካኤል📞 "በሰላም ሰበብ ቀቤና ወልቂጤ እንዲቆይ ፈልጌ እንዲሁም መንግስታችን/ፓርቲያችን የሚያወርዳቸው አጀንዳዎች የጉራጌ /የወልቂጤ አመራር /ማህበረሰብ አይቀበሉም ብዬ ሪፖርት ለማድረግ ፈልጌ ነው "
👉ተመስገን ካሳ📞" እሺ መልካም ቻው "
__
_👇👇👇👇
👉ስንታየሁ ወ/ሚካኤል:-የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሀላፊ
👉ተመስገን ካሳ :-የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ሃላፊ ነው።
👇👇👇👇👇👇በወልቂጤ ፤በእንሴኖ ፤ በቆሴ ፤በሶዶ ክስታኔና በአበሽጌ የሚፈጠሩ የሰላም እጦቶች የነዚህ ሰዎች እጅ አለበት ። ተመስገን ካሳ የሰጠው መግለጫ የክልሉ ኮሙኒኬሽን አንብቡት ።መንግስት እነዚህ ሰዎች ላይ እርምጃ መውሰድ አለበት ።

02/11/2024

መንግስት እንደሌላት ሀገር ሕዝብ በጉልበተኞች እየተገደለ ንብረቱ እየተዘረፈ መንግስት ግን ሀገር ሠላም ነው ይለናል‼️

አቶ አያልቅበት ግን የትኛው ፕላኔት ላይ የሚኖረው❓ 86 ሚሊዮን ህዝብ ደሀ ያደረገ፤ነጋ ጠባ የነጋዴውን ንብረት ለመቀማት የሚቋምጥ፤ህዝብ በድሮን የሚጨፈጭፍ ስርዓት ነው ኢትዮጲያን እየፈተናት ያለው‼️

29/10/2024

ድሮም ቢሆን ለአህያ ሳር መስጠት ትርፋ ፋንዲያ ነው።

28/10/2024

አምባገነኖች በሰው ልብ ውስጥ ለዘላለም ህያዋን ሆነን እንድንቆይ ያደርጋል የሚሉትን ታላቅ ፕሮጀክት በመንደፍና በመተግባር ይታወቃሉ። ታላላቅ ፕሮጀክቶች የአገርን እና የመሪን ገጽታ ከመገንባት አንፃር ትልቅ ፋይዳ አላቸው። የጀርመኑ አምባገነን መሪ ሂትለርና ፓርቲያቸው ናዚ ጀርመናዊያን ከጫፍ ጫፍ እንደልብ እንዲዘዋወሩ ያስቻለውን የኦቶባን መንገድ እንዲሰራ በማድረጋቸው ከፍተኛ ኩራት ይሰማቸው ነበር። በ1931 ተመርቆ ወደ ስራ የገባው እና የሶሻሊስም ርዕዮት አሸናፊ መስመር መሆኑን ማሳያ ነው ተብሎ ይነገርለት የነበረውን የሞስኮ ሜትሮ ግንባታ በመፍቀዱ ሊቀመንበር ጆስፍ ስታሊን እጅጉን ይሞካሹ ነበር።
የሮማኒያው አምባገነን መሪ ኒኮላይ ቻውቼስኩ በበኩሉ ቅንጡ ቤተ-መንግስትና ፓርላማ ለማስገንባት በሚል ሰበብ ብቻ የዋና ከተማዋን ቡከሬስት አንድ አምስተኛ አፍርሷል። ግንባታውን ለመጨረስ 13 ዓመታትን የፈጃ ሲሆን ከ4 ቢሊዮን ዩሮ በላይ ወጪ ተደርጎበታል። አስገራሚዊ ነገር ግንባታው ሳይጠናቀቅ መሪው ቻውቼስኩ ከስልጣን ተባሮ መገደሉ ነበር።
እነዚህ በዋቢነት የጠቀስናቸው ፕሮጀክቶች ዛሬም ድረስ በየአገሮቻቸው አገልግሎት እየሰጡ ቢሆኑም ግንባታውን የፈቀዱት መሪዎች ባሰቡት መንገድ ስማቸው አብሮ አይነሳም። መሪዎቹን ታሪክ የሚያነሳቸው በትክክለኛ መገለጫቸው ነው ፡ አምባገነን ፥ ጨፍጫፊ እና ሰው በላ እያለ!

Tyrants often embark on grand projects, seeking to immortalize themselves through monumental achievements. Hi**er and the N**i party promoted the Autobahn, promising Germans nationwide mobility. Stalin oversaw the creation of the Moscow Metro, hailed as a socialist triumph. Romanian dictator Ceausescu demolished a fifth of Bucharest to build the extravagant Palace of Parliament, costing billions and countless lives. Yet, despite their ambitions, history doesn’t honor them for these projects. Instead, they are remembered for what they truly were: dictators, killers, and oppressors.

ብልጽግናዎች ከእውነት ጋር ለመጋፈጥ፣ከሀቅ ጋር ለመተናነቅ ፍላጎቱም አቅሙም የላቸውም።አንዱን ችግር ለመፍታት ሳይሆን ለማስረሳት ከተሳካ ሌላ አጀንዳ ለህዝብ ማቅረብ ካልሆነ ደግሞ ከቀደመው ች...
27/10/2024

ብልጽግናዎች ከእውነት ጋር ለመጋፈጥ፣ከሀቅ ጋር ለመተናነቅ ፍላጎቱም አቅሙም የላቸውም።አንዱን ችግር ለመፍታት ሳይሆን ለማስረሳት ከተሳካ ሌላ አጀንዳ ለህዝብ ማቅረብ ካልሆነ ደግሞ ከቀደመው ችግር የተሻለ ሌላ ችግር በመፍጠር የበፊቱን ማስረሳት አይነተኛ የስልጣን ጉዟቸው ከሆነ ውሎ አድሯል።በየትኛውም የሀገራችን ክፍል የተለኮሰ፣የተፈጠረ ወይም ከሌላ ስፍራ የተዛመተ ችግር ተቀርፎ ወይንም ተፈትቶ አያውቅም።ይልቁንም ከመጀመሪያው ችግር በላይ እግር በእግር እየተከተለ የሚለኮስ በርካታና ለቁጥር የሚታክት ችግር ተከትሏል።የሚያሳዝነው ደግሞ አብዛኞቹ የሚከሰቱት ሀገርን ከችግርና ከቀውስ እንዲጠብቅ ዙፋን ላይ በተቀመጠው መንግስት አማካይነት መሆኑ ነው።ህግ አልበኝነት፣የፍትህ እጦት፣ጦርነትና ግጭቶች፣ወረርሽኞች፣የእንቅስቃሴ ገደቦች፣ሰብአዊ መብት አፈናዎች፣ ወዘተ የሚከሰቱት ሆነ ተብለውና የቀደሙ ችግሮችን ከመፍታት ይልቅ ያንን ለማስረሳት ሌላ ችግር የመፍጠርና የተበዳዮችን አስተሳስብ በማለት ያለውን ችግር እንዲቀበሉ የማድረግ ሸፍጥ ነው።ይህ የፖለቲካ ግልሙትና በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍሎች ከተገመተው በላይ ሰርቷል።

=>የብልጽግናዎች ችግሮችንም ሆነ የህዝብን ብሶት የሚረዱበት እንዲሁም ተርጉመው በጣም ለሚወዳቸው ህዝብ¡¡ የሚያስረዱበት መንገድ በጣም ያስደንቃል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰባት አመት የተከተሉት የተሳሳተ ብቻ ሳይሆን የተቃወሰ የምእራቡንና የአረቡን አለም የማገልገል ጉዞ ያስከተለውን ምስቅልቅል የሚያዩት እንደ ህይወታቸው ክፍል ስህተት ሳይሆን በመልካም ጉዟቸው ላይ የተቃጣ የጠላት ትንኮሳ አድርገው ይወስዱታል።ፍዳ መከራውን ለሚያየው ህዝብ በአጀንዳ ላይ አጀንዳ እየፈጠሩ የሚያደርጉትን ትውልድ የማደንቆር ውስልትናና በዚህ የተነሳ የሚከሰተውን የህዝብ አለመታገልና ዳተኝነት ደግሞ አምላክ ለእርሳቸውና ለመንግስታቸው እያደረገ ያለው የማሻገር ተአምራት አድርገው ይረዱታል።
በስልጣን ጉዟቸው በበቂ ምክንያትም ሆነ ያለ በቂ ምክንያት የተገዳደራቸውን ግለሰብም፣ማህበረሰብም ህዝብም በብሶቱና በእምቢተኝነቱ ላይ ተወያይቶ በሰላም መፍታት ለብልጽግናዎች እንደ ንጉስ ሳኦል ለጥፋት አለመታዘዝ አድርገው ይረዱታል።

=>ጠቅላይ ሚኒስትሩ ራሳቸውን የሚያዩት እየተማረ እንደሚታስተምር፣እየሰራ እንደሚያሰራ፣እየተሳሳተ እንደሚታረም፣ለስኬትም ሆነ ለውድቀት ከፍተኛው ተጠያቂ ራሳቸው እንደሆኑ አድርገው አይደለም።ዘመን መጥቶ ዘመን ሲተካ ስልጣንም ዙፋንም ገደብ አግኝቶ እንኳን እንዲህ አለም ባወቀው ጸሀይ በሞቀው ልክ ተደርጎ ይቅርና በስውርና በጓዳ የተፈጸሙ ወንጀሎች ተጠያቂ እንደሚያደርጉ አይደለም ።
ጠቅላዩ ራሳቸውን የሚያዩት እንደ ዳዊት አምላክ ኢትዮጵያን በአደራ የሰጣቸውና ስራቸውን ሲጨርሱ አምላክ እንደ ኤልያስ ከነ ህይወታቸው በእሳት ሰረገላ እንደሚወስዳቸው ነው።በዚህ ምድር ላይ ተከሰው በፍትህ አጥር ስር ተገኝተው ላደረጉት ጥፋት የሚጠየቁ አይመስላቸውም።
ይህንን እንዲያምኑ ያደረጋቸው ደግሞ እርሳቸውና ካቢኔአቸው የመከራ እንጀራ የሚመግቡት ከመቶ ሚሊዮን የሚልቀው ህዝብ አሁን የሚኖረው የመከራ ኑሮ የሚገባውና ምናልባትም የሚበዛበት ነው ብለው ማመናቸው ይመስለኛል።የኢኮኖሚ ጥያቄ ለሚያነሳባቸው ህዝብ ማነጻጸሪያቸው አብዛኛው የፓርላማ አባል የበቆሎ ቂጣ በጎመን አንድ ጊዜ ብቻ እየበላ ማደጉና በሰሌን ላይ ተኝቶ መማሩ ነው።የአገልግሎት መጓደል፣የሰላም እጦት፣የፍትህ መዛባት፣የወንጀል መብዛት ወዘተ ለሚያነሳው ህዝብ መልሳቸው በኢማጅኔሽን መኖር፣ከከተማ ውጭ መሰደድ፣ጠቅላይ ሚኒስትሩን ሚልሻ አለማለትና ቅጠላ ቅጠል በልቶ ይህንን ቀን ማለፍ መልሳቸውም መፍትሄያቸውም ሆኖ ከራሳቸው አንደበት ተሰምቷል።የገባንበት የማጥ መንገድ፣የገባንበት የውርደት በር፣የዘቀጥንበት የውድቀት ጉድጓድ የተሰወረበት ህዝብና መንግስት መውጫ መንገዱ ይታየዋል ብሎ ማሰብ የዋህነት ይመስለኛል።

የብል*ግናው መንግስት ቁልፍ ተግባር ለዜጎቹ ህይወትና ኑሮ መጨነቅ ሳይሆን ከተማን ማስዋብ ነውና ገና ብዙ ቤቶች አፍርሶ  ይፈርሳል🕔
26/10/2024

የብል*ግናው መንግስት ቁልፍ ተግባር ለዜጎቹ ህይወትና ኑሮ መጨነቅ ሳይሆን ከተማን ማስዋብ ነውና ገና ብዙ ቤቶች አፍርሶ ይፈርሳል🕔

All animals are equal but some are more equal. መደመር በተግባር ይህ ነው‼️በእውነት የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለሰ ዜናዊ ማረን ልንለው ደርሰናል።ለደሀ አነስተኛም...
24/10/2024

All animals are equal but some are more equal. መደመር በተግባር ይህ ነው‼️

በእውነት የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለሰ ዜናዊ ማረን ልንለው ደርሰናል።ለደሀ አነስተኛም ቢሆን ሱቅ ይሰጥ ነበር።ኮብል እስቶን ወጣቶችን አደራጅቶ ያሰራ ነበር።ኮንደሚኒየም አሰርቶ ሰጥቷል።ኢትዮጵያ ውስጥ ያለ ስጋት የትኛውም ቦታ ተዟዝሮ ሰርቶ መስራት መለወጥ ይቻል ነበር።ጥቃቅንና አነስተኛ አደራጅቶ ያሰራ ነበር።ፖሊሲው ድሀ መር ነበር ማለት ይቻላል‼️ኢትዮጵያን በአለምም በአፍሪካም የተከበረች ሀገር ነበረች‼️

እንግዲህ ከዛሬ 5 ዓመት የነበረችውን ኢትዮጵያ ዛሬ የት ነች ቢባል መልስ የለውም።ሰው አረብ ሀገር ሰርቶ ባመጣው ገንዘብ የተሰራ ቤት ማንነትና ብሔር አይቶ በግሬደር የሚያፈርስ፣ጭካኔ የተሞላው ስርዓት መደመር ነው። ብዙ ማለት ይቻላል።በቃላት የማይገለጽ ህዝቡ እራሱ እየተፈተነበት ያለ ስርአት ነው።ክልል የመሆን መብት ስትጠይቅ ላንተ አይገባም የሚል መርጦ ክልልነት የሚሰጥ ስርዐት ፈጣሪ ያንሳው እንጂ ምን ይባላል?ምንም!በዛ ላይ የኑሮ ውድነቱ ጣሪያ ነክቶ መንግሥት በተቀናጀ መልኩ የደሀ ቤት ያፈርሳል።

“የአዲስ አበባ የባለቤትነት ጉዳይ ቀዳሚው የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ ነው፡፡ እኛ እንደ ኦነግ አዲስ አበባ በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ስር መሆን አለባት ነው የምንለው! የፌደራሉ መንግስት መሬት የ...
24/10/2024

“የአዲስ አበባ የባለቤትነት ጉዳይ ቀዳሚው የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ ነው፡፡ እኛ እንደ ኦነግ አዲስ አበባ በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ስር መሆን አለባት ነው የምንለው! የፌደራሉ መንግስት መሬት የለውም፤ ከፈለገ ባህርዳርን ዋና ከተማው ማድረግ ይችላል፡፡”

የኮሪደር ልማት ...!!! ,ልማት ..?...የምን ልማት 1.የሰው ህይወት መጥፋት2.የሰው ህይወት ኑሮ ምስቅልቅሉ ማውጣት 3.የሚፈሰው በጀት ከዕጥፍ እጥፍ ከመሆኑም በላይ በጥራት የግንባታ ሂ...
24/10/2024

የኮሪደር ልማት ...!!! ,ልማት ..?...የምን ልማት
1.የሰው ህይወት መጥፋት
2.የሰው ህይወት ኑሮ ምስቅልቅሉ ማውጣት
3.የሚፈሰው በጀት ከዕጥፍ እጥፍ ከመሆኑም በላይ በጥራት የግንባታ ሂደቶችን ተከትሎ ያልተሰራ
4.የተሰራባቸው ቦታዎች ለኢኮኖሚ እድገት የሚያደበዝዝ እንጂ ለሰዎች የቢዝነስ አመቺ እንዳይሆን ተደርጎ የተሰራ
5.የፖለቲካ ፍጆታቸው ለማሳካትና የማይፈልጉት ሰው displace ለማድረግ
6.ከስራው ሰፋትና ጥቅም በበለጠ አጀንዳ (በማዘጋጃው በአንድ የስራ ክፍል የሚሰራ ስራ የፌደራሉና የሚኒስትሮች ጋጋታ መብዛት ያም የሆነበት በክልሎች ላይ ሜጋ ፕሮጀክቶች ተዟዙረው ማሰራት ባለመቻላቸው ምክንያት )ማስቀየሪያ መሆኑ
7.ሲጀምር ከተማው ላይ የመብራት ችግር ነበር ወይ ?,የተሰራው የመብራት ፖል ጥራት :የድሬይኔጅ ማስወገጃ ቱቦዎችና የመስመር ዝርጋታ በደንብ ተጠንቶ ነው ወይ ...???

23/10/2024

ሀገር ለመመስረት በሚደረገው ርብርብ!

በጉራጊኛ ቋንቋ ትምህርት  መጀመሩ መልካምና እጅግ የሚበረታታ ነው። አሁን እየተሰጠ ያለው ሁሉንም የጉራጊኛ ዘዬዋች የሚያካትት መሆን አለበት።ግን በቸሂኛ ዘዬ ብቻ ተመርጦ ሁሉም ወረዳዎች እን...
21/10/2024

በጉራጊኛ ቋንቋ ትምህርት መጀመሩ መልካምና እጅግ የሚበረታታ ነው። አሁን እየተሰጠ ያለው ሁሉንም የጉራጊኛ ዘዬዋች የሚያካትት መሆን አለበት።ግን በቸሂኛ ዘዬ ብቻ ተመርጦ ሁሉም ወረዳዎች እንዲማሩ ከተደረገ ተቀባይነት የለውም።በቂ ውይይት መደረግ አለበት።በኃላ አዳዲስ ትርክቶች ይዞ መጥቶ የልዪነት ማስፊያ አድርገው ፖለቲከኞች እንዳይጠቀሚበት መሆን አለበት።በዘዬ ከተባለ የእኖር ኤነር ህዝብ በዘዬው መማር አለበት።በግድ ጨቅላ ህጻናት ከአፍ መፍቻቸው ውጭ ሌላ ዘዬ ተማሩ ከተባሉ ተቀባይነት የለውም።የተሻለ ብለን የምናስበው በቸሂኛና በእኖር ኤነር Equivalent Meaning or ፊደሉ እራሱ ሆኖ በአከባቢው በሚነገር የእናትና አባት አፍ መፍቻ ቢደረግ መልካም ነው።ጣጣ ይዞብን እንዳይመጣ እንላለን።እውነት ነው ቋንቋ ማሳደግም በአፍ መፍቻ መማር ከቻልን ቅርስ ነው።

የጉራጊኛ ቋንቋ በስርዓተ ትምህርት ተካቶ ህጻናት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው መማር እጅግ የሚበረታታ ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እና እንዲጎለብት መደረግ እንዳለበት እናምናለን።

ጉራጌ በጊዜ ደንግጥ! ደንግጠህ ተዘጋጅ!=====================የጉራጌ ሕዝብ የእንቁራሪቷ ታሪክ እንዳይገጥምህ ተጠንቀቅ፤ በጊዜም ደንግጥ:-()()()()()()()(()()()()()(...
20/10/2024

ጉራጌ በጊዜ ደንግጥ! ደንግጠህ ተዘጋጅ!
=====================
የጉራጌ ሕዝብ የእንቁራሪቷ ታሪክ እንዳይገጥምህ ተጠንቀቅ፤ በጊዜም ደንግጥ:-
()()()()()()()(()()()()()()()()()

በጊዜ መደንገጥ የመጀመሪያ ጥበብ ነው ( The Boiling Frog Syndrome) ይላሉ
ጃፓኖች!!
"""""""""""""""""""'""""""""""""""'"""""
ከእለታት አንድ ቀን አንድ እንቁራሪት ውሃ በተሞላ ድስት ዘላ ትገባለች። በውሃ የሞላው ድስት ለማፍላት ተፈልጎ እሳት ላይ ይጣዳል። ውሃው እንዲፈላ ተፈልጎ ድስቱ ላይ ያለማቋረጥ እሳት ሲነድበት የድስቱ ግለትና የውሃው ሙቀት ይጨመረ ይሄዳል። የድስቱን ግለትና የውሃው ሙቀት እየጨመረ ሲመጣ የእንቁራሪቷ ሙቀት የመቋቋም እቅምና ችሎታ እየጨመረ ይሄዳል። እንቁራሪት በተፈጥሮ ሙቀትን የመቋቋም ልምድና ችሎታ አላት።

የድስቱን ግለትና የውሃው ሙቀት እየጨመረ ቢሄድም እንቁራሪቷ ከድስቱ ዘላ መውጣት እየቻለች ለመውጣት አልፈለገችም ፤ ሙከራም አላደረገችም።
የድስቱ የግለት/የሙቀት መጠን እጅግ ጨምሮ የውሃው ሙቀትም የመጨረሻ ደረጃ ላይ ( 100%) ሲደርስ እንቁራሪቷ ሙቀትን የመቋቋም ተፈጥሮአዊ ልምድና ችሎታ እየቀነሰና እየተዳከመ ሲሄድ ከድስቱ ዘሎ ለሙውጣት ብትጥርም መውጣት አቅቷት ውድ ሕይወቷን ለማጣት ተገደደች ወይም ሞታ ተገኘች።

እነሆ እንቁራሪቷ የውሃው ሙቀት የመጨረሻ ደረጃ ከመድረሱ በፊት ያላትን ችሎታና አቅም ተጠቅማ ፤ በጊዜ ደንግጣ ከድስቱ ዘላ ብትወጣ ኖሮ ሕይወቷን ከመሞት ማትረፍ ትችል ነበር።
ታድያ " በጊዜ መደንገጥ የመጀመሪያ ጥበብ ነው" የሚባለው ለዚህ ነው!!

መላው የጉራጌሕዝብ በጊዜ ደንግጦ ክላስተር ከሚባል ዳግም ጨፍላቂ ከሆነው የክልል አደረጃጀት ራሡን ማውጣት ካልቻለ በብልፅግና የፈላ ውሃ መግባቱን ሳይታለም የተፈታ ነው።

ጉራጌ " ማንነትህ፤ ታሪክህና ሕዝባዊ አቅምህ" ኢሕአዴግ በወለደው የፖለቲካ አሻጥር ወጥመድ ውስጥ እንዳትገባ ራስህን ማዳን የምትችልበት ጊዜና እድሉ ዛሬ እንደሆነ አበክሬ ልነግርህ እወዳለሁ።

እውነቴን ነው እመኑኝ ? ጉራጌ በአንድነትና በጋራ ተባብሮና ተረባርቦ ራሡን በራሡ የማስተዳደር ሕገ-መንግስታዊ መብቱ ማረጋገጥ ካልቻለ ከፊቱ አደገኛ ነገር ይገጥመዋል።
""""""""""""""""""""""""""""""""""""
( ለምትፈልገው መልካም ነገር ካልታገልክና ካልተፋለምክ ላጣኽው ነገር ብታለቅስ ይስቁብሃል ፤ ይሳለቁብሃልም ተጠንቀቅ)
""'""""""""""""”"""""""""""""""""""

Address

Johannesburg
00000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኛ ሰው ከደቡብ አፍሪካ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share