01/01/2023
ጋዜጠኝነት በኢትዮጵያ እዚህ ደረጃ ላይ ደርሷል ። ..
60 የሚደርሱ ተበዳይ ነን ባዬች ቤቴል አካባቢ የሚገኝ አንድ ሪል እስቴት ድርጅት ላይ ቅሬታ እንዳላቸው ለፋና ብሮድካስቲንግ ያሳውቃሉ።
ይህን የህዝብ ቅሬታ የሚድያ ሽፋን ለመስጠት የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ባልደረባ የሆኑት ጋዜጠኛ ብስራት መንግስቱ እና የካሜራ ባለሙያ ሳሙኤል ሀ/ሚካኤል ደግሞ ቦታው ላይ ተገኝተው መረጃ በመስብሰብ ላይ እያሉ የፖሊስ ልብስ የለበሱ ህግ አስከባሪዎች ምንም ዘገባ መስራት እንደማይችሉ ገልፀው በማመናጨቅ ወደ ቤተል ፖሊስ ጣቢያ ወስደው ያስሯቸዋል።
በእርግጥ ጋዜጠኞቹ ፤ ከአራት ሰዓታት የፖሊስ ጣቢያ እስር በሁላ ሊፈቱ ችለዋል። ሆኖም ግን የተበዳዮቹ ጉዳይ የሚድያ ሽፋን አላገኘም።
" የምርመራ ጋዜጠኝነት በቋሚነት እንዲሰራ እናደርጋለን " ብለው ፓርላማ ላይ ለተናገሩት ጠቅላይ ሚንስትር ፤ ይሄን መረጃ አድርሷቸው።
ሲሆን ሲሆን መንግስት ምርመራ ዘገባዎችን ለሚሰሩ ጋዜጠኞች ከለላ መሆን ይገባው ነበር። ጋዜጠኛ ውክልናው ለዜጎች ነው ። የዜጎች መረጃ የማግኘት መብት ደግሞ ሰብዓዊ መብት ነው። ጋዜጠኝነት ወንጀል አይደለም !
#ማናየእውነቱ