South Ethiopia Times

  • Home
  • South Ethiopia Times

South Ethiopia Times Official page of south Ethiopia Times media.

የሃጂ ጉዞ ካደረጉ እስልምና እምነት ተከታዮች ብያንስ 577 ሰዎች መሞታቸው ታወቀ************************************************በዘንድሮው ሃጂ ጉዞ ከ1.8 ሚሊዮ...
21/06/2024

የሃጂ ጉዞ ካደረጉ እስልምና እምነት ተከታዮች ብያንስ 577 ሰዎች መሞታቸው ታወቀ
************************************************
በዘንድሮው ሃጂ ጉዞ ከ1.8 ሚሊዮን በላይ የእስልምና እምነት ተካታዮች የተሳተፉበት ብሆንም በሳውዲ አረቢያ መካ ከተማ ባጋጠመው አየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ብያንስ 577 ሰዎች ሞተዋል።

መካ ከተማ መጠኑ 51.8 ዲግሪ ሴንቲግሬድ የሆነ ሙቀት መከሰቱም የታወቀም ስሆን፣ በዚሁ ሳቢያ ከሞቱት ውስጥ ቢያንስ 323ቱ ግብጻውያን መሆናቸውንም የአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘገባ ያመለክታል።

ከመጠን በላይ የሆነው ሙቀት ባስከተለው ጉዳት፣ ብዙን ቁጥር ከያዙ ግብፃዋውያን ሟቾች በተጨማሪ፣ 23 የቱኒዚያ ዜጎች እና አምስት የሞሮኮ ዘጎች ህይወትም አልፏል።

እንዲሁም ሶስት የሴነጋል ዜጎች እና ሁለት ናይጄሪያውያንም በዚሁ ሙቀት ምክንያት መሞታቸውን የዘገበው ዜና ወኪሉ፣ ከ577 ሟቾች ውስጥ በስኳር ህመም እና በደም ግፊት የመሳሰሉ ሥር በሰደዱ በሽታዎች የተጠቁ መኖራቸውንና ይህም ከሙቀቱ ጋር ተጨምሮ ለሕልፈት እንደዳረጋቸውም ታውቋል።

የዘንድሮው ሃጂ ጉዞው ፍጻሜውን ያገኘው ባለፈው ሰኞ ስሆን በታሪኩ ያልታየው መቁት የገጠመውና ብዙዎችን ለሕልፈት የዳረገው በዚሁ ዓመት ነው።

mail.com

‼️Alert -አስቸኳይ‼️Tohossa Toophphiyaa dalgga manttiyan ubbasn de"iya Yelagatti 5 nne 10 gididi eesuwan citaa medhdhanadan ...
09/06/2024

‼️Alert -አስቸኳይ‼️
Tohossa Toophphiyaa dalgga manttiyan ubbasn de"iya Yelagatti 5 nne 10 gididi eesuwan citaa medhdhanadan hasayissos‼️
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በሁሉም አካባቢ ያላቹ Yelagaዎች በአስቸኳይ በ5 እና 10 ሰው ሆናቹ እንድትደራጁ እናሳስባለን‼️

ይደረግ ‼️‼️

ወላይታ የፍቅር ሀገር !
07/05/2024

ወላይታ የፍቅር ሀገር !

ዳሞታ ተራራ - የወላይታ ሶዶ ውበት #ሀገሬየዳሞታ ተራራ ከወላይታ ሶዶ ከተማ በስተሰሜን የሚገኝና በደን የተሸፈነ የብዘሃ ህይወት አለኝታ ነው። ተራራው ታሪካዊ፣ ባህላዊና ሃይማኖታዊ ይዘት ያ...
06/05/2024

ዳሞታ ተራራ - የወላይታ ሶዶ ውበት
#ሀገሬ

የዳሞታ ተራራ ከወላይታ ሶዶ ከተማ በስተሰሜን የሚገኝና በደን የተሸፈነ የብዘሃ ህይወት አለኝታ ነው። ተራራው ታሪካዊ፣ ባህላዊና ሃይማኖታዊ ይዘት ያላቸው መስህብ ስፍራዎች የሚገኝበት ነው።

በሀገር በቀል ዕፅዋት የተሸፈነና አረንጓዴ ሸማ የለበሰው ይህ ተራራ በክፍታውና በግርማ ሞገሱ ወደ ከተማዋ የሚገቡትን ጎብኚዎች ቀልብ በመግዛትም ይታወቃል።

ተራራው የሚሸፍነው መሬት 12 ሺሕ 500 ሄክታር ሲሆን ከፍታው ከባህር ጠለል በላይ 3 ሺሕ ሜትር ነው። ዙሪያው 68 ኪሎ ሜትር በላይ ርቀት እንዳለውም ይነገራል።

የዳሞታ ተራራ በወላይታ ሕዝብ ዘንድ በዘርፈ ብዙ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው የሚታወቅ ታሪካዊ ስፍራ ሲሆን ከህዝቡ ታሪክና ባህል እንዲሁም ጀግንነት ጋር በማቆራኘትም ዳሞታን በሥነ ቃላቸው ያሞጋግሱታል በሙዚቃዎቻቸውም ታሪኩን ያወሣሉ።

ተራራው ከልምላሜው፣ ከዱር እንስሳትና ተፈጥሯዊ ብዝሃ ህይወት ማህደርነት ባሻገር በወላይታ ዞን የሚገኙ ወረዳዎች ስያሜዎቻቸውን ዳሞታን መነሻ አድርገው ይጠሩታል፡፡ ከእነዚህም ወረዳዎች ዳሞት ሶሬ፣ ዳሞት ወይዴ፣ ዳሞት ጋሌ እና ዳሞት ፑላሳ የሚጠቀሱ ሲሆን ለተለያዩ ቀቤሌዎችም የመጠሪያቸው መነሻ ነው የዳሞታ ተራራ፡፡

የዳሞታ ተራራ ለከርሰ-ምድርና ገጸ-ምድር ውሃ መበልጸግና መበራከት ከፍተኛ ሚና ያለው የብዙ ምንጮችና ጅረቶች ምንጭ ነው፡፡ ከተራራው መነሻቸውን አድርገው የሚፈሱ ወንዞችም ቁጥር ብዙ ሲሆን 32 ምንጮችና 12 ጅረቶች የተራራው ገጸ-በረከቶች እንደሆኑ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

በተጨማሪም የወላይታ ሶዶ ከተማን በከፊል የሚያጠጣው የንፁህ የመጠጥ ውሃ የሚገኘውም ከዚሁ ተራራ ነው፡፡ ከከተማዋ ሆነው ሲመለከቱት ቀልብን የሚስብ እይታ ያለውና ለከተማዋ ግርማ ሞገስና ውበት ያላበሰ የከተማዋ የመስህብ ተራራም ነው ዳሞታ፡፡

የዳሞታ ተራራ ጥንታዊ የወላይታ ነገስታት መናገሻና ታሪካዊ ስፍራ ሲሆን በርካታ ታሪካዊ ቅርሶች፣ ዋሻዎች እና የተለያዩ የተፈጥሮና የሰው ሠራሽ የቱሪስት መስህቦች የሚገኙበት ነው፡፡

በተራራው ከአምስት በላይ የተፈጥሮ ዋሻዎች ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህ መስህቦች መካከል የጥንታዊ "ሞቼና ቦራጎ" ዋሻ አንዱ ነው። ጥንት በዋሻው ሰዎች ይኖሩ እንደነበረም ታሪክ ያስረዳል። ዋሻው በውስጡ ከአምስት መቶ በላይ ሰዎች የመያዝ አቅም እንዳለውም ይነገራል፡፡ ስፋቱ 38 ሜትር ሲሆን የጣሪያው ከፍታ 33 ሜትር እንዲሁም የዋሻው ዙሪያ ልኬት ደግሞ 58 ሜትር መሆኑንም መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

ዳሞታ ተራራ የተለያዩ መስህቦች ባለቤት ሲሆን የነገስታት መኖሪያ ሥፍራዎች፣ ፏፏቴዎች፣ ደብረ-መንክራት አቡነ ተክለኃይማኖት ገዳምን ጨምሮ የተለያዩ አብያተ ክርስቲያናትና አድባራት የሚገኙበትና ድንቅ የቱሪዝም መዳረሻም ነው፡፡
ወላይታ ሶዶን ይጎብኙ አገርዎን ይወቁ!! ቸር እንሰንብት!!

የጀበና ቡና ሻጯ በትራፊክ አደጋ ህይወቷ አለፈ 😭   | የጀበና ቡና በመሸጥ ህይወቷን ስትመራ የነበረችው ወጣት በደረሰባት የመኪና አደጋ ህይወቷ ማለፉ ፖሊስ አስታውቋል፡፡የአዲስ አበባ ፖሊስ...
06/05/2024

የጀበና ቡና ሻጯ በትራፊክ አደጋ ህይወቷ አለፈ 😭

| የጀበና ቡና በመሸጥ ህይወቷን ስትመራ የነበረችው ወጣት በደረሰባት የመኪና አደጋ ህይወቷ ማለፉ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳስታወቀው እሁድ በፋሲካ እለት በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሶስት ቡና በመሸጥ ላይ የነበረችው ወጣት ወደ ኋላ እየሄደ በነበረ የኤፌሰር መኪና ተገጭታ ህይወቷ አልፋል ብሏል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግኙኝነት ባለሙያ ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት በጥንቃቄ ጉለት ወጣቷ ህይወት አልፏል ብለዋል፡፡

አሽከርካሪዎች ከብቃት ማነስ እና በተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ በሰው እና በንብረት ላይ የሚያደርሱት አደጋ ቀላል የሚባል አይደልም ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በትራፊክ አደጋ በርካቶች እንደወጡ ወደ ቤታቸው ሳይመለሱ ቀርተዋል ያሉት ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ እንደ ሃገር ምፍትሔ ሊሰጠው የሚገባ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

በጥንቃቄ ጉድለት ምክንያት በአንድ ሰው ላይ የሚደርሰው የትራፊክ አደጋ ከጀርባው የበርካቶችን ተስፋ ያጨልማል፣ የሞቀ ቤትን ያቀዘቅዛል እንዲሁም ፈርጀ ብዙ ጉዳትን ያስከትላል ብለዋል።

በሔኖክ ወ/ገብርኤል

መቀመጫውን ደቡብ አፍሪካ አድርጎ የኢትዮጵያ ሴቶች ገላን ለአፍሪካ ወሲ*ብ ገፅች የሚሸጥ የሀዲያ ብሔር ተወላጅ‼️ከዚህ ድርጊት እንዲቆጠብ አንዲት የዎላይታ ሴት ልጅ በማጋለጧ  የሀዲያ ወንዶች...
06/05/2024

መቀመጫውን ደቡብ አፍሪካ አድርጎ የኢትዮጵያ ሴቶች ገላን ለአፍሪካ ወሲ*ብ ገፅች የሚሸጥ የሀዲያ ብሔር ተወላጅ‼️
ከዚህ ድርጊት እንዲቆጠብ አንዲት የዎላይታ ሴት ልጅ በማጋለጧ የሀዲያ ወንዶች ከዎላይታ ሴቶች ውጭ መኖር አይችሉም በማለት ከሰሞኑ የዎላይታን ብሔር ማንቋሸሽ የዎላይታን ሴቶችን ክብር መንካት ስራዬ ብሎ ተያይዞታል።

ይህ ግለሰብ በTiktok ስሙ "Ye Gondre Liji ney" ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ትክክለኛ ስሙ Dawit ይባላል። ብሔሩ ደግሞ የሀዲያ ተወላጅ ነው። ይህ ግለሰብ በደቡብ አፍሪካ መቀመጫ ላደረጉ የአፍሪካ ወሲ*ብ ድህረገጾች የኢትዮጵያ ሴቶችን ገላ የሚቸረችር ሲሆን እሱ ብቻ አይደለም ከእሱ ጋር ወደ 5 የሚጠጉ ደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ የሀዲያ ብሔር ተወላጆ በTiktok , እና Telegram ላይ ከሴቶች የቀዱትን የራቁት ቪዲዮ ብር ካልሰጣችሁ በማለት የኢትዮጵያ ሴቶችነን ገላ ለአፍሪካ ወሲ*ብ ገፆች የሚቸረችሩ የሀዲያ ብሔር ተወላጆች ናቸው።

ውድ ኢትዮጵያዊያን ውድ የሀዲያ ብሔር ተወላጆች እንዲህ አይነት የሀገር እና የወጡበትን ብሔር የሚያሰድቡ ሰዎችን አይታቹ ዝም ብላችሁ ማለፍ ለሀዲያ ብሔር ስም መጥፋታ አልፎም የሀገራችን ሴቶች ክብር የኢትዮጵያ ስም ማርከስ ስለሆነ የተከበራችሁ የሀዲያ ብሔር ተወላጆች በእንደዚህ አይነት ግለሰቦች እና ቡድኖች ላይ እርምጃ እንድትወስዱ ስንል እንደ አንድ ኢትዮጵያዊን እንጠይቃለን።

በደቡብ አፍሪካ የሀዲያ ተወላጆች ጉዳዩን ጊዜ ሳትሰጡ ስነስርዓት እንድታስይዙ እንጠይቃለን።

09/09/2023

ራሱን Excellence center ብሎ
የሚጠራውን ግለሰብ እናጋልጣለን ማለታችን ይታወሳል ነገር ግን ወደ መስመር ስለተመለሰ ለጊዜው ይቆይ ብለን ወስነናል።

07/09/2023

ፕሬዚዳንቱ ሕፃን ልጅ አይደለም
መሠሪያ ቤት ገባ ወይ አልገባ
እያልክ የምትከታተለው!
አንተ የቀበሌ ካድሬ!

06/09/2023

ራሱን Excellence center ብሎ
የሚጠራ ግለሰብ ማን እንደሆነ እናውቃለን!
ካላረፍክ ይፋ እናደርጋለን!

06/09/2023

አንዳንድ ተራ የሰፈር ሚዲያዎች
ከሚሰራጩት ሀሰተኛ መረጃ
ተጠንቀቁ!

"ያሉንን ፀጋዎች ተጠቅመን በአዲሱ ዓመት ለዉጤታማነት መትጋት ይገባል" - ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደበጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ የግብርናና የገጠር ልማት ክላስተር ስራን በይፋ ለማስጀር ...
05/09/2023

"ያሉንን ፀጋዎች ተጠቅመን በአዲሱ ዓመት ለዉጤታማነት መትጋት ይገባል" - ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ

በጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ የግብርናና የገጠር ልማት ክላስተር ስራን በይፋ ለማስጀር በተዘጋጀ መርሃ ግብር ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ባስተላለፉት መልዕክት በአዲሱ ዓመት በክልሉ ያሉ ፀጋዎችን በመጠቀም ለዉጤታማነት መትጋት ይገባናል ብለዋል።

በክላስተሩ የተመደቡ አመራሮች ሕዝቡን በማስተባበር ዉጤታማ ስራ መስራት እንደሚገባም አሳስበዋል።

የዞኑ ነዋሪዎች ፣የሀገር ሽማግሌዎች ፣መሁራን ከክልሉ አመራር ጋር በትብብር እንዲሠሩም መልዕክት አስተላልፈዋል።

የተጋመድን ህዝቦች ነን ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ አንድነታችንን አፅንተን ከሄድን በርካታ ስኬቶችን ማስመዝገብ እንችላለን ብለዋል። በዞኑ ነዋሪዎች ለተደረገላቸው አቀባበልም ምስጋና አቅርበዋል ።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለማዕከልነት ከተመረጡ ከተሞች አንዷ በሆችዉ ዲላ ከተማ የግብርናና ገጠር ልማት ተቋሟት ስራቸዉን በይፋ ጀምረዋል ።
05/09/2023

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለማዕከልነት ከተመረጡ ከተሞች አንዷ በሆችዉ ዲላ ከተማ የግብርናና ገጠር ልማት ተቋሟት ስራቸዉን በይፋ ጀምረዋል ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መዲና ዎላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ የክልሉ ሕዝብ የዘመን መለወጫ በዓል ግፋታን ለማክበር በቂ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገለፅ። የከተማዋ አስተዳደርም ሰፊ ዝግጅቶ...
05/09/2023

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መዲና ዎላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ የክልሉ ሕዝብ የዘመን መለወጫ በዓል ግፋታን ለማክበር በቂ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገለፅ። የከተማዋ አስተዳደርም ሰፊ ዝግጅቶችን እያካሄደ ነው።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተደድር አቶ ጥላሁን ከበደ ዲላ ከተማ ገቡርዕሰ መስተዳደሩ እና ሌሎች ከፍተኛ የክልሉ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች የግብርናና የገጠር ልማት ክላስተር ስራን በይ...
05/09/2023

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተደድር አቶ ጥላሁን ከበደ ዲላ ከተማ ገቡ

ርዕሰ መስተዳደሩ እና ሌሎች ከፍተኛ የክልሉ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች የግብርናና የገጠር ልማት ክላስተር ስራን በይፋ ለማስጀመር ዲላ ከተማ ገብተዋል።

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳደር አቶ አክልሉ ለማ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ የተሰጠውን ሹመት ውድቅ ማድረጉ ታውቋል። ከጠቅላይ ሚኒስቴር ዓብይ አሕመድ ጋር ጉዳ...
05/09/2023

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳደር አቶ አክልሉ ለማ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ የተሰጠውን ሹመት ውድቅ ማድረጉ ታውቋል። ከጠቅላይ ሚኒስቴር ዓብይ አሕመድ ጋር ጉዳይ ያለው ይመስላል።

"ህዝቡ ለክልሉ ምስረታ ያበረከተውን አስተዋጽ በልማቱ ስራ መድገም አለበት"  ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደነሐሴ 24/2015 የክልሉ ህዝብ አዲሱን ክልል ለመመስረት ያበረከተውን አስተዋጽ በ...
30/08/2023

"ህዝቡ ለክልሉ ምስረታ ያበረከተውን አስተዋጽ በልማቱ ስራ መድገም አለበት" ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

ነሐሴ 24/2015 የክልሉ ህዝብ አዲሱን ክልል ለመመስረት ያበረከተውን አስተዋጽ በልማት ስራው እንድደግም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰመስተዳድር አቶ ጥላሁን ጠየቁ።

ርዕሰ መስተዳድሩ የክልሉን ቀጣይ አቅጣጫዎችን በሚመለክት ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው መግለጫ ሰጥቷል።

ክልሉ ከነገ ከነሐሴ 25/2015 ዓ ም ጀምሮ በሁሉም ክላስተር ማዕከላት መደበኛ ስራቸውን እንደሚጀምሩ ርዕሰ መስተዳደሩ ዛሬ በጽህፌት ቤታቸው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ገልጸዋል።

በክልሉ በስድስቱ ማዕከላት አመራሮች ዋና ዋና ምደባዎች በዚህ ሳምንት እንደምጠናቀቁና ከነባር ሰራተኞች ጋር በማቀናጀት ወደ ስራ የማስገባት ዝግጅት መደረጉንም ርዕሰ መስተዳድሩ በመግለጫቸው አንስተዋል።

የክልሉን ሠላምና ደህንነት የማጠናከር ስራ ከሁሉም ቅድሚያ ተሰጥቶ እንደሚሠራ የገለጹት አቶ ጥላሁን በዚሁም "የሠላሙ ባለበት የሆነው ህዝባችን ለተግባራዊነቱ የራሱን ድርሻ እንድወጣ እጠይቃለው" ሲሉም ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

በግብርናው መስክ የመኸር ስራውን በግብዓት መደገፍ፣ መስኖ ገብ አከባቢ ስራዎችን ማጠናከርና የምግብ ዋስትና ስራዎች ላይ ያተኮሩ ስራዎች ላይ ያተኮሩ ድጋፎች እንደሚካሄዱም ገልጸዋል።

ያደሩ የፕሮጀክት ስራዎችን ማጠናቀቅም ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ገልጸው፣ የክልሉ ህዝብ የሚያነሳቸውን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ወጪ ቆጣቢ በሆነ መንገድ በሁሉም ክላስተር ማዕከላት ለመስጠት ዝግጅት መደረጉንም ገልጸዋል።

የክልሉን ህዝቦች ከሚያለያዩት በላይ የሚያቀራረቡት ይበዛሉ ያሉት ርዕሰ መስተዳደሩ፣ የክልሉን ህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ስራዎችን በሁሉም ማህበራዊ መሠረቶች ለማጠናከር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሠራም ገልጸዋል።

የክልሉ ምስረታ በሰላም እንድጠናቀቅ የክልሉ ህዝብ ላበረከተው አስተዋጽኦ ያላቸውን አድናቆትና ምስጋና አቅርበው ይህንን በጎ ተግባር በቀጣይ በልማትም እንድደግም ጠይቀዋል።

ዜና ሹመትአቶ ሐይለማሪያም ተስፋዬ (የቀድሞ ደቡብ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ የነበሩ ከጌዴኦ )የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ቢሮ ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል ።
30/08/2023

ዜና ሹመት
አቶ ሐይለማሪያም ተስፋዬ (የቀድሞ ደቡብ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ የነበሩ ከጌዴኦ )

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ቢሮ ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል ።

ዜና ሹመት አቶ ብርሃኑ ዘውዴ ( ጋሞ ዞን አስተዳዳሪ የነበሩ ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል።
30/08/2023

ዜና ሹመት
አቶ ብርሃኑ ዘውዴ ( ጋሞ ዞን አስተዳዳሪ የነበሩ )

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል።

ዜና ሹመት አቶ አክልሉ ለማ (የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ የነበሩ ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል።
30/08/2023

ዜና ሹመት
አቶ አክልሉ ለማ (የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ የነበሩ )

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል።

የክልሉን አቅም አሟጦ በመጠቀም የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል--ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የክልሉን አቅም አሟጦ በመጠቀም በአጭር ጊዜ ውስጥ ለውጥ ለማምጣትና የህዝብን ተጠቃሚነ...
24/08/2023

የክልሉን አቅም አሟጦ በመጠቀም የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል--ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

የክልሉን አቅም አሟጦ በመጠቀም በአጭር ጊዜ ውስጥ ለውጥ ለማምጣትና የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድሩ እንደገለጹት በቅርቡ የተመሰረተውን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚመሩ አመራሮች ተመድበው ሥራ ጀምረዋል።

በክላስተር አወቃቀር የተደራጀው ክልሉ ስድስት መቀመጫ ከተሞችን በመምረጥ በዋናነት የመንግስትና የህዝብ አገልግሎትን ተደራሽ ማድረግ የሚያስችሉ ሥራዎችን ለማከናወን እየተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት ቢሮዎችን የማደራጀት፣ የሰው ሃይል የመመደብና ሌሎችም የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን አቶ ጥላሁን ገልጸዋል።

ቀድሞ የነበረው ክልል ለአንዳንድ አካባቢዎች ርቀት ስለነበረው የመንግሥት አገልግሎት ተደራሽነት ላይ ክፍተት ከመኖሩ ባለፈ የህዝብን ተጠቃሚነትና ወቅታዊ ፍላጎትን ያላማከለ እንደነበር አስታውሰዋል።

ይህንን ሁኔታ ለመቀየር፣ የህዝቡን መሰረታዊ ፍላጎት ለማሟላትና ባለቤትነቱን በተጨባጭ ለማረጋገጥ ክልሉ መመስረቱንም አቶ ጥላሁን አስታውቀዋል።

ለክልሉ በመቀመጫነት የተመረጡት ከተሞች ለህዝቡ ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመዘርጋትና መልካም አስተዳደርን ማስፈጸም የሚያስችል ነው ብለዋል።

ይህም ህዝቡ በቅርበት አገልግሎት እንዲያገኝ፣ የከተሞችም እድገት የተመጣጠነና የተቀራረበ እንዲሆን ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር አስታውቀዋል።

ክልሉ የተፈጥሮ ጸጋን የተጎናጸፈ መሆኑን ጠቁመው፣ በተለይ ለሜካናይዜሽን ግብርና ልማት አመቺ የሆነ ሰፊ ያልታረሰ መሬት፣ አመቱን ሙሉ የሚፈሱ ወንዞች፣ ሰፊ የከርሰ ምድርና የገጸ ምድር ውሃ ሀብት ባለቤት መሆኑንም አመልክተዋል።

በክልሉ በሁሉም መስክ በተነደፉ የአጭር፣ የመካከለኛና የረዥም ጊዜ እቅዶች ፈጣን ልማት ለማረጋገጥና ህዝብን ተጠቃሚ ለማድረግ የክልሉ መንግሥት አበክሮ ይሰራል ብለዋል።

ይህንን አቅም በአግባቡ ለመጠቀም የባለሀብቱንና የህዝቡን ተሳትፎ ከማሳደግ ባለፈ የክልሉን ኢኮኖሚያዊ አቅም አሟጦ በመጠቀም በአጭር ጊዜ ውስጥ ለውጥ ለማምጣትና ህዝብን ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

በዚህ ረገድ ክልሉ የገቢ አቅም እንዳለው የጠቆሙት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ ከተለያዩ አካላት ጋር በመምከር የገቢ አቅምን ከፍ ለማድረግ ጥረት ይደረጋል ብለዋል።

በቀጣይ በክልሉ ልማትና እድገትን ለማረጋገጥ በሚደረገው እንቅስቃሴ ሁሉም አካላት የበኩሉን እገዛ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል ሲል ኢዚአ ዘግቧል።

ከክልል አደረጃጀት ጋር ተያይዞ የነበረው የህዝብ ጥያቄ ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እልባት አግኝቷል - ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ነሐሴ 15/2015 (አዲስ ዋልታ) ከክልል አደረጃጀት ጋ...
21/08/2023

ከክልል አደረጃጀት ጋር ተያይዞ የነበረው የህዝብ ጥያቄ ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እልባት አግኝቷል - ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

ነሐሴ 15/2015 (አዲስ ዋልታ) ከክልል አደረጃጀት ጋር ተያይዞ የነበረው የህዝብ ጥያቄ ሰላማዊ፣ ፍትሃዊ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እልባት ማግኘቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ በሰጡት መግለጫ ከዚህ ቀደም ህዝቡ በልማት እና በመልካም አስተዳደር ላይ በርካታ ጥያቄዎችን ሲያነሳ እንደነበር አስታውሰው በተለይ ከክልል አደረጃጀት ጋር ተያይዞ የነበረው ጥያቄ እልባት ማግኘቱን አንስተዋል።

ከዚህ ቀደም በልዩ ወረዳነት መዋቅር ስር የነበሩ ህዝቦች በዞን የመደራጀት ፍላጎት እንዳላቸው ስጠይቁ መቆየታቸውን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ መንግስት እና መሪው ፓርቲ የህዝቡን የመልማት ጥያቄ በማጤን ምላሽ ለመስጠት ቃል በገባው መሰረት አሁን ላይ ምላሽ ማግኘቱን አብራርተዋል።

አዲስ በተመሰረተው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማግስት ላይ የህዝቡ በዞን የመደራጀት ፍላጎቱ እውን መሆኑን ተከትሎ ህዝቡ ለመንግስት እና ለመሪው ፓርቲ አደባባይ በመውጣት ደስታውንና ምስጋናውን ሲገልጽ መቆየቱን በመግለጫቸው ጠቁመዋል።

በዞን የመደራጀት ዋናው አላማ መንግስታዊ አገልግሎቶችን በቅርበት ለህዝቡ ማድረስ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን አዲስ የተመሰረቱትን የዞን እና የወረዳ መዋቅሮች ፈጥነው ወደ ስራ መግባት እንዳለባቸውና ለዚህም የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
ለህዝብ በቅርበት አገልግሎት መስጠትን መሰረት ባደረገው የክልል፣ የዞን እና የወረዳ መዋቅር በክልሉ ያለውን አቅም በማስተባበር የላቀ የልማት ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሰራም ርዕሰ መስተዳድሩ ማብራራታቸውን ከክልሉ ኮሙዩኒኬሽን መረጃ አመላክቷል።

ከክልል እስከ ዞን ያለውን አዲስ መዋቅር የህብረተሰቡን የመልማት እና የማደግ ፍላጎት ማሳኪያ አዲስ ምዕራፍ እንደመሆኑ ህብረተሰቡ በሁሉም መስክ መንግስት እና ፓርቲ በሚያደርገው ጥሪ የላቀ ድጋፍና ተሳትፎ እንዲያደርግም ጥሪ አቅርበዋል።

21/08/2023

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል
ወቅታዊ መረጃዎችን
ማድረስ እንቀጥላለን።
Like , share አድረሰጉ!

ኮሬ ዞን መዋቅር መልስ ማግኘቱን ተከትሎ በከተማዋ ሕዝቡ ከአመራሮች ጋር ደስታውን ገለፀ። የኮሬ ዞን፦አንድነታችንን ያጠናከረ ፣ቤታችንን በፍቅር ያደሰ ፣የትግል አጋሮችን በደስታ ያፈነደቀ፣ የ...
21/08/2023

ኮሬ ዞን መዋቅር መልስ ማግኘቱን ተከትሎ በከተማዋ ሕዝቡ ከአመራሮች ጋር ደስታውን ገለፀ።
የኮሬ ዞን፦አንድነታችንን ያጠናከረ ፣ቤታችንን በፍቅር ያደሰ ፣የትግል አጋሮችን በደስታ ያፈነደቀ፣ የልዩነት ሰንሰለት ያበጣጠሰ ፣የቂምና የጥላቻ ምዕራፍ ያዘጋ እና በሕሊናችንንና በመንፈሳችን ታድሰን በለውጥ ጎዳና ተደምረን ደስታን እንድናጣጥም ያደረገ ነው።ስለሆኔም ተከበራችሁ የአማሮ ኮሬ ዞን ነዋሪዎች ፣የሀገር ሽማግሌዎች ፣የሀይማኖት መሪዎች ፣አመራሮችና ምሁራንኖች ፣የነብር ጣት የሆናችሁ ወጣቶችና ሴቶች እንድሁም የተፎካካሪ ፓርቲ አባላቶች የኮሬ ህዝብ የዘመናት ጥያቄ የነበረው የአደረጃጀት ጥያቄ ምላሽ በማግኘቱ በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ/አልን።ከዚህ በሃላ ለኮሬ ዞን እድገት በሃሳብም በተግባርም በአንድነት እጅ ለእጅ ተያይዘን የምንሰለፍበት ወቅት ነው።
ኮሮ ነደንሶይ ኡከኮ በራይ ኑኑኑ በራኮ!!!

ከኮሬ ዞን የደረሰ መረጃ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ ከተማ ዎላይታ ሶዶ የፖለቲካ እና የአስተዳደር ዋና መቀመጫ።
21/08/2023

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ ከተማ ዎላይታ ሶዶ የፖለቲካ እና የአስተዳደር ዋና መቀመጫ።

በጋሞ ዞን የትኛውም አከባቢ የተፈቀደ ምንም ዓይነት ሰላማዊ ሰልፍ አለመኖሩን የዞኑ ፀጥታ ኮማንድ ፖስት ገለፀ አርባምንጭ  ነሐሴ 03/2015 ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሚዩኒኬሽን)፦ በተለያዩ ማ...
09/08/2023

በጋሞ ዞን የትኛውም አከባቢ የተፈቀደ ምንም ዓይነት ሰላማዊ ሰልፍ አለመኖሩን የዞኑ ፀጥታ ኮማንድ ፖስት ገለፀ

አርባምንጭ ነሐሴ 03/2015 ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሚዩኒኬሽን)፦ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ነገ ሐሙስ ነሃሴ 04/2015 ዓ.ም በዞኑ ሁሉም አከባቢዎች በተለይ አርባምንጭ ከተማ ሠላማዊ ሰልፍ እንደሚካሄድ የሚገልፁ መረጃዎች እየተሰራጩ እንደሚገኝ የጋሞ ዞን ፀጥታ ኮማንድ ፖስት ገልጿል ።

ባለፉት ጊዜያት በመላው የሃገሪቱ ክፍል የፀጥታ መደፍረስ በገጠመ ጊዜ እንኳ የጋሞ ህዝብ ባህላዊ እሴቱን ተጠቅሞ የአከባቢውን ሰላም አስጠብቆ መዝለቁን የገለፀው የኮማንድ ፖስቱ መግለጫ ይህን ለማሳጣት እና የህዝቡን ስነ-ልቦና የማይመጥን ተግባር ለመፈፀም እኩይ አካላት ቀን ከሌት እየሰሩ ይገኛሉ ብሏል።

ለአከባቢው ሰላም እና ለህዝብ ደህንት ሲባል በዞኑ የትኛውም አከባቢ የተፈቀደ ምንም አይነት ሰላማዊ ሠልፍ አለመኖሩን የገለፀው ኮማንድ ፖስቱ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ይህን በመገንዘብ የዕለት ተዕለት ተግባሩን እንዲቀጥልም አሳስቧል።

የጋሞ ዞን በዓለም የሚታወቀው በሰላም አምባሳደርነቱ በመሆኑ ሁሉም የዞኑ ነዋሪ ይህን እሴቱን ለማጥፋት የሚሯሯጡ አካላትን ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ሊከላከላቸው እንደሚገባም የዞኑ ፀጥታ ኮማንድ ፖስት ጥሪ አቅርቧል።

የጋሞ ዞን በዓለም የሰላም አምባሳደርነት ተጠናክሮ ይቀጥላል።

የወላይታ ሶዶ ከተማ እንግዶቿን ለመቀበል የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶችን አጠናክራ ቀጥላለች።በዛሬው ዕለትም የከተማዉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ከከተማዉ ወጣቶች አደረጃጀቶች ጋር በመቀናጀት...
08/08/2023

የወላይታ ሶዶ ከተማ እንግዶቿን ለመቀበል የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶችን አጠናክራ ቀጥላለች።

በዛሬው ዕለትም የከተማዉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ከከተማዉ ወጣቶች አደረጃጀቶች ጋር በመቀናጀት ዋና ዋና የእግረኛ መሸጋገሪያን በተለምዶ ዜብራን የማስዋብ ሥራ በመከናወን ላይ ይገኛ።

የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ምክር ቤት አዲሱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በይፋ መመስረቱን መግለፁ ይታወሳል።

ዘገባው የከተማ አስተዳደር ነው።

የክልሉ ርዕሰ መዲና ዎላይታ ሶዶ ብሔር ብሔረሰቦች ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን የከተማዋ ከንቲባ አስታወቀ።South Ethiopia Times
08/08/2023

የክልሉ ርዕሰ መዲና ዎላይታ ሶዶ ብሔር ብሔረሰቦች ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን የከተማዋ ከንቲባ አስታወቀ።
South Ethiopia Times

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Ethiopia Times posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Videos
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share