WE Ethiopians

WE Ethiopians የመንግስት ዋነኛው ተግባር የዜጎች ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ ነው !!
ይህንን ተግባር የማያከናውን መንግስት እንደ መንግስት አይቆጠርም !!

government's primary duties are maintaining peace and security for the citizens
If the government is not provide the above activities it is fragile government .

ለአብይ እና ለብልፅግና ደጋፊዎች...========================ለለማ መገርሳ ያልሆነ አብይ በዚህች ምድር ላይ ለማንም አይሆንም:: ለማ ባይኖር አብይ የሚባልን ስው አናውቀውም ነበ...
01/20/2025

ለአብይ እና ለብልፅግና ደጋፊዎች...
========================
ለለማ መገርሳ ያልሆነ አብይ በዚህች ምድር ላይ ለማንም አይሆንም:: ለማ ባይኖር አብይ የሚባልን ስው አናውቀውም ነበር:: አብይን እጁን ይዞ አሁን ላለበት ደረጀ ያደረስው ለማ መገርሳ ነው:: ይህ ሀገር ያወቀው ፁሃይ የሞቀው እውነት ነው:: አብይ ግን መጀመሪያ ያባረረው እና ያዋረደው ለማን ነው:: አብይ በአንድ ወቅት "የችግር ጊዜ ወዳጄ" ባለው ለማ ላይ ይህንን ያህል ክደት ከፍፀመ; ለማንም አይመለስም የሚለው::

ሌላው ለታዬ ደንደአ ያልሆነ ብልፅግናና መደመር ለማንም አይሆንም:: በኢትዮጵያ እንደ ታዬ ደንደአ ብልፅግናና የስበከ መደመርን ከልቡ ተቀብሎ ያስተጋባና defend ያደረገ የለም::አሁን ያሉት ሺ ካድሬዎች አንድ ላይ ተደምረው አንዱን ታዬን አያክሉትም:: ነገር ግን ብልፅግናና መደመር ታዬን ከመታስር ቤተስቦቹም ሜዳ ላይ ከመበተን አላድኑትም ምህረትም አላደረጉለትም::

በአጭሩ አብይና ብልፅግና; የሚጨነቁት ለአንድ ስው እና ለስልጣኑ ብቻ ነው:: ስለ ሀገር, ስለ ህዝብ, ስለ አንተና ስለ ቤተስብህ ግድ የላቸውም:: ስለዚህ አብይና ብልፅግና ለማዳንና ለማትረፍ ከሚትጋጋጥ; ራስህንና ቤተስብህን አድን:: ምክሬ ነው

የትግራይ ትፕፈናቃዮች  ወድ ቦታችን መልሱን ብለው ለ3 ቀን ሌሊትም ጭምር ሰልፍ ወጥተዋል
01/15/2025

የትግራይ ትፕፈናቃዮች ወድ ቦታችን መልሱን ብለው ለ3 ቀን ሌሊትም ጭምር ሰልፍ ወጥተዋል

!!
👇👇👇
#ይኣኽል!!

አሁን ላለው የኢትይጵያ   ውጥንቅጥ ጅሓር ግምባር ቀደም ተጠያቂ ሰው ነው እንደ ጲላጦስ ንፁህ ነኝ እንዳትል ፀፀትማ ይገባክ ነበር ላጠፋከው ጥፋት !!
01/14/2025

አሁን ላለው የኢትይጵያ ውጥንቅጥ ጅሓር ግምባር ቀደም ተጠያቂ ሰው ነው እንደ ጲላጦስ ንፁህ ነኝ እንዳትል

ፀፀትማ ይገባክ ነበር ላጠፋከው ጥፋት !!

"አልጸጸትም" የሚለውንና 433 ገጾች ያሉትን በብዙ ድካም የታተመውና ሚሊዮን ብሮች ይታፈሱበታል የተባለውን መጽሐፍ በPDF አስረው በነጻ ማሰራጨታቸው ሳያንስ ጭራሽ በድምጽ አንብበውት ቀርጸው...
01/14/2025

"አልጸጸትም" የሚለውንና 433 ገጾች ያሉትን በብዙ ድካም የታተመውና ሚሊዮን ብሮች ይታፈሱበታል የተባለውን መጽሐፍ በPDF አስረው በነጻ ማሰራጨታቸው ሳያንስ ጭራሽ በድምጽ አንብበውት ቀርጸው በነጻ በየቴሌግራሙ አጋሩትና "ምነው ነውር አይደለም እንዴ የሰዉን ልፋት መና ማስቀረት ?" ተብለው ሲጠየቁ፣ እሱ እራሱ ማትሪክ ያለማንም ፈቃድ ሰርቆ በማሰራጨት ልምድ ያካፈለን ሰው ስለሆነ የእጁን እንዲያገኝ ነው አሉኝ። ለማንኛውም የመጽሐፉን ኮፒው ያላችሁ ላላገኙት በኮመንት ቦታ ሼር አድርጉላቸው።

12/12/2024

ህወሓት ምንጀሪኖ

12/12/2024

ህወሓትና ሞንጅሪኖ አለም ?

12/04/2024

ታዬ ደንደአ ከእስር ቢለቀቁም “ማስክ ባደረጉና በታጠቁ ሰዎች ተወስደዋል ተባለ

አቶ ታዬ ደንደዓ ዛሬ ህዳር 25 ቀን 2017 ዓ.ም. አመሻሹን ከማረሚያ ቤት ብለቀቁም ቤተሰቦቻቸውን ሳይቀላቀሉ ከማረሚያ ቤቱ በራፍ በጸጥታ ኃይሎች መወሰዳቸውን ቤተሰቦቻቸው ለዶይቼ ቬለ ገለጹ፡፡ ክስ ተመስርቶባቸው በእስር ላይ የሚገኙት አቶ ታዬ ደንደዓ ከትናንት በስቲያ ሰኞ ህዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም. የዋስትና መብት ተጠብቆላቸው ከእስር እንዲለቀቁ በፌዴራሉ ሰበር ሰሚ ችሎት መወሰኑ ይታወሳል፡፡

በተወሰነላቸውም መሰረት ቤተሰቦቻቸው በፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ መሰረት የሕግ ሂደቶቹን ባለፉት ሁለት ቀናት አጠናቀው አቶ ታዬ ዛሬ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር አመሻሹን 11 ሰዓት ላይ ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ቢለቀቁም የፀጥታ ኃይሎች የማረሚያ ቤቱ በራፍ ላይ ጠብቀው ወዳልታወቀ ስፍራ እንደወሰዱዋቸው ባለቤታቸው ወ/ሮ ስንታየሁ ዓለማየሁ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል፡፡

“ወደ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ስንመጣ ፊትለፊቱ ሁለት ፓትሮሎች ነበሩ” ያሉት ወ/ሮ ስንታየሁ “ማስክ ያደረጉ የደህንነት ሰዎች የሚመስሉ ሲቪል የለበሱና የታጠቁ አካላት ልክ አቶ ታዬ ከማረሚያ ቤቱ ወጥተው ደጅ ላይ ልንቀበለው ስንሄድበት መኪና አዘጋጅተሃል ወይ አሉትና ከዚያም አስቀድሞም እንደተጠራጠርነው ለሌላ ጉዳይ ትፈለጋለህ ብለውት ያዙት” ብለዋል፡፡
የአቶ ታዬ ባለቤት ወ/ሮ ስንታየሁ አክለው እንዳሉት ባለፈው ሰኞ የፌዴራል ሰበር ሰሚ ችሎት አቶ ታዬ እስካሁንም የዋስትና መብታቸው “በጠባብ የህግ ትርጉም ሳይጠበቅ መቆየቱን” አስረድቶ በ20 ሺህ ብር ዋስትና ክሳቸውን ከውጪ መከታተል እንዲችሉ ነበር ያለው፡፡ በዚሁ መሰረት ትናንትና የአቶ ታዬ ቤተሰቦች ወደ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ስያቀኑ በፍርድ ቤቱ የተላለፈላቸው ትዕዛዝ የቀንና የቁጥር ስህተት ያለው በመሆኑ እንዲስተካከል በተባለው መሰረት ዛሬ ከፍርድ ቤቱ ያንኑን አስተካክለው ወደ ማረሚያ ቤት ተመልሰው ሂደቱን አጠናቀው ማረሚያ ቤቱ በፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ መሰረት ብለቃቸውም ከወጡ በኋላ መወሰዳቸውን አሳዛኝ ሲሉ ገልጸውታልም፡፡

“ችሎቱ የተቻለውን ቢያደርግም የምናየው ነገር በጣም ያሳዝናል” ያሉት ወ/ሮ ስንታየሁ “ደብዳቤው ታርሞ በመምጣቱ ማረሚያ ቤት ቢለቃቸውም በውሉ ሰላምታ እንኳ ሳንባባል ነው ውጪው ላይ ከመሃላችን ነጥቀው የወሰዱት” በማለት የት እንደሚወስዱዋቸውም እንዳልተነገራቸው አስረድተዋል፡፡

የቀድሞ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታና የገዢው ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ ባለስልጣን የነበሩት አቶ ታዬ ደንደዓ ከተከሰሱባቸው ሦስት ክሶች ሁለቱ ውድቅ ተደርጎላቸው “ከህግ አግባብ ውጪ የጦር መሳሪያ ይዘው ተገኝተዋል” በሚል የተመሰረተባቸውን አንዱን ክስ በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት በመከላከል ሂደት ላይ እንደነበሩ የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ሥዩም ጌቱ በላከው ዜና አስታውሷል፡፡(DW)

Address

Washington D.C., DC
22145

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when WE Ethiopians posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to WE Ethiopians:

Videos

Share