Hagere Infotainment

Hagere Infotainment Time is everything ! ይህ የቁምነገርና የመረጃ መለዋወጫ መማማሪያ ገጽ ነው ። ማንኛውንም አስተያየት ወይም ሀሳብ በጨዋነት መግለጽ የሀገራችን ሰው ባህል ነውና ካልተገባ ንግግር እንቆጠብ፣

በአዋሽ ፈንታሌ በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ወደ አጎራባች ስፍራዎች እየሸሹ መሆኑ ተገለጸበአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ከሰሞኑን በተደጋጋሚ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ...
01/02/2025

በአዋሽ ፈንታሌ በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ወደ አጎራባች ስፍራዎች እየሸሹ መሆኑ ተገለጸ

በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ከሰሞኑን በተደጋጋሚ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ በርካታ ሰዎች አከባቢያቸውን ለቀው አጎራባች ወደሆኑ ስፍራዎች እየሸሹ መሆናቸውን ነዋሪዎች ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።

ከሰሞኑ በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ እና ዱለሳ ወረዳዎች በተደጋጋሚ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ሳቢያ ከ30 በላይ ቤቶች መፍረሳቸውን ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ አንድ ነዋሪ በበኩላቸው ለአዲስ ስታንዳርድ ገልጸዋል።

መሬት መንቀጥቀጡ በብዛት ያለውና ጉዳት ያደረሰው ስኳር ፋብሪካ በሚገኝበት ዱለሳ ወረዳ ሰገንቶ ቀበሌ ላይ ነው ያሉት ነዋሪው፤ በተጨማሪም አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ ላይ በስፋት እየተከሰተ መሆንና ቤቶች ቀን በቀን እየፈረሱ መሆናቸውን ተልጸዋል።

አክለውም በርካታ ቤቶች መፍረሳቸውን፣ በአከባቢው የሚገኙ በርካታ ትምህርት ቤቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማጋጠሙን ተናግረዋል።

ለአብነትም በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ ሳቡሬ ቀበሌ የሚገኘው ኡንጋይቱ ት/ቤት ላይ ከፍተኛ ጉደት በመድረሱ የተነሳ ከትናንት ጀምሮ የመማር ማስተማር ሂደት መቋረጡን አመልክተዋል።

“ከዚህ ቀደም ተመሣሣይ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶች በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም ሲስተዋሉ ነበር” ያሉት ነዋሪ አክለውም በወቅቱ ተነካክተው ዘመም ብለው የነበሩ ቤቶች አሁን ላይ ከሰሞኑ እንደአዲስ ባገረሸው የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተት ምክንያት ሙሉ በሙሉ በመፍረስ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በተጨማሪም በአሁኑ ሰዓት በአከባቢው በተፈጠረ ስጋት የተነሳ በርካታ ሰዎች በተለይም ከዱለሳ ወረዳ ከሰም ስኳር ፋብሪካ አከባቢ ተነስተው ወደ አጎራባች ወደ ሆኑ አከባቢዎች በመሸሽ ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።

“ስኳር ፋብሪካው አከባቢ ያሉ ሰዎች ሙሉ በሙሉ አከባቢያቸውን ለቀው ወጥተዋል። ቤቶች ፈርሰዋል። ሰውም እቃውን ይዞ እየተሰደደ ነው ወደ አዋሽ አርባ። ብር ያለው በመኪና ይወጣል የሌለው በእግሩ በጫካም አድርጎ እየሸሸ ነው። የገጠሩ ማህበረሰብ ደግሞ እቃውን በግመል እየጫነ ከብቱን እየነዳ እየወጣ ነው። በጣም ችግር ውስጥ ነን ያለነው። አፋር ክልል ዞን ሶስት ፈንታሌ እና ዱለሳ ወረዳ በጠቅላላ ትልቅ ችግር ውስጥ ነው ያለው።” ብለዋል።

በመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት አስፋልት ሲሰነጠቅ ማየታቸውን ገልጸው አሁን ላይ ስንጣቂው እየሰፋ መምጣቱን እና ከሰዎች መኖሪያ ቤት ውስጥ ሳይቀር ውሃ ሲፈልቅ ማየታቸውን ጠቁመዋል።

ሌላኛው ኡስማን አብዲ የተባሉ ነዋሪ በበኩላቸው ተመሣሣይ ክስተቶች ከሶስት ወራት በፊት መከሰታቸውን አንስተው አሁን ላይ በድጋሚ የመሬት መንቀጥቀጡ ሳቡሬ፣ ቦሊቃ፣ ቀበና እና አርብሃራ በተሰኙ አከባቢዎች በስፋት መከሰቱን ገልጸዋል።

“በተለይም በአርብሃራ እና ቦሊቃ መካከል የተሰነጠቀው አስፋልት ጥልቀቱ በጣም ትልቅ ነው” ብለዋል።አያይዘውም በዱለሳ ወረዳ የሚኖረው አብዘሃኛው አርብቶ አደር የማህበረሰብ ክፍል ወደ አዋሻ ሰባት እና አርጎባ እየሸሸ መሆኑን ተናግረዋል።

እንዲሁም “በአዋሽ ፈንታሌ ሀራሜ በተሰኘው ስፍራ የሚገኘው የከሰም ግድብ ሊደረመስ ነው የሚል ወሬ በአከባቢው በመሰራጨቱ ምክንያት ባለፈው እሁድ ታህሳስ 19 ሌሊቱን ብዙ ሰዎች ቤት ንብረታቸውን ጥለው ሸሽተዋል” ብለዋል።

አክለውም የሚመለከተው አካል ለአከባቢው የተለየ ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል።ሌላኛው ስማቸውን እንዳንጠቀስ የጠየቁ በአዋሽ ሰባት ነዋሪ የሆኑ ግለሰብ በበኩላቸው ለአዲስ ስታንዳርድ እንደገለጹት “ከፍተኛ ስጋት አለባት” ብለው ከገለጿት እና በአዋሽ ፈንታሌ ከምትገኘው የዱሃ ቀበሌ በርካታ ሰዎች ቤት ንብረታቸውን ጥለው 43 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ወደሚገኘው አዋሽ ሰባት አከባቢ በመምጣት ላይ መሆናቸውን አስረድተዋል።

“በርካታ ሰዎች ናቸው በመግባት ላይ ያሉት። አቅም ያለው ቤት ተከራይቶ ገብቷል። ሌላው ደግሞ ከዘመድ ጋር ተጠግቶ ነው ያለው። ሸሽተው ሲመጡም አብዘሀኞቹ ከልጆቻቸው እና ከቤተሰቦቻቸው በቀር ይዘው የመጡት ንብረት የለም” ሲሉ ስለ ሁኔታው ያዩትን አብራርተዋል።

አዲስ ስታንዳርድ ጉዳዩን በተመለከተ ያነጋገራቸው የአዋሻ ፈንታሌ ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ አደን በለአ በበኩላቸው የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቱ ከዚህ ቀደም በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም በስፋት ሲታይ እንደነበረ ገልጸው አሁን ላይ ክስተቱ እንደአዲስ ማገርሸቱን ተናግረዋል።

አክለውም በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ ሳቡሬ ቀበሌ የሚገኘው የኡንጋይቱ መጀመርያ ደረጃ ት/ቤት ላይ ጉዳት መድረሱንና ትምህርት መቋረጡን አረጋግጠዋል። በተጨማሪም በዱሃ ቀበሌ የሚገኝ መስጂድ ላይ መሰነጣጠቅ አጋጥሟል ብለዋል።

በአሁኑ ሰዓትም ከጤና፣ ከትምህርት፣ ከሴቶችና ህጻናት፣ ከግብርና እና ከጸጥታ ጽ/ቤቶች የተውጣጣ የቴክኒክ ቡድን ተዋቅሮ ለህብረተሰቡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አመልክተዋል።

እንዲሁም በአከባቢው ከሚንቀሳቀሱ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር በመተባበር በስጋት ቀጠና ውስጥ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ወደ ተሻለ ቦታ የማዘዋወር ስራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በተጨማሪም ከክልሉ እና ከፌደራል የአደጋ መከላከል ኮሚሽኖች ጋር በመናበብ የተቀናጀ ስራ እየተሠራ እንደሚገኝ አበክረዋል።

ሰኞ ታኅሳስ 21 ቀን 2017 ዓ.ም. በተለይም በአዋሽ ተፋሰስ አካባቢ ንዘረታቸው እስከ አዲስ አበባ የተሰሙ ከ10 በላይ የተመዘገቡ የመሬት መንቀጥቀጦች መከሰታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

ሁኔታውን በተመለከተ ለቢቢሲ አስተያየታቸውን የሰጡት የኢትዮጵያ የርዕደ መሬት መመዝገቢያ መረብ ኃላፊ የሆኑት ፕ/ር አታላይ አየለ በበኩላቸው “መደናገጥ አያስፈገልግም” ብለዋል።

ፕ/ር አታላይ ሰሞነኛ ክስተቶች “መካከለኛ” ደረጃ የሚሰጣቸው ርዕደ መሬቶች መሆናቸውን ጠቁመው፤ ርዕደ መሬቶቹ የሚከሰቱባቸው ስፍራዎች ግን የጉዳት ደረጃቸውን እንደሚወስኑት መግለጻቸውን ከጣቢያው ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

“ጉዳት ለማድረስ መሀል ከተማ ከተፈጠረ 3.0 ሬክተር ስኬል ጉዳት ሊያደርስ ይችላል። የተፈጠረበት ቦታ የት ነው? የሚለው እንጂ አሁን የተፈጠረው ከፍተኛ ነው የሚባል አይደለም” ሲሉ አብራርተዋል።

ቀጠል አድርገው በኢትዮጵያ የርዕደ መሬት ክስተት ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚችል ሲናገሩም፤ “ከዚህ ከፍ ሊል የሚችልበትም እድል ይኖራል፤ እየቀነሰ ሊሄድም ይችላል። በቅርብ ጊዜ ግን የሚያቋርጥ አይመስልም” ብለዋል።

“ንዝረቱም እስከ አዲስ አበባ ድረስ ሊሰማ ይችላል። ግን በጉዳት ደረጃ እስካሁን የተመዘገበ የለም። ወደፊትም በ160 ኪ.ሜ በላይ ሄዶ ጉዳት ያደርሳል ብለን አንጠብቅም። ብዙ መደናገጥ አያስፈልግም ብለዋል።

ተጨማሪ መረጃዎች▻ https://t.me/felegethiopia

ሟቹ የአሜሪካ ፕሬዝደንት ጂሚ ካርተር ለመንግሥቱ ኃይለማርያም የላኩት ደብዳቤ "በቅርቡ በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ግጭት አስመልክቶ በተናገርኩት ንግግር የተፈጠረው አለመግባባት እጅግ አስገርሞኛል...
01/01/2025

ሟቹ የአሜሪካ ፕሬዝደንት ጂሚ ካርተር ለመንግሥቱ ኃይለማርያም የላኩት ደብዳቤ

"በቅርቡ በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ግጭት አስመልክቶ በተናገርኩት ንግግር የተፈጠረው አለመግባባት እጅግ አስገርሞኛል" ይላል ጂሚ ካርተር ከ46 ዓመታት በፊት ለቀድሞው ፕሬዝደንት ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም የላኩት ደብዳቤ። ጥር 19/1978 ፕሬዝደንት ጂሚ ለሊቀ መንበር መንግሥቱ የላኩት ደብዳቤ አሜሪካ እና ኢትዮጵያ ግንኙነታቸው በሻከረበት ወቅት የተፃፈ ነው።

ደብዳቤው 'ኦፊስ ኦፍ ዘ ሂስቶሪያን' የተሰኘው የአሜሪካ መንግሥት ታሪክ የሚመዘግብበት ድረ ገፅ ላይ ይገኛል። በዚህ ሳምንት በ100 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝደንት ጂሚ ካርተር ከአፍሪካ በተለይም ከአፍሪካ ቀንድ ጋር የነበራቸው ግንኙነት ስኬታማ የሚባል አልነበረም።

"አሜሪካ ሁሉም የአፍሪካ ሀገራት የግዛት አንድነታቸውን እንዲያስጠብቁ ድጋፍ ታደርጋለች። ሀገራት ግጭት ለመፍታት ሰላማዊ ያልሆነ አማራጭ መከተላቸውን እንወቅሳለን" ሲሉ ካርተር አቋማቸውን ይገልፃሉ። ከጂሚ ካርተር በፊት የነበሩት ሁለቱ የአሜሪካ ፕሬዝደንቶች ኒክሰን እና ፎርድ "ትዊን ፒላር" የተሰኘ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ነበር የሚከተሉት።

ጂሚ ካርተር ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ በመካከለኛው ምሥራቅ ሰላም ማስፈናቸው ምናልባት አሜሪካ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋን ቀይራ ይሆናል የሚል ግምት አጭሮ ነበር። በአውሮፓውያኑ 1977 ፕሬዝደንት ጂሚ ካርተር የአሜሪካ ፕሬዝደንት ሆነው ቃለ መሐላ በፈፀሙ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም የኢትዮጵያ መሪ ሆኑ።

ሚያዚያ 1977 ላይ አሜሪካ የቃኘው ጣቢያ መዘጋቱን እና በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል የተገባው ስምምነት ማብቃቱን አሳወቀች። ከዚህ በኋላ ነው የመንግሥቱ ኃይላማርያም መንግሥት ሙሉ በሙሉ ፊቱን ወደ ሶቪየት ያዞረው፤ አሜሪካ ደግሞ ወደ ሶማሊያ በመዞር ወታደራዊ እርዳታ ማድረግ ጀመረች።

ካርተር ለፕሬዝደንት መንግሥቱ የላኩት ደብዳቤ የሶማሊያ መሪ የነበሩት ሜጀር ጄኔራል ሲያድ ባሬ ኢትዮጵያን በወረሩበት ወቅት የተፃፈ ነበር። ጂሚ ካርተር በደብዳቤያቸው "እኛ ሶማሊያ ኦጋዴንን መውረሯን አንደግፍም። ለሶማሊያዎች የነገርናቸውም በኢትዮጵያ ምድር እስካሉ ድረስ ከእኛ ወታደራዊ ድጋፍ እንደማያገኙ ነው" ይላል።

በወቅቱ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል የነበረው ቁርሾ ከዐፄ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግሥት የተሻገረ ነው። አሜሪካ በኒክሰን ዘመነ መንግሥትም ሆነ በፎርድ አስተዳዳር ትከተለው የነበረው "ትዊን ፒላር" የተሰኘው ፖሊሲ "ትክክል አልነበረም" ብለው የሚከራከሩት ፖለቲካል ሳይንቲስቱ አዮዋኒስ ማንዚኮስ ናቸው።

ምሁሩ 'አሜሪካን ዲፕሎማሲ' በተሰኘው ድረ ገፅ ላይ አሜሪካ በሶማሊያ እና በኢትዮጵያ ላይ ታራምድ የነበረው የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የሚል ጽሑፍ ለንባብ አብቅተዋል። አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር የ25 ዓመታት የመከላከያ ስምምነት በአውሮፓውያኑ 1953 የገባቸው ምሥራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር በቀጣናው ቁልፍ ሚና አላት ብላ በማሰብ ነበር። ተጨማሪ ቴሌግራም ላይ ያንብቡ▻https://t.me/felegethiopia/24907

የናሳ መንኩራኩር 6.1 ሚሊዮን ኪሎ ሜትር ወደ ፀሐይ በመጠጋት ታሪክ ሠራች !የናሳ መንኩራኩር ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ሙቀት በመቋቋም ወደ ፀሐይ መጠጋቷ ተሰማ። ፓርከር ሶላር ፕሮብ የተሰኘችው ...
12/27/2024

የናሳ መንኩራኩር 6.1 ሚሊዮን ኪሎ ሜትር ወደ ፀሐይ በመጠጋት ታሪክ ሠራች !

የናሳ መንኩራኩር ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ሙቀት በመቋቋም ወደ ፀሐይ መጠጋቷ ተሰማ። ፓርከር ሶላር ፕሮብ የተሰኘችው መንኩራኩር ሐሙስ ምሽት ምልክት በማሳየት የፀሐይን ሙቀት ተቋቁሟ መጠጋት መቻሉን አሳውቃለች።

ናሳ እንዳስታወቀው መንኩራኩሯ ከፀሐይ 6.1 ሚሊዮን ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ መሽከርከር እንደቻለች አሳውቋል። ፓርከር ሶላር ፕሮብ ለቀናት ከግኝኑት ውጭ ሆና መቆየቷ የናሳ ሳይንቲስቶችን አሳስቦ ነበር።

መንኩራኩር የፀሐይን ከፍተኛ ሙቀት እና ጨረር መቋቋም መቻሏ ፀሐይ እንዴት ነው የምትሠራው የሚለውን ለመረዳት ጠቀሜታ እንዳለው ተመራማሪዎች ይናገራሉ። የናሳ ድረ-ገፅ መረጃ እንደሚጠቁመው መንኩራኩሯ 692 ሺህ ኪሎ ሜትር በሰዓት በመጓዝ 980 ሴልሲዬስ የሆነ ሙቀት ተቋቁማ አልፋለች።

የአሜሪካው የሕዋ ምርምር ተቋም መንኩራኩር በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ወደ ፀሐይ የመጠጋት ሙከራ ያደረገው። ፓርከር ሶላር ፕሮብ በአውሮፓውያኑ 2018 ነው ወደ ሶላር ሲስተም ማዕከላዊ ክፍል ያቀናችው።

መንኩራኩሯ እስካሁን 21 ጊዜ ፀሐይን የዞረች ሲሆን በየወቅቱ ወደ ፀሐይ ስትጠጋ ቆይታለች። በአውሮፓውያኑ ገና ዋዜማ ግን ከምን ጊዜውም በላይ ወደ ፀሐይ በመጠጋት ታሪክ ፅፋለች። የናሳ የሳይንስ ክፍል ኃላፊ ዶ/ር ኒኮላ ፎክስ እንደሚሉት ይህ ርቀት በጣም የበዛ ቢመስልም በንፅፅር እጅግ ቅርብ ነው።

"እኛ ከፀሐይ 93 ሚሊዮን ማይል ርቀት ላይ ነው የምንገኘው። ለምሳሌ ፀሐይ እና መሬት አንድ ሜትር ርቀት ላይ ቢሆኑ ፓርከር ሶላር ከፀሐይ 4 ሴንቲ ሜትር ርቀት ላይ ነው ማለት ነው። ይህን ያህል ቅርብ ነው" ይላሉ። መንኩራኩሯ ወደ ፀሐይ ስትጠጋ 1400 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ሙቀት ተቋቁማ ነው። የፀሐይ ሙቀት የመንኩራኩሯን ክፍሎች የማቅለጥ ኃይል አለው።

ፓርከር ሶላር 11.5 ሴንቲሜትር ስፋት ባለው ካርበን-ኮምፖሲት የተሸፈነች ቢሆንም ዓላማዋ ቶሎ ገብቶ መውጣት ነው። መንኩራኩሯ የሰው ልጆች ከሠሯቸው ቁሶች እጅግ ፈጣን ስትሆን በሰዓት 430 ሺህ ማይል ትጓዛለች። ይህ ማለት ከለንደን ኒው ዮርክ በ30 ሰከንድ እንደመጓዝ ነው።

ሳይንቲስቶች፣ መንኩራኩሯ ኮሮና በተባለው በትልቋ ኮከብ የውጭኛው ክፍል አልፋ ለዘመናት ያልተፈታ ጥያቄ ምላሽ ታስገኛለች የሚል ተስፋ አላቸው። "ኮሮና በጣም በጣም ሞቃት ነው። ለምን እንዲህ ሞቃት እንደሆነ የምናውቀው ነገር የለም" ይላሉ የፊፍዝ ሰታር ላብስ የጠፈር ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር ጄኒፈር ሚላርድ።

"የፀሐይ ሙቀት 6 ሺህ ሴልሺየስ አካባቢ ነው። ነገር ግን ኮሮና የተባለው የውጭኛው ክፍል በፀሐይ ግርዶሽ ጊዜ የምናየው ሲሆን ሚሊዮን ዲግሪዎች ሊደርስ ይችላል። የሚገኘው ከፀሐይ ራቅ ብሎ ነው። እንዴት ነው ይህ ከባቢ ሞቃት የሚሆነው?"

ከዚህ በተጨማሪ ሳይንቲስቶች 'ሶላር ዊንድን' ለመረዳት ሙከራ ያደርጋሉ። ሶላር ዊንድ ከኮሮና የሚመነጭ ነው። ይህ ሶላር ዊንድ ከመሬት 'ማግኔቲክ ፊልድ' ጋር ሲዋሀድ አውሮራ የተባለውን ሰማይ ላይ የሚያበራ ብርሃን ይሰጣል።

ይህ የሕዋ የአየር ሁኔታ የተባለ ሒደት ኤሌክትሪክ ማመንጫዎችን፣ ኤሌክትሮኒክስ እና የኮሚዩኒኬሽን ሥርዓቶችን ሊያውክ ይችላል። "ሐይን መረዳት፣ ሒደቱን ማወቅ፣ የሕዋ የአየር ሁኔታ እና ሶላር ዊንድን መገንዘብ መሬት ላይ ለምንኖር ሰዎች እጅግ አስፈላጊ ነው" ይላሉ ዶ/ር ሚላርድ።

ተጨማሪ ▻https://t.me/felegethiopia

ቆየት ያሉና ተወዳጅ የሆኑ ዘመን አይሽሬ ሙዚቃዎችን ለሚወዱ ብቻ የተዘጋጀ የቴሌግራም ቻናል ነው !ይሄ የቴሌግራም ፕራይቬት ( ለተወሰኑ ሰዎች ብቻ የተዘጋጀ ) ቻናል ነው join 🤝👉 http...
12/25/2024

ቆየት ያሉና ተወዳጅ የሆኑ ዘመን አይሽሬ ሙዚቃዎችን ለሚወዱ ብቻ የተዘጋጀ የቴሌግራም ቻናል ነው !

ይሄ የቴሌግራም ፕራይቬት ( ለተወሰኑ ሰዎች ብቻ የተዘጋጀ ) ቻናል ነው join 🤝👉 https://t.me/+KlKhPC5Z1pA3ODc0?sub_confirmation=1

😁😊
12/25/2024

😁😊

ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ፀሐይ ለመጠጋት እየሞከረች ያለችው የናሳ መንኩራኩርፓርከር ሶላር ፕሮብ የተባለችው መንኩራኩር ወደ ፀሐይ በመጠጋት የመጀመሪያዋ ናትየአሜሪካው የሕዋ ምርምር ተቋም መንኩራኩ...
12/25/2024

ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ፀሐይ ለመጠጋት እየሞከረች ያለችው የናሳ መንኩራኩር

ፓርከር ሶላር ፕሮብ የተባለችው መንኩራኩር ወደ ፀሐይ በመጠጋት የመጀመሪያዋ ናት

የአሜሪካው የሕዋ ምርምር ተቋም መንኩራኩር በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ፀሐይ የመጠጋት ሙከራ እያደረገች ነው። ፓርከር ሶላር ፕሮብ የተባለችው መንኩራኩር እጅግ ከፍተኛ ሙቀት እና ላቅ ያለ ጨረር ተቋቁማ ወደ ፀሐይ የመጠጋት ሙከራ ታደርጋለች።

መንኩራኩሯ ለበርካታ ቀናት ከግንኙት ውጭ ስትሆን ሳይንቲስቶች የፀሐይን ቃጠሎ ተቋቁማ ይሆን ወይ የሚለውን በጉጉት እየተጠባበቁ ነው። መንኩራኩሯ መትረፍ አለመትረፏ በአውሮፓውያኑ ታኅሣሥ 27 ይታወቃል ተብሏል። ፓርከር ሶላር ይህን ሙከራ የምታደርገው ፀሐይ እንዴት ነው የምትሠራው የሚለውን ለመረዳት ነው።

የናሳ የሳይንስ ክፍል ኃላፊ ዶ/ር ኒኮላ ፎክስ "ላለፉት መቶ ዓመታት ሰዎች ፀሐይን ሲመረምሯት ቆይተዋል። ነገር ግን የአንድ ሥፍራ ከባቢያዊ ሁኔታ ለማወቅ ተጠግቶ ማየት ያስፈልጋል" ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። "ስለዚህ የኮከባችንን ከባቢያዊ ሁኔታ ለማወቅ በአቅራቢያዋ መብረር አለብን ማለት ነው"

ፓርከር ሶላር ፕሮብ በአውሮፓውያኑ 2018 ነው ወደ ሶላር ሲስተም ማዕከላዊ ክፍል ያቀናችው። መንኩራኩሯ እስካሁን 21 ጊዜ ፀሐይን የዞረች ሲሆን በየወቅቱ ወደ ፀሐይ እየተጠጋች ትገኛለች። በአውሮፓውያኑ ገና ዋዜማ ግን ከምን ጊዜውም በላይ ወደ ፀሐይ ተጠግታለች።

ፓርከር ሶላር ወደ ፀሐይ የተጠጋችው 6.2 ሚሊዮን ኪሎ ሜትር (3.8 ሚሊዮን ማይል) ርቀት ላይ ነው። "እኛ ከፀሐይ 93 ሚሊዮን ማይል ርቀት ላይ ነው የምንገኘው።ለምሳሌ ፀሐይ እና መሬት አንድ ሜትር ርቀት ላይ ቢሆኑ ፓርከር ሶላር ከፀሐይ 4 ሴንቲ ሜትር ርቀት ላይ ነው ማለት ነው። ይህን ያህል ቅርብ ነው" ይላሉ።

መንኩራኩሯ ወደ ፀሐይ ስትጠጋ 1400 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ሙቀት ተቋቁማ ነው። የፀሐይ ሙቀት የመንኩራኩሯን ክፍሎች የማቅለጥ ኃይል አለው። ፓርከር ሶላር 11.5 ሴንቲሜትር ስፋት ባለው ካርበን-ኮምፖሲት የተሸፈነች ቢሆንም ዓላማዋ ቶሎ ገብቶ መውጣት ነው።

መንኩራኩሯ የሰው ልጆች ከሠሯቸው ቁሶች እጅግ ፈጣን ስትሆን በሰዓት 430 ሺህ ማይል ትጓዛለች። ይህ ማለት ከለንደን ኒው ዮርክ በ30 ሰከንድ እንደመጓዝ ነው። መንኩራኩሯ በፀሐይ የውጭኛው ክፍል ነው የምትዞረው። ተጨማሪ ▻ https://t.me/felegethiopia/24819 ያንብቡ

ከ2መቶ 78ሺህ ብር በላይ ከደንበኞች አካውንት በመቀነስ ለግል ጥቅሙ ያዋለ የባንክ ሰራተኛ በቁጥጥር ስር ዋለ!ተከሳሹ ግለሰብ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመው በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 በ...
12/20/2024

ከ2መቶ 78ሺህ ብር በላይ ከደንበኞች አካውንት በመቀነስ ለግል ጥቅሙ ያዋለ የባንክ ሰራተኛ በቁጥጥር ስር ዋለ!

ተከሳሹ ግለሰብ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመው በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 በሻሌ 72 አካባቢ ከሚገኝ የግል ባንክ ውስጥ የደንበኞች አገልግሎት መኮንን ሆኖ በሚሰራበት ባንክ ውስጥ በተደጋጋሚ ከተለያዩ ግለሰቦች የባንክ ሂሳብ ወደ ግል ሂሳቡ በሞባይል ባንኪንግ እና በቀጥታ በማስተላለፍ ሲጠቀም እንደነበረ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የበሻሌ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ገልጿል።

ግለሰቡ በቁጥጥር ስር እስከ ዋለበት ጊዜ ድረስ ከ5 የባንኩ ደንበኞች ያለ ፈቃዳቸው ከግል ሂሳባቸው 2መቶ 78 ሺህ 6 መቶ 91 ብር ከ7 ሳንቲም በጥሬ ገንዘብ ወጪ በማድረግ፣ ከሂሳብ ወደ ሂሳብ እና በሞባይል ባንኪንግ በማስተላለፍ የወሰደ መሆኑ በምርመራ መረጋገጡን እና ተከሳሹ ያለ ምንም ተፅዕኖ በሰጠው የእምነት ቃል በተደጋጋሚ ድርጊቱን የፈፀመ መሆኑን ያመነ ሲሆን ድርጊቱ የኃላፊዎቹን አለመኖር በመጠቀም ለደንበኞች መልዕክት እንዳይደርስ ሲስተም ላይ የራሱን ስልክ ቁጥር በማስገባት በፈፀመው ወንጀል ክስ ተመስርቶበታል።

ተከሳሹ የአንደኛ የግል ተበዳይ ለወላጅ አባታቸው በባንክ ቤቱ በአካል ቀርበው ገንዘብ አስተላልፈው ሊሄዱ ሲሉ ስልኮትን ይስጡኝ ሞባይል ባንኪንግ እንዲጠቀሙ ላስተካክል በማለት ተቀብሎ ለኃላፊው የግል ተበዳይ የስልክ ቁጥር መቀየራቸውን ዋሽቶ በመግለፅ አዲስ ስልክ ላይ መልዕክት እንዲደርሳቸው ጠይቀውኛል በማለት ኃላፊውን በማታለል የራሱን ስልክ በመሙላት ከ35ሺህ ብር በላይ ወደ ግል ሂሳቡ ያስተላለፈ እና የሌሎችን ግለሰቦችንም ስልክ ቁጥር በመቀየር የተጣለበትን ኃላፊነት ወደ ጎን በማለት በፈፀመው ወንጀል አንደኛ ከሳሽ ወደ ፖሊስ ጣቢያው ቀርበው ባመለከቱት መሰረት በቁጥጥር ስር ሊውልም ችሏል።

በግልም ሆነ በመንግስት ባንኮች ላይ ያሉ ኃላፊዎች በተገቢው የኮምፒተራቸውን ሚስጥራዊ ቁጥር በመሰወር እንዲሁም በሰራተኞቻቸው ላይ ተገቢውን ቁጥጥር የማድረግ ስራ በመስራት ከደንበኞቻቸው የሚቀርቡ ቅሬታዎችን በመቀበል ሊሰሩ እንደሚገባና ህብረተሰቡም የባንክ ሂሳቡን ሲያንቀሳቅስ በስልኩ ላይ ምንም አይነት መልዕክት ካልደረሰው በአካል ወደ ባንኩ ቀርቦ ሊያመለክት እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል።

ተጨማሪ መረጃዎች ቴሌግራም ላይ
https://t.me/felegethiopia

በኤሌክተሪክ ፍጆታ እና በልዩ ልዩ ክፍያዎች ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ ተግባራዊ ተደረገከ200 ኪሎ ዋት ሠዓት በላይ በሚጠቀሙ ደንበኞች የፍጆታ ሂሳብ ላይ እና አዲስ ደንበኛ ማገናኘትን ጨምሮ ...
12/20/2024

በኤሌክተሪክ ፍጆታ እና በልዩ ልዩ ክፍያዎች ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ ተግባራዊ ተደረገ

ከ200 ኪሎ ዋት ሠዓት በላይ በሚጠቀሙ ደንበኞች የፍጆታ ሂሳብ ላይ እና አዲስ ደንበኛ ማገናኘትን ጨምሮ ደንበኞች በሚፈፅሟቸው ልዩ ልዩ የአገልግሎት ክፍያዎች ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተግባራዊ መደረጉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ፡፡

የገንዘብ ሚኒስቴር ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ የሚሆነውን የመኖሪያ ቤት የኤሌክትሪክ ኃይልና የውኃ ፍጆታ መጠን ለመወሰን ባወጣው አዋጅ መመሪያ መሠረት ክፍያው ከመስከረም ወር ጀምሮ ተግባራዊ መደረጉን ነው አገልግሎቱ ያስታወቀው፡፡

በመመሪያው መሰረትም ከአገልግሎታችን ተጠቃሚ ደንበኞች ከወርሀዊ የፍጆታ ሂሳብ ጋር ተጨምሮ እንዲከፍሉ በማድረግ የተሰበሰበው ገንዘብ በየወሩ ለገቢዎች ሚኒስቴር ገቢ እንደሚያደርግም ነው የገለጸው፡፡

ተቋሙ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተግባራዊ ያደረገው ከሕዳር ወር የክፍያ ደረሰኝ ጀምሮ ሲሆን የድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞች ከመስከረም ወር ጀምሮ ያለባቸውን የኋላ ክፍያ በታሕሣሥ ወር በሚወጣው ቢል ላይ ተጨምሮ የሚከፍሉ ይሆናል ነው የተባለው፡፡

ተቋሙ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተግባራዊ ያደረገው ከሕዳር ወር የክፍያ ደረሰኝ ጀምሮ ሲሆን የድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞች ከመስከረም ወር ጀምሮ ያለባቸውን የኋላ ክፍያ በታሕሣሥ ወር በሚወጣው ቢል ላይ ተጨምሮ የሚከፍሉ ይሆናል ተብሏል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ደንበኞች ለአገልግሎቱ በሚከፍሉት ልዩ ልዩ ክፍያዎች ላይም ተግባራዊ እንደሚደረግ ተመላክቷል።በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቲቪ) ዓመታዊ የቴሌቪዥን አገልግሎት ክፍያ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ ላይ በመጨመር እንዲከፍሉ ሲያደርግ መቆየቱን ጠቅሷል፡፡

ተጨማሪ መረጃዎች ቴሌግራም ላይ ይመልከቱ
https://t.me/felegethiopia

ብርዱ እንዴት እያደረጋችሁ ነው ? 🥶🥶
12/19/2024

ብርዱ እንዴት እያደረጋችሁ ነው ? 🥶🥶



ባለቤቱን ለዓመታት ከ50 በላይ በሚሆኑ ወንዶች ያስደፈረው ፈረንሳያዊ 20 ዓመት ተፈረደበት፦ባለቤቱን ለዓመታት እያደነዘዘ የደፈረው እና ከ50 በላይ በሚሆኑ ወንዶች ያስደፈረው ዶሚኒክ ፔሊኮት...
12/19/2024

ባለቤቱን ለዓመታት ከ50 በላይ በሚሆኑ ወንዶች ያስደፈረው ፈረንሳያዊ 20 ዓመት ተፈረደበት፦

ባለቤቱን ለዓመታት እያደነዘዘ የደፈረው እና ከ50 በላይ በሚሆኑ ወንዶች ያስደፈረው ዶሚኒክ ፔሊኮት የተባለው ፈረንሳያዊ በመድፈር ወንጀል ጥፋተኛ ተብሏል።

ግለሰቡ ጄዚል ፔሊኮት የተባለች ባለቤቱን አደንዝዝዞ በመድፈር እና የማያውቋትን ወንዶች በመልመል ለዓመታት በማስደፈሩ የ20 ዓመት እስር ተፈርዶበታል። ከሱ በተጨማሪ ሌሎች የደፈሯት ግለሰቦች የተለያዩ የእስር ቅጣቶች ውሳኔ ተላልፎባቸዋል።

የ72 ዓመቷ አያት የቀድሞ ባለቤቷን ብያኔ ሲተላለፍ በፍርድ ቤቱ ግድግዳ ላይ ጭንቅላቷን አረፍ እንዳደረገች የቢቢሲ ዘጋቢ ተመልክቷል። ግለሰቡ ከዚህም በተጨማሪ ከተከሳሾቹ መካከል ዣን ፒየር ማርቻል የተባለውን ግለሰብ በመድፈር እንዲሁም የሴት ልጁን ካሮሊን እና የልጆቹን ባለቤቶች የተጋለጡ ምስሎች በማንሳት ጥፋተኛ ሆኖ ተገኝቷል።

ጥቃቱ የተፈጸመባት የ72 ዓመቷ ጂዜል ፔሊኮት የፈረንሳይ ሕግ የሰጣትን ማንነቷን የመደበቅ መብቷን በመተው ታሪኳንም ሆነ ራሷን ለሕዝብ ይፋ አድርጋለች። በፈረንይ ለሰው ህሊና የሚዘገንነው ወንጀል የበርካቶች መነጋገሪያ ሆኖ ቆይቷል። ጄዚል ፔሊኮትን የቀድሞ ባለቤቷ እያደነዘዘ ከ80 በላይ በሚሆኑ ወንዶች ለዓመታት አስደፍሯታል።

ይህም ለአስር ዓመታት ያህል የተፈጸመ ሲሆን፣ ግለሰቡ ባለቤቱን በተደጋጋሚ የደፈረበትን እና የማያውቋትን ወንዶች እያጋበዘ ያስደፈረባቸው ቪዲዮዎች እና ፎቶዎች ኮምፒውተሩ ላይ ተገኝተዋል።ግለሰቡ ባለቤቱን የደፈረበት እና ያስደፈረበትን በሺዎች የሚቆጠሩ ፎቶዎች በማንሳት እና ቪዲዮዎችን በመቅረጽ አስቀምጧል።

አነስተኛ በሆነችው በደቡባዊቷ ፈረንሳይ፣ ማዛን የተፈጸመው ይህ ድርጊት በርካቶችን ያንቀጠቀጠ ነው። የድርጊቱን ፈጻሚዎች ሰብዓዊነት ጥያቄ ውስጥ የከተተ፣ የጭካኔ ጥግን ያጋለጠ እንዲሁም የሰማውን ሁሉ ህሊና የረበሸ ሆኗል።

ግለሰቡ ለዓመታት የባለቤቱን ምግብ እና መጠጥ በጭንቀት መድኃኒት እና በእንቅልፍ እንክብል ሲመርዝ ቆይቷል። ሚስቱ በየምሽቱ ራሷን ከመሳት በተጨማሪ ጤንነቷ ክፉኛውኑ ተጎድቷል። ጂዜል ይህንን አስደንጋጭ ሁኔታ የተረዳችው ከአራት ዓመታት በፊት ነው።

ለአምስት አስርት ዓመታት በትዳር አብራው የኖረችው ባለቤቷ ከ80 በላይ የሚሆኑ ወንዶችን በመጋበዝ እንዳስደፈራት እና ድርጊቱን እንደቀረጸው የተረዳችው ከፖሊስ ነው። በመድፈር ወንጀሉ ላይ የተሳተፉት ወንዶች ቁጥር ብዛት ፈረንሳይን አስደንግጧል።

በቪዲዮው ላይ ከታዩት 83 ወንዶች መካከል ፖሊስ መለየት የቻለው 50ዎቹን ብቻ ነው። ዕድሜያቸው ከ26 እስከ 68 ሲሆን፣ በተለያዩ ሙያዎች ውስጥ ያሉ ናቸው። የእሳት አደጋ ሠራተኞች፣ ፋርማሲስቶች፣ ነርስ፣ የእስር ቤት ጠባቂ፣ ጋዜጠኞች ተካተውበታል።

በርካቶች የልጆች አባት እና ባለትዳሮች ናቸው። አንደኛው ኤችአይቪ በደሙ እያለ እያወቀ ስድስት ጊዜ እንደደፈራት ፖሊስ ይፋ አድርጓል። ምንም እንኳን ኤችአይቪ ባይተላለፍባትም ሌሎች በወሲብ በሚተላለፉ በሽታዎች ተይዛ እንደነበር የጤና ባለሙያ ምስክርነቱን ሰጥቷል።

ከዚህም በተጨማሪ በርካታ የጤና እክሎች እንደተከሱባት ተገልጿል። ዶሚኒክ በአንድ ድረ ገጽ ላይ "እሷ ሳታውቅ" ከባለቤቱ ጋር ወሲብ እንዲፈጽሙ አንድ ጽሁፍ መለጠፉን ተከትሎ ነው በርካቶች የመጡት።

ድረ ገጹ በአሁኑ ወቅት የተዘጋ ሲሆን፣ ባለፈው ዓመት 500 ሺህ ጎብኚዎች ነበሩት። ፖሊስ ባደረገው ምርመራ 4 ሺህ የሚሆኑ ጂሴል የምትደፈርበትን ፎቶዎች እና ቪዲዮዎች አግኝቷል። ድርጊቱ ከአውሮፓውያኑ 2011 እስከ 2020 የተፈጸመ ሲሆን፣ 200 ገደማ መደፈሮችን ይዘዋል። ሁኔታው ይፋ የሆነው ግለሰቡ በአንድ መደብር ውስጥ ተደብቆ የሴቶች ቀሚስ ስር ፎቶ ሲያነሳ በመያዙ ነበር በማለት ቢቢሲ ዘግቧል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ቴሌግራም ላይ ይመልከቱ ▻https://t.me/felegethiopia

በሰሜን ወሎ "ከፍተኛ" የምግብ እጥረት ህፃናትን ጨምሮ 10 ሺህ የሚሆኑ ሰዎች መጎዳታቸው ተነገረ፦በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ቡግና ወረዳ በተከሰተ ድርቅ እና የምግብ እጥረት ከአምስት ዓመ...
12/17/2024

በሰሜን ወሎ "ከፍተኛ" የምግብ እጥረት ህፃናትን ጨምሮ 10 ሺህ የሚሆኑ ሰዎች መጎዳታቸው ተነገረ፦

በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ቡግና ወረዳ በተከሰተ ድርቅ እና የምግብ እጥረት ከአምስት ዓመት በታች ያሉ ህፃናትን ጨምሮ 10 ሺህ የሚሆኑ ሰዎች መጎዳታቸውን ወረዳው አስታወቀ።

በክልሉ ባለው ግጭት እና ተፈጥሯዊ ተፅዕኖ ምክንያት ወረዳው ለድርቅ እና የምግብ እጥረት መጋለጡን የቡግና ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ገ/መስቀል ዓለሙ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

በአማራ ክልል የተነሳው ግጭት አንድ ዓመት ከመንፈቅ ያለፈው ሲሆን ከግጭቱ ባለፈ ወረዳው "ዝናብ አጠር እና በተፈጥሮ የተጎዳ ነው" ያሉት ኃላፊው በተደራራቢ ችግሮች ምክንያት የምግብ እጥረት መከሰቱን አስታውቀዋል።

"ማኅበረሰቡ ምርት ባለማግኘቱ እናቶች ልጆቻቸውን በአግባቡ መግበው የተሻለ የጤና እድገት እንዳይኖራቸው [አድርጓል]" ሲሉ ተፈጥሯዊውን ተጽዕኖ የገለጹት አቶ ገ/መስቀል፤ "ረድኤት ድርጅቶችም ለማኅበረሰቡ አልደረሱለትም" ብለዋል።

በወረዳው ብርኮ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ የካባ የአንድ ዓመት ከሦስት ወር መንታ ወንድና ሴት ልጆቻቸው በምግብ እጥረት "ስቃይ" ውስጥ እንደሆኑ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

"ምን አግኝተን እንርዳቸው? እስካሁን ድረስ በተቻለን ይዘናቸው ነበር። ከአዲስ ዓመት ወዲህ ግን ምንም ነገር የለም። ተያይዞ ቁልጭልጭ ሆነ እኮ?" ሲሉ ስላሉበት ሁኔታ አስረድተዋል።

"ጡጦ የምልበት ጎን [አቅም] የለኝም። ጡቴን ብቻ ነው ሳጠባቸው የከረምኩት። የጡት ወተት አሁን አነሳቸው፤ እንዴት ይድረሳቸው?. . . የተገኘው ምግብም አልሆናቸው አለ፤ አልስማማቸው አለ።"

ጠላ በመሸጥ ይተዳደሩ ነበሩት ወ/ሮ የካባ ልጆቻቸው ሲታመሙ ስራ እንዳቆሙ ይናገራሉ። ከቤተሰቦቻቸው ያገኙት የነበረውን የምግብ ድጋፍ በማጣታቸው መቸገራቸውንም ያስረዳሉ።

"ሐኪሞቹ «መግቧቸው፤ የምግብ እጥረት ነው» ይላሉ። እኛ ደግሞ ከየት እናመጣዋለን? ጊዜው ከፋብን። መሬቱ [ደረቀ]፤ እናት አባት አንድ ሁለት ኬሻ [እህል] ይሰጡን ነበር። ከዛ ብሶም ዘመኑ አጠፋው" ሲሉ እርሳቸውም በቂ ምግብ ባለማግኘታቸው ሕፃናት ልጆቻቸው እየተጎዱ እንደሆነ ገልፀዋል።

እርሻቸውን በረዶ እንደመታባቸው የሚናገሩት የወረዳው ነዋሪ አቶ ደሳለው አለባቸውም፤ ባለቤታቸው እና የ10 ወር መንታ ልጆቻቸው በምግብ እጥረት ተጎድተው ጤና ጣቢያ መግባታቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ባቄላ፣ ገብስ እና ጤፍ ያመርቱ እንደነበር የተናገሩት አቶ ደሳለው፤ "እናት የምትበላው የላትም፤ ልጆቹም የሚጠቡት የለም" ሲሉ ዘንድሮ "የተለየ" ችግር ገጥሞናል ብለዋል።

"በጣም ሲብስብን፤ ሲጨንቀን [ወደ ጤና ጣቢያ] አመጣናቸው። ሁለተኛ ቀናችን ነው። . . . [የምግብ] እጥረት ስላለባቸው ተዳክመዋል፤ ከስተዋል" ሲሉ ልጆቻቸው ያሉበትን ሁኔታ ገልጸዋል።

ቡግና ወረዳ ከአንድ ዓመት በላይ በፋኖ ኃይሎች ቁጥጥር ስር የሚገኝ ሲሆን፤ ቡድኑ መንግሥት ለወረዳው መድረስ የሚገባውን መድኃኒት እና ሌሎች ግብዓቶች አቅርቦት አስተጓጉሏል ሲል ወቅሷል።

በወረዳው ዋና ከተማ አይና ቡግና የሚገኘው አይና ጤና ጣቢያ ኃላፊ አቶ መኮንን አሻግሬ አካባቢው ካለበት ተፈጥሯዊ ችግር በተጨማሪ ከአዲሱ በጀት ዓመት በኋላ የተመጣጠነ የምግብ ላይ የሚሰሩ ረድኤት ድርጅቶች ግብዓት ማቆማቸውን ያሳያውቃሉ።

አንድ የጤና ባለሞያም ወረዳው የምግብ እጥረት ችግር ያለበት መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይም ካለፈው ዓመት ሐምሌ ወር ጀምሮ ችግሩ ጎልቶ መታየቱን ለቢቢሲ ይናገራሉ።

በአካባቢው ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት የአልሚ ምግቦች እና መድኃኒቶች አቅርቦት በመስተጓጎሉ ነፍሰ ጡር እናቶች እና ሕፃናት "ለተወሳሰበ ምግብ እጥረት" እንደተዳረጉ ይገልፃሉ።

በታኅሣሥ ወር መጀመሪያ የጤና ባለሞያዎች ለክትባት ዘመቻ ሲወጡ ነፍሰ ጡር እናቶች እና ሕፃናት 'በሥርዓተ ምግብ ልየታ' "የከፋ" የምግብ እጥረት ላይ እንደሆኑ መታዘብ ችለዋል።

ቢቢሲ የደረሰው እና በማኅበራዊ ትስስር ገጾች የተለቀቁ ምስሎች የችግሩን ጥልቀት የሚያሳዩ እና ለእይታ የሚረብሹ ናቸው።

በቡግና ወረዳ ካሉ 16 ቀበሌዎች በተለይም ላይድባ፣ ብርኮ፣ ጉልሃ፣ በርኳኳ እና ፈልፈሊቅ በተባሉ ቀበሌዎች ከስድስት ወር እስከ አምስት ዓመት ያሉ ሕፃናት "አሳሳቢ" የምግብ እጥረት ላይ እንደሚገኙ የተተደረገው ጥናት አሳይቷል።

ተጨማሪ መረጃ ቴሌግራም
ላይ ያንብቡ▻ https://t.me/felegethiopia/24749

የአዋሽ -ኮምቦልቻ- ወልድያ ሀራ ገበያ የባቡር መስመር ግንባታ ፕሮጀክት  ሰራተኞች "የዘጠኝ ወር ደሞዛችን አልተከፈለንም " አሉ።1.7 ቢልዮን የአሜሪካ ዶላር ወጭ የተደረገበት የአዋሽ ወልድ...
12/16/2024

የአዋሽ -ኮምቦልቻ- ወልድያ ሀራ ገበያ የባቡር መስመር ግንባታ ፕሮጀክት ሰራተኞች "የዘጠኝ ወር ደሞዛችን አልተከፈለንም " አሉ።

1.7 ቢልዮን የአሜሪካ ዶላር ወጭ የተደረገበት የአዋሽ ወልድያ ሀራ ገበያ የባቡር መስመር ግንባታ ላይ ይሰሩ የነበሩ 3500 የሚደርሱ ሰራተኞች ደመወዝ እንዳልተከፈላቸዉ ገለፁ።

ግንባታዉ በቱርኩ ስራ ተቋራጭ ያፒ መርከዚ ኮንስትራክሽን ኢንደስትሪ ኮርፖሬሽን ሲከናወን የነበረ ሲሆን ከሰሜኑ ጦርነት ጋር በተያያዘ በመቋረጡ በተለይም በጥበቃ ስራ ተሰማርተዉ የነበሩ ሰራተኞች ደመወዛቸዉን በወቅቱ ሊከፈሉ እንዳልቻሉ ይናገራሉ።

አስተያየታቸዉን ለዶቼቬለ የተናገሩት የጥበቃ ሰራተኛ የ9 ወራት ደመወዝ እንዳልተከፈላቸዉ ገልፀዉ በርካታ ሰራተኞች ሌላ የስራ አማራጭ ፍለጋ እንደለቀቁ ይናገራሉ።

10 ጣቢያዎች፤10 ኪ.ሜ ርዝመት ያላቸው 12 ዋሻዎች፤ 52 የተለያዩ ርዝመት ያላቸው ድልድዮች ፤ 8 የሀይል መቆጣጠሪያ ጣቢያዎች (ሰብስቴሽንስ) 12 የሬዲዮ ምሰሶዎች፤ አንድ የጥገና ማእከል ያሉት፡፡

የአዋሽ-ኮምቦልቻ ባቡር ፕሮጀክት ባለፉት አመታት ከፍተኛ የሆነ ስርቆት እንደተፈፀመበት የጥበቃ ሰራተኞቹ ይናገራሉ። በተለይም በባቡር መስመሩ ላይ የሚፈፀም ዝርፊያ ምሽትን ተገን በማድረግ የሚፈፀም ሲሆን የተደራጁ ቡድኖች ይከናወናል።

ሌላዉ ለዶቼ ቬለ ሀሳባቸዉን ያጋሩት አቶ አንተነህ አሊ ከባቡር ፕሮጀክቱ የተዘረፉ እቃዎችን በአገለገለ ስም መሸጥ እየተለመደ መጥቷል ያሉ ሲሆን የባቡር ሀዲዱም ለአደጋ ተጋልጧል ይላሉ።

የባቡር መስመር ዝርጋታዉ 11ቀበሌዎቹን የሚያቋርጥበት በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን አስተዳደር የጂሌ ጥሙጋ ወረዳ ፖሊስ ፅፈት ቤት ኃላፊ ኮማንደር መሀመድ አሊ እንደሚገልፁት ዝርፊያዉ በተሽከርካሪ የታገዘና የሰለጠኑ ሰዎች የሚፈፅሙት በመሆኑ በሀገር ሀብት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ያደርሳል ይላሉ ይሁን እንጂ በዋናነት ለዝርፊያዉ መባባስ ለጥበቃዎቹ ክፍያ የሚፈፅመዉ የቢራሮ ሴኩዮሪቲ ኤጀንሲ ክፍያዉን በጊዜ አለመፈፀሙ ምክንያት ነዉ ሲሉ ነው የሚናገሩት።

392 ኪሎሜትር የባቡር መሰረተ ልማት ለመጠበቅ 3500 ሰራተኞችን ቀጥሮ ያፒ መርከዚ ጋር ውል የወሰደው የቢራሮ የሴኩሪቲ ኤጀንሲ ዋና ሀላፊ አቶ አህመድ ሰይድ የኢትዮጽያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን የአዋሽ ወልድያ ሀራ ገበያ ፐሮጀክት ጽህፈት ቤት በውላችን መሰረት መክፈል ያለበትን 100 ሚልየን ብር ሰላልከፈለ ለሰራተኛ መክፍልም ሆነ ሀብቱን መጠበቅ አልቻልንም ይላሉ።

1.7 ቢልዮን የአሜሪካ ዶላር ወጭ ተደርጎበት የተሰራው የባቡር መሰረተ ልማት አሁን ላይ ምንም አይነት አገልግሎት ባለመስጠቱ ለዝርፊያ እተጋለጠ ነው የሚሉት አቶ አህመድ ሰይድ እኛም በህጋዊ መንገድ ውላችንን አቑርጠናል ይላሉ። በዚህ ዜና ላይ የኢትዮጽያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን የአዋሽ ወልድያ ሀራ ገበያ ፐሮጀክት ጽህፈት ቤት የስራ ኃላፊዎችን ለማካተት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም በማለት ዶቸቬለ ዘግቧል።

ተጨማሪ መረጃ ቴሌግራም ላይ ይመልከቱ ▻ t.me/felegethiopia

የአፍሪካ የዓመቱ ኮከብ ተጫዋች ምሽት ይታወቃል የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ዛሬ ምሽት የዓመቱቱን ኮከብ ተጫዋች ይመርጣል። በሞሮኮ ማራካሽ በሚደረገው ምርጫ ናይጀሪያዊው የመስመር...
12/16/2024

የአፍሪካ የዓመቱ ኮከብ ተጫዋች ምሽት ይታወቃል

የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ዛሬ ምሽት የዓመቱቱን ኮከብ ተጫዋች ይመርጣል። በሞሮኮ ማራካሽ በሚደረገው ምርጫ ናይጀሪያዊው የመስመር አጥቂ አዴሞላ ሉክማን የአሸናፊነት ግምት አግኝቷል።

ደቡብ አፍሪካዊው ሮንዌን ዊሊያምስ፣ የኮቲዲቯሩ ሲሞን አዲንጋራ፣ የጊኒው ሴይኮ ጉራሲ እና የሞሮኮው አሽረፍ ሃኪሚ የመጨረሻ ዕጩዎች ናቸው። ባለፈው ዓመት ናይጀሪያዊው ቪክቶር ኦሲሜን ማሸነፉ ይታወሳል።

ተጨማሪ መረጃዎች ቴሌግራም ላይ ▻ t.me/felegethiopia

እንደዚህም ቅሸባ አለ 😃
12/16/2024

እንደዚህም ቅሸባ አለ 😃

ክቡር ዶ/ር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ እና የ1953 ዓ.ም መፈንቅለ መንግስት ታሪክ"የመፈንቀለ መንግስት ሙከራው በተካሄደ በአራተኛው ቀን መሰለኝ ጃንሆይ ጉብኝታቸውን አቋርጠው አዲስ አበባ ገቡ...
12/15/2024

ክቡር ዶ/ር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ እና የ1953 ዓ.ም መፈንቅለ መንግስት ታሪክ

"የመፈንቀለ መንግስት ሙከራው በተካሄደ በአራተኛው ቀን መሰለኝ ጃንሆይ ጉብኝታቸውን አቋርጠው አዲስ አበባ ገቡ። አሁን አገር ሰላም ነው አልሁና እኖርበት ወይም በጭንቅ ሆኜ ሁኔታውን እከታተልበት ከነበረው ፊት በር እየተባለ ከሚጠራው ሰፈር ወጣሁና አራት ኪሎ አቶ ሻወል ቤት ገባሁ። ለካ ጦር ሰራዊት ይከታተለኛል። ድንገት ጀርባዬን በሰደፍ ደቅኖ ቀጥል አለኝ።

ከዛ ሌሎችም በጥፊ በርግጫ እያዳፋ እንዲያውም የሌለኝን መአረግ ሁሉ እየስጡኝ ''የኛ መቶ አለቃ! የሾሙህ የሸለሙህ ጃንሆይ መጥተዋል ምን ይዋጥህ? አንተ ከሀዲ! ለሰንደቅ አላማህና ለንጉስህ የገባህውን ቃል በልተህ መንግስት ልትገለብጥ ሞከርህ አይደል...''አሳሬን ያሳዩኝ ጀመር። መልስ ለመስጠትና ''መቶ አለቃ ቀርቶ ወታደር አይደለሁም ሲቪል ነኝ ''ብዬ ለመናገር እንኳ ፋታ አልሰጡኝም ቁም ስቅሌን አሳዩኝ።

በዚህ አይነት ሁኔታ መከራዬን እያሳዩ ወስደው አሁን ሸራተን አዲስ ወደ ተሰራበት አካባቢ ከነበረ ሽንት ቤት ውስጥ አስገቡኝ። እውነት ለመናገር ያን ሁሉ መከራ ከማየት ያን እለት ብሞት እመርጥ ነበር። አንዴ በርግጫ ሊያውም በወታደር ጫማ ፣እንደገና በጥፊ ፣እንደገና በቆመጥ... እረ ስንቱ ይነገራል? እና እንዲህ እንደ አውድማ ላይ ገብስ ሲወቁኝ ውለው ሽንት ቤት ከዘጉብኝ ከተወሰነ ሰአት በኃላ ''አራተኛ ክፍለጦር '' ወሰዱኝ።

እዚያ ስደርስ የያዙኝ ወታደሮች በኩርንችት ጫማ እስከሚበቃቸው ከወቀሩኝ በሁዋላ ለዘቦች አስረከቡኝ። ሰውን እንደ እባብ መቀጥቀጥ በህግ የተፈቀደ እስኪ መስል ድረስ የአራተኛ ክፍለጦር ወታደሮችም መፈጠሬን እስክጠላ ገረፋኝ ። እረ ''ገረፋኝ'' የሚለው ቃል አይገልጸውም።

"ሕሊና ያለው ሰው በመሰሉ ላይ ይፈጽመዋል ተብሎ የማይታሰበውን የጭካኔ እርምጃ ወሰዱብኝ ።"

ጋሽ ጥላሁንን ያስጠረጠረው እና ለእስር ያበቃው ጉዳይ መፈንቀል መንግስቱ ሊደረግ ቀናት ሲቀረው “ኡኡታ አያስከፋም ሲለዩ ተዋዶ” በሚል ርዕስ ስር ለህዝብ ባቀረበው ተወዳጅ ሙዚቃ ተጠርጥሮ ነበር።

ኡኡታ አያስከፋም ሲለዩ ተዋዶ
ከዚህ የበለጠ ከየት ይምጣል መርዶ....

እያለ በመጫወቱ እና ከአቶ ንዋይ ልጆች ጋር በነበረው ወዳጅነት በአሸባሪነት ተጥርጥሮ ለብዙ ሳምንታት መታሰሩ የዘመኑ ሰበር ዜና እንደነበር በታሪክ ተጽፎአል።..ክቡር ዶ/ር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ እንደተናገረው። በምስሉ ላይ ጥላሁን ገሠሠ በወታደሮች በቁጥጥር ስር ሲውል ነው።(ታሪክን ወደኋላ)

ዘመን አይሽሬ ሙዚቃዎችን ያዳምጡ https://youtube.com/?sub_confirmation=1

Address

Tucker, GA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hagere Infotainment posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hagere Infotainment:

Videos

Share