ነጋሪት ሚዲያ

  • Home
  • ነጋሪት ሚዲያ

ነጋሪት ሚዲያ news & media web

01/10/2025

በሰሜን ሸዋ ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ አረርቲ ማርያም ርብራብ እንጨት ተደርምሶ ከ20 በላይ ሰዎች ሞቱ!

በአማራ ክልል፣ ሰሜን ሸዋ ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ አረርቲ ማርያም ለግንባታ የተረበረበ እንጨት ተደርምሶ ከ20 በላይ ሰዎች ሕይወት አለፈ።

ዛሬ መስከረም 21 2018 ዓ.ም. የማሪያምን ዓመታዊ ክብረ በዓል ለማክበር በስፍራው የተገኘው ምዕመን እየተሰራ ያለውን ቤተክርስትያን እየጎበኘ ባለበት ሰዓት የተረበረበው እንጨት በመደርመሱ በሰው ላይ የሞት እና የአካል ጉዳት ደርሷል።

አደጋው የደረሰው ማለዳ ከጠዋቱ 1:45 ላይ መሆኑን የአረርቲ ከተማ ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ አጥናፉ አባተ ለብሔራዊ የቴሌቪዥን ጣብያ ተናግረዋል።
በአደጋው 22 ሰዎች እስካሁን ድረስ ሕይወታቸው ማለፉ ሲረጋገጥ ከ200 ሰዎች በላይ ደግሞ ጉዳት እንደደረሰባቸው የወረዳው ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር አህመድ ገበየሁ ለፋና ብሮድካስቲንግ ተናግረዋል።
በመደርመስ አደጋው የተጎዱ ሰዎችን የአካባቢው ኃላፊዎች በወረዳው ወደሚገኙ የተለያዩ የሕክምና ተቋማት መወሰዳቸውን ይናገራሉ።

የአረርቲ ከተማ ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ አጥናፉ አባተ ለብሔራዊ የቴሌቪዥን ጣብያ አሁንም ከርብራቡ ሥር ያልወጡ ዜጎች እንደሚገኙ እና እነርሱን የማውጣት ሥራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የአረርቲ ሆስፒታል ኃላፊ ተወካይ አቶ ስዩም አልታዬ በበኩላቸው ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ ወደ አረርቲ ሆስፒታል የመጡ ተጎጂዎችን ሕክምና እየሠጡ መሆናቸውን ገልፀዋል።

ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው ሰዎች መካከል አምስቱ ወደ አዲስ አበባ መላካቸውን ጨምረው ተናግረዋል።

ዘገባው የቢቢሲ ነው!

27/09/2025

s

27/09/2025

ደሴ አሁንም ወጥረቱ አይሏል፣ የአገዛዙ ኃይሎች በኩታበር፣ በኮምቦልቻ፣ በሀይቅ እና በምዕራብ ወሎ አቅጣጫ ተከበዋል።

ያላቸው አማራጭ ለኃያሉ ፋኖ እጅ መስጠት ነው!

26/09/2025

ሰበር

25/09/2025

2ተኛ ቀን ዘመቻ አርበኛ አደም አሊ (አባ ናደው) በታላቅ ድል ታጅቦ እንደቀጠለ ነው።

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ መስከረም 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከጧቱ 12:00 ሰዓት የተጀመረው ዘመቻ አርበኛ አደም አሊ (አባ ናደው) በአምስቱም ኮሮች እና በዕዙ ልዩ ዘመቻ ከፍተኛ ተጋድሎ በማድረግ አስደናቂ ድሎችን እያስመዘገበ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

2ተኛ ቀኑን በያዘው “ዘመቻ አርበኛ አደም አሊ (አባ ናደው) በዛሬው ዕለት መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ.ም ተጠንክሮ የቀጠለ ሲሆን በዚህ ተጋድሎም አገዛዙ ለሁለት ዓመት የሰሜን ወሎ ዞን የጦር ማዘዣ ጣቢያ አድርጎት የነበረው የግዳን ወረዳ ሙጃ ከተማ በርካታ ምሽጎችን በመስበር በምኒልክ ዕዝ ሰራዊት በቁጥጥር ስር ውሏል።

በዘመቻ አርበኛ አደም አሊ (አባ ናደው) በትላንትናው ዕለትና በዛሬው ዕለት ነጻ የወጡ ቦታዎች:-

• ሰሜን ወሎ ዞን ግዳን ወረዳ ዋና መቀመጫ የሆነችው ሙጃ ከተማ ጨምሮ ሙሉ ለሙሉ ወረዳው በፋኖ ቁጥጥር ስር ገብቷል።

• ⁠ሰሜን ወሎ ዞን ጋዞ ወረዳ መቀመጫ የሆነችው አስታይሽን ጨምሮ ወረዳው ሙሉ በሙሉ በፋኖ ቁጥጥር ስር ገብቷል።

• ⁠ሰሜን ወሎ ዞን ራስ አንጎት ወረዳ መቀመጫ የሆነችውን አሁን ተገኝ ከተማን ጨምሮ ሙሉ በሙሉ በፋኖ ቁጥጥር ስር ገብቷል።

• ⁠ሰሜን ወሎ ዞን ላስታ ወረዳ ብልባለ ከተማን ጨምሮ ከሹምሽሃ ቀበሌ ውጭ በፋኖ ቁጥጥር ስር ገብቷል።

• ⁠ሰሜን ወሎ ዞን ጉባላፍቶ ወረዳ ከወልደያ ከተማ ውጭ ያለው ሙሉ በሙሉ በፋኖ ቁጥጥር ስር ውሏል።

• ⁠ሰሜን ወሎ ዞን ዳውንት ወረዳ ዋና መቀመጫ የሆነችው ኩርባ ከተማን ጨምሮ ወረዳውን ሙሉ በሙሉ በፋኖ ቁጥጥር ስር ገብቷል።

• ⁠ሰሜን ወሎ ዞን ዋድላ ወረዳ ከኮን ከተማ ውጭ ያለው ሙሉለሙሉ በፋኖ ቁጥጥፍ ስር ገብቷል።

• ⁠ሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ ከፍላቂትና ከገራገራ ከተማ ውጭ ያለው ሙሉ በሙሉ በፋኖ ቁጥጥር ስር ውሏል። ፍላቂትና ገረገራ ከተማ ላይ ትንቅንቅ እየተደረገ ነው።

ውጊያውና ትንቅንቁ አሁንም እንደቀጠለ ነው፣ ከመረጃው ብዛት የተነሳ ቁጥር ለመመዝገብ ተቸግረናል፣ ዝርዝር የቁጥር መረጃዎችን ይዘን የምንመለስ ይሆናል!

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ዘመቻ አርበኛ አደም አሊ (አባ ናደው)

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
መስከረም 15/2018 ዓ.ም

25/09/2025

ሰበር የድል ዜና
===========
በዛሬው ዕለት መስከረም 14 ቀን 2018 ዓ.ም ጧት 12:00 ሰዓት የጀመረው ውጊያ አሁንም እንደቀጠለ ቢሆንም እስከ 8:00 ሰዓት በተካሄደው ውጊያ አጠቃላይ የተገኙ ድሎች:-
• ⁠ሞርተር - 6
• ⁠ዲሽቃ - 6
• ⁠ብሬን - 14
• ⁠ስናይፐር - 9
• ⁠ክላሽ - 438
• ⁠የተደመሠሠ ጠላት - 471
• ⁠የተማረከ - 175
• ⁠ተተኳሽ - 52,600
• ⁠ወታደራዊ ሬዲዮ - 9
• ⁠F1 Bomb - 148
• ⁠ቁስለኛ - 126 ይዞት የወጣው
• ⁠የሞርተር ቅንቡላ - 37
• ⁠1 ሲኖ ትራክ ሙሉ ወታደራዊ ቁሳቁስና ሬሽን

አገዛዙ የሚተማመንባቸው የሰሜን ምስራቅ ዕዝ አካል የሆኑት 12ኛና 61ኛ ክፈለጦር መካከል የ12ኛ ክፍለጦር 70% ኃይላቸውን መማረክ፣ መደምሰስ እና ማፍረስ ተችሏል።

#ማስታወሻ:- የልጅ እያሱና የንጉስ ሚካኤል ኮር የአውደ ውጊያ መረጃዎች እንደደረሱን የምናሳውቅ ይሆናል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ዘመቻ አርበኛ አደም አሊ (አባ ናደው) በታላቅ በድል ተጀምሯል! ይቀጥላል..

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ
መስከረም 14/2018 ዓ.ም

ግልባጭ
~~~~~
ለጀነራል ፃድቃን የፒፒ ነጭለባሽ ሰራዊት ዋና ኣዛዥ

ረኣይዎ በሉ እዚኣ እያ እታ ዓቕሚ ናይ ፒፒ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

22/09/2025

ኮ/ር አሰግድ መኮንን የት ናቸው?

የጦር እስረኛን መደበቅ በአለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ህግ ላይ ከፍተኛ ጥሰት ነው።

ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የሲቪል እና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳንን (ICCPR) በ1993 አጽድቃለች። የአለም አቀፍ የሰብአዊነት ህግ (IHL) በጦርነት እና በሲቪል እስረኞች ላይ ግልፅነት ያለወሰ ሰብአዊ አያያዝን ያዛል።

አሰግድ የጦርነት እስረኛ ነው። እ.ኤ.አ ከጁላይ 22 ቀን 2024 ጀምሮ በሸዋ ውስጥ ደራሲ እና ታዋቂው የፋኖ መሪ ኮ/ር አሰግድ መኮንን በኢትዮጵያ መንግስት ሃይሎች ታስረዋል። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የት እንዳለ አይታወቅም።

ኮ/ር አሰግድ መኮንን የት ናቸው?

21/09/2025

ሰበር ዜና
=======
3 ከፍተኛ ኮሎኔሎች የፋሽስት አብይ አህመድን መከላከያ መክዳታቸው ከታማኝ ምንጭ አረጋጫለሁ:: ማንነታቸውን ጊዜ ሲፈቅድ አጋራችሗለሁ

21/09/2025

🔥 ‼ # ነጋሪት ሚዲያ️

መስከረም 11/2018 ዓ.ም

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል(አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ በግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ስር የሚገኙት ማረጉ ተማረ ክፍለ ጦር፣እሸት ክፍለ ጦር፣ተፈራ ማሞ ክፍለ ጦር፣ነብሮ ተወርዋሪ ኮማንዶ የተውጣጡ ፋኖዎች በጥምረት ከብልባላ ቄርቆስ ባውሽ መረዝ በር እስከ ሶርባ ሚካኤል ባካለለ አውደ ውGIያ ጠLAትን አይቀጡ ቅጣት ቀጥTEውታል።

በዚህ አውደ ውGIያ የጠLAት ኃይል ከላሊበላ ወደ ብልባላ ከተማ ሬሽን ለማስገባት ሲሞክር ሜካናይዝድ ኃይሉን ይዞ የተንቀሳቀሰ ቢሆንም መውጫ መግቢያውን ተራራና ሸንተረሩን የሚያውቁት ፋኖዎቹ ከጧቱ 12:00 እስከ ቀኑ 10:00 ሰዓት ድረስ ጠLAትን ሲገREፉት ውለዋል።

በተደረገው Oፕሬሽን አንድ ሻለቃ መሪን ጨምሮ 35 የጠLAት ኃይል ሲDEመSEስ አንድ ብሬንና 10 ጥቂር ክላሽ ተማርኳል ጠLAትም ከ40 በላይ ቁስLEኛWUን በአምBUላንስ ወደ ላሊበላ ከተማ ሲያመላልስ እንደዋለ ታውቋል።

በተያያዘ መረጃ ኃይሉ ከበደ ክፍለጦር ከአስከተማ ወደ ላልኪው ዘሎ ለመግባት የመጣውን የJUላን ሰRAዊት በፋኖዎች ቋንቋ ሲያናግሩት ውለው አይQጡ ቅጣት በመቅጣት ወደ ነበረበት መደበቂያ አሳፍረው መልሰውታል።

በመጨረሻም የብልፅግና WOንበር አስጠባቂ ሰRAዊት ዘሎ እንደገባው ዘሎ መውጣት እንደማይችል እንዲሁም የአማራ ህዝብ ህልውና እስካልተረጋገጠ ድረስ ትግላችን እስከ ቀራኒዮ ነው ሲል የላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ፋኖ ታዘበው ሻምበል አስታወቋል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተGAድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የኮሩ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ቢሆነኝ ቢያበይን መረጃውን አድርሷል!

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
©የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ

‼️
‼️
💪
💪
💪

11/ዐ1/2018 ዓ.ም

20/09/2025

በአፋብኃ አፄ ምኒልክ ዕዝ በአርበኛ ሰለሞን አሊ በሚመራው ልጅ እያሱ ኮር ስር ከሚገኙ ክፍለጦሮች የተወጣጡ የፋኖ ኃይሎች ትናንት መስከረም 06/2018 ዓ/ም በአምባሰል ወረዳ አበት ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ላይ ባደረጉት ውጊያ፡ የሚሊሻ አባላትን ጨምሮ በርካታ ቁጥር ያላቸው የአገዛዙ ወታደሮችን በመደምሰስ ድል መቀዳጀታቸውን የዕዙ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ለመረብ ሚዲያ በላከው መረጃ አስታውቋል።

በዚህም በርካታ ቁጥር ያላቸው የገዢው ቡድን ወታደሮች ሲገደሉ፡ የአከባቢው ማሕበረሰብ ተገዶ ሙትና ቁስለኛ የሆኑ የአገዛዙ ወታደሮችን ከምሽግ እያነሳ ወደ ሐይቅና ውጫሌ በሚወስዱ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች ላይ ሲጭን መዋሉ ታውቋል።

በውጊያው ከተገደሉ በሰሜን ምስራቅ ዕዝ 802ኛ ኮር 47ኛ ክ/ጦር ወታደሮች በተጨማሪ፡ ከፍተኛውን ቁጥር የሚይዙት የሚሊሻና የፖሊስ አባላት ናቸው የተባለ ሲሆን፡ እነዚህ ተላላኪ ባንዳዎች ሰልጥነው የወጡት ጃራ በሚገኘው ወታደራዊ ካምፕ መሆኑን ታውቋል።

ከበርካታ ወራቶች በፊት ጀምሮ የተቋቋመው የጃራ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ጣቢያ፡ የማይቀረውን የአማራ ሕዝብ ነፃነትን ጉዞውን ለማደናቀፍ የሚሰሩ ሚሊሻና ፖሊስ እንዲሁም ሌሎች የአገዛዙ ተላላኪ የሆኑ ታጣቂዎችን ሲያፈራ ቆይቷል።

ከዚህ ማሰልጠኛ ጣቢያ ስልጠናቸውን አጠናቀው የሚወጡ የሚሊሻና የፖሊስ አባላት በተለያዩ የሰሜን ወሎና የደቡብ ወሎ አከባቢዎች እንዲሰማሩ ተደርገው ለመከላከያ ሰራዊቱ መንገድ በመምራትና ጥቆማ በመስጠት እንዲሁም የፋኖ ቤተሰቦች እንዲታፈኑና እንዲገደሉ በማድረግ፡ ከዚህ አልፎ በየከተማው የሚገኙ የባለሀብቶችን ስም ዝርዝርና አድራሻን ለመከላከያ ሰራዊት አዛዦች በመስጠት እንዲታፈኑና ከፍተኛ ገንዘብ እንዲከፍሉ በማስደረግ ሲሰሩ መቆየታቸውን መረብ ሚዲያ ካሰባሰበው መረጃ ለማረጋገጥ ችሏል።

እንዲህ አይነት የነፃነት አሜካላ እሾህ የሆኑ ሆድ እንጂ ሕሊና አልባ ተላላኪ ባንዳዎችን መልምሎ ሲያሰለጥን የነበረው ጃራ ወታደራዊ ካምፕ ትናንት መስከረም 06/2018 ዓ/ም ንጋት ጀምሮ በተፈፀመበት ጥቃት ሙሉ በሙሉ ወድሟል።

በዚህ ኦፕሬሽን በመቶዎች የሚቆጠሩ የሚሊሻ አባላት ሙትና ምርኮኛ ሲሆኑ፡ በርካታ የጦር መሳሪያም በፋኖ እጅ ገብቷል።

ከወራት በፊት ከዚህ ጣቢያ ተመርቀው በአምባሰል ወረዳ ውስጥ በውጫሌ ከተማና በአከባቢው ስምሪት ተሰቷቸው የነበሩ የሚሊሻ አባላት ናቸው የልጅ እያሱ ኮር ፋኖዎች በወሰዱት እርምጃ የተገደሉት።

16/09/2025

አሁን ደግሞ አምባሰልና ወረኢሉ ላይ ደውሉና በምኒልክ ዕዝ በአገዛዙ ሠራዊት ምን እንደደረሰ አረጋግጡ!

አፋብኃ ይችላል!

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ነጋሪት ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share