ሰበር ዜና Ethiopian Breaking News

ሰበር ዜና Ethiopian Breaking News Connect with ሰበር ዜና to find daily breaking news as they happen in Ethiopia & around the globe all in one place by providing 24/7 coverage from all sources.

02/22/2025
03 Aug Afternoon Rateዛሬ በግል ባንኮች ያለው የውጭ ምንዛሬ ዋጋ ከላይ ተያይዟል።
08/03/2024

03 Aug Afternoon Rate

ዛሬ በግል ባንኮች ያለው የውጭ ምንዛሬ ዋጋ ከላይ ተያይዟል።

August 03 Rateበትናንትናውና  በዛሬው  በሚውለው በዶላር ምዛሬ ዋጋ መግዣው ላይ የ12 ብር ልዩነት ፤ በመሸጫው ላይ የ15 ብር ልዩነት ታይቷል።
08/03/2024

August 03 Rate

በትናንትናውና በዛሬው በሚውለው በዶላር ምዛሬ ዋጋ መግዣው ላይ የ12 ብር ልዩነት ፤ በመሸጫው ላይ የ15 ብር ልዩነት ታይቷል።

August 1 rate
08/01/2024

August 1 rate

07/10/2024

የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉhttps://t.me/BreakingNewsEthiopiaa" የተሰረቀ ስልካችሁን ማስረጃ በማቅረብ መውሰድ ትችላላችሁ " - ፖሊስየአዲስ አበባ ፖሊስ የተሰረቁ ሞባይ...
05/13/2024

የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/BreakingNewsEthiopiaa

" የተሰረቀ ስልካችሁን ማስረጃ በማቅረብ መውሰድ ትችላላችሁ " - ፖሊስ

የአዲስ አበባ ፖሊስ የተሰረቁ ሞባይል ስልኮችን ከሌቦች የሚረከብ ግለሰብን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አሳውቋል።

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው ማሞ ድልድይ አካባቢ ግንቦት 4/2016 ዓ/ም ከማለዳ 12 ሰዓት ከ20 ላይ አንድ ግለሰብ ሞባይል ስልክ መቀማታቸውን ገንደ ቆሬ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ቀርበው ሪፖርት ያደርጋሉ፡፡

ፖሊስ ጣቢያው ወንጀል ፈፃሚውን ለመያዝ ባደረገው ክትትል የተሰረቁ የሞባይል ስልኮችን ከሌቦቹ ላይ የሚረከብ " ታምራት ፍቅረማርያም " የተባለን ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሏል፡፡

በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ ባደረገው ብርበራ በእለቱ የተሰረቀውን የሞባይል ስልክና በልዩ ልዩ ጊዚያት ከሌቦች የተረከባቸውን ፦
➡️ 61 ስማርት ሞባይል ስልኮችን ፣
➡️ 251 የታብሌት ስልክ ሽፋኖችን ፣
➡️ 2 ላፕቶፖችን እና በጥሬ 60 ሺ አንድ መቶ ብር ከሌባ ተቀባዩ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ መያዙን አስታውቋል፡፡

ግለሰቡ የተሰረቁ ሞባይል ስልኮችን እና ልዩ ልዩ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን ከሌቦች ተቀብሎ የሚያስቀምጠው በተከራየው ቤት ውስጥ ነው ተብሏል።

ቤት የሚያከራዩ ግለሰቦች የተከራይን ማንነነት እና በምን ስራ ላይ እንደተሰማራ የማረጋገጥ ግዴታ እንደለባቸው ፖሊስ አሳስቧል።

" የሞባይል ስልክ ጠፍቶብኛል / ተሰርቂያለሁ " የሚል ማንኛውም ግለሰብ ገንደ ቆሬ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ በአካል በመቅረብ ስልኩን በመለየትና አስፈላጊውን ማስረጃ በማቅረብ ንብረቱን መረከብ እንደሚችል ተገልጿል።

የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉhttps://t.me/BreakingNewsEthiopiaaየቤንዚን የችርቻሮ መሸጫ ላይ ጭማሪ ተደረገ።የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፤ ከግንቦት 1 ቀን 20...
05/09/2024

የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/BreakingNewsEthiopiaa

የቤንዚን የችርቻሮ መሸጫ ላይ ጭማሪ ተደረገ።

የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፤ ከግንቦት 1 ቀን 2016 ዓ/ም ለሊት 6፡00 ሰዓት ጀምሮ በስራ ላይ ያለው የነጭ ናፍጣ ፣ የኬሮሲን ፣ የአይሮፕላን ነዳጅ ፣ የቀላል ጥቁር ናፍጣና የከባድ ጥቁር ናፍጣ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ አሳውቋል።

በዚህ መሰረት ፦

- ነጭ ናፍጣ ➡ ብር 79.75 በሊትር
- ኬሮሲን ➡ ብር 79.75 በሊትር
- የአውሮፕላን ነዳጅ ➡ ብር 70.83 በሊትር
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ ➡ ብር 62.36 በሊትር
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ ➡ ብር 61.16 በሊትር ሆኖ ባለበት ይቀጥላል።

የቤንዚን ችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ተደርጎ በሊትር 78 ብር 67 ሳንቲም ገብቷል።

 የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉhttps://t.me/BreakingNewsEthiopiaaበኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ መርሐ ግብር ሊጀምር ነው።የአዲስ...
05/08/2024



የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/BreakingNewsEthiopiaa

በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ መርሐ ግብር ሊጀምር ነው።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከመጪው ጀምሮ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ መርሐግብር እንደሚጀምር አስታውቋል።

ዩኒቨርሲቲው በቅደመ ምረቃና ድህረ ምረቃ ትምህርት ፕሮግራሞች ተመርቀው የስራ ዓለም ውስጥ ለሚገቡ ተመራቂዎች ራሱን የቻለ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ እንደሚሰጥ ገልጿል።

ፕሮግራሙ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀና የገበያውን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ነው ያለው ዩኒቨርሲቲው " ይህ መርሐ ግብር በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሰጥ ነው " ብሏል።

" የፕሮግራሙ መጀመር በሥራ ገበያው ውስጥ ብቁ ሙያተኞችን ለማግኘትና የዩኒቨርሲቲውን አቅምና ብቃት ያለው ባለሙያ የማፍራት ተልዕኮ የሚያሳካ ነው " ሲል ገልጿል።

የሙያ ብቃት ማረጋገጫው ላይ የሚሰጥ ሲሆን ይህ የሚመራበት አሰራር ይዘረጋል ተብሏል።

በትምህርት ስርዓት ውስጥ ያሉ #ተማሪዎችም ሆኑ በስራ ገበያ ያሉ ሰራተኞችና ምሁራን ለተማሩበት ሙያ የብቃት ማረጋገጫ ወይም መውሰድ እንደሚችሉ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አሳውቋል። #ኢዜአ

 የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉhttps://t.me/BreakingNewsEthiopiaaሀሙስ ግንቦት 1 ቀን 2016 ዓ/ም በአዲስ አበባ ለመምህራንና ለትምህርት ቤት አመራሮች የሙያ ብቃት ምዘ...
05/08/2024



የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/BreakingNewsEthiopiaa

ሀሙስ ግንቦት 1 ቀን 2016 ዓ/ም በአዲስ አበባ ለመምህራንና ለትምህርት ቤት አመራሮች የሙያ ብቃት ምዘና ፈተና እንደሚሰጥ ተነግሯል።

ፈተናው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ እና የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በጋራ በመሆን ነው የሚሰጡት ተብሏል።

ፈተናው በተመረጡ የመፈተኛ ጣቢያዎች በፈቃደኝነት ለተመዘገቡ 18 ሺህ 591 ለሚሆኑ መምህራንና የትምህርት አመራሮች እንደሚሰጥ ተገልጿል።

በፈተና ወቅት ተመዛኞች ስልክ ሆነ ማንኛውንም አይነት ኤሌክትሮኒክስ ግብአቶች ይዞ ፈተና ክፍል መግባት እንደማቻል ተገልጿል።

ተመዛኞች ፦

➡️ የታደሠ መታወቂያ ይዘው መገኘት እንደሚጠበቅባቸው ፣

➡️ ፈተናው ከመጀመሩ በፊት 1:00 ሠዓት ቀደም ብለው (1:30) ላይ የምዘና ፈተና መስጫ ቅጥር ግቢ ውስጥ መገኘት እንዳለባቸው እና አርፍዶ መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው ተብሏል።

ምንም እንኳን ፈተናው በፍቃደኝነት ለተመዘገቡ 18,491 መምህራን እና የትምህርት አመራሮች እንደሚሰጥ ቢገለጽም የምዘና ፈተና ለመውሰድ #ስላልተመዘገቡ ወይም ፍቃደኛ ስላልሆኑ መምህራን እና የትምህርት አመራሮች ምንም የተባለ ነገር የለም።

 የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉhttps://t.me/BreakingNewsEthiopiaaታግታ 150 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የተጠየቀባት ህጻን ተገኘች።የ2 ዓመት ከ8 ወር ዕድሜ ያላት አቢጊያ ዳን...
05/07/2024



የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/BreakingNewsEthiopiaa

ታግታ 150 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የተጠየቀባት ህጻን ተገኘች።

የ2 ዓመት ከ8 ወር ዕድሜ ያላት አቢጊያ ዳንኤል የተባለች ህፃን ነዋሪነቷ በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 " ሳርቤት ' አካባቢ ሲሆን ከመኖሪያ ቤታቸው ተወስዳ ትታገታለች።

አጋቿ ቸርነት ጥላሁን የተባለው ግለሰብ ነው።

ግለሰቡ ከቤተሰቡ ጋር በነበረው ቅርበት ህፃን አቢጊያን በተለያዩ ቦታዎች እየወሰደ በማዝናናት እንደ ቤተሰቡ አባል ያጫውታት እንደነበረ እና ከ5 ወር በላይ ከቤተሰቡ ጋር በትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪነት የነበረው ቅርብ ወንጀሉን በቀላሉ ለመፈፀም ምቹ ሁኔታን እንደፈጠረለት የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

ግለሰቡ ሚያዚያ 25 ቀን 2016 ዓ/ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ተኩል ገደማ ወደ ህፃኗ ወላጆች መኖሪያ ቤት በመሄድና "እናቷ አምጣት ብላኛለች "ብሎ ለቤት ሰራተኛዋ ከነገረ በሗላ ህፃን አቢጊያ ዳንኤልን ወስዶ በማገት ገንዘብ እንዲሰጠው ከወላጆቿ ጋር ሲደራደር ቆይቷል።

ተጠርጣሪው ግለሰብ 150 ሺህ የአሜሪካ ዶላር እንዲሰጠው በመጠየቅ ገንዘቡን ማግኘት ካልቻለ ግን ህፃኗን በህይወት እንደማያገኟት ሲዝት ነበር።

የአዲስ አበባ ፖሊስ፤ ህፃኗን ለማስመለስ እና ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ለማዋል ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመቀናጀት ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል።

በተደረገው ክትትልም ዛሬ ሚያዚያ 28/ 2016 ዓ/ም በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 አለም ሰላም ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተጠርጣሪው ተከራይቶ በሚኖርበት መኖሪያ ቤት ውስጥ ለ3 ቀናት ያህል ታግታ የቆየችው ህፃን አቢጊያ ዳንኤል ልትገኝ መቻሏን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

ምንም እንኳን ፖሊስ ህጿን መገኘቷን ቢገልጽም አጋቹ በቁጥጥር ስር ስለመዋሉ ያብራራው ነገር የለም።

የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉhttps://t.me/BreakingNewsEthiopiaaዛሬ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ET154 ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ እያለ በአውሮፕላ...
05/07/2024

የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/BreakingNewsEthiopiaa

ዛሬ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ET154 ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ እያለ በአውሮፕላን ውስጥ ጭስ ታይቷል።

ነገር ግን አውሮፕላኑ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያ በተመደበለት የመንገደኞች ማስተናገጃ በር ያለ ምንም እክል መቆሙን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሳውቋል።

መንገዶኞቹም ከአውሮፕላን ላይ ደህንነታቸው እንደተጠበቀ መወርዳቸውን ገልጿል።

" በአሁኑ ሰአት የክስተቱ መንስኤ በመጣራት ላይ ይገኛል " ያለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለተፈጠረው ክስተት ደንበኞቹን ይቅርታ ይጠይቋል።

" ፍጹም ሀሰተኛ ነው " - የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርየትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ከሰሞኑን የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሃይል /Rapid Support Forces - RSF/ በሚባል የሚጠራው " የህ...
05/07/2024

" ፍጹም ሀሰተኛ ነው " - የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ከሰሞኑን የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሃይል /Rapid Support Forces - RSF/ በሚባል የሚጠራው " የህወሓት ታጣቂዎች ከሱዳን ወታደራዊ ሃይል /SUDANESE ARMED FORCES SAF/ ጋር በማበር እየወጉኝ ነው " በማለት ያወጣውን መግለጫ ፍጹም ሀሰተኛ እና መሰረተ ቢስ እንደሆነ ገለጸ።

ሱዳን በእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ ከገባች በርከታ ወራት ያለፉ ሲሆን በዚህም የሱዳን ጦር እና ፈጥኖ ደራሹ ኃይል ደም አፋሳሽ ግጭት እያደረጉ ናቸው።

ታዲያ ፈጥኖ ደራሹ ኃይል " ህወሓት (TPLF) ከሱዳን ጦር ጋር ሆኖ ወግቶኛል " ብሏል።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ መግለጫ ለዘመናት የቆየውና በፅኑ መሰረት የቆመው የትግራይና የሱዳን ህዝቦች ወዳጅነት ከግምት ያላስገባ ነው ብሎታል።

" በሱዳን ያለው የአርስበርስ ግጭት ዓለምአቀፍ መልክ ለማስያዝና እርዳታ ለማግኘ ያለመ ነው " ሲልም ገልጿል።

ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ በዚሁ የሺዎች ህይወት በመቅጠፍ ላይ ያለውን የአገሪቱ የእርስ በርስ ጦርነት ላክ የህወሓት ሃይሎች ተሳትፈዋል የሚል ክስ ማቅረቡ " ሃሳባዊና መሬት ላይ መረጋገጥ የማይችል የለየለት ፈጠራ " ሲል አጣጥሎታል።

" በመሰረቱ ህወሓት የፓለቲካ ድርጅት እንጂ የሚያዘውና የሚያስተዳድረው ታጣቂ ሃይል የለውም " ያለው የጊዚያዊ አስተዳደሩ መግለጫ " የትግራይ ህዝብ ከወንድም የሱዳን ህዝብ የረጅም ጊዜ መልካም ግንኙነትና ጉርብትና አለው " ብሏል።

" ከዚህ አኳያ ትግራይ በሱዳን የውስጥ ጉዳይ ነገሮች በማጋጋል የምትገባበት ምክንያትና የምታገኘው ጥቅም የለም " ሲል አሳውቋል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ ፤ በሱዳን የተፈጠረው አውዳሚ የአርስ በርስ ጦርነት የሚያስከትለው አደጋ በመረዳት የውጭ ሃይሎች በአገሪቱ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ከመግባት እንዲቆጠቡ አሳስቧል።

የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/BreakingNewsEthiopiaa

ትላንት በአዲስ አበባ ፣ በቦሌ ክ/ከተማ " ስካይ ላይት ሆቴል " አካባቢ  #እግረኞች ላይ በደረሰ የትራራፊክ ግጭት 1 ሰው ሞቷል። አንድ ሰዉ ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል።በአቃቂ ቃሊቲ...
05/06/2024

ትላንት በአዲስ አበባ ፣ በቦሌ ክ/ከተማ " ስካይ ላይት ሆቴል " አካባቢ #እግረኞች ላይ በደረሰ የትራራፊክ ግጭት 1 ሰው ሞቷል። አንድ ሰዉ ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል።

በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በተለምዶው " ቸራአሊያ " በሚባል አካባቢ #እግረኛ ላይ በደረሰ ግጭት ደግሞ አንድ ሰዉ ሞቷል።

ልደታ ክ/ከተማም በተመሳሳይ የአንድ ሰው በትራፊክ አደጋ ሞቷል።

በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ደግሞ ቡና በመሸጥ ላይ የነበረችው ወጣት ወደ ኋላ እየሄደ በነበረ ኤፍኤሳር መኪና ተገጭታ ሞታለች።

የመረጃዎቹ ምንጮች የአዲስ አበባ ከተማ የትራፊክ ማኔጅመንት / የአዲስ አበባ ፖሊስ (ኢትዮ ኤፍ ኤም) ናቸው።

የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/BreakingNewsEthiopiaa

Address

Ring Road
Washington D.C., DC
2005

Opening Hours

Monday 9am - 5pm
Tuesday 9am - 5pm
Wednesday 9am - 5pm
Thursday 9am - 5pm
Friday 9am - 5pm
Saturday 9am - 5pm
6pm - 7pm

Telephone

+16479780112

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሰበር ዜና Ethiopian Breaking News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ሰበር ዜና Ethiopian Breaking News:

Share

Category