SDD-Sagalee Dirree Dhawaa

SDD-Sagalee Dirree Dhawaa SDD is stand for Dirree Dhawaa and all of oromo people

12/22/2025
12/19/2025

“የካድሬ መንደር” ጉዳይ፤ የድሬዳዋ ነዋሪዎች እውነቱ እንዲገለጥ ጠየቁ!!

​ከንቲባ ከድር ጁሃር የሚመሩት የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር “የካድሬ መንደር” የሚባል ነገር የለም ሲል የካደ ሲሆን፣ ስለ ግንባታው የሚወጡ ዘገባዎችም “የሚዲያ ፈጠራ ናቸው” በማለት አጣጥሏል። ሆኖም ይህ ማብራሪያ ግልጽነትና ተጠያቂነትን እየጠየቁ ያሉትን የድሬዳዋ ነዋሪዎችን ሊያሳምን አልቻለም።

​በመሬት ላይ ያለው ተጨባጭ ሁኔታ ግን ሌላ ታሪክ ይናገራል። በፖሊስና በፀጥታ ኃይሎች ጥበቃ እየተደረገለት በቦታው ላይ መጠነ ሰፊ ግንባታ እየተካሄደ ሲሆን፣ አንዳንድ ነዋሪዎችም መፈናቀላቸው ተነግሯል። እነዚህ እውነታዎች ከአስተዳደሩ መግለጫዎች ጋር የሚጋጩ ከመሆናቸውም በላይ፣ የከተማዋ የልማት ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች እና የአመራር ብቃት ላይ ከባድ ጥያቄዎችን ያስነሳሉ።

​ዜጎች እና ታዛቢዎች እውነቱን በንግግር ብቻ መደበቅ እንደማይቻል ያሳስባሉ። እየተከናወነ ያለውን ግንባታና ተያያዥ እንቅስቃሴዎችን የሚያሳዩ የቪዲዮ ማስረጃዎች ይፋ እንደሚደረጉና እውነታው ለመላው ከተማ ነዋሪ ግልጽ እንደሚሆን ተገልጿል።

​ነዋሪዎቹ #ድሬ ቲቪን እና #የድሬዳዋ ኮሙኒኬሽን ቢሮን ጨምሮ የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን ወደ ቦታው በመሄድ እየሆነ ያለውን ነገር በትክክል እንዲዘግቡ እየወተወቱ ነው። የሕዝብን እምነት ለመመለስ ከመገናኛ ብዙኃን እና ከከተማው ባለሥልጣናት ግልጽነት ይፈለጋል።

​የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ግልጽና በማስረጃ የተደገፈ ምላሽ የመስጠት ኃላፊነት አለበት። የሕዝቡ አቤቱታ ስህተት ከሆነ፣ ባለሥልጣናቱ መረጃውን የማስተካከል ዕድል አላቸው። ነገር ግን “የካድሬ መንደር” እንደተባለው ያለ ከሆነ፣ የድሬዳዋ ነዋሪዎች እውነቱን የማወቅ መብት አላቸው።

​ድሬዳዋ እውነት ናት፤ ልማቷም ተጠያቂነት የሰፈነበት፣ ግልጽ እና በተጨባጭ እውነታ ላይ የተመሰረተ መሆን አለበት። እውነትን መቅበር አይቻልም፤ ዜጎችም እውነቱ እንዲወጣ ያደርጋሉ።

12/19/2025

‎ከህዝብ ይልቅ ለባለስልጣናቱ የወገነው ጋዜጠኛ!

‎ከህዝብ ወገንተኝነት የሸሸው የድሬ ቲቪ አንጋፋ ጋዜጠኛ ሙሉዓለም ከለውጡ ወዲህ የድሬዳዋውን ህዝብ የልማት የዲሞክራሲ መሰረታዊ ችግሮች ለመቅረፍ የተለያዩ የቅሬታዎችን በመስራት የምርመራ ጋዜጠኝነት በስፋት በመዘገብ ብዙ የወረዳ የቀበሌ አመራሮችን ያጋለጠው ጠንካራ ጋዜጠኛ ተብሎ ይመሰገን የነበረው ጋዜጠኛ ሙሉዓለም ሰለሞን አሁን ግን ከመንግሥት ሹማምት ጋር በመሞዳሞድ የድሬደዋን ህዝብ ጥቅም ወደ ጎን ችላ በማለት የህዙቡን የኢኮኖሚ የማህበራዊ ፍላጎት እንዳይሳካ የህዝብ እንባን ማበስ ያቃተው የመንግስት ቀኝ እጅ በመሆን እያገለገ ያለ ጋዜጠኛ ነው።

‎ጋዜጠኛው ከአደም ፋራህ ጀምሮ ትልልቅ የሀገሪቱ ባለስልጣናትን ለምሳሌ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል የፕላን ኮምሽን ሚኒስትር ዶ/ፍፁም አሰፋ የሴቶችና ህፃናት ማህበራዊ ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ የተለያዩ የክልል ርዕሳነ መስተዳደር አመራሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀጥተኛ ትዕዛዝ የመጡበትን አጀንዳ በማስቀየስ ስራ ላይ የተጠመደ ሞያዊ ግዴታውን መወጣት ያቃተው ጋዜጠኛ ነው።

የድሬደዋ መሰረታዊ የህዝቡን ፍላጎት እና የድሬደዋ አስተዳደር አመራሮች ግምገማ እና የስራ አፈፃፀም በአግባቡ ገምግመው ለፌደራሉ መንግስት ትክክለኛ መረጃ እንዳያደረሱ ቀደሞ እስቲዲዮ በመጋበዝ ስለ አስተዳደሩ መልካም ገፅታ እና ስለተደረገላቸው አቀባበል ብቻ በማስወራት የህዝቡን ጥቅም እያሳጣ ያለ የመንግስት አፈ ቀላጤ ነው።

የተማረበትን የጋዜጠኝነት ሞያ ወደ ጎን በመተው በተሽሞነሞነ ጥያቄዎቹ አማካኝነት ለድሬደዋ አመራር በማድላት የፌደራል ከፍተኛ አመራሮችን ያለተሰራውን ተሰርቷል ያልሆነውን ሆኗል እያለ በመጠየቅና በመረጃ በማደናገር የተዛባ መረጃ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲደርስ የሚያደርግ የህዝብ ወገንተኝነት ፈፅሞ የማያውቅ ሲሆን የድሬደዋ ነዋሪዎች በኮሪደር ልማት ምክኒያት ባላስፈላጊ ወጪ ሲንገላቱ ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ እሱ ግን ልማቱ ዳሃ አልጎዳም አላፈናቀለም የድሬደዋ አመራሮች ፃዲቅ ናቸው እያለ የተለመደውን ዘገባ እየሰራ ለድሬደዋ አመራሮች ሽፋን የሚሰጥ ከድሬደዋ አመራር ጋር የጥቅም ትስስር የፈጠረ ጋዜጤኛ ነው።

‎ጋዜጠኛ ሙሉዓለም ከባለስልጣኖች ካለው ቅርርብ የተነሳ ለአመራሮች መረጃ የማጥፋት ስራ እና የህዝብ ተቃውሞ የሚያስነሱ ጉዳዮችን እግር በእግርእየየተከታተለ የሚያጠፋላቸው እና የሚያድበሰብስ የብልፅግና አፈ ቀላጤ በመሆን አመራሩ እንዳይሳጡ ቀን ከሌት የሚተጋ ሲሆን የተለያዩ ሀገር አቀፍ ሚዲያዎችን ባለሞያዎችን በሞዳሞድ በመደለል ስለድሬደዋ ከተማ እና ስለ አመራሩ እርስ በእርስ ግንኙነት የተዛባ የዘገባ ሽፋን እንዲሰጡ በማገናኘት የፕሮፖጋዳ ስራ እንዲሰሩ የማግባባት ስራ የሚሰራ ሲሆን ለዚህም ስራው ለጋዜጠኞኙ የተለያዩ ወጪያቸው በአስተዳደሩ እንዲሸፈን በማድረግ ኪስ ገንዘብ እንዲያገኙ የተለያዩ አልባሳት ከአስተዳደሩ ካዝና በማውጣት እንዲሸለሙ በማድረግ የድሬደዋ አስተዳደር አመራሮች ግፅታ ግንባታ ላይ የተጠመደ የሚዲያው ዘርፍ ግንባር ቀደብ የድለላ ስራ የሚሰራ ሲሆን አልፎ ተርፎ በተለያዩ ሚዲያዎች እስቲዲዮ እየተጠሩ የድሬዳዋ አመራሮች እንዲጋበዙ በማድረግ መልካም ገፅታቸው እንዲገነባ ድልድይ በመሆን የጋዜጠኝነት ሞያውን ለግል ጥቅሙ የሚያውል የአስተዳደሩ አመራሮች የግል ሚዲያ ፕሮፖጋዲስት ነው።

‎ለአመራሮች ካለው ቀረቤታ አንፃር የግል ጠባቂዎቻቸው እንኳን የማይናገሩት እንደፈለገው ቢሮአቸው ያለ ምንም ፍቃድ ዘው ብሎ እንዲገባ የተፈቀደለት ሲሆን ለአስተዳደሩ የየሳምንቱን አጀዳ ቀርፆ የሚያዘጋጅ አመራሮችን የተቃወመ ካለ ባለው የቴክኖሎጂ እውቀት አሳዶ ለእስር እዲዳረጉ የሚያደርግ እና የጋዜጠኝነት ሞያውን ተገን በማድረግ የህዝብን ስነልቦና ላይ የሚጫወት ከህዝብ ጥቅም ይልቅ ለከንቲባው ፍላጎት ለፓርቲ ሃላፊው ክብር ፣ለአቶ ሮቤል፣ ለአቶ ደረጀ ፣ለኢንጂነር ዑመር ክብር እና ስራ ብቻ አብዝቶ የሚጨነቅ እና የነሱን ስራ በማጉላት ብቻ የተጠመደ ግለሰብ ነው።

‎ለዚህም ውለታው ሲባል የቀበሌ ቤት ለሚስቱ የስራ ቦታ ይሆን ዘድ ዋና መንገድ ከደሃ ላይ ተነጥቆ የተሰጠው ሲሆን ሌላም ለግል መኖሪያ ቤት 250 ካሬ ሜሬት በሚኖርበት አካባቢ በጓደኛው ከንቲባ አማካኝነት የተሰጠው እና የኮንዶሚኒየም የጋራ መኖሪያ ቤት ለመውሰድ ጫፍ ላይ የደረሰ አይነኬ ጋዜጠኛ በየጊዜው ከተለያዩ ቢሮዎች አበል የሚሰጠው አልፎ ተርፎ ህገወጥ የጉዞ ውሎ አበል የሚፃፍለት በጥቅም የተሳሰረ የድሬዳዋ ህዝብ ጥቅም ያሳጣ ጋዜጠኛ ነው
‎ #በቀጣይ የፎቶ የቪዲዮ ማስረጃዎችን እንዳስፈላጊነቱ የምናደርስ መሆኑን ለድሬዳዋ ህዝብ እናሳውቃለን።

12/16/2025
12/16/2025

-Dhawaa Updated!
KOMISHINARRI KOMISHINII DIRREE-DHAWAA "Kom. Alamuu Margaa" jannata seenuuf ABO/WBO ajjeesuun qaba jedhee dubbate!

Komishinarri kun bulchiinsa magaalaa Dirre-Dhawaatti itti gaafatamaadha. Af_Gaafii dheengadda taasifameef irratti kana dubbate. WBO jechuun qubee 'W' fi qubee 'B' yoo irraa kaafne qubee (O) Oromootu hafa. Kanaafuu, Komishinar Alamuun jannata seenuuf Dirre-Dhawaa keessatti Oromoo ajjeesuun irratti waajiba jechuudha

Bubbullu waa hedduu dhageenya dhugaa!

Address

Minneapolis, MN

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when SDD-Sagalee Dirree Dhawaa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to SDD-Sagalee Dirree Dhawaa:

Share